
Get clients in any niche!
Delegate the launch of advertising to us — for free
Learn more
18.5

Advertising on the Telegram channel «TIKVAH-ETH»
5.0
16
Not everyone has the time to look up to news channels on TV every night to stay updated about the news. you are in the right place to get breaking news.
stay updated.
Share
Add to favorite
Channel temporarily not accepting requests
Choose another channel from recommendations or get a tailored list within your budget using AI
AI Channel Picker
Recent Channel Posts
በምሥራቅ ጎጃም በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን BBC ዘገብ
የቢቢሲ ዘገባ እንደሚከተለው ይነበባል
በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሐሙስ ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም. በትምህርት ቤት ዙሪያ በደረሰ የድሮን ጥቃት ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።
በዞኑ እናርጅ እናውጋ ወረዳ ገደብ በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ የትምህርት ቤት አጥር ለማጠር እና ቤት ለመሥራት 'ለልማት ሥራ' የወጡ "ሰላማዊ ሰዎች" በጥቃቱ መገደላቸውን ገልፀዋል።
የአካባቢው አስተዳደር ግን ጥቃቱ በአካባቢው ተሰብስበው በነበሩ የፋኖ ታጣቂዎች ላይ እንጂ በንፁሃን ነዋሪዎች ላይ አለመፈጸሙን ለቢቢሲ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተፈጸመ ስለተባለው ጥቃት ክትትል እያደረገ መሆኑን አመልክቷል።
ነዋሪዎች ለቢቢሲ እንደተናገሩት "ተሰብስበው" በከተማዋ ያለው ገደብ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አጥርን እያጠሩ በነበሩ የሰዎች ላይ ነው ጥቃቱ የተፈፀመው።
ጥቃቱ በተፈፀመበት አካባቢ በቅርብ ርቀት ላይ እንደነበሩ የተናገሩ ሌላ የዓይን እማኝ ወዲያው ጩኸት፣ ግርግር እና ድንጋጤ መፈጠሩን ጠቁመው "የሆነውን አናውቀውም" ሲሉ በቅፅበቱ የነበረውን ሁኔታ ገልፀዋል።
እሳቸውን ጨምሮ ሥራ ላይ የነበሩ ሰዎች ጥቃቱ ወደተፈፀመበት አካባቢ ሲጠጉ "ሰው የሚባል አይለይም" ሲሉ ስለ ጉዳቱ ተናግረዋል።
"እንዳለ በሙሉ ጥቁር ነገር ነው የሆነው። አካባቢው በሙሉ ሰው የሚባል ነገር የለም። ከወደቀው ውስጥ የሚጮህ አለ፤ የሚንከባለል አለ። የተፈጠረው ነገር ይዘገንናል። ሰው ለሆነ እጅግ የሚዘገንን ድርጊት ነው" ብለዋል።
የፈረሰውን የትምህርት ቤቱን አጥር እያጠሩ እያለ ቀኝ እጃቸውን ተመትተው መቁሰላቸውን የተናገሩ ሌላ ነዋሪ "ከባድ ፍንዳታ" መከሰቱን ጠቅሰው "ብዙ ሰው ነው የተጎዳው" ብለዋል።
"ባሕር ዛር የሚቆርጥ፤ ሚስማር የሚመታ አለ፤ ማገር የሚቆርጥ አለ፤ የሚይዝ አለ" ሲሉ ማኅበረሰቡ መሰባሰቡን የገለፁ ሌላ የዓይን እማኝ የሟቾቹን ቁጥር "ብዛት ይኖረዋል" በማለት ገልፀዋል።
አስከሬን ስለማንሳታቸው የተናገሩ ሌላ እማኝ ደግሞ አብዛኛው የጥቃቱ ተጎጂዎች ወዲያው ሕይወታቸው ማለፉን ገልፀው፤ ሟቾቹ በአብዛኛው ወጣቶች ናቸው ብለዋል።
ከ24 በላይ ቁስለኞችንም ወደ ሕክምና መወሰዳቸውን የገለፁት እማኞች፤ አብዛኞቹ በከተማዋ ወደሚገኘው ገደብ ጤና ጣቢያ ከደረሱ በኋላ ሕይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል።
ከ70 በላይ አስከሬን አንስተው በባጃጅ ወደ ቤተ ክርስቲያን ማመላለሳቸውን የተናገሩ አንድ የዓይን እማኝ፤ ታዳጊዎችን እና ሽማግሌዎችን ጨምሮ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 120 እንደሚደርስ ገልፀዋል።
"ከ115 እስከ 120 የሚሆን አስከሬን ነው የተቀበረው። ያልታወቀም ይኖራል ብዬ አስባለሁ። ምክንያቱም ድንጋጤ ውስጥ ስለነበርን" ብለዋል።
ሌላ የዓይን እማኝ በበኩላቸው 57 አስከሬን እስከሚነሳ ድረስ እንደነበሩ ጠቁመው የሟቾቹ ቁጥር ከ100 በላይ እንደሚሆን ገምተዋል።
አስከሬኖቹ ላይ ከባድ ጉዳት በመድረሱ ሟቾችን መለየት ከባድ እንደነበር የተናገሩት እማኞች በዚህ ምክንያት እና በስጋት እስከ ቀትር 08፡00 ድረስ ገደብ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በጅምላ እንደተቀበሩ ገልፀዋል።
"አሞራ እንዳይበላቸው ቅበሩ ሲባል ማኅበረሰቡ በፍጥነት አምስት የሚሆን መቃብር ውስጥ ነው የቀበራቸው" ሲሉ አንድ ነዋሪ ተናግረዋል።
የመንግሥት ኃይሎች ጥቃቱ ከደረሰ በኋላ ወደ ከተማዋ መግባታቸውን ተከትሎ ስጋት ያደረባቸው አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች መሸሸታቸውን የተናገሩ አንድ ነዋሪ፤ ተጨማሪ ጥቃቶች መፈፀማቸውንም ጠቁመዋል።
ማኅበረሰቡ ከተረጋጋ በኋላ ለሟቾቹ ድንኳን እንደተጣለ እና ከቀናት በኋላ በአካባቢው "ፍራጅ" የሚባለው ማስተዛዘኛ መርሃ ግብር እንደተደረገም ነዋሪዎች ተናግረዋል።
"ሰሞኑን ሲሸበር ነበር። ሕዝቡ በሙሉ ሽብር ላይ ነው ያለው" ሲሉ ዳግም የድሮን ጥቃት ይደርሳል በሚል የፋሲካ በዓልን በስጋት ማሳለፋቸውን "በዓል የሚባል ነገር የለም" ብለዋል።
"ከባድ ሐዘን ውስጥ ነው ያለው። በዓል ምንም አይመስልም ነበር። ለበዓል ከከተማ የሚመጡ ልጆች አልመጡም" ሲሉ አካባቢው በሐዘን ድባብ ውስጥ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
የአማራ ክልል ግጭት በ2015 ዓ.ም. መጨረሻ ከተቀሰቀሰ ወዲህ ከተማዋ በፋኖ ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር እንደሆነች ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ጥቃቱ ሲፈፀም ግን የፋኖ ታጣቂዎች ከተማዋ ውስጥ እንዳልነበሩ እና በአካባቢው ግጭት እንዳልነበረ ጠቁመዋል።
ታጣቂዎቹ "አንዳንድ ሥራ ለመሥራት ካልመጡ በቀር ከተማው ውስጥ አይታዩም" ሲሉ አንድ ነዋሪ ተናግረዋል።
ነጋዴ እንደሆኑ የተናገሩ አንድ የዓይን እማኝ ሟቾቹ ንፁሃን ስለመሆናቸው ሲናገሩ "በርካቶቹን በንግድ ሥራቸው" የሚያውቋቸው መሆናቸውን ገልጸዋል።
"የፋኖ አባላት ቢሆኑ [አስከሬን ሲነሳ] ታጣቂ እናገኝ ነበር። ፋኖዎችን እና ማኅበረሰቡን [ለይተን] እናውቃቸዋለን። [ፋኖዎች] በአንድ ላይ ነው የሚንቀሳቀሱት" ሲሉ ሌላ ነዋሪ ተናግረዋል።
ሌላ ነዋሪ በበኩላቸው "የተሰበሰው አጥር የሚያጥረው እና ቤት የሚሠራው ሰው በቀረፃው [የድሮን ቅኝት] የፋኖ ስብስብ ነው ተብሎ ታስቦ ይሁን ያወቅነው ነገር የለም። . . .ምንአልባት ሲሰበሰብ ፋኖ ነው ተብሎ ታስቦ [ይሆናል] እንደዚያ ነው እኛ የተረዳነው" ሲሉ ጥቃት ሊፈጸም የቻለበትን ምክንያት ግምታቸውን ገልፀዋል።
የእናርጅ እናውጋ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሙሉ ጌቴ ንፁሃን ሰዎች ተገደሉ መባሉን "የጠላት ወሬ" ያሉ ሲሆን፤ እርምጃው "ፅንፈኛ" ያሏቸው የፋኖ ታጣቂዎች ላይ መወሰዱን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
"እዚህ አካባቢ ቁጥሩ በርከት ያለ የኃይል ስብስብ አለ። ሰብስበው ሥልጠና ጭምር [እንደሚሰጡ] መረጃው አለኝ። የትምህርት ቤት አጥር፤ ቤት ሥራ የሚባለው ነገር ማሳመሪያ ነው . . ." በማለት ንፁሃን በፍንጣሪም ቢሆን አልተገደሉም ሲሉ አስተባብለዋል።
የፋኖ ታጣቂዎች በበኩላቸው በወረዳው በስፋት እንደሚንቀሳቀሱ ጠቁመው ገደብ ከተማ አካባቢ ላይ ግን በወቅቱ "ምንም ዓይነት የታጠቀ ኃይል" አልነበረም በማለት በጥቃቱ የተገደለ አባል እንደሌላቸው ተናግረዋል።
አካባቢውን ለሥልጠና እንደማይጠቀሙት የተናገሩት የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ሰብሳቢ አቶ አስረስ ማረ ዳምጤ "ሁሉም ግድያው የተፈፀመባቸው ሲቪሊያን ናቸው። አንድም የታጠቀ ኃይል በቦታው ላይ አልነበረም" በማለት ግድያውን ማኅበረሰቡን ከማሸበር ጋር አያይዘውታል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የድሮን ጥቃቱ ላይ ክትትል እያደረገ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግሯል።
@Tikfahethiopia
659
06:45
24.04.2025
imageImage preview is unavailable
በኢትዮጵያ "ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለረሃብ" መጋለጣቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስታወቀ።
ድርጅቱ በዛሬው ዕለተ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ፕሮግራሙ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚያከናውነው ሥራ የሚውል ተጨማሪ ገንዘብ በአስቸኳይ የማያገኝ ከሆነ "ለ3.6 ሚሊዮን" ሰዎች የሚያቀርበው "የነፍስ አድን ምግብ" ድጋፍ "በመጪዎቹ ሳምንታት" እንደሚያቋረጥ አስጠንቅቋል።
ተቋሙ ኢትዮጵያ ውስጥ የረሃብ እና የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እየጨመረ የመጣው ሀገሪቱ ውስጥ ባሉ የተለያዩ ችግሮች ምክንያት እንደሆነ በመግለጫው ላይ ጠቅሷል።
ግጭት፣ ቀጣናዊ አለመረጋጋት እና መፈናቀል ተቋሙ ከጠቀሳቸው ምክንያቶች መካከል ናቸው።
በሀገሪቱ ውስጥ ያለው "ኢኮኖሚያዊ ቀውስ" እና ድርቅ እየጨመረ ለመጣው ረሃብ እና ተመጣጠነ ምግብ እጥረት በምክንያትነት ተጠቅሰዋል።
እነዚህ ችግሮች "ሚሊዮኖችን ያለ በቂ የተመጣጠ ምግብ እንዳስቀሩ" የዓለም የምግብ ፕሮግራም ገልጿል።
የተቋሙ መግለጫ፤ "በመላው ኢትዮጵያ ከአስር ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለረሃብ እና ምግብ እጥረት ተጋልጠዋል" ብሏል።
ከእነዚህ ሰዎች መካከል "ሦስት ሚሊዮን ያህሉ በግጭት እና በአስቸጋሪ የአየር ጠባይ ምክንያት ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ" እንደሆኑም ጠቅሷል።
Via_ቢቢሲ
@Tikfahethiopia
962
06:55
23.04.2025
imageImage preview is unavailable
ግብዣውን ውድቅ አደረገ!
አቶ ጌታቸው ረዳ የክብር ሽኝት እንዲደረግላቸው በጀነራል ታደሰ ወረደ የቀረበላቸውን ጥሪ ውድቅ አደረጉ።
መጀመሪያ ፀጥታውን ያስከብር መቀሌ አይደለም ለኔ ለሱም አደገኛ እንደሆነች ያውቀዋል ።
ያለን አማራጭ እኔ ወደ አዲስአበባ እነሱ ወደ አስመራ መሸሻቸው ነው ብለዋል።
ጋቢ ለመቀበልና በድግስ ለመወዝወዝ አልሄድም ብለዋል::
@Tikfagethiopia
875
06:54
23.04.2025
imageImage preview is unavailable
የፌደራል ዳኛ የትራምፕ አስተዳደር በአሜሪካ ድምጽ ላይ የጣለውን ዕገዳ አነሱ
የፌደራል ዳኛ ማክሰኞ ዕለት የትራምፕ አስተዳደር የአሜሪካን ድምጽ (ቪኦኤ) እና ተዛማጅ የዜና አገልግሎቶችን ለማፍረስ ያደረገው ጥረት ሕጋዊ እንዳልሆነ በመወሰን፣ የመንግስት የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግላቸው እነዚህ የዜና ማሰራጫዎች ሥራቸውን እንዲቀጥሉ አዘዙ።
ዳኛው ሮይስ ላምበርዝ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ሚዲያ ኤጀንሲ (USAGM) ቪኦኤን እና ሌሎች ማሰራጫዎችን እንዲመልስና በሕግ የተቀመጠላቸውን ኃላፊነት እንዳይስተጓጎል አዘዋል። በተጨማሪም በዕረፍት ላይ የነበሩ ሠራተኞች ወደ ሥራ እንዲመለሱና የሠራተኞች ቅነሳ እንዳይደረግ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።
ዳኛ ላምበርዝ የትራምፕ አስተዳደር USAGMን ለመዝጋት ያሳየው አካሄድ "የዘፈቀደ" ድርጊት እንደሆነ ገልጸዋል። ይህ ውሳኔ VOA እና ተዛማጅ ተቋማት ሥራቸውን እንዲቀጥሉ አስችሏል።
@Tikfahethiopia
855
06:53
23.04.2025
imageImage preview is unavailable
【DPK-AI ትሬዲንግ】 አውቶማቲክ መጠናዊ ስርዓቱ ዝቅተኛውን የዲጂታል ገንዘቦች መሸጫ ዋጋ እንደ BTC፣ ETH፣ USDT ወዘተ በዋና ልውውጦች ላይ መፈለግ እና በሰከንዶች ውስጥ በፍጥነት መግዛት ይችላል።
1.DPKAI-quantitative, ፈንዶች ተቀማጭ እና ማውጣት በራስ-ሰር ወደ መለያው ገቢ ይደረጋል.
2. VIP1-VIP11፣ መጠናዊ ተመላሾች 20% -35%.
3. ከ 25% ወደ 40% በመጨመር ብዙ ምንዛሬዎችን እና ብልጥ የኢንቨስትመንት ገቢን ይደግፉ.
4. መጠኗ በየ24 ሰዓቱ እንደገና ይጀመራል፣ እና እያንዳንዱ ሰው በቀን አንድ ጊዜ በመጠን የገቢ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ይችላል።
5. የሶስተኛ ደረጃ ወኪል ግብዣ ሽልማቶችን ጠቁም። ብዙ ግብዣዎች ባደረጉ ቁጥር፣ የበለጠ ሽልማቶችን ያገኛሉ። ምንም ከፍተኛ ገደብ የለም [አንድ ሽልማት 10%, B ሽልማት 5%, C ሽልማት 3% = 18% ሽልማት]. እንደ ቲክቶክ፣ ፌስቡክ፣ ትዊተር፣ ዩቲዩብ፣ ኢንስታግራም፣ የዋትስአፕ ቡድን፣ የቴሌግራም ቡድን፣ ወዘተ ባሉ ማህበራዊ ሶፍትዌሮችዎ ላይ ለማጋራት የግብዣ ሊንኩን ይላኩ።
【DPK-AI ትሬዲንግ】 የምዝገባ አገናኝ፡ https://dpk-ai.com/#/register?ref=563723
【DPK-AI ትሬዲንግ】 የመስመር ላይ የደንበኞች አገልግሎት፡ https://chat.ssrchat.com/service/gomw2j
754
21:15
22.04.2025
imageImage preview is unavailable
#ትንሣኤ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ !
" በዚህ የለም ፤ እርሱ እንደተናገረው ተነሥቷል "
መልካም የትንሣኤ በዓል !
በዓሉ የሰላምና የፍቅር ይሆን ዘንድ እንመኛለን !
1765
00:40
20.04.2025
imageImage preview is unavailable
በሻሸመኔ ከተማ የበርበሬ ምርትን ከበዓድ ነገር ጋር ሲቀላቅል የነበረ ተቋም በጥቆማ ተያዘ
ምግብን ከባዕድ ነገር ጋር መቀላቀል በህብረተሰብ ጤናና ኢኮኖሚ ላይ ከፍ ያለ ጉዳት የሚያደርስ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑንም የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታውቋል።
ባለስልጣኑ ለህብረተሰቡ የሚቀርቡ የምግብ ምርቶች ጥራትና ደህንነታቸው ይጠበቅ ዘንድ የቁጥጥር ስራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከፊታችን የሚከበረውን የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በሻሸመኔ ከተማ ባዕድ ነገርን ከበርበሬ ምርት ጋር በመቀላቀል ለህብረተሰቡ ሊያቀርን የነበረ ተቋም መያዙን ይ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ሐዋሳ ቅርንጫፍ ከጉምሩክ ኮሚሽን ሐዋሳ ቅርንጫፍ ኢንተለጀንስ ባለሙያዎች፣ ከኦሮሚያ ጤና ቢሮ ጤና ጤና ነክ ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እንዲሁም ከሻሸመኔ ከተማ ጤና መምሪያና ከሻሸመኔ ከተማ ፖሊስ ጋር ባካሄደው በሰርቬይላንስ በታገዘ ክትትል ምርቱ ከመሰራጨቱ በፊት በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል።
በርበሬን ከበዓድ ነገር ጋር ሲቀላቅል የተገኘውን ተቋም ለመያዝ በተደረገው ኦፕሬሽን ተቋሙ በርበሬውን ለማቅለም ሲጠቀምበት የነበረው ቀሰም ቀለም፣ የበርበሬ ተረፈ ምርት የሆነ ፎሼ እንዲሁም ሌሎች ግብዓቶችን መያዝ የተቻለ ሲሆን በኦፕሬሽኑ ወቅት የሻሸመኔ ህዝብ ህገወጥ ተግባር ላይ የተሰማራውን ተቋም ለመያዝ ላደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ምስጋና ማቅረቡን ብስራት ሬዲዮ ከባለስልጣኑ ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
Via dagu
@Tikfahethiopia
1874
06:30
18.04.2025
imageImage preview is unavailable
የመምህራን የኅብረት ሥራ ባንክ” በሚቀጥለው ዓመት ሥራ ሊጀምር እንደሚችል ተስፋ እንዳላቸው የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ ተናገሩ
የኑሮ ውድነት የበረታባቸው የኢትዮጵያ አስተማሪዎችን ለመርዳት ይቋቋማል የተባለው “የመምህራን የኅብረት ሥራ ባንክ” በሚቀጥለው ዓመት ሥራ ሊጀምር እንደሚችል የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ ፍንጭ ሰጡ።
መንግሥት ለአስተማሪዎች ለቤት መሥሪያ የሚሆን መሬት ቢያቀርብ የሚቋቋመው ባንክ በአነስተኛ ወለድ ብድር የሚሰጥ ይሆናል።
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ባንኩ በሚቀጥለው ዓመት ሥራ ሊጀምር እደሚችል ተስፋቸውን የገለጹት ትላንት ማክሰኞ የትምህርት ሚኒስቴርን የ2017 የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት ነው።
በትላንትናው የምክር ቤቱ ውሎ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል በግጭት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎች ቁጥር እና ችግሩን እንዴት ይፈታል የሚለው ይገኝበታል።
ከትምህርት ቤት ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ቁጥር በተባበሩት መንግሥታት የሕጻናት መርጃ ድርጅት “እስከ 10 ሚሊዮን ያደርሰዋል” ያሉት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ “ቢያንስ ሰላም እስኪሰፍን ድረስ ምን እየተሠራ” እንደሆነ ጠይቀዋል።
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ግን በተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት የተጠቀሰውን ቁጥር “በፍጹም አላምንም” ሲሉ ተናግረዋል።
ቢሆንም “7.2 ሚሊዮን ልጆቻችን ትምህርት ቤት አለመግባታቸው በጣም በጣም ሊያሳስበን የሚገባ ጉዳይ ነው” ሲሉ ተደምጠዋል። የኢትዮጵያን ልጆች ከትምህርት ገበታ ያራቀው “ትልቁ” ምክንያት በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚካሔዱ ግጭቶች መሆናቸውንም አምነዋል።
1688
18:13
17.04.2025
“የፕሪቶርያ የሰላም ስምምነት አተገባበር ዙሪያ ያሉ ሁኔታዎች አሳሳቢ በመሆናቸው #የአፍሪካ ህብረት ፓኔል ውይይት ሊያደርግ ይገባል ሲሉ” የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ።
ሊቀመንበሩ ይህንን ጥሪ ያቀረቡት በአፍሪካ ህብረት የፕሪቶርያ ስምምነት የክትትል፣ ማረጋገጥ እና ማስከበር ተልዕኮ ኮሚቴ ሃላፊ ሁነው ከተሾሙት ሜጀር ጀነራል ሳማድ አላዴ ትላንት ሚያዚያ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ባካሄዱት ውይይት መሆኑን ፓርቲው ባጋራው መረጃ አስታውቋል።
“በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ከመከላከያ ሰራዊት ውጭ ውጭ ያሉት ታጣቂዎች ከትግራይ ግዛት እስካሁን አለመውጣታቸውን፣ የተሰደዱ እና የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀያቸው መመለስ አለመቻላቸውን እንዲሁም የትግራይ ሉዓላዊ መሬቶች በወራሪዎች ቁጥጥር ስር ይገኛሉ ሲሉ ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ለተሿሚው መናገራቸውንም አካቷል።
ሊቀመንበሩ ደብረጺዮን “የፖለቲካ ድርድር እስካሁን አለመጀመሩን፣ የስምምነቱ ፈራሚ የሆነው ህወሓት የተሰረዘው ህጋዊ ሰውነቱ አለመመለሱን” ለተሿሚው ማስታወቃቸውን መረጃው አመላክቷል።
1528
08:47
15.04.2025
imageImage preview is unavailable
ሳይንቲስቶች ለመጀመሪያ ጊዜ የሰውን ጥርስ በላብራቶሪ ውስጥ አሳደጉ - ቴሌግራፍ አንድ ጥናት ጠቅሶ ዘግቧል።
ሳይንቲስቶች ይህ ዘዴ የጥርስን መልሶ ማሳደግ ህክምና በእጅጉ ሊለውጠው እንደሚችል ያምናሉ።
በኪንግስ ኮሌጅ ሎንዶን ተመራማሪዎች እንደገለጹት ይህ ግኝት በመጨረሻ ታካሚዎች የጠፉ ጥርሶቻቸውን የጥርስ ተከላዎችን ወይም ሙላቶችን እንደ አማራጭ እንዲተኩ ሊያስችላቸው ይችላል። ቡድኑ የጥርስ መፈጠርን የሚጠይቁ ሁኔታዎችን የሚመስል ንጥረ ነገር ፈጥሯል፣ ይህም ሴሎች እንዲግባቡ እና የጥርስ መፈጠር ሂደትን እንዲጀምሩ ያስችላል።
በኪንግስ ኮሌጅ የሪጄኔራቲቭ የጥርስ ህክምና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አና አንጀሎቫ ቮልፖኒ ጥናቱ "የጥርስ
ከተከላ እና ከመሙላት በተለየ፣ ያደገው ጥርስ በመንጋጋው ውስጥ ሊዋሃድ እና እንደገና ሊያድግ ይችላል። በተጨማሪም ጠንካራ ይሆናል ተብሏል።
@Tikfahethiopia
1592
07:11
15.04.2025
close
New items
Selected
0
channels for:$0.00
Subscribers:
0
Views:
lock_outline
Add to CartBuy for:$0.00
Комментарий