
- Main
- Catalog
- Books, Audiobooks & Podcasts
- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
"በተማርከው እና በተረዳኸው ነገር ፀንተ ኑር" የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትምህርቶች እና ስንክሳር ያሉበት
Channel statistics
"" እንደ ኒቆዲሞስ ቆራጥ ልብ እንዲኖረን ምን እናድርግ ? ""
✝ ለጥያቄዎት መልስ ፦ ቆራጥ ልብን የሚያድል እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነው ። ሰማዕታት አንገታቸውን ለሰይፍ እስከመስጠት የሚታመኑት ለእግዚአብሔር ጥልቅ ፍቅር እንዲሁም በዓላማ የተሞላ ቆራጥ ልብ ስላላቸው ነው ። ዛሬ ወዳጃችንን በመውደድ ከተማንን ነገ ጠላታችንን በመውደድ ላይ ይሾመናል ። የክርስትና ጉዞ ይህ ነው ።
ኒቆዲሞስ የቆረጠ ልብ ያገኘው በፈተና እንዲሁም በትምህርት ነው ። አስቀድሞ የተማረውን መረመረ ኋላም በሌሊት ከጌታችን ቀርቦ እውነቱን ተረዳ ። የክብሩ ጉዳይ ፣ የአይሁድ ሕግ ሳያስጨንቀው በዕለተ አርብ ጌታን ከመስቀል ለማውረድ ታደለ ። ይህ ሁሉ ቆራጥነት የተገኘው ከመፈተን ነው ። ፈተና የሌለበት ክርስትና አሰልቺ ነው ። ፈተና ካለ ውጤት ሊከተል ግድ ነው ነገር ግን ውጤቱ ዜሮ ከሆነ ችግሩ አለመማር እንዲሁም አለመጸለይ ነው ። ስለዚህ ከመፈተን አስቀድሞ መማር ፣ መጸለይ ይገባልና ።
"ከእግዚአብሔር የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰማል ።” /ዮሐ 8፥47/ እንዲል ዘወትር ተግተን በመማር ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን በማንበብ ላይ ከታመንን እርሱ ደግሞ በሚበልጠው ጸጋ ይሾመናል ። ስለዚህ እንደ ኒቆዲሞስ ቆራጥ ልብ ኖሮን ወደ ጌታችን እንዳንቀርብ ፣ እንዳንማር ያደረጉንን ነገሮች ምንድን ናቸው ? እነዚህን አስቀድመን ለይተን እንወቅ ። ኋላ በሽታው ከታወቀ መድኃኒቱ ቅርብ ነው ።
✍ ብርሃነ ሥላሴ [ መጋቢት 22 ቀን 2018 ]
« ወስብሐት ለእግዚአብሔር »
ለጥያቄ @Tyake_alegn_bot
JOIN
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
ምሮኝ እኮነው ምሮኝ/2/
ስወድቅ እጁ ደግፎኝ
በቅቼ አይደለሞ ነጽቼ
ኃጢአት ሳልሰራ ቀርቼ
አዝ
ከቁጥር ቢያልፍም ነውሬ
መች አዋረደኝ ከክብሬ
አነሳኝ በምህረት እጁ
ዳግም አደረገኝ ልጁ/2/
አዝ
በደሌ አልነበረም የዋዛ
መልኬ ግን በፍቅሩ ወዛ
ነው በቸርነት የሚገዛ
አምላኬ ትእግስቱ በዛ
ጌታዬ ትእግስቱ በዛ
አዝ
ተከደነልኝ ሀጢአቴ
መች ተወኝ በጥፋቴ
ይደንቃል የጌታ ፍቅሩ
በደሌ ቢበዛም ቁጥሩ/2/
አዝ
በጽድቄ አይደለም መኖሬ
አንድስ እንኳን በመግባሬ
ይሄው ደረስኩኝ ለዛሬ
ምህረት በዝቶልኝ ተምሬ/2/
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
https://t.me/Abel_mekebeb
https://t.me/Abel_mekebeb
https://t.me/Abel_mekebeb
ኒቆዲሞስ /2/
ትሁቱ ተማሪ የኢየሱስ ክርስቶስ /2/
አዝ
የሰው ልጅ መክበሩን በዳግመኛ ልደት
ከውሃ ከመንፈስ እንዲገኝ ልጅነት
የአይሁድ መምህር ከጌታ ስር ሆኖ
ጠይቆ ተረዳ ተቀበለው አምኖ
አዝ
የመከራው ጊዜ ዘመኑ ሲያበቃ
የኦሪቱ መምህር የአይሁድ አለቃ
ብሉዩን ከሐዲስ እያመሳጠረ
ከጌታ እግር ስር ቁጭ ብሎ ተማረ
አዝ
ሊቅ ሲሆን ተማሪ ሊሆን የተመኘ
በጨለማ ሄዶ ብርሃኑን አገኘ
ኒቆዲሞስ ትሁት ጽድቅን የተጠማ
ምንጩን ተጎነጨ ወጣ ከጨለማ
አዝ
በአይሁድ ጭካኔ ብዙዎች ሲፈሩ
የክፉ ቀን ወዳጅ ሆነ ለመምህሩ
ጽድቅና መንግሥቱን እየመሰከረ
በአዲስ መቃብር ስጋውን አኖረ
ዘማሪ ዲ/ን አቤል ተስፋዬ
https://t.me/Abel_mekebeb
https://t.me/Abel_mekebeb
https://t.me/Abel_mekebeb
የካስከው አንተ የበደልኩ እኔ
የቆሰልከው አንተ የዳንኩት እኔ
ወሰን የለውም መጠን መመርመር
ከሕሊና ይልቃል ጌታ ያንተስ ፍቅር
አዝ
እስከ መስቀል ሞት የደረስክልኝ
ስለ እኔ ብለህ የደማህልኝ
በደምህ ዋጋ ተገዝቻለው
ከእንግዲህ ወዲህ የራሴ አይደለሁ/2/
አዝ
አንተ ተደፋህ እኔ እንድል ቀና
የእዳዬን ሸክም ተሸከምክና
ጌተ ሴማኔ ጌታ ጸለየ
አስተምረኸኛል አረአያ ሆነህ/2/
አዝ
ጌታ ደወዬን በእውነት ተቀበልክ
ሁሉን ቻይ ጌታ ስለኔ ደከምክ
ልብ ኩላሊትን የምትመረምረው
ማን መታህ አሉ አይንህን አስረው/2/
አዝ
በአይሁድ ሸንጎ ለፍርድ የቆምከው
ንፁሁ በሐሰት የተከሰስከው
አበሳ በደል አይደል ኖሮብህ
እኔን ወደህ ነው ለዚህ መድረስህ/2/
ዘማሪ ገብረዮሐንስ ገብረፃድቅ
https://t.me/Abel_mekebeb
https://t.me/Abel_mekebeb
https://t.me/Abel_mekebeb
ቅዱስ ያሬድ ንብ የማትቀስመው አበባ እንደሌላት ሁሉን ቀስማ ያማረ የጣፈጠ ማር እንድትሠራ እርሱም ሐዲሳትን ከብሉያት እያስማማ ለጀሮ የሚስማማ ኅሊናን የሚመስጥ ድንቅ ዜማ ባዘጋጀልን መሠረት የዐቢይ ጾም ሰባተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ተብሎ ይጠራል፡፡ ሊቁ “ኒቆዲሞስ ስሙ ዘሖረ ኀቤሁ ቀዲሙ ሌሊተ ወይቤሎ በጽሚት ረቢ ነአምን ብከ ከመ እምኀበ አብ መጽአከ ሖረ ኀቤሁ ዘስሙ ኒቆዲሞስ ወይቤሎ ለኢየሱስ ረቢ ሊቅ ንሕነ ነአምን ብከ ከመ እምኀበ አብ መጻአከ ከመ ትኩን መምሕረ ወበምጽአትከ አብራህከ ለነ ወሰላመ ጸጎከነ አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ፤ አስቀድሞ በሌሊት ወደርሱ ይሔድ የነበረ ስሙ ኒቆድሞስ የሚባል ሰው በቀስታ “ሊቅ ሆይ ከአብ ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን” አለው። ኒቆዲሞስም ወደ እርሱ ሔደ፤ ረቢ ኢየሱስንም ሊቅ (አዋቂ) እንደሆንክ ለማስተማር ከአብ ዘንድም እንደመጣህ እኛ እናውቃለን፤ በምጽአትህም አበራህልን፤ ሰላምንም ሰጠኸን፤ ኃይልህን አንሳ፤ መጥተህም አድነን አለው” ይለናል። (ጾመ ድጓ)
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ሲያስተምር የአይሁድ አለቃ የሚሆን ኒቆዲሞስ የሚባል ሰው በሌሊት መጣ፤ ስለምን በሌሊት መጣ ቢሉ ከንቱ ውዳሴን ሽቶ አንተ የአይሁድ አለቃ ስትሆን እንዴት ትማራለህ እንዳይባል ሰው በማይመጣበት ከሰው ተለይቶ ሊማር ሽቶ በሌሊት መጣ። እንደዚሁም ምሁረ ኦሪት ነውና ምሥጢር ሊያደላድል ነው። በቀን ጌታን አምስት ገበያ ሕዝብ ይከተለው ስለነበር ለመጠየቅ አልተመቸውም ነበር፡፡ ጌታም በአእምሮ ያልጎለመሱ ሰዎችን ያስተምር ነበርና በምሳሌ እየመሰለ ያስተምራቸው ነበር። ቅዱስ ጳውሎስ “እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ የሥጋ እንደ መሆናችሁ፥ በክርስቶስም ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደ መሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም። ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበርና ወተት ጋትኋችሁ፤ ገና ሥጋውያን ናችሁና እስከ አሁን ድረስ ገና አትችሉም። ቅናትና ክርክር ስለሚገኝባችሁ ሥጋውያን መሆናችሁ አይደላችሁምን? እንደ ሰው ልማድስ አትመላለሱምን?” እንዲል አጥንት ለመቆርጠም አልደረሱም ነበር። (፩ኛቆሮ.፫፥፩-፫) ኒቆዲሞስ ግን ምሁረ ኦሪት ነውና ጠንከር ያለ ትምህርት ሽቶ በሌሊት መጣ። በተጨማሪም የቀን ልቡና ባካና ነው ኅሊና ይሠረቃልና ክት ሊኅና ሽቶ በሌሊት ሊማር መጣ።
አባቶቻችን በሠሩት የትምህርት ሥርዓትም ምንኛ ጥበበኛ እንደ ሆኑ አስተውሉ! በቀን ጆሯችን የአካባቢ ድምጽ ይሰማል፤ ዓይናችን ሌላ ይመለከታል፤ ወጭ ወራጁ አላፊ አግዳሚው ይረብሻል። በሌሊት ግን ኅሊናን የሚሠርቅ ምንም ነገር የለምና ሐሳብን ሰብስቦ ለማስተማር እንዲመች የአብነት ትምህርቱን የሌሊትና የቀን ብለው ከፍለው የቃል ትምህርቱን በሌሊት እንድንማር አደረጉን። የጠቢቡ ሰሎሞን “ሌሊት በምንጣፌ ላይ ነፍሴ የወደደችውን ፈለግሁት” የሚለው ቃል ምነኛ ይደንቃል! (መኃ.፫፥፩) ኒቆዲሞስ ነፍሱ የፈለገችውን ሊፈልግ በሌሊት መጣ። ሌሊት ሁሉ ሰው ተኝቶ ባለበት ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር መቻል እንዴት መታደል ነው። ክርስቲያኖች እስኪ አስቡት! ማንም በሌለበት፣ ሁሉ በተኛበት ሰዓት አልጋችሁ ላይ ሁናችሁ ክርስቶስን መፈለግ በጨለማ ውስጥ ውሳጣዊ ዓይናችሁ ብቻ ተከፍቶ ከአምላካችሁ ጋር መነጋገር እጅግ ልዩ ነውና ሌሊቱን ከእግዚአብሔር ጋር በመሆን አሳልፉት።
ኒቆዲሞስ የአይሁድ አለቃ በመሆኑ ቀን ሥራ ውሎ ሌሊት በእግዚአብሔር ቃል ያርፍ ነበር። ይህ ሐሳብ ለእኛ ዘመንም የሚጠቅም ነውና እንማርበት ዘንድ ወደድኩኝ። ዛሬ የሕዝብ አለቃዎች ሹማምንቶች መኳንንቶች እናንተስ መቼ ነው የምትማሩ? የምትበልጠዋን ጸጋ ታገኟት ዘንድ ያገኛችኋትን ታጸኗት ዘንድ ኑ! የእግዚአብሔር አካል በሆነችዋ ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔርን ቃል እየሰማችሁ ዕረፉ። ዛሬ ብዙ ሰው ለምን አትማርም ሲባል ሥራ በዝቶብኝ፣ ቢዚ ሁኜ በማለት መመለሱ እየተለመደ መጥቶአል። እኔ ግን እንዲህ ብዬ እጠይቃችኋለሁ፣ በውኑ የእናንተ ሥራ ከኒቆዲሞስ ይበልጣልን? ወይስ ከዳዊት በላይ ትሠራላችሁ? ወይንስ ከላል ይበላ በላይ ሠርታችሁ ነው? እኔ ግን በመኃልየ መኃልይ እንደ ተጻፈ በምክንያት እየራቃችሁ ነው። “እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል፤ የውዴ ቃል ነው፥ እርሱም ደጁን ይመታል፤ እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥ በራሴ ጠል፥ በቈንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ ሞልቶበታልና ክፈችልኝ። ቀሚሴን አወለቅሁ፤ እንዴት እለብሰዋለሁ? እግሬን ታጠብሁ፤ እንዴት አሳድፈዋለሁ?” በማለት እንደተናገረችው ሰው የሆን ይመስለኛል። (መኃ.፭፥፪) ይህች ሰው ከረፈደ በኋላ ፍለጋ ብትወጣም ማግኘት ግን አልቻለችም፤ እናም ሁላችንም ዛሬ ሳይረፍድብን ታግለን መጣል ሩጠን መቅደም በምንችልበት ጊዜ ምክንያት በመደርደር አንራቅ ለማለት እወዳለሁ።
ኒቆዲሞስ በሌሊት መጥቶ ከጌታችን እግር ሥር ተቀምጦ ሲማር በዓይነ ኅሊናችን እንመልከተው! ግርማ ሌሊቱ ጸብአ አራዊቱ ሳያስፈራው፣ ድካም ሳይበግረው በጌታው እግር ሥር ቁጭ ብሎ ሲማር ቅዱስ ዳዊት ” ቃልህ ለጕሮሮዬ ጣፋጭ ነው፤ ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ። ከትእዛዝህ የተነሣ አስተዋልሁ፤ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ። ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው።” እንዳለ ከማርና ከሥኳር የሚጣፍጠውን ቃለ እግዚአብሔር ሲሰማ ሰው እንዳያየው ተደብቆ የመጣው ኒቆዲሞስ ከመስቀሉ ሥር የሚገኝ የመከራ ቀን ሐዋርያ ሆነ። (መዝ.፻፲፱፥፻፫-፻፭) ሌሊት በመከራ ይመሰላል፤ በመከራ መጥቶ የተማረው ኒቆዲሞስ ሐዋርያት እንኳን ጥለውት በሸሹ ጊዜ ከመስቀሉ ሥር ተገኘ። ሥጦታ ይሆን ዘንድ የክርስቶስን ሥጋ ገንዞ ለመቅበር የበቃ ሆነ። ክርስቲያኖች! እናንተስ ክርስቶስን ልትገንዙ ትሻላችሁን? በዚያ በመስቀል ላይ ሳለ ቅድስት ሥጋው ከቅድስት ነፍሱ ሲለይ ከመስቀል አውርዶ የሚቀብረው አጥቶ እናቱ ድንግል ማርያም እያለቀሰች ሳለ የተገኘ የእመ ብርሃንን እንባ ያበሰ ቅዱስ ለመሆን በቃ።
አሁንም እንደ ኒቆዲሞስ ሌሊት መጥቶ የሚማር ሰው አጥታ ቤተ ክርስቲያን ስታለቅስ፣ ሰቃልያነ ክርስቶስ ጌታን ዳግመኛ ሊሰቅሉት ሲሹ ከመስቀሉ ሥር የሚገኝ በመከራ የሚጸና ሰው ያስፈልጋልና የዓለም ውጣ ውረድ ሳያግዳችሁ ከቤቱ መጥታችሁ ትማሩ ዘንድ እለምናችኋለሁ። ዛሬ ላይ አንድ ነገር ይደንቀኛል! ሰው ሥልጣን ሲይዝ ከቤተ ክርስቲያን የሚያደርገውን ሽሽት አስተውሉ! ኒቆዲሞስ የአይሁድ አለቃ ቢሆንም ግን ወደ ጌታ ከመምጣት አላገደውም፤ የዛሬዎቹ አለቃ ግን አለመምጣት ብቻ ሳይሆን ክርስቲያን ሆኖ መታየት እንኳን ያሳፍራቸዋል። የልቤ እምነት እንጅ ማተብ ባላደርግስ በሚል ሐሳብም ማተባቸውን የሚፈቱም አይጠፉ፤ አንዳንዶች ደግሞ ለመመሳሰል ሐብል ያደርጋሉ። ክርስቲያኖች ከአምላካችን በእውነት ወዴት እንሄዳለን? እንደ አባቶቻችን ሐዋርያት “ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘለዓለም ሕይወት ቃል አለህ፤ እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ አምነናል አውቀናልም ብሎ መለሰለት” እንዲል፤ እንዲህ እያልን ልንኖር ያስፈልጋል፡፡ (ዮሐ ፮፥፷፰)
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
« ወርቅን ሊያጣራ የሚፈልግ ሰው እሳቱን አንድ ጊዜ የሚያነድና እንደ ገና መልሶ የሚያጠፋ ከሆነ ለሥራው አይጠቅመውም፡፡ እንዲሁም ነፍስ አንድ ጊዜ ለእግዚአብሔር የምትገዛ ሌላ ጊዜ ደግሞ ቸል የምትል ከሆነ አይጠቅማትም፡፡"ምክር ዘ አበው ቀደምት
ሼር ✞
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
ቅዱስ ባስልዮስ
ከክፉ ሐሳብ መድኃኔዓለም ይጠብቀን
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
በዚህ ሳምንት የታሰሩ ወንድሞች!!!
መምህር ደረጀ ነጋሽ
ጋዜጠኛ ነጋሽ በዳዳ
መምህር ሲሳይ አዳነ
በዚህ ሳምንት የታሰሩ ወንድሞች!!!
መምህር ደረጀ ነጋሽ
ጋዜጠኛ ነጋሽ በዳዳ
መምህር ሲሳይ አዳነ
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
✞⌲
ˢʰᵃʳᵉ
አንድ ቀን ባለሀብቱ ለሁለቱ አገልጋዮች እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ትልቅ ድስት ሰጣቸው። "እነዚህን ድስቶች ውሰዱና እዚያ ማዶ ካለው ምንጭ ውኃ እየቀዳችሁ ይህን ትልቅ በርሜል ሙሉልኝ" አላቸው። የሚገርመው ግን የሁለቱም ድስቶች የታችኛው ክፍል ትላልቅ ቀዳዳዎች ነበሯቸው።
ትጉሁ አገልጋይ ምንም ጥያቄ ሳይጠይቅ ድስቱን ይዞ ውኃ ሊቀዳ ሄደ። ስነፉ አገልጋይ ግን ድስቱን ሲያየው ሳቀ። "ጌታችን አርጅቷል መሰል? የተበሳ ድስት ሰጥቶን ውኃ ቅዱ ይላል? ይሄ እኮ አይሞላም!" አለና ጥሎት ሄዶ ዛፍ ስር ተኛ።
ትጉሁ አገልጋይ ግን ቀን ሙሉ ከምንጩ እየቀዳ ወደ በርሜሉ ይሮጣል። ድስቱ የተበሳ ስለሆነ ውኃው ሁሉ መንገድ ላይ ይፈሳል፤ ነገር ግን እሱ ሳይታክት "ጌታዬ እዘዘኝ እንጂ ውጤቱን አልተቆጣጠረም" ብሎ ደጋግሞ መቅዳቱን ቀጠለ።
በመጨረሻም ፀሐይ ስትጠልቅ፣ ትጉሁ አገልጋይ ከድስቱ ውስጥ ውኃው አልቆ በድስቱ ግርጌ ላይ አንድ ትልቅ አልማዝ አገኘ። ምንጩ ውስጥ ተደብቆ የነበረው አልማዝ፣ ሰውየው ደጋግሞ ሲቀዳ በድስቱ ውስጥ ቀርቶ ነበር።
ባለሀብቱም መጣና ስነፉን አገልጋይ "ለምን አልሠራህም?" አለው። ስነፉም "ድስቱ የተበሳ ስለሆነ ለምን ጊዜዬን አጠፋለሁ?" አለው። ባለሀብቱም ትጉሁን አገልጋይ ጠርቶ "አየህ፣ አንተ ታማኝ ስለሆንክና ሳታጉረመርም ስለታዘዝክ፣ በድስቱ ግርጌ ያገኘኸው አልማዝ የአንተ ነው" አለው። "እኔ የፈለግኩት በርሜሉን እንድትሞሉ ሳይሆን፣ ድስቶቹ በውኃው እንዲጸዱና ድስቱ ውስጥ ያለውን ሀብት እንድታገኙ ነበር" አላቸው።
***
እግዚአብሔር አንዳንዴ ውጤቱ የማይታይ የሚመስል ትእዛዝ ሊሰጠን ይችላል (ለምሳሌ ጸልዩ፣ ታገሡ፣ ስጡ...)። እኛ ግን "ይህ ምን ጥቅም አለው?" ብለን መጠራጠር የለብንም። እግዚአብሔር የሚፈልገው የእኛን "ውጤት" ሳይሆን "ታማኝነት" ነው። በትጋት ለሚታዘዙ ሰዎች፣ በድካማቸው ውስጥ ያላሰቡት ትልቅ አልማዝ (በረከት) ተደብቆ ይጠብቃቸዋል።
ሼር ✞
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
https://t.me/tewahdo2780
Reviews channel
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን is a Telegram channel in the category «Книги, Аудиокниги и Подкасты», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 1.9K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 7.1, with 0 reviews and an average score of 0.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.8 ₽, and with 0 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий