
🌸 May Sale Weeks on Telega.io
Up to 70% off + 3.5% extra discount with promo code MAYFINAL!
Go to Catalog
24.2

Advertising on the Telegram channel «እንማር»
5.0
11
Share
Add to favorite
Buy advertising in this channel
Placement Format:
keyboard_arrow_down
- 1/24
- 2/48
- 3/72
- Native
- 7 days
- Forwards
1 hour in the top / 24 hours in the feed
Quantity
%keyboard_arrow_down
- 1
- 2
- 3
- 4
- 5
- 8
- 10
- 15
Advertising publication cost
local_activity
$18.00$18.00local_mall
0.0%
Remaining at this price:0
Recent Channel Posts
imageImage preview is unavailable
አየችኝ ከዛ የበለጠ ሳመችው እና እዚህ ምን እየሰራሁ እንደሆነ ጠየቀችኝ?.
እሷ እና የወንድ ጓደኛዋ ተመስጠው እየተመለከቱኝ ነበር እና ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነበር የሄድኩት...
10900
07:54
09.05.2025
imageImage preview is unavailable
ፈረንሳዊ ነው። ከ50 በላይ ፊልሞች ውስጥ እጁ አለበት። ፊልሞቹ ውስብስብ አይደሉም፣ ግን በጣም አዝናኝ ናቸው። በጣም የተወደዱ፦
❶ ለመጀመሪያ ግዜ ያየሁት የሉክ ቤሰን ፊልም Leon or The Professional ነው።
አንዳንድ ነገሮች ስለ Leon/The Professional
፨ ፊልሙ የናታሊ ፖርትማን የመጀመሪያ ፊልሟ ነው። ገፀባህሪዋ አጫሽ ብትሆንም ናታሊ አንድም ሲጋራ አልነካችም
፨ የፈረንሳዊው ሉክ ቤሰን ሰቃይ ፊልም ይሄ ይመስለኛል
❷
አክሽን ፊልም እምብዛም ነኝ በቂ የኋላ ታሪክ ሲኖረው ግን አላልፍም። ከአክሽን ፊልም ዳይሬክተሮች ፈረንሳዊው ሉክ ቤሰን ከድብድቡ ባሻገር ትልቅ ርእስ ይዞ ይነሳል። ለምሳሌ Leon: The Professional, Taken and Lucy.
—ዝግመተ-ለውጥ
—ንቃተ-ህሊና
—የተፈጥሮ ባህሪ ወዘተ ወዘተ
100% አእምሯችንን ብንጠቀምስ?
✅—ወደ ኢነርጁ እንቀየራለን
✅—በሁሉም ቦታ እንገኛለን ወዘተ ወዘተ
ፊልሙ በአጭሩ ሶስት አስደናቂ አንኳር ነገሮች አሉት፦
—
—
—
ሌላ ደግሞ ተመሳሳይ ጉዳይ የያዘ ፊልም አለ—Limitless.ፈልጋችሁ እዩት።
10300
06:45
09.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-18✨✨
ከክሊኒኩ እንደወጣሁ ቅርብ ያለ ቤተክርስትያን ጠይቄ ላመሰግን ሄድኩ.........ከተወሰኑ ቀናት በፊት "እዚህ አካባቢ መቃብር ስፍራ ካለ ጠቁሙኝ" ያልኩ ሴትዮ ዛሬ "ቤተክርስትያን ጠቁሙኝ" እያልኩ ነው....
ጊዜ እንዲህ ነው...."የማይነጋ ለሊት ማያልፍ ቀን የለም....." የሚል የመዝሙር ስንኝ አቃጨለብኝ...."እውነትም" አልኩኝ በለሆሳስ.....ይሆናል ብለው ከነገሩን በላይ ሆኖ ስናየው እናምናለን.....እኛ እንደሀገርም ሆነ እንደ ህዝብ....እንደ አህጉርም ቢሆን እንደ አለም የሚያመሳስለን ነገር አለ.....እንደ ቶማስ ካላየን አናምንም....እንደ ኤሳው ሆዳችን ከብኩርናችን ይበልጥብናል....ፈጣሪ የሰጠንን ፀጋ ከላያችን ለመላጨት ደሊላ ትበቃናለች.....
የኢዮብን ስም የያዝን ከጂዎች.....የስምኦንን ስም የያዝን አሳቾች....የአብርሀምን ስም የያዝን ንፉጎች....የኢያሱን ስም ይዘን ለአምላካችን ግድ የሌለን ከንቱዎች ሆነናል....ሙሴ ተብሎ አሻጋሪ ጠፍቷል.....የዘመኑ ሙሴ ላሻግራችሁ ብሎ ባህር ከፋይ....ህዝብ አምኖ ከክፋዩ ውሀ መሀል ሲገባ ውሀ የሚያስበላ ነው.....
የዘመኑ ስምኦን እንደ "ስምኦን ጫማ ሰፊው" ሰው አሳትኩኝ ብሎ አይኑ ላይ ወስፌ አይሰድም....ይልቁንም ሰው ለማሳት ጫማው እስኪያልቅ ይኳትናል እንጂ...
ስማችን አይከብደንም.....ምግባራችን አንገት አያስደፋንም.....ደህና ነገር እንደሰራ ሰው እንታበያለን.....እንዳልከፋን እንስቃለን....እንዳለለት እንዘላለን.....መፍራት ያለብንን አንፈራም....መፀየፍ ካለብን ጋር እንጣበቃለን.....ስጋችንን እናምነዋለን....ስጋ ብቻ እንዳለው ሰው እንኖራለን.....
***
"ዛሬ ምሳ የምጋብዝሽ እኔ ነኝ" አልኳት ሀኒን ....የሆነ የማላውቀው መንፈስ ውስጤ አለ አምጫት አምጫት የሚለኝ....ደስታሽ ደስታዋ ነው ንገሪያት የሚለኝ.....ለምን ብቻሽን እሷ እያለችልሽ የሚለኝ መንፈስ ሲታገለኝ ነበር የደወለችልኝ....እግዜር ይስጣት።
ከተገናኘን ወር ሊያልፈን ነበር.....ለአመታት እንዳልተገናኘ ዘመድ ተቃቀፍን.....ደስ አለኝ።
የምንወደውን ምግብ አዘን ሳንጎራረስ እና ሳንተያይ በላን.....እዚህ ጋር ከመክብብ ጋር ስለነበረን የመጀመሪያ ቀን አስታወስኩ.....ትንሽ ትንሽ መደበር እንደጀመርኩ አስተውላ "ምነው.....?" አለቺኝ
"ኧረ ምንም...."....አልኩና ለምን እንደዘጋችኝ ጠየቅኳት....
"አንቺም ዘግተሽኛል እኮ....".....የሚል የሰነፍ መልስ መለሰችልኝ....
"ያንቺን አይደል የጠየቅኩሽ ለምን አትመልሺም".....አልኳት።
"ልጠላሽ አልፈለግኩም.....ትንሽ ትግል ውስጥ ነበርኩ....".....አለችኝ ድምጿ ቀዝቅዞ።
ትንሽ አርፋ ቀጠለች...."ትግል ውስጥ ነበርኩ....እየታገልኩ ነበር.....እኔ በፈለግኩት እና የፈለግኩት በሚፈልገው መሀል ያለውን ልዩነት ላጠብ ስጣጣር ነበር...አንቺን ከመክብብ ጭንቅላት ለማስወጣት እየታገልኩ ነበር...."......አለችና በልምምጥ አይነት አየችኝ......
"ተይልኝ ልልሽ አይደለም.....ምን ብለሽው እንዲህ እንደሆነልሽ ብቻ ንገሪኝ.....እኔ ለሰባት አመት የእሱን ትኩረት ለማግኘት የተጋጋጥኩትን በአንድ ቀን እንዴት ከመሬት ቀላቀልሽው.....እንዴት አርገሽ ብታይው ነው.....አሳሳቅሽ እንዴት ነበር.....ፀጉርሽን አንጨባረሺው ነበር አይደል....የዛን እለት የለበስሽው ልብስ መናኛ ነበር አይደል.....እንዴት ያለ አስተያየት እንዴት ያለ አወራር ነበረሽ.....?.....ወይስ አበላልሽ ነው....አስታውሳለሁ አካሄድሽ እስከዚም ነበር.....ጫማሽ አቧራ ጠጥቶ ነበር.....ትዝ አለሽ ቀሚስሽ ጭቃ ነክቶት ነበር.....".......አለችኝ እና ያለቀው ትሪ ላይ አፈጠጠች.....
አንጀቴ ተላወሰ......"ሀኒ ካንቺ አይበልጥም.....የምሬን ነው.....ይኧውልሽማ....."......ከማለቴ አቋረጠችኝ......እውነቱን ለመናገር "ካንቺ አይበልጥም" ያልኩትን ቃል ስሜታዊነቴ ነው ያበጃጀው.....አንዳንዴ የማናወዳድራቸው ነገሮች አሉ.....እንደ እኔ እንደ እኔ ደረጃ ከመስጠት ሁሉንም እንደ ራሱ መውደድ ይሻላል።
"እንደስምሽ ነሽ ታውቂያለሽ.....እድል አለሽ.....ምን አልባት ፈጣሪ በእሱ ሊክስሽ ይሆናል......"
"የሚክሰው በዳይ ነው.....ሰው እንጂ ፈጣሪ በድሎኝ አያውቅም.....ሀኒ....".......በድጋሚ አቋረጠችኝ.....
"ትናንት መክብብ እንዴት አድርጎ የፍቅር ጥያቄ እንደሚያቀርብልሽ ሲጨነቅ ነው ያመሸው.....ምን ትወድ ይሆን እያለ ልቤን ሲጠባ ነበር.....የምትወጂውን ሳይሆን የምወደውን ልነግረው ስንቴ ከአፌ እንደመለስኩት አታውቂም.....ስንት ጊዜ እድል ፊት እንዳለህ እያሰብክ "አፈቅርሻለሁ" በል እንዳልኩት እና በልቤ ጮክ ብዬ "እኔም አፈቅርሀለሁ" እንዳልኩት አታውቂም.....አንቺን እያሰበ ስንት ጊዜ አፈቅርሻለሁ ሲለኝ እንዳመሸ አታውቂም.....አእምሮዬ ሊፈነዳ አንድ ሀሙስ እንደቀረው አታውቂም....."......አለችና መንታ መንታ እምባ ከአይኖችዋ ተንቆሮቆሩ።
በወደድኩት በመወደዴ ደስ ባለኝ ቅፅበት እንባዋ እንደ እሳት ፈጀኝ.....ልቡ ውስጥ ለመግባት በተመኘሁት እኩል መውጣት አሰኘኝ.....አሳዘነችኝ.....
"ትዝ ይልሻል ልጅ እያለን ያየነው ሻሩክ የሚሰራበት የህንድ ፊልም......"
በህይወት ዘመኔ ያየሁት የህንድ ፊልም እሱ ብቻ ስለነበር አልረሳሁትም.....አንገቴን በአዎንታ ነቀነቅኩላት.....
"እሱ ላይ እንዳለችው እንስት ሳሳሁ.....'ለአንድ ወንድ ምነው እንደዚህ' እንዳላልኩ ለአንድ አሱ ቆዳዬ ሳሳ....".....ከቦርሳዋ ሶፍት አውጥታ አይኗን አደራረቀች።
"ሀኒ......".....አልኳት ጠረጴዛ ላይ ያዳደመችውን ያልበላችበትን እጇን ባልበላሁበት እጄ ጨብጬ.....
"ውሰጂው....."......አልኳት.....የምሬን ነበር።
"ሰው እኮ ነው እድል ኳስ አይደለም.....እንደ ኳስ በጨለዝሽው በኩል አይሄድም.....ልቡ በሚመራው መንገድ እንጂ.....ወደ እኔ ብትገፊው አይደለም ንፋስ አምጥቶ ከእኔ ጋር ቢያላትመው እንኳን ንፋሱ ሲሸሽ ይሸሻል.....ሰው ነው"......አለችኝ እና ፈገግ ነገር አለችልኝ.....
ወዲያው "ፍቅሬን ቀማሽኝ" የሚባባሉ እንስቶች እና ተባዕቶች አእምሮዬ ላይ መጡ.....ሀኒ እውነቷን ነው.....ሰው ናቸው ጆተኒ አልያም ኳስ አይደሉም.....ፈቅደው ይሄዳሉ እንጂ በተወረወሩበት እግር አቅጣጫ አይነዱም።
የሀኒ ስልክ ሲነዝር ያልበላበትን እጇን አስለቀቀችኝ.....
ጉሮሮዋን ጠራርጋ "ሄለው መኬ" ስትል አንገቴን ቀበርኩ.....
አላለቀም......
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
ከክሊኒኩ እንደወጣሁ ቅርብ ያለ ቤተክርስትያን ጠይቄ ላመሰግን ሄድኩ.........ከተወሰኑ ቀናት በፊት "እዚህ አካባቢ መቃብር ስፍራ ካለ ጠቁሙኝ" ያልኩ ሴትዮ ዛሬ "ቤተክርስትያን ጠቁሙኝ" እያልኩ ነው....
ጊዜ እንዲህ ነው...."የማይነጋ ለሊት ማያልፍ ቀን የለም....." የሚል የመዝሙር ስንኝ አቃጨለብኝ...."እውነትም" አልኩኝ በለሆሳስ.....ይሆናል ብለው ከነገሩን በላይ ሆኖ ስናየው እናምናለን.....እኛ እንደሀገርም ሆነ እንደ ህዝብ....እንደ አህጉርም ቢሆን እንደ አለም የሚያመሳስለን ነገር አለ.....እንደ ቶማስ ካላየን አናምንም....እንደ ኤሳው ሆዳችን ከብኩርናችን ይበልጥብናል....ፈጣሪ የሰጠንን ፀጋ ከላያችን ለመላጨት ደሊላ ትበቃናለች.....
የኢዮብን ስም የያዝን ከጂዎች.....የስምኦንን ስም የያዝን አሳቾች....የአብርሀምን ስም የያዝን ንፉጎች....የኢያሱን ስም ይዘን ለአምላካችን ግድ የሌለን ከንቱዎች ሆነናል....ሙሴ ተብሎ አሻጋሪ ጠፍቷል.....የዘመኑ ሙሴ ላሻግራችሁ ብሎ ባህር ከፋይ....ህዝብ አምኖ ከክፋዩ ውሀ መሀል ሲገባ ውሀ የሚያስበላ ነው.....
የዘመኑ ስምኦን እንደ "ስምኦን ጫማ ሰፊው" ሰው አሳትኩኝ ብሎ አይኑ ላይ ወስፌ አይሰድም....ይልቁንም ሰው ለማሳት ጫማው እስኪያልቅ ይኳትናል እንጂ...
ስማችን አይከብደንም.....ምግባራችን አንገት አያስደፋንም.....ደህና ነገር እንደሰራ ሰው እንታበያለን.....እንዳልከፋን እንስቃለን....እንዳለለት እንዘላለን.....መፍራት ያለብንን አንፈራም....መፀየፍ ካለብን ጋር እንጣበቃለን.....ስጋችንን እናምነዋለን....ስጋ ብቻ እንዳለው ሰው እንኖራለን.....
***
"ዛሬ ምሳ የምጋብዝሽ እኔ ነኝ" አልኳት ሀኒን ....የሆነ የማላውቀው መንፈስ ውስጤ አለ አምጫት አምጫት የሚለኝ....ደስታሽ ደስታዋ ነው ንገሪያት የሚለኝ.....ለምን ብቻሽን እሷ እያለችልሽ የሚለኝ መንፈስ ሲታገለኝ ነበር የደወለችልኝ....እግዜር ይስጣት።
ከተገናኘን ወር ሊያልፈን ነበር.....ለአመታት እንዳልተገናኘ ዘመድ ተቃቀፍን.....ደስ አለኝ።
የምንወደውን ምግብ አዘን ሳንጎራረስ እና ሳንተያይ በላን.....እዚህ ጋር ከመክብብ ጋር ስለነበረን የመጀመሪያ ቀን አስታወስኩ.....ትንሽ ትንሽ መደበር እንደጀመርኩ አስተውላ "ምነው.....?" አለቺኝ
"ኧረ ምንም...."....አልኩና ለምን እንደዘጋችኝ ጠየቅኳት....
"አንቺም ዘግተሽኛል እኮ....".....የሚል የሰነፍ መልስ መለሰችልኝ....
"ያንቺን አይደል የጠየቅኩሽ ለምን አትመልሺም".....አልኳት።
"ልጠላሽ አልፈለግኩም.....ትንሽ ትግል ውስጥ ነበርኩ....".....አለችኝ ድምጿ ቀዝቅዞ።
ትንሽ አርፋ ቀጠለች...."ትግል ውስጥ ነበርኩ....እየታገልኩ ነበር.....እኔ በፈለግኩት እና የፈለግኩት በሚፈልገው መሀል ያለውን ልዩነት ላጠብ ስጣጣር ነበር...አንቺን ከመክብብ ጭንቅላት ለማስወጣት እየታገልኩ ነበር...."......አለችና በልምምጥ አይነት አየችኝ......
"ተይልኝ ልልሽ አይደለም.....ምን ብለሽው እንዲህ እንደሆነልሽ ብቻ ንገሪኝ.....እኔ ለሰባት አመት የእሱን ትኩረት ለማግኘት የተጋጋጥኩትን በአንድ ቀን እንዴት ከመሬት ቀላቀልሽው.....እንዴት አርገሽ ብታይው ነው.....አሳሳቅሽ እንዴት ነበር.....ፀጉርሽን አንጨባረሺው ነበር አይደል....የዛን እለት የለበስሽው ልብስ መናኛ ነበር አይደል.....እንዴት ያለ አስተያየት እንዴት ያለ አወራር ነበረሽ.....?.....ወይስ አበላልሽ ነው....አስታውሳለሁ አካሄድሽ እስከዚም ነበር.....ጫማሽ አቧራ ጠጥቶ ነበር.....ትዝ አለሽ ቀሚስሽ ጭቃ ነክቶት ነበር.....".......አለችኝ እና ያለቀው ትሪ ላይ አፈጠጠች.....
አንጀቴ ተላወሰ......"ሀኒ ካንቺ አይበልጥም.....የምሬን ነው.....ይኧውልሽማ....."......ከማለቴ አቋረጠችኝ......እውነቱን ለመናገር "ካንቺ አይበልጥም" ያልኩትን ቃል ስሜታዊነቴ ነው ያበጃጀው.....አንዳንዴ የማናወዳድራቸው ነገሮች አሉ.....እንደ እኔ እንደ እኔ ደረጃ ከመስጠት ሁሉንም እንደ ራሱ መውደድ ይሻላል።
"እንደስምሽ ነሽ ታውቂያለሽ.....እድል አለሽ.....ምን አልባት ፈጣሪ በእሱ ሊክስሽ ይሆናል......"
"የሚክሰው በዳይ ነው.....ሰው እንጂ ፈጣሪ በድሎኝ አያውቅም.....ሀኒ....".......በድጋሚ አቋረጠችኝ.....
"ትናንት መክብብ እንዴት አድርጎ የፍቅር ጥያቄ እንደሚያቀርብልሽ ሲጨነቅ ነው ያመሸው.....ምን ትወድ ይሆን እያለ ልቤን ሲጠባ ነበር.....የምትወጂውን ሳይሆን የምወደውን ልነግረው ስንቴ ከአፌ እንደመለስኩት አታውቂም.....ስንት ጊዜ እድል ፊት እንዳለህ እያሰብክ "አፈቅርሻለሁ" በል እንዳልኩት እና በልቤ ጮክ ብዬ "እኔም አፈቅርሀለሁ" እንዳልኩት አታውቂም.....አንቺን እያሰበ ስንት ጊዜ አፈቅርሻለሁ ሲለኝ እንዳመሸ አታውቂም.....አእምሮዬ ሊፈነዳ አንድ ሀሙስ እንደቀረው አታውቂም....."......አለችና መንታ መንታ እምባ ከአይኖችዋ ተንቆሮቆሩ።
በወደድኩት በመወደዴ ደስ ባለኝ ቅፅበት እንባዋ እንደ እሳት ፈጀኝ.....ልቡ ውስጥ ለመግባት በተመኘሁት እኩል መውጣት አሰኘኝ.....አሳዘነችኝ.....
"ትዝ ይልሻል ልጅ እያለን ያየነው ሻሩክ የሚሰራበት የህንድ ፊልም......"
በህይወት ዘመኔ ያየሁት የህንድ ፊልም እሱ ብቻ ስለነበር አልረሳሁትም.....አንገቴን በአዎንታ ነቀነቅኩላት.....
"እሱ ላይ እንዳለችው እንስት ሳሳሁ.....'ለአንድ ወንድ ምነው እንደዚህ' እንዳላልኩ ለአንድ አሱ ቆዳዬ ሳሳ....".....ከቦርሳዋ ሶፍት አውጥታ አይኗን አደራረቀች።
"ሀኒ......".....አልኳት ጠረጴዛ ላይ ያዳደመችውን ያልበላችበትን እጇን ባልበላሁበት እጄ ጨብጬ.....
"ውሰጂው....."......አልኳት.....የምሬን ነበር።
"ሰው እኮ ነው እድል ኳስ አይደለም.....እንደ ኳስ በጨለዝሽው በኩል አይሄድም.....ልቡ በሚመራው መንገድ እንጂ.....ወደ እኔ ብትገፊው አይደለም ንፋስ አምጥቶ ከእኔ ጋር ቢያላትመው እንኳን ንፋሱ ሲሸሽ ይሸሻል.....ሰው ነው"......አለችኝ እና ፈገግ ነገር አለችልኝ.....
ወዲያው "ፍቅሬን ቀማሽኝ" የሚባባሉ እንስቶች እና ተባዕቶች አእምሮዬ ላይ መጡ.....ሀኒ እውነቷን ነው.....ሰው ናቸው ጆተኒ አልያም ኳስ አይደሉም.....ፈቅደው ይሄዳሉ እንጂ በተወረወሩበት እግር አቅጣጫ አይነዱም።
የሀኒ ስልክ ሲነዝር ያልበላበትን እጇን አስለቀቀችኝ.....
ጉሮሮዋን ጠራርጋ "ሄለው መኬ" ስትል አንገቴን ቀበርኩ.....
አላለቀም......
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
9800
19:56
08.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-17✨✨
"እድል.....".....አለኝና ወደ ወንበሩ ጠቆመኝ.....የያዘውን ትኩስ ምድጃ ለማስቀመጥ እንደሚጣደፍ ሰው ተንድርድሬ ተቀመጥኩ....
ከተቀመጥኩ በኃላ ከቫይረሱ ጋር እንዴት እንደሚኖር አጭር መግለጫ ሲሰጥ ውስጤ ሰለለ...የተቀመጥኩበት ወንበር እንዲያሰምጠኝ ተመኘሁ....መሬት አፏን ከፍታ እንድትውጠኝ ተመኘሁ....እንዳለቀ ጢስ መሰወር አሰኘኝ....መጥፋት እና "በፎቶው ላይ የምትመለከቷት ወጣት እድል ሰጠኝ በእለተ ሀሙስ ከቤት እንደወጣች አልተመለሰችም....በእለቱ የለበሰችው ልብስ....."......ምናምን የሚል የራሴን አፋልጉኝ ማስታወቂያ መንገድ ዳር ቆሞ ማንበብ አማረኝ......
"በቃ እንግዲህ እድል እራስሽን አዘጋጂ...."....."መኖር ይቻላል እኮ.....".....ሌላ ሌላም አልኩ....."ግን አባትሽ ምን ይላል..."...."ለእትሽ ምን ትያታለሽ....".....ጡዘት።
"እውነቱን ለመናገር ከበሽታው በላይ በሽታው ወደ እኔ የመጣበት መንገድ ያንገበግበኛል.... ስንት ቀን ለፍቼ ያመጣሁት በሽታ እንደሆነ ብታውቅ....".....አልኩት እና ፈገግ አልኩለት ልጅ እግር ዶክተሩን....ተረጋግቻለሁ.....መረጋጋቴ ለራሴ ራሱ አልገባኝም.....እንዴት እረጋጋለሁ....?....እንዴት አይኔ ደረቀ....?....መርበትበት አልነበረብኝም.....?....እድል ስጠኝ ያልኩትን አምላክ ላይ መጮህ አልነበረብኝም.....ተረጋግቻለሁ.....ጭንቅላቴ ነገርየውን ገና ፕሮሰስ አላደረገውም ይሆን አላውቅም....ተረጋግቻለሁ።
"ይኧውልሽ እድል.....".....ከማለቱ አቋረጥኩት....ትንሽ ትንሽ ገባኝ....ፈግታዬ ከት ወዳለ ሳቅ ተለወጠ...."እንዴት በባዶ ሆዴ ለፍቼ ያመጣሁት እንደሆነ ብታውቅ ትሸልመኝ ነበር ካካካካካ...."....ሳቄ እንባ ቀላቀለ.....አእምሮዬ ከቁጥጥሬ ውጪ ወደመሆን አዘነበለ.....
"እድል!!!......".....አለና ጠረጴዛውን አንድ ጊዜ በመዳፉ ለጠፈው....
"እድለ ቢስ ብትለኝ አይሻልም....".....አፈጠጥኩበት።
"አንድ ጊዜ ተረጋግተሽ.....".....አሁንም አቋረጥኩት.....
"ስለምን መረጋጋት ነው የምታወራኝ....የምስራች እንደሚነግር ሰው ነጭ ለብሶ መቀመጥማ ቀላል ነው.....ቀላል ነው.....ከቫይረሱ ጋር መኖር ይቻላል ማለትማ ቀላል ነው.....ቆይ መኖር ምንድን ነው.....?....መኖር ላንተ ምንድን ነው.....በየእለቱ አየር መማግና መስደድ ነው ....?......"......እንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ......
ወትሮም የምኖር አይመስለኝም.....አንዳንዴ 'መኖር አስጠላኝ' እልና መልሼ 'እየኖርኩ ነው እንዴ' እላለሁ.....ለኔ መኖር እንዲህ አይደለም።
"ዶክተር ፍቅር ይዞኛል እኮ.....ልቤ የሚያርፍበት አጊኝቷል እኮ....ዶክተር አልገባህም.....አባቴ ፊቴን አያየውም ከንግዲህ....እናቴ የለችም እኮ....አታውቅም አንተ ታናሽ እህት አለኝ እኮ......"......ከዚህም ከዚያም እያማታሁ ማልቀስ ጀመርኩ....
***
መረጋጋቴን ሲጠብቅ የነበረው ዶክተር ዝምታውን ሰበረ.... ነጩን ጋውን አውልቆ ከረባቱን ፈታ.... ከተሰየመበት ወንበር ተነሳና ፊትለፊቴ ተቀመጠ.....
"እንዳትመክረኝ ዶክተር...መኖር ይቻላል እንዳትለኝ ዶክተር....አውቃለሁ....አውቃለሁ እሱን....እኔን ያንገበገበኝ......".....ከማለቴ ሰፌድ በሚያክለው መዳፉ አፌን ያዘና "ከቫይረሱ ነፃ ነሽ!!!" አለኝ።
*
ውበት አይን ይመርጣል....እንደተመልካቹ ነው.....ለኔ ነፃነትንም እንደዛው ነው..... ነፃ መሆንን ካላወቅንበት ራሱ መታሰር ሊሆን ይችላል......
ህመምን ያለ መድሀኒት አይሰጥም....መድሀኒታችን ምን አልባት እኛ እንደምናስበው አይነት መድሀኒት ላይሆን ይችላል.....ምናልባት የሚፈወሰው መንፈሳችን ይሆናል.....ምናልባት ምግባራችን .....ምናልባት ግንኙነታችን.....ምናልባት ስብእናችን....ምናልባት እኛነታችን።
ወዲያው ትናንት በቤተክርስቲያን ደጃፍ ሳልፍ ጆሮዬን የያዘው ትምህርት ትዝ አለኝ....."እረኛ በጎቹን መጀመሪያ በድምፅ ይገስፃቸዋል.....አልመለስ ካሉ በጅራፍ ከገደል አፋፍ ይመልሳቸዋል....በሽታችሁ ከገደል አፋፍ የመለሳችሁ የላችሁም.....?".....ጥያቄ።
*
እንባዬን ጠራርጌ ልጅ እግሩን ዶክተር አመሰገንኩ....ለሌላ ጊዜ ነፃነትን ለማወጅ እንዲህ የሰው ልብ ከፍ ዝቅ እስኪል ባይጠበቅ መልካም እንደሆነ አሳሰብኩ.....
" ላለፉት ሁለት አመታት በዚህ መልኩ ነው ውጤት የምንናገረው...." አለኝ እየሳቀ.....
"ያልታመመውንም ሰው....?".....በአግርሞት ጠየቅኩ።
"አዎ አለኝ በልበ ሙሉነት...."
"ለምን...."....መልሱን ለመስማት ጓጓሁ።
"ኤቲክሱ ግን ብለሽ የማትከራከሪኝ ከሆነ እነግርሻለሁ....".....አለኝና ያስቀመጠውን ጋውን ለበሰ....
"የልብ ድካም አልያም ሌላ severe case ከሌለባቸው በስተቀር ነፃነታቸውን ከማወጃችን በፊት ነፃነታቸውን ለደይቃዎች እንነጥቃቸዋለን.....አለመያዛቸውን ከመናገራችን በፊት ለደይቃዎች መያዝን አእምሯቸው ውስጥ እንከታለን...."
"እኮ ለምን....?......"
"በነፃ የተገኘ ነፃነት አይዘልቅም.....ያላየነው ስሜት አያስፈራንም....ለማናውቀውን መጥፎ ስሜት አንታገልም....ነፃነት አክባሪውን ያከብራል.....በነፃ አንሰጣቸውም".......አፌን ከፍቼ ቀረሁ።
አላለቀም.....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
"እድል.....".....አለኝና ወደ ወንበሩ ጠቆመኝ.....የያዘውን ትኩስ ምድጃ ለማስቀመጥ እንደሚጣደፍ ሰው ተንድርድሬ ተቀመጥኩ....
ከተቀመጥኩ በኃላ ከቫይረሱ ጋር እንዴት እንደሚኖር አጭር መግለጫ ሲሰጥ ውስጤ ሰለለ...የተቀመጥኩበት ወንበር እንዲያሰምጠኝ ተመኘሁ....መሬት አፏን ከፍታ እንድትውጠኝ ተመኘሁ....እንዳለቀ ጢስ መሰወር አሰኘኝ....መጥፋት እና "በፎቶው ላይ የምትመለከቷት ወጣት እድል ሰጠኝ በእለተ ሀሙስ ከቤት እንደወጣች አልተመለሰችም....በእለቱ የለበሰችው ልብስ....."......ምናምን የሚል የራሴን አፋልጉኝ ማስታወቂያ መንገድ ዳር ቆሞ ማንበብ አማረኝ......
"በቃ እንግዲህ እድል እራስሽን አዘጋጂ...."....."መኖር ይቻላል እኮ.....".....ሌላ ሌላም አልኩ....."ግን አባትሽ ምን ይላል..."...."ለእትሽ ምን ትያታለሽ....".....ጡዘት።
"እውነቱን ለመናገር ከበሽታው በላይ በሽታው ወደ እኔ የመጣበት መንገድ ያንገበግበኛል.... ስንት ቀን ለፍቼ ያመጣሁት በሽታ እንደሆነ ብታውቅ....".....አልኩት እና ፈገግ አልኩለት ልጅ እግር ዶክተሩን....ተረጋግቻለሁ.....መረጋጋቴ ለራሴ ራሱ አልገባኝም.....እንዴት እረጋጋለሁ....?....እንዴት አይኔ ደረቀ....?....መርበትበት አልነበረብኝም.....?....እድል ስጠኝ ያልኩትን አምላክ ላይ መጮህ አልነበረብኝም.....ተረጋግቻለሁ.....ጭንቅላቴ ነገርየውን ገና ፕሮሰስ አላደረገውም ይሆን አላውቅም....ተረጋግቻለሁ።
"ይኧውልሽ እድል.....".....ከማለቱ አቋረጥኩት....ትንሽ ትንሽ ገባኝ....ፈግታዬ ከት ወዳለ ሳቅ ተለወጠ...."እንዴት በባዶ ሆዴ ለፍቼ ያመጣሁት እንደሆነ ብታውቅ ትሸልመኝ ነበር ካካካካካ...."....ሳቄ እንባ ቀላቀለ.....አእምሮዬ ከቁጥጥሬ ውጪ ወደመሆን አዘነበለ.....
"እድል!!!......".....አለና ጠረጴዛውን አንድ ጊዜ በመዳፉ ለጠፈው....
"እድለ ቢስ ብትለኝ አይሻልም....".....አፈጠጥኩበት።
"አንድ ጊዜ ተረጋግተሽ.....".....አሁንም አቋረጥኩት.....
"ስለምን መረጋጋት ነው የምታወራኝ....የምስራች እንደሚነግር ሰው ነጭ ለብሶ መቀመጥማ ቀላል ነው.....ቀላል ነው.....ከቫይረሱ ጋር መኖር ይቻላል ማለትማ ቀላል ነው.....ቆይ መኖር ምንድን ነው.....?....መኖር ላንተ ምንድን ነው.....በየእለቱ አየር መማግና መስደድ ነው ....?......"......እንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ......
ወትሮም የምኖር አይመስለኝም.....አንዳንዴ 'መኖር አስጠላኝ' እልና መልሼ 'እየኖርኩ ነው እንዴ' እላለሁ.....ለኔ መኖር እንዲህ አይደለም።
"ዶክተር ፍቅር ይዞኛል እኮ.....ልቤ የሚያርፍበት አጊኝቷል እኮ....ዶክተር አልገባህም.....አባቴ ፊቴን አያየውም ከንግዲህ....እናቴ የለችም እኮ....አታውቅም አንተ ታናሽ እህት አለኝ እኮ......"......ከዚህም ከዚያም እያማታሁ ማልቀስ ጀመርኩ....
***
መረጋጋቴን ሲጠብቅ የነበረው ዶክተር ዝምታውን ሰበረ.... ነጩን ጋውን አውልቆ ከረባቱን ፈታ.... ከተሰየመበት ወንበር ተነሳና ፊትለፊቴ ተቀመጠ.....
"እንዳትመክረኝ ዶክተር...መኖር ይቻላል እንዳትለኝ ዶክተር....አውቃለሁ....አውቃለሁ እሱን....እኔን ያንገበገበኝ......".....ከማለቴ ሰፌድ በሚያክለው መዳፉ አፌን ያዘና "ከቫይረሱ ነፃ ነሽ!!!" አለኝ።
*
ውበት አይን ይመርጣል....እንደተመልካቹ ነው.....ለኔ ነፃነትንም እንደዛው ነው..... ነፃ መሆንን ካላወቅንበት ራሱ መታሰር ሊሆን ይችላል......
ህመምን ያለ መድሀኒት አይሰጥም....መድሀኒታችን ምን አልባት እኛ እንደምናስበው አይነት መድሀኒት ላይሆን ይችላል.....ምናልባት የሚፈወሰው መንፈሳችን ይሆናል.....ምናልባት ምግባራችን .....ምናልባት ግንኙነታችን.....ምናልባት ስብእናችን....ምናልባት እኛነታችን።
ወዲያው ትናንት በቤተክርስቲያን ደጃፍ ሳልፍ ጆሮዬን የያዘው ትምህርት ትዝ አለኝ....."እረኛ በጎቹን መጀመሪያ በድምፅ ይገስፃቸዋል.....አልመለስ ካሉ በጅራፍ ከገደል አፋፍ ይመልሳቸዋል....በሽታችሁ ከገደል አፋፍ የመለሳችሁ የላችሁም.....?".....ጥያቄ።
*
እንባዬን ጠራርጌ ልጅ እግሩን ዶክተር አመሰገንኩ....ለሌላ ጊዜ ነፃነትን ለማወጅ እንዲህ የሰው ልብ ከፍ ዝቅ እስኪል ባይጠበቅ መልካም እንደሆነ አሳሰብኩ.....
" ላለፉት ሁለት አመታት በዚህ መልኩ ነው ውጤት የምንናገረው...." አለኝ እየሳቀ.....
"ያልታመመውንም ሰው....?".....በአግርሞት ጠየቅኩ።
"አዎ አለኝ በልበ ሙሉነት...."
"ለምን...."....መልሱን ለመስማት ጓጓሁ።
"ኤቲክሱ ግን ብለሽ የማትከራከሪኝ ከሆነ እነግርሻለሁ....".....አለኝና ያስቀመጠውን ጋውን ለበሰ....
"የልብ ድካም አልያም ሌላ severe case ከሌለባቸው በስተቀር ነፃነታቸውን ከማወጃችን በፊት ነፃነታቸውን ለደይቃዎች እንነጥቃቸዋለን.....አለመያዛቸውን ከመናገራችን በፊት ለደይቃዎች መያዝን አእምሯቸው ውስጥ እንከታለን...."
"እኮ ለምን....?......"
"በነፃ የተገኘ ነፃነት አይዘልቅም.....ያላየነው ስሜት አያስፈራንም....ለማናውቀውን መጥፎ ስሜት አንታገልም....ነፃነት አክባሪውን ያከብራል.....በነፃ አንሰጣቸውም".......አፌን ከፍቼ ቀረሁ።
አላለቀም.....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
10800
19:50
07.05.2025
imageImage preview is unavailable
ፊልሙ ፊልም አይደለም። ማለቴ መነሻው መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ ተወዳጅ ሲሆን በፊልም ተሰርቶ መጣ
።በባህሪዬ አንድ ነገር እጅግ ሲገን ራቅ ብዬ መመልከት እመርጣለሁ። አያችሁ! ያ ነገር አልሰከነም። እጅ በዝቶበታል፤ ተመልካችም እንዲሁ። እጅ የበዛበት ነገር ደግሞ የሚሰክነው ግዜ ወስዶ ነው። አለም ሁሉ ነገሩን ረስቶ በሚቀመጥበት ግዜ የኔ ተራ ነው—ያኔ መጽሐፉን አነበዋለህ፤ ፊልሙን አየዋለህ። የወረት ፍቅር አልወድም።
9500
18:13
07.05.2025
imageImage preview is unavailable
🚥የትም ብትሄዱ እንደዚህ አይነት ቻናል አታገኙም! እመነኝ እስካሁን ይሄ ቻናል ከሌለህ 100% ተበልተሀል! ብዙ ነገር አምልጦሀል!
🚥አስደንጋጭ እና አነጋጋሪ የአለም ክስተቶችን ከአዝናኝ እና አስተማሪ ዝግጅቶች እያሰናዳ የሚያቀርብ ምርጥዬ ቻናል እናስተዋውቅዎ!
🚥በየቀኑ የሚለቀቁ አለምን ያስገረሙ ድንቃ ድንቅ ወሬዎች ፣ በቪድዮ የተደገፉ አስደናቂ እና አስደንጋጭ ሁነቶች ፣ አስገራሚ ሰዎች ፣ መሳጭ ታሪኮች ማታ ላይ ፈታኘ የጠቅላላ እውቀት ጥያቄዎች ሁሉ በአንድ ላይ የያዘ ሁሉን አቀፍ ቻናል😎
💛እውነት ዝም ብላችሁ "JOIN" በሉ በኔ ይሁንባችሁ !! ይወቁ ይማሩ ይዝናኑ ይደሰቱ*
👇JOIN❤️
https://t.me/+ntT8Z8jyixswZDE0
https://t.me/+ntT8Z8jyixswZDE0
🚥አስደንጋጭ እና አነጋጋሪ የአለም ክስተቶችን ከአዝናኝ እና አስተማሪ ዝግጅቶች እያሰናዳ የሚያቀርብ ምርጥዬ ቻናል እናስተዋውቅዎ!
🚥በየቀኑ የሚለቀቁ አለምን ያስገረሙ ድንቃ ድንቅ ወሬዎች ፣ በቪድዮ የተደገፉ አስደናቂ እና አስደንጋጭ ሁነቶች ፣ አስገራሚ ሰዎች ፣ መሳጭ ታሪኮች ማታ ላይ ፈታኘ የጠቅላላ እውቀት ጥያቄዎች ሁሉ በአንድ ላይ የያዘ ሁሉን አቀፍ ቻናል😎
💛እውነት ዝም ብላችሁ "JOIN" በሉ በኔ ይሁንባችሁ !! ይወቁ ይማሩ ይዝናኑ ይደሰቱ*
👇JOIN❤️
https://t.me/+ntT8Z8jyixswZDE0
https://t.me/+ntT8Z8jyixswZDE0
3300
18:01
07.05.2025
በቴሌግራም ለረጅም ጊዜ እንግሊዘኛ ቋንቋን በማስተማር በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈው Learn English language በአዲስ አቀራረብ እና በአዲስ ይዘት መቷል።
በቴሌግራም ቻናላችን👇👇
⭐️ Daily speaking practice
⭐️ Spoken English
⭐️ Most used vocabularies
⭐️ Daily phrases
⭐️ Idioms
⭐️ Listening practice
⭐️ Quiz
⭐️ English learning tips
ቻናላችንንን ይቀላቀሉ 👇👇
Learn English Language✅
Learn English Language✅
በቴሌግራም ቻናላችን👇👇
ቻናላችንንን ይቀላቀሉ 👇👇
Learn English Language
Learn English Language
1200
15:29
07.05.2025
imageImage preview is unavailable
....
ታዳጊዋ Rahaf እንዲህ ስጋዋ አልቆ በአጥንቷ ያስቀራት ረሀብ ነው ። ሰው ሰራሽ ረሀብ 😥
የአለም ህዝብ አይቶ እንዳላየ ችላ ያለው ረሀብ ። እሱ ነው እንዲህ የልጅነት መልኳን የመጠጠው ።
.....
...
.....
Wassihun tesfaye
9800
14:56
07.05.2025
imageImage preview is unavailable
ባሸንፍ እንኳ ያልቅልኛል፡- ፍልሚያን የመምረጥ ምስጢር
(“ትኩረት” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)
ወቅቱ ግሪክና ሮም የጦርነት ፍጥጫ ላይ የነበሩበት ዘመን ነው፡፡ በሁለቱም ወገን 40 ሺህ የሚያክል ጽኑ የጦር ሰራዊት ተሰልፏል፡፡ የግሪኩ ንጉስ ፓይረስ (King Pyrrus) አይኖቹን ሮም ላይ ተክሏል፡፡ “ሮምን ካላሸነፍኩ አላርፍም” ያለ ይመስላል፤ ማንም ሰው ከዚህ አቋሙ ሊመልሰው እስከማይችል ድረስ ቆርጦ ነበር፡፡ የጦር መሳሪያ አይነት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸውን ዝሆኖች ሁሉ ሳይቀር ሰብስቧል፡፡
ከዚህ በፊት የተፋለመውን ፍልሚያ ሁሉ በማሸነፍ የታወቀ ንጉስ ነው፡፡ የሮም አገዛዝ ያበቃለት ይመስላል፡፡ ውጊያው ጀምሮ ብዙ መራራ ቀናትን ካስቆጠረ በኋላ ማንም የማያሸንፍበት የእልቂት ፍጥጫ ሆነ፡፡ ሆኖም፣ በድንገት ግሪኮች ድልን ተቀዳጁ፡፡ ግዙፍ ዝሆኖቻቸው በብዙ ቁጥር ሆነው ወደ ሮማውያን ክልል ጥሰው በመግባታቸው ከሞት የተረፉት ሮማውያን ወደ ኋላ መሸሽ ግድ ሆነባቸው፡፡
የንጉስ ፓይረስ ሰራዊት ግን እጅግ ደክሟል፡፡ ጉልበትን ለመሰብሰብ ባለበት ስፍራ ከሰራዊቱ ጋር ተከማችቶ እንዳለ አንድ ወዳጁ ስላገኘው ድል “እንኳን ደስ ያለህ” አለው፡፡ ንጉስ ፓይረስ የመለሰው መልስ እንዲህ የሚል ነበር፣ “ከአሁን ወዲያ አንድ ፍልሚያ ተፋልሜ ባሸንፍ እንኳ ያልቅልኛል”፡፡
አንዳንድ ጊዜ በፊታችን የመጣውን ፍልሚያ ሁሉ መዋጋትና ማሸነፍ ያለብን ይመስለናል፡፡ የተጫረ ጸብ ውስጥ ሁሉ ራሳችንን እንጨምራለን፣ ለተናገረን ሰው ሁሉ መልስ ለመስጠት ጊዜ አይፈጅብንም፣ ለነካን ሰው አጸፋ ሳንመልስ እንቅልፍ አይወስደንም፡፡ በዚህ “ብርታታችን” ከዚህ በፊት ብዙዎችን አንበርክከን ሊሆን ይችላል፡፡
መለስ ብለን ሕይወታችንን ስናጤነው ግን አንድ ሺህ ፍልሚያዎችን አሸንፈን፣ ነገር ግን አንድን ነገር ለመገንባት ጊዜ ያጣን ሰዎች ሆነን ራሳችንን እናገኘዋለን፡፡ ብዙ የተዋጋናቸው ሁኔታዎችና ሰዎች በታሪካችን ተመዝግበው አንድም የገነባነው ቁም ነገር ከሌለ ትኩረት የተነጠቀ ሰው የመሆናችን እውነታ አከራካሪ አይደለም፡፡
የሕይወትን ውጣ ውረድ በሚገባ ስንቃኘውና ስንጨምቀው እውነተኛ ፍልሚያን ልንፋለምባቸው የሚገቡን ነገሮች በጣም ጥቂት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡
ብዙ ሰዎች በሞት አልጋቸው ላይ ሆነው ሲጠየቁ ወይም የመናገር እድል ሲያገኙ በሕይወት ዘመናቸው በወሰዷቸው አንዳንድ እርምጃዎችና ውሳኔዎች ላይ የሚናገሩት ነገር አላቸው፡፡
አንዳንዶች፣ “እገሌን ጥሩልኝና ይቅርታ ልጠይቀው” በማለት በዘመናቸው ሲጋፉት የኖሩትን ሰው በመጨረሻ ትንፋሻቸው ሊያቅፉት ይሞክራሉ፡፡ ሌሎች፣ “ለእገሌ የወሰድኩበትን ይህንና ያንን ነገር እባካችሁ መልሱልኝ” በማለት በውጊያ የወሰዱትን በልመና ሊመልሱ ይመኛሉ፡፡
“ይህንን ንብረቴን ለእገሌ አውርሱልኝ” በማለትም በብዙ ፍልሚያ የሰበሰቡትን ንብረት መልቀቅ ምርጫ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ አይተውና አሳይተው የሚያልፉም ብዙ ናቸው፡፡
ሕይወት ምንድን ነች? ሕይወት ሁለተኛ እድል የማትሰጥና ከራሳችን አልፈን ለሌላው የሚጠቅም ነገር አድርገን አጣጥመናት ልናልፋት የምትገባ ትእይንት ናት እንጂ ሕይወት በጠላት የተከበበችና ለፍልሚያ የተወሰነች የጦርነት ሜዳ አይደለችም፡፡
ለአንዳንዶች ግን ይህ የሕይወት ስእል በፍጹም ተቀባይነት የማያገኝ ጉዳይ ነው፡፡ የሚያውቁት ሌላ ነውና፡፡ በእርግጥ ነው በዚህች ምድር ላይ ስንኖር የማንፈልጋቸው ሙግቶችና ትግሎች አልፈው ወደ እኛ ይመጣሉ፡፡ ስለሆነም፣ ሕይወት ከምንም ችግር ነጻ የሆነች ጎዳና ነች ማለት አስቸጋሪ ነው፡፡
ለማለት የተፈለገው የመጣውን ግፊያ ሁሉ መጋፋት፣ የተነሳውን ውድድር ሁሉ መወዳደር፣ የተከሰተውን ፍትጊያ ሁሉ የመፋተግ ግዴታ የለብንም፡፡ የምንፋለማቸውን ፍልሚያዎች የመምረጥ እድሉም ሆነ ብቃቱ አለን፡፡
የሕይወታችን ጥራት የሚለካው ባሸነፍናቸው ፍልሚያዎች ሳይሆን በመረጥናቸው የፍልሚያ አይነቶች ነው፡፡ የምትሰለፍለት ዓላማና የምትከራከርለት ነጥብ የውስጥህን አመለካከት ጠቋሚ ነውና፡፡ ተራ ሰው ለተራ ነገር ይጋፋል፣ የከበረው ሰው ደግሞ ፍልሚያዎቹን መዝኖ ለከበረውና ለዘላቂው ነገር ራሱን ያቀርባል፡፡ ልዩነቱ እዚህ ላይ ነው፡፡
➡️ @Enmare1988
➡️ @Enmare1988
(“ትኩረት” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)
ወቅቱ ግሪክና ሮም የጦርነት ፍጥጫ ላይ የነበሩበት ዘመን ነው፡፡ በሁለቱም ወገን 40 ሺህ የሚያክል ጽኑ የጦር ሰራዊት ተሰልፏል፡፡ የግሪኩ ንጉስ ፓይረስ (King Pyrrus) አይኖቹን ሮም ላይ ተክሏል፡፡ “ሮምን ካላሸነፍኩ አላርፍም” ያለ ይመስላል፤ ማንም ሰው ከዚህ አቋሙ ሊመልሰው እስከማይችል ድረስ ቆርጦ ነበር፡፡ የጦር መሳሪያ አይነት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸውን ዝሆኖች ሁሉ ሳይቀር ሰብስቧል፡፡
ከዚህ በፊት የተፋለመውን ፍልሚያ ሁሉ በማሸነፍ የታወቀ ንጉስ ነው፡፡ የሮም አገዛዝ ያበቃለት ይመስላል፡፡ ውጊያው ጀምሮ ብዙ መራራ ቀናትን ካስቆጠረ በኋላ ማንም የማያሸንፍበት የእልቂት ፍጥጫ ሆነ፡፡ ሆኖም፣ በድንገት ግሪኮች ድልን ተቀዳጁ፡፡ ግዙፍ ዝሆኖቻቸው በብዙ ቁጥር ሆነው ወደ ሮማውያን ክልል ጥሰው በመግባታቸው ከሞት የተረፉት ሮማውያን ወደ ኋላ መሸሽ ግድ ሆነባቸው፡፡
የንጉስ ፓይረስ ሰራዊት ግን እጅግ ደክሟል፡፡ ጉልበትን ለመሰብሰብ ባለበት ስፍራ ከሰራዊቱ ጋር ተከማችቶ እንዳለ አንድ ወዳጁ ስላገኘው ድል “እንኳን ደስ ያለህ” አለው፡፡ ንጉስ ፓይረስ የመለሰው መልስ እንዲህ የሚል ነበር፣ “ከአሁን ወዲያ አንድ ፍልሚያ ተፋልሜ ባሸንፍ እንኳ ያልቅልኛል”፡፡
አንዳንድ ጊዜ በፊታችን የመጣውን ፍልሚያ ሁሉ መዋጋትና ማሸነፍ ያለብን ይመስለናል፡፡ የተጫረ ጸብ ውስጥ ሁሉ ራሳችንን እንጨምራለን፣ ለተናገረን ሰው ሁሉ መልስ ለመስጠት ጊዜ አይፈጅብንም፣ ለነካን ሰው አጸፋ ሳንመልስ እንቅልፍ አይወስደንም፡፡ በዚህ “ብርታታችን” ከዚህ በፊት ብዙዎችን አንበርክከን ሊሆን ይችላል፡፡
መለስ ብለን ሕይወታችንን ስናጤነው ግን አንድ ሺህ ፍልሚያዎችን አሸንፈን፣ ነገር ግን አንድን ነገር ለመገንባት ጊዜ ያጣን ሰዎች ሆነን ራሳችንን እናገኘዋለን፡፡ ብዙ የተዋጋናቸው ሁኔታዎችና ሰዎች በታሪካችን ተመዝግበው አንድም የገነባነው ቁም ነገር ከሌለ ትኩረት የተነጠቀ ሰው የመሆናችን እውነታ አከራካሪ አይደለም፡፡
የሕይወትን ውጣ ውረድ በሚገባ ስንቃኘውና ስንጨምቀው እውነተኛ ፍልሚያን ልንፋለምባቸው የሚገቡን ነገሮች በጣም ጥቂት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡
ብዙ ሰዎች በሞት አልጋቸው ላይ ሆነው ሲጠየቁ ወይም የመናገር እድል ሲያገኙ በሕይወት ዘመናቸው በወሰዷቸው አንዳንድ እርምጃዎችና ውሳኔዎች ላይ የሚናገሩት ነገር አላቸው፡፡
አንዳንዶች፣ “እገሌን ጥሩልኝና ይቅርታ ልጠይቀው” በማለት በዘመናቸው ሲጋፉት የኖሩትን ሰው በመጨረሻ ትንፋሻቸው ሊያቅፉት ይሞክራሉ፡፡ ሌሎች፣ “ለእገሌ የወሰድኩበትን ይህንና ያንን ነገር እባካችሁ መልሱልኝ” በማለት በውጊያ የወሰዱትን በልመና ሊመልሱ ይመኛሉ፡፡
“ይህንን ንብረቴን ለእገሌ አውርሱልኝ” በማለትም በብዙ ፍልሚያ የሰበሰቡትን ንብረት መልቀቅ ምርጫ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ አይተውና አሳይተው የሚያልፉም ብዙ ናቸው፡፡
ሕይወት ምንድን ነች? ሕይወት ሁለተኛ እድል የማትሰጥና ከራሳችን አልፈን ለሌላው የሚጠቅም ነገር አድርገን አጣጥመናት ልናልፋት የምትገባ ትእይንት ናት እንጂ ሕይወት በጠላት የተከበበችና ለፍልሚያ የተወሰነች የጦርነት ሜዳ አይደለችም፡፡
ለአንዳንዶች ግን ይህ የሕይወት ስእል በፍጹም ተቀባይነት የማያገኝ ጉዳይ ነው፡፡ የሚያውቁት ሌላ ነውና፡፡ በእርግጥ ነው በዚህች ምድር ላይ ስንኖር የማንፈልጋቸው ሙግቶችና ትግሎች አልፈው ወደ እኛ ይመጣሉ፡፡ ስለሆነም፣ ሕይወት ከምንም ችግር ነጻ የሆነች ጎዳና ነች ማለት አስቸጋሪ ነው፡፡
ለማለት የተፈለገው የመጣውን ግፊያ ሁሉ መጋፋት፣ የተነሳውን ውድድር ሁሉ መወዳደር፣ የተከሰተውን ፍትጊያ ሁሉ የመፋተግ ግዴታ የለብንም፡፡ የምንፋለማቸውን ፍልሚያዎች የመምረጥ እድሉም ሆነ ብቃቱ አለን፡፡
የሕይወታችን ጥራት የሚለካው ባሸነፍናቸው ፍልሚያዎች ሳይሆን በመረጥናቸው የፍልሚያ አይነቶች ነው፡፡ የምትሰለፍለት ዓላማና የምትከራከርለት ነጥብ የውስጥህን አመለካከት ጠቋሚ ነውና፡፡ ተራ ሰው ለተራ ነገር ይጋፋል፣ የከበረው ሰው ደግሞ ፍልሚያዎቹን መዝኖ ለከበረውና ለዘላቂው ነገር ራሱን ያቀርባል፡፡ ልዩነቱ እዚህ ላይ ነው፡፡
10600
05:37
07.05.2025
imageImage preview is unavailable
ባሸንፍ እንኳ ያልቅልኛል፡- ፍልሚያን የመምረጥ ምስጢር
(“ትኩረት” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)
ወቅቱ ግሪክና ሮም የጦርነት ፍጥጫ ላይ የነበሩበት ዘመን ነው፡፡ በሁለቱም ወገን 40 ሺህ የሚያክል ጽኑ የጦር ሰራዊት ተሰልፏል፡፡ የግሪኩ ንጉስ ፓይረስ (King Pyrrus) አይኖቹን ሮም ላይ ተክሏል፡፡ “ሮምን ካላሸነፍኩ አላርፍም” ያለ ይመስላል፤ ማንም ሰው ከዚህ አቋሙ ሊመልሰው እስከማይችል ድረስ ቆርጦ ነበር፡፡ የጦር መሳሪያ አይነት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸውን ዝሆኖች ሁሉ ሳይቀር ሰብስቧል፡፡
ከዚህ በፊት የተፋለመውን ፍልሚያ ሁሉ በማሸነፍ የታወቀ ንጉስ ነው፡፡ የሮም አገዛዝ ያበቃለት ይመስላል፡፡ ውጊያው ጀምሮ ብዙ መራራ ቀናትን ካስቆጠረ በኋላ ማንም የማያሸንፍበት የእልቂት ፍጥጫ ሆነ፡፡ ሆኖም፣ በድንገት ግሪኮች ድልን ተቀዳጁ፡፡ ግዙፍ ዝሆኖቻቸው በብዙ ቁጥር ሆነው ወደ ሮማውያን ክልል ጥሰው በመግባታቸው ከሞት የተረፉት ሮማውያን ወደ ኋላ መሸሽ ግድ ሆነባቸው፡፡
የንጉስ ፓይረስ ሰራዊት ግን እጅግ ደክሟል፡፡ ጉልበትን ለመሰብሰብ ባለበት ስፍራ ከሰራዊቱ ጋር ተከማችቶ እንዳለ አንድ ወዳጁ ስላገኘው ድል “እንኳን ደስ ያለህ” አለው፡፡ ንጉስ ፓይረስ የመለሰው መልስ እንዲህ የሚል ነበር፣ “ከአሁን ወዲያ አንድ ፍልሚያ ተፋልሜ ባሸንፍ እንኳ ያልቅልኛል”፡፡
አንዳንድ ጊዜ በፊታችን የመጣውን ፍልሚያ ሁሉ መዋጋትና ማሸነፍ ያለብን ይመስለናል፡፡ የተጫረ ጸብ ውስጥ ሁሉ ራሳችንን እንጨምራለን፣ ለተናገረን ሰው ሁሉ መልስ ለመስጠት ጊዜ አይፈጅብንም፣ ለነካን ሰው አጸፋ ሳንመልስ እንቅልፍ አይወስደንም፡፡ በዚህ “ብርታታችን” ከዚህ በፊት ብዙዎችን አንበርክከን ሊሆን ይችላል፡፡
መለስ ብለን ሕይወታችንን ስናጤነው ግን አንድ ሺህ ፍልሚያዎችን አሸንፈን፣ ነገር ግን አንድን ነገር ለመገንባት ጊዜ ያጣን ሰዎች ሆነን ራሳችንን እናገኘዋለን፡፡ ብዙ የተዋጋናቸው ሁኔታዎችና ሰዎች በታሪካችን ተመዝግበው አንድም የገነባነው ቁም ነገር ከሌለ ትኩረት የተነጠቀ ሰው የመሆናችን እውነታ አከራካሪ አይደለም፡፡
የሕይወትን ውጣ ውረድ በሚገባ ስንቃኘውና ስንጨምቀው እውነተኛ ፍልሚያን ልንፋለምባቸው የሚገቡን ነገሮች በጣም ጥቂት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡
ብዙ ሰዎች በሞት አልጋቸው ላይ ሆነው ሲጠየቁ ወይም የመናገር እድል ሲያገኙ በሕይወት ዘመናቸው በወሰዷቸው አንዳንድ እርምጃዎችና ውሳኔዎች ላይ የሚናገሩት ነገር አላቸው፡፡
አንዳንዶች፣ “እገሌን ጥሩልኝና ይቅርታ ልጠይቀው” በማለት በዘመናቸው ሲጋፉት የኖሩትን ሰው በመጨረሻ ትንፋሻቸው ሊያቅፉት ይሞክራሉ፡፡ ሌሎች፣ “ለእገሌ የወሰድኩበትን ይህንና ያንን ነገር እባካችሁ መልሱልኝ” በማለት በውጊያ የወሰዱትን በልመና ሊመልሱ ይመኛሉ፡፡
“ይህንን ንብረቴን ለእገሌ አውርሱልኝ” በማለትም በብዙ ፍልሚያ የሰበሰቡትን ንብረት መልቀቅ ምርጫ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ አይተውና አሳይተው የሚያልፉም ብዙ ናቸው፡፡
ሕይወት ምንድን ነች? ሕይወት ሁለተኛ እድል የማትሰጥና ከራሳችን አልፈን ለሌላው የሚጠቅም ነገር አድርገን አጣጥመናት ልናልፋት የምትገባ ትእይንት ናት እንጂ ሕይወት በጠላት የተከበበችና ለፍልሚያ የተወሰነች የጦርነት ሜዳ አይደለችም፡፡
ለአንዳንዶች ግን ይህ የሕይወት ስእል በፍጹም ተቀባይነት የማያገኝ ጉዳይ ነው፡፡ የሚያውቁት ሌላ ነውና፡፡ በእርግጥ ነው በዚህች ምድር ላይ ስንኖር የማንፈልጋቸው ሙግቶችና ትግሎች አልፈው ወደ እኛ ይመጣሉ፡፡ ስለሆነም፣ ሕይወት ከምንም ችግር ነጻ የሆነች ጎዳና ነች ማለት አስቸጋሪ ነው፡፡
ለማለት የተፈለገው የመጣውን ግፊያ ሁሉ መጋፋት፣ የተነሳውን ውድድር ሁሉ መወዳደር፣ የተከሰተውን ፍትጊያ ሁሉ የመፋተግ ግዴታ የለብንም፡፡ የምንፋለማቸውን ፍልሚያዎች የመምረጥ እድሉም ሆነ ብቃቱ አለን፡፡
የሕይወታችን ጥራት የሚለካው ባሸነፍናቸው ፍልሚያዎች ሳይሆን በመረጥናቸው የፍልሚያ አይነቶች ነው፡፡ የምትሰለፍለት ዓላማና የምትከራከርለት ነጥብ የውስጥህን አመለካከት ጠቋሚ ነውና፡፡ ተራ ሰው ለተራ ነገር ይጋፋል፣ የከበረው ሰው ደግሞ ፍልሚያዎቹን መዝኖ ለከበረውና ለዘላቂው ነገር ራሱን ያቀርባል፡፡ ልዩነቱ እዚህ ላይ ነው፡፡
(“ትኩረት” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)
ወቅቱ ግሪክና ሮም የጦርነት ፍጥጫ ላይ የነበሩበት ዘመን ነው፡፡ በሁለቱም ወገን 40 ሺህ የሚያክል ጽኑ የጦር ሰራዊት ተሰልፏል፡፡ የግሪኩ ንጉስ ፓይረስ (King Pyrrus) አይኖቹን ሮም ላይ ተክሏል፡፡ “ሮምን ካላሸነፍኩ አላርፍም” ያለ ይመስላል፤ ማንም ሰው ከዚህ አቋሙ ሊመልሰው እስከማይችል ድረስ ቆርጦ ነበር፡፡ የጦር መሳሪያ አይነት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸውን ዝሆኖች ሁሉ ሳይቀር ሰብስቧል፡፡
ከዚህ በፊት የተፋለመውን ፍልሚያ ሁሉ በማሸነፍ የታወቀ ንጉስ ነው፡፡ የሮም አገዛዝ ያበቃለት ይመስላል፡፡ ውጊያው ጀምሮ ብዙ መራራ ቀናትን ካስቆጠረ በኋላ ማንም የማያሸንፍበት የእልቂት ፍጥጫ ሆነ፡፡ ሆኖም፣ በድንገት ግሪኮች ድልን ተቀዳጁ፡፡ ግዙፍ ዝሆኖቻቸው በብዙ ቁጥር ሆነው ወደ ሮማውያን ክልል ጥሰው በመግባታቸው ከሞት የተረፉት ሮማውያን ወደ ኋላ መሸሽ ግድ ሆነባቸው፡፡
የንጉስ ፓይረስ ሰራዊት ግን እጅግ ደክሟል፡፡ ጉልበትን ለመሰብሰብ ባለበት ስፍራ ከሰራዊቱ ጋር ተከማችቶ እንዳለ አንድ ወዳጁ ስላገኘው ድል “እንኳን ደስ ያለህ” አለው፡፡ ንጉስ ፓይረስ የመለሰው መልስ እንዲህ የሚል ነበር፣ “ከአሁን ወዲያ አንድ ፍልሚያ ተፋልሜ ባሸንፍ እንኳ ያልቅልኛል”፡፡
አንዳንድ ጊዜ በፊታችን የመጣውን ፍልሚያ ሁሉ መዋጋትና ማሸነፍ ያለብን ይመስለናል፡፡ የተጫረ ጸብ ውስጥ ሁሉ ራሳችንን እንጨምራለን፣ ለተናገረን ሰው ሁሉ መልስ ለመስጠት ጊዜ አይፈጅብንም፣ ለነካን ሰው አጸፋ ሳንመልስ እንቅልፍ አይወስደንም፡፡ በዚህ “ብርታታችን” ከዚህ በፊት ብዙዎችን አንበርክከን ሊሆን ይችላል፡፡
መለስ ብለን ሕይወታችንን ስናጤነው ግን አንድ ሺህ ፍልሚያዎችን አሸንፈን፣ ነገር ግን አንድን ነገር ለመገንባት ጊዜ ያጣን ሰዎች ሆነን ራሳችንን እናገኘዋለን፡፡ ብዙ የተዋጋናቸው ሁኔታዎችና ሰዎች በታሪካችን ተመዝግበው አንድም የገነባነው ቁም ነገር ከሌለ ትኩረት የተነጠቀ ሰው የመሆናችን እውነታ አከራካሪ አይደለም፡፡
የሕይወትን ውጣ ውረድ በሚገባ ስንቃኘውና ስንጨምቀው እውነተኛ ፍልሚያን ልንፋለምባቸው የሚገቡን ነገሮች በጣም ጥቂት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡
ብዙ ሰዎች በሞት አልጋቸው ላይ ሆነው ሲጠየቁ ወይም የመናገር እድል ሲያገኙ በሕይወት ዘመናቸው በወሰዷቸው አንዳንድ እርምጃዎችና ውሳኔዎች ላይ የሚናገሩት ነገር አላቸው፡፡
አንዳንዶች፣ “እገሌን ጥሩልኝና ይቅርታ ልጠይቀው” በማለት በዘመናቸው ሲጋፉት የኖሩትን ሰው በመጨረሻ ትንፋሻቸው ሊያቅፉት ይሞክራሉ፡፡ ሌሎች፣ “ለእገሌ የወሰድኩበትን ይህንና ያንን ነገር እባካችሁ መልሱልኝ” በማለት በውጊያ የወሰዱትን በልመና ሊመልሱ ይመኛሉ፡፡
“ይህንን ንብረቴን ለእገሌ አውርሱልኝ” በማለትም በብዙ ፍልሚያ የሰበሰቡትን ንብረት መልቀቅ ምርጫ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ አይተውና አሳይተው የሚያልፉም ብዙ ናቸው፡፡
ሕይወት ምንድን ነች? ሕይወት ሁለተኛ እድል የማትሰጥና ከራሳችን አልፈን ለሌላው የሚጠቅም ነገር አድርገን አጣጥመናት ልናልፋት የምትገባ ትእይንት ናት እንጂ ሕይወት በጠላት የተከበበችና ለፍልሚያ የተወሰነች የጦርነት ሜዳ አይደለችም፡፡
ለአንዳንዶች ግን ይህ የሕይወት ስእል በፍጹም ተቀባይነት የማያገኝ ጉዳይ ነው፡፡ የሚያውቁት ሌላ ነውና፡፡ በእርግጥ ነው በዚህች ምድር ላይ ስንኖር የማንፈልጋቸው ሙግቶችና ትግሎች አልፈው ወደ እኛ ይመጣሉ፡፡ ስለሆነም፣ ሕይወት ከምንም ችግር ነጻ የሆነች ጎዳና ነች ማለት አስቸጋሪ ነው፡፡
ለማለት የተፈለገው የመጣውን ግፊያ ሁሉ መጋፋት፣ የተነሳውን ውድድር ሁሉ መወዳደር፣ የተከሰተውን ፍትጊያ ሁሉ የመፋተግ ግዴታ የለብንም፡፡ የምንፋለማቸውን ፍልሚያዎች የመምረጥ እድሉም ሆነ ብቃቱ አለን፡፡
የሕይወታችን ጥራት የሚለካው ባሸነፍናቸው ፍልሚያዎች ሳይሆን በመረጥናቸው የፍልሚያ አይነቶች ነው፡፡ የምትሰለፍለት ዓላማና የምትከራከርለት ነጥብ የውስጥህን አመለካከት ጠቋሚ ነውና፡፡ ተራ ሰው ለተራ ነገር ይጋፋል፣ የከበረው ሰው ደግሞ ፍልሚያዎቹን መዝኖ ለከበረውና ለዘላቂው ነገር ራሱን ያቀርባል፡፡ ልዩነቱ እዚህ ላይ ነው፡፡
10600
05:37
07.05.2025
close
Reviews channel
keyboard_arrow_down
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
5.0
6 reviews over 6 months
Excellent (100%) In the last 6 months
f
**biubiu@*****.com
On the service since January 2025
18.03.202518:18
5
Precise task compliance
Show more
New items
Channel statistics
Rating
24.2
Rating reviews
5.0
Сhannel Rating
28
Subscribers:
126K
APV
lock_outline
ER
4.3%
Posts per day:
5.0
CPM
lock_outlineSelected
0
channels for:$0.00
Subscribers:
0
Views:
lock_outline
Add to CartBuy for:$0.00
Комментарий