
- Main
- Catalog
- Books, Audiobooks & Podcasts
- ❤❤የኪያ ደብዳቤዎች❤❤
Channel statistics
<ይቅርታ> ነበር ያለኝ የጀመረውን ጦርነት እንደማቋረጥ እያለ
<ችግር የለውም> አልኩት ከሚያቃጥለኝ ብሽሽቴ ጋር ታግዬ ፈገግ ለማለት እየሞከርኩ
<በጣም ይቅርታ አላወኩም ነበር> እንደተማረከ ወታደር እጆቹን ወደላይ አድርጎ ወደኋላው አፈገፈገ
<ነግሬህ ነበር እኮ> ይሄኔ ግራ ገባኝ
ፊቱ ላይ ንዴት ቁጭት ሃዘን ግራ መጋባት እና በሃይለኛው ድንጋጤ ይነበብበታል። እዛው በተንጋለልኩበት እሱ እንደከፋፈተኝ ፍርክክ ብዬ ተኝቻለሁ። እሱ ከላይ ሆኖ ፊቴን እየሸሸ ሆዴ . እምብርቴ እና ጭኖቼ መሃል የሆነ ነገር የሚፈልግ ይመስል በአይኖቹ ይርመሰመሳል።
<ምነው? > አልኩት። ቀጥል እንጂ ማለት አፍሬ
እንደዛው ድንግጥ እንዳለ... እንደዛው እንዳፈጠጠ ... እንደዛው ግራ እንደተጋባ የነበርንበትን ክፍል... ተክለፍልፎ ተቻኩሎ ተከራይቶት የነበረውን ክፍል... ጥሎ ወጣ... ቅድም ተስገብግቦ ከፍቶት የነበረውን በር ጓ አድርጎ ዘግቶት ወጣ.. ሄደ... ሸሸኝ ...
ለምን ሸሸኝ? ቆቡ ላይ የነበረው ደም የሱ ነበር እንዴ? እኔ ነኝ ያደማሁት?
ለምን ሸሸ? ራሱ እንደጀመረ የራሱ አያደርገኝም ነበር? አሁን ቀጣይ የሚመጣው ሰው <ምን አንዴ የተከፈተ በር ስንት ሰው እንደገባበት አይታወቅ > ብሎ ያረክሰኝ ይሆናል እኮ። ለምን ተወኝ?
ለምን ሸሸኝ? አላመነኝም ነበር? ከሱ በፊት ወንድ እንዳልነካኝ እየማልኩ የነገርኩትን አረጋገጥኩለት አይደል? ከስንት ጭቅጨቃው በኋላ <አብረሽኝ ተኝተሽ የዘላለሜ እንደሆንሽ የኔ እንደሆንሽ እንድታረጋግጪልኝ እፈልጋለሁ> እንዳለው አረጋገጥኩለት አይደል? ማረጋገጥ ብቻ ነበር የፈለገው? በእኔ ላይ የተሸረሸረውን እምነቱን መጠገን ብቻ ነበር የፈለገው? እሺ የእሱን እምነት መጀመሪያ ስንገናኝ ወደነበረው መለስኩለት ... አመነኝ። እኔስ? እንደነበርኩት እሆናለሁ?
ለምን ሸሸ?እውነትም በአለም አንደኛ ስሜት
አገባሁ ግን እሱን አይደለም። መስመር ጀመርኩ ግን ከሱ ጋር አይደለም። ከልቤ ሰው ጋር አይደለም። ያገባሁት የልጅነቴን ያፈቀርኩትን የተመኘሁትን አይደለም።
አውቃለሁ ይህ የብዙ ሰው ህመም ነው። በተለይ የአብዛኛዋ ሴት ህመም። ያፈቀሩትን ትቶ አለት ላይ መውደቅ። በቃ እንግዲህ ካልሆነ ምን ይደረጋል ተብሎ የተገባበት ህይወት። እንደ ባዕድ ከሚሰማን ሰው ጋር ለመኖር መስመር መጀመር... አንድም ቀን አጣዋለው ብለን ያላሰብነውን ሰው አጥተን አንድም ቀን እወድቅበታለሁ ብለን ያላሰብነው ሰው ላይ መውደቅ። ግዑዝ ላይ መውደቅ። ፍርክስ ብሎ መውደቅ። ይሁና ብሎ መውደቅ። ጠዋት ከእንቅልፋችን ስንነቃ የምናየው ሰው እንግዳ ሲሆንብን <ምናለ እሱ ቢሆን> እያሉ በምኞት መናወዝ <ያገባሁት .... እስከመጨረሻው አብሬው የምሆነው ምናለ እሱ ቢሆን ኖሮ> እያሉ በሰቀቀን ማለቅ።
ለወደቅንበት ሰው መፈገግ እንኳን ሲከብደን <አትወጂኝም እንዴ?> በተባልን ቁጥር በሃፍረት መሸማቀቅ።
እሱ አይደለም። ከባድ ቃል ከባድ ህመም ማለት ድሮ ለሚያውቁን ሰዎች <ባሌ እኮ እሱ አይደለም። ያፈቀርኩት አይደለም። ሌላ ሰው ነው> ብሎ ማውራት ይመስለኛል። ከቤት እንደወጣ እንኳን ትዝ ሳይለኝ ወደቤት ሲመለስ እንደናፈቁ መሆን። በቀለደ ጊዜ ሁሉ በግድ መገልፈጥ። በተለይ ወሲብ (ኤጭ) በተለይ ከአለም አንደኛ ስሜት ነው ያሉት ወሲብ የዚህ ሰዓት ሲያስጠላ። ጥሩ ነገሩ ማስመሰል ይቻላል። በቃ ማቃሰት ነው የታባቱ። እሱም ፈጣሪ ያክብረው ከአምስት ሰከንድ በላይ አያስቸግረኝም። ቶሎ ጣጣውን ይጨርሳል። ይጨርሳል።
ሌሎች ሴቶች እንደሚሆኑት ...አይኔን ሳልጨፍን .. ሳላስለመልመው .. < የኔ ውድ.. እ... ኧረ ተው... ወይኔ> ምናምን የሚሉ ቃላቶች ላይ ሳልደርስ ... ጀርባውን በጥፍሬ የመቧጠጥ ደረጃ ላይ ሳልደርስ... ሳይነዝረኝ ... <ጨረሽ ልጨርስ?> ምናምን ሳይለኝ... ይህ ሁሉ ሳይሆን በአምስት ሰከንድ ውስጥ ብሽሽቴን ሲረጥበኝ ይሰማኛል። ያኔ ተገላገልኩ ብዬ ሃሴት አደርጋለሁ። ምክንያቱም ያቺ አምስት ሰከንድ ለኔ አምስት ሰዓት ነው። ገና ሳስበው ጭንቅ የሚለኝ ሰዓት። ገና ልፊያ እንዳማረው ሳውቅ ጀምሮ የቀን ስራ እንዳለብኝ ይሰማኛል። የሱን ከንፈር መሳም ኮብልስቶን የመፍለጥ ያህል ይደክማል። ጡቴን ሲጨብጥ የሆነ ተራ መንገደኛ ቂጤን ቸብ ያደረገኝ ይመስል ንድድ እላለሁ። <ቶሎ አይገባም እንዴ> የሚል ትዕግስት ማጣት ይተናነቀኛል። ከገባ አይቆይማ።
አለመቆየቱን እንደ በሽታ የሚያየው እሱ <ልታከመው እንዴ?> ይለኛል
አለመቆየቱን እንደበረከት የማየው እኔ <እኔ እኮ አምኜ ተቀብዬዋለሁ ባሌ አይደለህ > እለዋለሁ
<ደሞ ደስተኛ ነኝ .. እኔም እኮ ብዙ አልቆይም > እለዋለሁ... ህም የመጨረስ አይደለም የመጀመር ስሜት ላይ ደርሼ የማላውቀው እኔ... በገዛ ባለቤቴ እየተደፈርኩ እንደሆነ የሚሰማኝ እኔ... ሁሌም ያ ሰዓት ለኔ እነዚህን ስሜቶች የማስተናግድበት ሰዓት ነው።
ንዴት.. ቁጭት.. ብስጭት.. ትዕግስት ማጣት... እልህ... እውነትም ወሲብ አለም ላይ ካሉ ስሜቶች ሁሉ አንደኛ ነው። ለኔ።እውነታኛ ነው በ Fantu emu
፩፡ ጥሩ አባት ለልጁ ሙሉ ሀላፊነት ይወስዳል።
፪፡ ጥሩ አባት ልጁን ፈፅሞ አይደበድብም።
፫: ጥሩ አባት ለልጁ ምሳሌ ለመሆን ይጥራል።
፬: ጥሩ አባት ለልጁ Shortcutና ውንብድናን አያስተምርም።
፭: ጥሩ አባት ሴት ልጁን አጥብቆ ይወዳል።
፮፡ ጥሩ አባት ያለውን ሁሉ ሳይሰስት ለልጆቹ ይሰጣል።
፯፡ ጥሩ አባት ልጆቹ ከሱ በላይ ስኬታማ እንዲሆኑ የእውነቱን ይመኛል።
፰፡ ጥሩ አባት ልጆቹን ይጠብቃል፣ ይንከባከባል፣ የብርሀን መንገድ ይሆናል።
፱፡ ጥሩ አባት የልጆቹን እናት ይወዳል፣ ቅድሚያ ይሰጣል።
፲፡ ጥሩ አባት ለልጆቹ መልካምነትን እና ለሰው መትረፍን ያወርሳል።
ጥሩ ልጅ ደግሞ አባቱን ለዘለዓለም ይወዳል 🖤🖤🖤ወንድ ሞገስ ነው። የእውነት። ማለት ምንም ባያደርግ እንኳን ከአንዲት ሴት አጠገብ ስለቆመ ብቻ ፤ ህይወቷ ውስጥ ስላለ ብቻ ሞገስ ነው። አባት አለኝ ፤ ወንድም አለኝ የማለት ትርጉሙ ጫፌን አትነኳትም ብሎ መመካት ማለት ነው።
ሴት ልጅ እንደሚታወቀው ገና ማጎጥጎጥ ስትጀምር የሚጎነትላት ብዙ ነው። ያቺን እድሜዬን አስታውሳታለሁ። <በናትህ እስቅያስ ብቻ ሸኘኝ> ብዬ አንዱን የክፍሌን ልጅ ይዤው ስሄድ ማንም ቀና ብሎ አያየኝም ነበር። ምናልባት ለካፊዎቼ በእድሜ ሊበልጡት ይችላሉ ግን አይነኩኝም። ለምን? ወንድ ስለሆነ ብቻ። ወንድ ከለላ ነው። ወንድ የእህቱም የእናቱም ጠባቂ ነው።
አፍቅረን ቦይፍሬንድ የያዝን ሰሞንም ወንድም ወይም አባት ሲኖረን እና ሳይኖረን ይለያያል። ማንም ካልወደደን አይጠጋንም። ተጠግቶን የወንድም ወይም የአባታችንን ቁጣ ችሎ ተቋቁሞ ከእኛ ጋር ከቆየ ያ ሰው የምርም እንደሚወደን መተማመን እንችላለን። ወንድ የሚወደንን ቦይፍሬንድ እና ሊጠቀምብን የመጣውን ቦይፍሬንድ መለያ ወንፊታችን ነው።
ወንድ የቤት ምሰሶ ነው። ወንድ ጫንቃ ነው። ወንድ ባል ነው። <አይገርምህም..> እያልን ለስስ ልባችን የከበደንን መጥፎ ቀናችንን የምናሸክመው ጫንቃ ነው ወንድ።
<የእንትና ሰርግ አለ እንሂድ... እንትን ፕሮግራም አለ አብረኸኝ ሂድ...> እያልን አስከትለን ተደግፈነው የምንሄደው ጌጣችን ነው ወንድ።
<ፐ ባለትዳር እና የልጆች እናት ናት የተባረከች የታደለች > የሚያስብለን መመስገኛችን ነው ወንድ ማለት።
ብዙ <ምናለበት ወንድም በኖረኝ > የሚያስብሉ መጭበርበሮች ... <ምን አለበት አባት በኖረኝ > የሚያስብሉ መደፈሮች ደርሰውብኛል። ወንድ አጠገቤ አለመኖሩ ብቻ ያጎደለብኝ ብዙ አለ።
ምንም ሳይናገር የሚያስከብረን ወንድ ነው። ምንም ሳያደርግ የሚያኮራን ወንድ ነው። መኖሩ ብቻ ጌጥ የሚሆንልን ወንድ ነው። አላት መባሉ ብቻ ሞገስ ነው።
ኖትድ፦ ከላይ ያወራሁት ወንድ ስለሆነ ሰው እንጂ ወ*ላ ስላለው ሰው አይደለም።
ሌላ ኖትድ፦ ወንድ አያስፈልገኝም እኔ ለራሴ ሞገስ ነኝ ማለት ይቻላል።Fantu Emu
~አመዛኙ ሴቶች Cheatingን አይጠሉም~
Yup! that's the title : )
ድሮ አብረን ቤተስኪያን የምንስም እና ሚስማር ጥምዝ የምንጫወት ወዳጄ ዛሬ ደወለችና፤ «ስማ የድሮ ፎቶዎቻችን ስልክህ ላይ አሉ እንዴ» አለችኝ፤ «ኧረ የሉም የጠፋው ስልኬ ላይ ናቸው»፤ «ሲያናድድ!» አለች፤ «አዎ! ከፋይሉ በላይ የስልኩ መጥፋት ያናድዳል»፤ «ዝጋ ባክህ ድሮም አንተ ለStory Time አትሆንም» ብላ ስልኩን ዘጋች።
ሰሞኑን ሴቶቻችን በTikTok እየመጡ ከድሮ ፍቅረኞቻቸው ጋር ያሳለፉትን ጊዜ በሄሮሺማ እና ኦሽዊትዝ የትረካ ዘይቤ እያቀረቡ ሀዘኔታ እና ተከታይ እያፈሱበት ይገኛሉ፤ ለታሪካቸው ማጣፈጫ የሚጠቀሙት ዋነኛ Plot ደግሞ "cheat" ያደርግብኝ ነበር የምትለዋን ነገር ነው።
ነገር ግን ሴቶች ሚዲያ ላይ በሚንገበገቡት ልክ ለcheating እዚህ ግባ የሚባል ጥላቻ የሌላቸው መሆኑን ሳበስርህ በደስታ ነው፤ በወከባው አትረበሽ፤ እኔ አንቂ ወንድምህ ቆንጆ አፍ የማዘጊያ ነጥብ ልሰጥህ ነው።
ይሄን የሚያነቡ ሴቶች፤ ምናባህ ለማለት ፈልገህ ነው እንደሚሉ ጥርጥር የለውም፤ ነገር ግን መጀመሪያ let's get some facts out of the way!
1. Most men are dogs
2. አመዛኙ ባለትዳር ወንድ ያማግጣል
3. Girls who tell their genuine stories for the sole sake of teaching others are brave!
ይሄን ካልን ዘንዳ።
አመዛኙ ሴቶች Cheatingን በሚሉት መጠን አይጠሉም፤ የሚጠሉት እነሱ ቺት ሲደረግባቸው ብቻ ነው።
ፍረድ!
አመዛኙ ሴቶች፤ ወይ ያገባ፤ ወይ ደግሞ Serious Relationship ላይ ያለ ወንድ በህይወት ዘመናቸው ቢያንስ አንድ ጊዜ date አድርገው ያውቃሉ፤ አለያ ደግሞ ይሄን ስታደርግ አይተው ያለፏት ሴት የቅርብ ጓደኛ አለቻቸው።
ይሄ የማይካድ ሀቅ ነው!
ሴቶች ባሎቻችሁን ወይም ያገቡ ወንድሞቻችሁን ጠይቁ፤ ቀለበት ያደረገ ወንድ ከላጤ ወንድ በላይ ከብዙ ሴቶች attention ያገኛል።
ይሄም ሌላ የማይካድ ሀቅ ነው!
ብዙ ባለትዳር ወንድ cheat ያደርጋል ብለን ከተስማማን፤ ከማን ጋር ነው ቺት የሚያደርገው የሚለውንም አብረን መጠየቅ ይኖርብናል። መልሱ እዚሁ social media ላይ የቺቲንግ ታሪክ ሲሰሙ ከሰማይ የወረደ ነገር አድርገው ወሬ ከሚያዳምቁት hypocrite እህቶቻችን ጋር ነዉ።
እነሱ በሚሉት ልክ ቺቲንግ ቢጠየፉ ኖሮ ይሄ ይሆን ነበር ወይ?
ስማ!
የሀጥያቱ እኩል ተካፋይ ሆነው፤ በዚህ ልክ propaganda እንዲሰሩብህ አትፍቀድ፤ fyi እነሱ አይያዙም እንጂ እኩል ቺት ያደርጋሉ፤ ራይድ የሚሰራ አለያ ሆቴል ያለው ጀለስ ካለህ ጠይቀው፤ ታሪክ ትሰማለህ።@yefekerdebdabe
@yefekerdebdabe
ደንግጦም ወደ እርሷ ጠጋ አለና፤ "እመቤቴ፣ ደህና ነሽ? ምን ሆንሽ?" አላት ወደ ላይ ቀና እያደረጋት።
ወጣቷም ትንፋሽ እያጠራት፤ "ጌታዬ... እባክዎን ይሄ 35ኛው ፎቅ ነው?" ስትል ጠየቀችው።
እሷም "አዎ ጌታዬ፤ በአስቸኳይ 35ኛው ፎቅ መድረስ አለብኝ። የህንጻው ሊፍት ብልሽት ስላለበት ለሰራተኞች ብቻ ነው የተፈቀደው። ይህ ምግብ የታዘዘለት ሰውዬ 'በአምስት ደቂቃ ውስጥ ካላመጣሽልኝ ከስራሽ እንዲያባርሩሽ አደርጋለሁ' ብሎ ዝቶብኛል። ወርደው እንዲቀበሉኝ ብማጸናቸውም ፈቃደኛ አልሆኑም" አለችው።
ሚስተር ኮስቢ በድንጋጤ ተነስቶ "ጌታዬ! እርስዎ ምግቡን ለምን አመጡት?" ሲል ጠየቀ።
አለቃውም በቁጣ አይን እያየው "አይዞህ... መጀመሪያ ምግብህን ብላ፤ ከዚያም እቃህን ጠቅልለህ ከዚህ ድርጅት ውጣ!" አለው።
ሚስተር ኮስቢ ግራ በመጋባት "ጌታዬ... ለአንዲት ተራ ምግብ አቅራቢ ብለው ያባርሩኛል? ምንም ይሁን ምን ምግቡን ማድረስ እኮ ስራዋ ነው!" ሲል ተከራከረ።
አለቃውም በረጋ ግን ቁርጠኛ በሆነ ድምፅ እንዲህ አለው፦ "እንግዲያውስ አንድ እድል ልስጥህ። አሁኑኑ ወርደህ ከአንደኛ ፎቅ እስከ 35ኛው ፎቅ በአምስት ደቂቃ ውስጥ በደረጃ ውጣ፤ ያኔ ስራህን ታስጠብቃለህ።"
ሚስተር ኮስቢ ጮክ ብሎ "ምን? ይሄ እኮ የማይቻል ነገር ነው!" አለ።
ቦሱም "ለአንተ የማይቻል የሆነውን ነገር ሌላው የሰው ልጅ እንዲያደርገው እንዴት ትገፋፋለህ? አንተ ሰው የመሆን ህሊና ጎድሎሃል። በሰው ላይ ጭካኔ የምታሳይ ሰው በዚህ ድርጅት ውስጥ ቦታ የለህም... ውጣ!" ሲል አባረረው።
-------------- ------------ -----------
የሰው ልጅን ክብር ከያዘው ስራና ከደረጃው ጋር አታያይዘው፤ ሰው መሆኑ ብቻ እንዲከበር በቂ ነው።
ራስህ ልትሸከመው የማትችለውን ከባድ ሸክም በሌሎች ላይ ለመጫን አትሞክር።
:
ስልክ ሲደውልልኝ አለማንሳቴን ለምዶታል።
ለፅሁፍ መልዕክቶቹ መልስ መስጠት .. ልክ የታክሲ ረዳት መልስ መመለስ የሚከብደውን ያህል ይከብደኛል።
ለኔ የሚሰጠኝ ለራሱ የከለከለውን ፍቅር እንደሆነ ስለማውቅበት ያሳዝነኛል። ግን ለሀዘኔ ፊት አልሰጠውም። ለሀዘን ያልሆነ ፊት ደሞ ለእዘኑልኝ ባይ አይሆንምና ለሱም ቢሆን ፊት መንሳት እንጂ መስጠት አልችልበትም።
ፍግግ እያለ ሲመጣ .. ስኳር ሳይጨመርበት የተማሰለ ግልምጫ ፉት አስብዬ ወደመጣበት እመልሰዋለሁ።
መምጫውም መሄጃውም እሩቅ አይደለም። ጎረቤቴ ነው (የቢሮ 😏)። ቡና አንጠራራም ፥ ቁጭ ብለን ሰው አናማም ፥ አብሬው ነጠላ አልቋጭም .. ግን መሀላችን ያልተቋጨ ምስጢር አለ። እሱ .. ከራሱ ቀጥሎ ለሁሉ የነገረው .. እኔደሞ ከሁሉ በፊት ለራሴ የካድኩት።
አብርሀም ይባላል። እኔ ግን ከአብርሀምነቱ የአብርሀም በግነቱ ይጎላብኛል። አብርሀም .. አስቦበትም ባይሆን .. አልፎ አልፎ እግረመንገዱን .. የአጉሊ መነፅር ብጉንጅ የሚያህሉ ክብ ብርጭቆዎችን እይታዬን ያግዝልኛል ብሎ ይለብሳል።
የማይገርመው ነገር .. 'ትንሽ' ነገር ማጉላት የለመደ መነፅሩ .. እኔም ላይ አልሰነፈም። 'አይታየውም' ብሎ አጎላኝ .. 'ታዛቢ የለም' ብሎ አገዘፈኝ።
ድሮም ለታማሚ ሰው ከመነፅሩ በላይ ጠላት የለበትም።
አልወደውም። ግን ስህተቴ .. ሲወደኝ ዝም ብዬዋለሁ።
አልወደውም። ግን ስህተቴ .. ሲስመኝ መልሼ ስሜዋለሁ (አንዴ ብቻ ቢሆንም)።
አልወደውም። ግን ስህተቴ .. 'ልተንፍስሽ' ሲለኝ .. የእግዜር አየር ሳልሆን.. ጥሪት የሚከፈልበት ሰውሰራሽ የኦክሲጅን ታንክ መሆኔን ለመናገር አልደፈርኩም።
'ተንፍስ' አልኩት.. ተነፈሰኝ .. ከሞት መንታ መንገድ ወደኋላ አስፈገፈግኩት። ከሞት አፈግፍጎ ወደሞት።
ድሮም ሞት ሲመጣ ዘጠኝ ሆኖ አይደል?😏 አንዱን ላመለጠው ሚስኪን .. የተቀረው ስምንቱ ሞት እኔ ነኝ።
እኔን አገኘኋት ብሎ .. ለመገኘት የሚታመመውን 'እራሱን' አጣ። እየተነፈሰም ትንፋሽ እንዳጠረው ሰው ገረጣ።
እያኖርኩት .. ብዙ ሞት ሞት የሚሉ ሌሊቶችን ከቤቴ በረንዳ አሳደርኩት። በፍርፋሪ .. በብጫቂ ጨርቅ .. በመሰንበቻ።
"አንድ ቀን ትወደኛለች" ብሎ እንደሆነኮ አውቃለሁ .. ምክንያቱም እኔም ሌላ "አንድ ቀን ይወደኛል" የምለው ሰው ነበር።
አንድ ቀን የሚባለው ቀን አይመጣም። ለኔም ለሱም አይመጣም። የሚመጣው የሆነ ቀን የሚባለው ቀን ነው
የሆነ ቀን .. ከኔ ይለምነው የነበረውን ፍቅር ከራሱ መለመን ይለምዳል። አንድ ቀን .. ምናልባት አንድ ቀን .. አብርሀም አብርሀምን ይወደው ይሆናል።
"አብርሽ" አልኩት
"አ .. አቤት .. ወይ .. ወዬ" ተርበተበተ
"ወዴት እና እመት ቀርተውሀል" አልኩት እየተቃለድኩ (ቀልቤ ተይ ይላል ከኋላ እያንዣበበ። የራስን ጥርስ ለመንከስ እየተገለገሉ .. የተነካሽን ጥርስ ለሳቅ ማንደርደር ልክ አይደለማ።)
ኮስተር አልኩ።
"ዛሬ ምሳ አብረን እንብላ?" አልኩት ምንም በማይነበብበት ሌጣ አስተያየት
ምሳ ሰዐት .. ቤሎን ካፌ .. በጠረጴዛ ገላጋይነት በመተማመን ትይዪ ወንበር ላይ ተቀምጠናል።
እያወራሁት እጁን በጨረፍታዎች ቦረሽ እያደረግኩት ነው። አፌ የሚስተውን ጣቴ እንደሚያርም አይነት።
ዝም ብሎ እያዳመጠኝ ነው። ትዕግስተኛ ነው። ድሮም አብርሀም ለተባለ ሰው .. አንድን ልጅ 99 አመት ሙሉ መጠበቅ ብርቅ አይደለም።
99 ጊዜ ክብሩን ሸጦ .. ከገበያው ምንጣፉን ብድግ እንኳ ሳያደርግ .. ትርፉ ሁሉ በሆዱ እስኪጠፋ ድረስ ጠብቆኛል።
የምነግረውኮ ልብ አንጠልጣይ ልብወለድ አልነበረም። ከአመታት በፊት በጣም አፈቅረው ስለነበር ሰው ነው። እያወራሁት አይኖቹን እመረምራለሁ። ስለሞቴ እየተረኩለት ህያውነቱ ይታወሰው ይሆን ብዬ ደሞ ትክዝ እላለሁም።
የምናገረው ሁሉ ሲያሳምመው ወይ ሲያክመው ይታየኛል። ካከምኩት ግን ያሳመምኩት ይበልጣል። ሆኖም ግን አይኖቹ ውስጥ ከህመም ሌላ የማነብበው ደባል ስሜት ነበር። የሚያምር ስሜት ህህ .. መንሰፍሰፍ።
አለመወደዱ እያንገበገበው .. አለመወደዴም ሲያንገበግበው።
"ፍቅር .. ለልብ ግብር ከፋይ .. ህጋዊ የአዕምሮ በሽታ ነው። እብድ ያገግማል እንዪ አይድንም ሲባል አልሰማህም 😏 " አልኩት የመጨረሻ የሻይ ፉትታዬን እየፎትኩ።
"ግን ትወጂኛለሽ?" አለኝ አይኖቹ እንባ እንዳቀረሩ
"አንተ ራስህን የምትወደውን ያህል እወድሀለሁ።" አልኩት
የተሰባበረ ልቡን ከአምስት የ2 መቶ ብር ኖቶች ጋር ጠረጴዛ ላይ ተወልኝና ወጣ።
ድጋሚ አልተመለሰም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እነሆ ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ እንደተባለ ሰምታችኋል
ለአንዳንዶች ግን እላለሁ
እራሳችሁን እንደባልንጀሮቻችሁ ውደዱ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ደር'ሃሲ ከዜሮላይ የምወዳት አንዲት አባባል አለች። በመከራ ላይ የተነገረች እውነተኛ ምክር፦
“ጠባሳው ባንተ ላይ ቢቀርም ህመሙ እንዲወስድህ አታድርግ። ካለስቃይ ካለ መስዋትነት ምንም ነገር አናገኝም ነበር። መጀመርያ ተስፋ መቁረጥ አለብህ። ይህ ፍርሃት አይደለም የሆነ ቀን ትሞታለህ በቃ። ሁሉንም ነገር ካጣን በኋላ ምንም ነገር ለማድረግ ነፃ እንሆናለን።”
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
❤❤የኪያ ደብዳቤዎች❤❤ is a Telegram channel in the category «Книги, Аудиокниги и Подкасты», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 6.4K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 12.4, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 4.8 ₽, and with 2 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий