
Monetize Telegram Mini App with Telega.io
Connect your app, set CPM, and watch your revenue grow!
Start monetizing
17.5

Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️»
5.0
2
Religion & Spirituality
Language:
Amharic
130
1
Share
Add to favorite
Buy advertising in this channel
Placement Format:
keyboard_arrow_down
- 1/24
- 2/48
- 3/72
- Native
- 7 days
- Forwards
1 hour in the top / 24 hours in the feed
Quantity
%keyboard_arrow_down
- 1
- 2
- 3
- 4
- 5
- 8
- 10
- 15
Advertising publication cost
local_activity
$1.20$1.20local_mall
0.0%
Remaining at this price:0
Recent Channel Posts
#የነሐሴ_17_ግጻዌ
ፊልጵስዩስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በቀረውስ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ በጌታ ደስ ይበላችሁ። ስለ አንድ ነገር መልሼ ልጽፍላችሁ እኔን አይታክተኝም ለእናንተ ግን ደኅና ነው።
² ከውሾች ተጠበቁ፥ ከክፉዎችም ሠራተኞች ተጠበቁ፥ ከሐሰተኛም መገረዝ ተጠበቁ።
³ እኛ በመንፈስ እግዚአብሔርን የምናመልክ በክርስቶስ ኢየሱስም የምንመካ በሥጋም የማንታመን እኛ የተገረዝን ነንና።
⁴ እኔ ግን በሥጋ ደግሞ የምታመንበት አለኝ። ሌላ ሰው ማንም ቢሆን በሥጋ የሚታመንበት እንዳለው ቢመስለው፥ እኔ እበልጠዋለሁ።
⁵ በስምንተኛው ቀን የተገረዝሁ፥ ከእስራኤል ትውልድ፥ ከብንያም ወገን፥ ከዕብራውያን ዕብራዊ ነኝ፤ ስለ ሕግ ብትጠይቁ፥ ፈሪሳዊ ነበርሁ፤
⁶ ስለ ቅንዓት ብትጠይቁ፥ ቤተ ክርስቲያንን አሳዳጅ ነበርሁ፤ በሕግ ስለሚገኝ ጽድቅ ብትጠይቁ፥ ያለ ነቀፋ ነበርሁ።
1ኛ ጴጥሮስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ወዳጆች ሆይ፥ በእናንተ መካከል እንደ እሳት ሊፈትናችሁ ስለሚሆነው መከራ ድንቅ ነገር እንደ መጣባችሁ አትደነቁ፤
¹³ ነገር ግን ክብሩ ሲገለጥ ደግሞ ሐሤት እያደረጋችሁ ደስ እንዲላችሁ፥ በክርስቶስ መከራ በምትካፈሉበት ልክ ደስ ይበላችሁ።
¹⁴ ስለ ክርስቶስ ስም ብትነቀፉ የክብር መንፈስ የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ላይ ያርፋልና ብፁዓን ናችሁ።
¹⁵ ከእናንተ ማንም ነፍሰ ገዳይ ወይም ሌባ ወይም ክፉ አድራጊ እንደሚሆን ወይም በሌሎች ጒዳይ እንደሚገባ ሆኖ መከራን አይቀበል፤
¹⁶ ክርስቲያን እንደሚሆን ግን መከራን ቢቀበል ስለዚህ ስም እግዚአብሔርን ያመስግን እንጂ አይፈር።
¹⁷ ፍርድ ከእግዚአብሔር ቤት ተነሥቶ የሚጀመርበት ጊዜ ደርሶአልና፤ አስቀድሞም በእኛ የሚጀመር ከሆነ ለእግዚአብሔር ወንጌል የማይታዘዙ መጨረሻቸው ምን ይሆን?
¹⁸ ጻድቅም በጭንቅ የሚድን ከሆነ ዓመፀኛውና ኃጢአተኛው ወዴት ይታይ ዘንድ አለው?
¹⁹ ስለዚህ ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መከራን የሚቀበሉ፥ መልካምን እያደረጉ ነፍሳቸውን ለታመነ ፈጣሪ አደራ ይስጡ።
ሐዋርያት 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ሳውል ግን የጌታን ደቀ መዛሙርት እንዲገድላቸው ገና እየዛተ ወደ ሊቀ ካህናት ሄደ፥
² በዚህ መንገድ ያሉትንም ሰዎች ወንዶችንም ሴቶችንም ቢያገኝ፥ እያሰረ ወደ ኢየሩሳሌም ያመጣቸው ዘንድ በደማስቆ ላሉት ምኵራቦች ደብዳቤ ከእርሱ ለመነ።
³ ሲሄድም ወደ ደማስቆ በቀረበ ጊዜ ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ፤
⁴ በምድርም ላይ ወድቆ ሳለ፦ ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ ሰማ።
⁵ ጌታ ሆይ፥ ማን ነህ? አለው። እርሱም፦ አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል አለው።
⁶ እየተንቀጠቀጠና እየተደነቀ፦ ጌታ ሆይ፥ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ? አለው። ጌታም፦ ተነሥተህ ወደ ከተማ ግባና ታደርገው ዘንድ የሚያስፈልግህን ይነግሩሃል አለው።
⁷ ከእርሱም ጋር በመንገድ የሄዱ ሰዎች ድምፁን እየሰሙ ማንን ግን ሳያዩ እንደ ዲዳዎች ቆሙ።
⁸ ሳውልም ከምድር ተነሣ፥ አይኖቹም በተከፈቱ ጊዜ ምንም አላየም፤ እጁንም ይዘው እየመሩ ወደ ደማስቆ አገቡት።
#ምስባክ👇
ገሥፆሰ ገሠፀኒ #እግዚአብሔር። ወለሞትሰ ባሕቱ ኢመጠወኒ። አርኅው ሊተ አናቅጸ ጽድቅ።#ትርጉም፦
መገሠጽስ #እግዚአብሔር ገሠጸኝ፤ ለሞት ግን አልሰጠኝም። የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ፤ ወደ እነርሱ ገብቼ #እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።{}
መዝ. 117፥18-19
ወይም👇
ወትቀውም ንግሥት በየማንከ። በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኁብርት። ስምዒ ወለትየ ወርእዩ። ወአጽምኢ እዝነኪ ወርስዒ። ሕዝበኪ ወቤተ አቡኪ።#ትርጉም፦
የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች። ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ {}
መዝ.44፥9-10።
#ወንጌል📖
ዮሐንስ 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት።
¹³ ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም።
¹⁴ እኔ ያዘዝኋችሁን ሁሉ ብታደርጉ እናንተ ወዳጆቼ ናችሁ።
¹⁵ ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ፥ ከአባቴ የሰማሁትን ሁሉ ለእናንተ አስታውቄአችኋለሁና።
¹⁶ እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ እንዲሰጣችሁ፥ ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ።
¹⁷ እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ይህን አዛችኋለሁ።
¹⁸ ዓለም ቢጠላችሁ ከእናንተ በፊት እኔን እንደ ጠላኝ እወቁ።
¹⁹ ከዓለምስ ብትሆኑ ዓለም የራሱ የሆነውን ይወድ ነበር፤ ነገር ግን እኔ ከዓለም መረጥኋችሁ እንጂ ከዓለም ስለ አይደላችሁ ስለዚህ ዓለም ይጠላችኋል።
²⁰ ባርያ ከጌታው አይበልጥም ብዬ የነገርኋችሁን ቃል አስቡ። እኔን አሳደውኝ እንደ ሆኑ እናንተን ደግሞ ያሳድዱአችኋል፤ ቃሌን ጠብቀው እንደ ሆኑ ቃላችሁን ደግሞ ይጠብቃሉ።
²¹ ዳሩ ግን የላከኝን አያውቁምና ይህን ሁሉ ስለ ስሜ ያደርጉባችኋል።
²² እኔ መጥቼ ባልነገርኋቸውስ ኃጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ አሁን ግን ለኃጢአታቸው ምክንያት የላቸውም።
²³ እኔን የሚጠላ አባቴን ደግሞ ይጠላል።
²⁴ ሌላ ሰው ያላደረገውን ሥራ በመካከላቸው ባላደረግሁ፥ ኃጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ አሁን ግን እኔንም አባቴንም አይተውማል ጠልተውማል።
²⁵ ነገር ግን በሕጋቸው። በከንቱ ጠሉኝ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው።
ወይም👇
ሉቃስ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁹ ማርያምም በዚያ ወራት ተነሥታ ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ከተማ ፈጥና ወጣች፥
⁴⁰ ወደ ዘካርያስም ቤት ገብታ ኤልሳቤጥን ተሳለመቻት።
⁴¹ ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥
⁴² በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች፦ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው።
⁴³ የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?
⁴⁴ እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና።
⁴⁵ ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት።
⁴⁶ ማርያምም እንዲህ አለች፦
⁴⁷ ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፥ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤
⁴⁸ የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤
⁴⁹ ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው።
⁵⁰ ምሕረቱም ለሚፈሩት እስከ ትውልድና ትውልድ ይኖራል።
⁵¹ በክንዱ ኃይል አድርጎአል፤ ትዕቢተኞችን በልባቸው አሳብ በትኖአል፤
⁵² ገዥዎችን ከዙፋናቸው አዋርዶአል፤ ትሑታንንም ከፍ አድርጎአል፤
⁵³ የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአል፤ ባለ ጠጎችንም ባዶአቸውን ሰዶአቸዋል።
⁵⁴-⁵⁵ ለአባቶቻችን እንደ ተናገረ፥ ለአብርሃምና ለዘሩ ለዘላለም ምሕረቱ ትዝ እያለው እስራኤልን ብላቴናውን ረድቶአል።
⁵⁶ ማርያምም ሦስት ወር የሚያህል በእርስዋ ዘንድ ተቀመጠች ወደ ቤትዋም ተመለሰች።
✝️ ቅዳሴ ማርያም ቅዳሴ ነው።
መልካም የ #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_ወላዲተ_አምላክ የትንሣኤና የዕርገት በዓል ሰሞኑ ለሁላችንም ይሁንልን።245
19:39
23.08.2025
🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵
ስርዓተ ማኅሌት ዘነሐሴ ገብርኤል
🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷
መሪ ወገን ና አንሽ ወገን አንድ ላይ፦ ለዓለመ ወለዓለመ ዓለም ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡፡ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፡፡ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኵሉ ዓለመ በአሐቲ ቃል
💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠
ያለ ከበሮና ጽናጽል በፊት በጉረሮ
👉 ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
በቁም ከከበሮና ጽናጽል ጋር
👉ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡
👉በአሐቲ ቃል።
በመረግድ
👉ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡
👉በአሐቲ ቃል።
በቁም
👉ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
በመረግድ-
👉ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
በቁም
👉ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
በመረግድ
👉ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
በቁም
👉ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡
"ልዑል" ብለው እንደጨረሱ እንደሌላው መልክዕ ስምዓኒ ተብሎ በመረገድ አይባሉም እዛው በቁም እንደተባለ ሁሉም ጽናጽሉን አስቀምጦ በጉረሮ 👇👇
👉ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
በጉረሮ እንደጨረሱ ሁሉም ከታች ያሉትን ይበሉ
( #በሕብረት_የሚባል )
ዳዊት ነቢይ በከመ ጸለየ፤እጼሊ ኀቤከ እግዚአብሔር አምላኪየ እንዘ ዕብል ከመዝ፤ፀወንየ ወኰኲሕየ፤ወታድኅነኒ ሊተ እምጸላዕትየ፤ወዐቃቤየ ትከውነኒ፤ወእትዌከል ብከ ምዕመንየ ወዘመነ ፍቃንርየ፤ረዳኢየ ወምስካይየ፤ ወሕይወትየ ወታድኅነኒ፤ እምእደ ገፋዕየ፤ሃሌ ሉያ በስብሐት ዕጼውዓከ፤ንጉሥየ ወአምላኪየ፤ሚካኤል መልአክ፤ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ፤ወበእንተ ነፍሰ ኵልነ፤ መልአኪየ ይቤሎ፤እመላእክት ሠምሮ፤መልአከ ኪዳኑ ለክርስቶስ
( #በሕብረት_የሚባል )
ሰላም ለክሙ ማኅበረ መላእክት ትጉሃን: ሰላም ለክሙ ማኅበረ ነቢያት ቅዱሳን: ሰላም ለክሙ ማኅበረ ሐዋርያት ፍንዋን: ሰላም ለክሙ ማኅበረ ሰማዕት ወጻድቃን:
ሰላም ለክሙ ማኅበረ ሥላሴ ጉቡዓን: ወሰላም ለማርያም ዘእሳት ክዳን።
( #በሕብረት_የሚባል )
ማኅበረ መላእክት ወሰብእ፤ተዓይነ
ክርስቶስ ወእሙ፤ሰላም ለክሙ ሶበ እከሥት አፉየ ለውዳሴክሙ፤ፍሬ ማኅሌት እምልሳንየ ትቅስሙ፤ምስሌየ ሀልዉ ወምስሌየ ቁሙ።
( #ካህን_የሚለው )
#ሰላም ለአብ ወለወልድ ቃሉ፤ለመንፈስ ቅዱስ ሰላም ዘአካሎሙ አካሉ፤ለማርያም ሰላም እንተ ተሳተፈት ስብሐተ እሉ፤ሰላም ለመላእክት ወለማኅበረ በኩር ኵሉ፤ጽሑፋነ መልክእ ወስም በሰማይ ዘላዕሉ።
#ሰላም ለአብ ገባሬ ኵሉ ዓለም፤ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ
ሰላም፤ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም፤ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም፤ለሰማዕታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም።
ዚቅ፦
ሃሌ ሉያ ለአብ ንሴብሕ፣ሐዋርያት አምገዳም ነሥዕዋ ሃሌ ሉያ ለወልድ ወለመንፈስ ቅዱስ፣ቤተ ወይኑ ለዋህድ አብዕዋ፣ለመርዓተ ጽድቅ አሠርቱ ወክልኤቱ አፍላጋት ዖድዋ፣ ሰማያዊተ ገነተ ሰመይዋ
ዘጣዕሙ፦
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙለወልድኪ፤ አምሳለ ደሙ፤መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ለሙ፤እግዚአብአሄር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ
ዚቅ
አዕረግዋ መላእክት ውስተ ሰማያት፤ጥዕምት በቃላ ወሠናይት በምግባራ፤አዕረግዋ መላእክት ውስተ ሰማያት፤ወትባርክ ነቢያተ ወሐዋርያተ፤አዕረግዋ መላእክት ውስተ ሰማያት፤ወትባርክ ጻድቃነ ወሰማዕተ፤አዕረግዋ መላእክት ውስተ ሰማያት፤በህየ ትባርክ ነገሥተ ወነገሥያተ፤አዕረግዋ መላእክት ውስተ ሰማያት፤አዕረግዋ መላእክት ውስተ ሰማያት።
መልክዓ ገብርኤል
ሰላመ ገብርኤል (በሰላመ ገብርኤል) መልአክ በላዕለ ማርያም ዘአዕረፈ፣ከመ እዜኑ ኅዳጠ ወአኮ ትሩፈ፣እግዚአብሔር ሀበኒ ሲሳየ ልቡና መጽሐፈ፤ ወአፉየ ሙሴ ለእመ ኮነ ጸያፈ፣ጰራቀሊጦስ አሮን ይኩነኒ አፈ
ዚቅ፦
ወይቤላ ውእቱ መልአክ ሰላም ለኪ ሰላመ ዚአየ የሀሉ ምስሌኪ ተፈስሒ ፍሥሕት
መልክዓ ገብርኤል
ሰላም ለአእናፊከ አናቅጸ ፍትው ጼና፣ወለከናፍሪከ ሰላም ከናፍረ ንጽሕ ወቅድስና፣ገብርኤል ፍሡሕ መልአከ ማርያም ወሐና፣አብሥረኒ ብሥራተ ጽድቅ ወዜንወኒ ዳኅና፤እስመ መክፈልተ ኮነ አብሥሮ ወዜና
ዚቅ፦
ዘለዓለም ፍሡሕ ጉጹ ብሩህ እምነቢያት ልሳኑ በሊህ ዘለዓለም ፍሡሕ ቆሙ ነዊህ ዲበ ዕንግድዓሁ ጽሕሙ ስፉሕ ዘለዓለም ፍሡሕ ዕንባቆምኒ ይቤ ድምፆ ሰማዕኩ ግብሮ አንከርኩ ፍኖቶ ዘእምዓለም ርኢኩ
መልክዓ ገብርኤል
ሰላም ለጕርዔከ ኆኅተ ጥዑም ዜማ፣ወለክሳድከ ሥርግወ ቃማ፣ጊዜ ወረድከ ገብርኤል ኀበ ማርያም እምነ ራማ፣ቃል ኃደረ ላዕሌሃ እንበለ ፃዕር ወጻማ፣ኀይለ ልዑል ጸለላ በመንክር ግርማ
ዚቅ፦
ፆረቶ በከርሳ፤ውእቱኒ ቀደሳ፤መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ
ምልጣን፦
በብሩህ ደመና ዘከለላ፤በሐኪ ማርያም እሞሙ ለሰማዕት፤ ወእኅቶሙ ለመላእክት ፤እንተ እምአፉሃ ይወጽእ ቃለ ጽድቅ
እስመ ለዓለም፦
በአምሳለ ዖፍ ርግብ ፀዓዳ ትመስል፣ይእቲኬ ማርያም እሞሙ ለሰማዕት፣ወእኅቶሙ ለመላእክት፣ደመና ቀሊል፣ዘበላዕሌሃ ተመርዓወ ቃል
205
19:41
24.08.2025
218
19:48
24.08.2025
#የነሐሴ_19_ግጻዌ
ሮሜ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ እምነታችሁ በዓለም ሁሉ ስለ ተሰማች አስቀድሜ ስለ ሁላችሁ አምላኬን በኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ።
⁹-¹⁰ በልጁ ወንጌል በመንፈሴ የማገለግለው እግዚአብሔር ምስክሬ ነውና፤ ምናልባት ብዙ ቆይቼ ወደ እናንተ አሁን እንድመጣ በእግዚአብሔር ፈቃድ መንገዴን እንዲያቀናልኝ እየለመንሁ ሁልጊዜ ስጸልይ ስለ እናንተ ሳላቋርጥ አሳስባለሁ።
¹¹ ትጸኑ ዘንድ መንፈሳዊ ስጦታ እንዳካፍላችሁ ላያችሁ እናፍቃለሁና፤
¹² ይህንም ማለቴ በመካከላችን ባለች በእናንተና በእኔ እምነት አብረን በእናንተ እንድንጽናና ነው።
¹³ ወንድሞች ሆይ፥ በሌሎቹ አሕዛብ ደግሞ እንደ ሆነ በእናንተም ፍሬ አገኝ ዘንድ ብዙ ጊዜ ወደ እናንተ ልመጣ እንዳሰብሁ እስከ አሁን ግን እንደ ተከለከልሁ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ።
¹⁴ ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ አለብኝ፤
¹⁵ ስለዚህም በሚቻለኝ መጠን በሮሜ ላላችሁ ለእናንተ ደግሞ ወንጌልን ልሰብክ ተዘጋጅቼአለሁ።
1ኛ ጴጥሮስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ በመጨረሻው ሁላችሁ በአንድ ልብ ሁኑ፥ የሌላው መከራ ለእናንተ እንደሚሆን አድርጉ፥ እንደ ወንድሞች ተዋደዱ፥ ርኅሩኆችና ትሑታን ሁኑ፤
⁹ ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና።
¹⁰ ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤
¹¹ ከክፉ ፈቀቅ ይበል፥ መልካምንም ያድርግ፥ ሰላምን ይሻ ይከተለውም፤
¹² የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና፥ ጆሮዎቹም ለጸሎታቸው ተከፍተዋል፥ የጌታ ፊት ግን ክፉ ነገርን በሚያደርጉ ላይ ነው።
¹³ በጎንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው?
¹⁴ ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ ብፁዓን ናችሁ። ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ አትናወጡም፥
¹⁵ ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት። በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁአችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን።
ሐዋርያት 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁵ በነጋም ጊዜ ገዢዎቹ፦ እነዚያን ሰዎች ፍታቸው ብለው ሎሌዎቻቸውን ላኩ።
³⁶ የወኅኒውም ጠባቂ፦ ትፈቱ ዘንድ ገዢዎቹ ልከዋል፤ እንግዲህ አሁን ወጥታችሁ በሰላም ሂዱ ብሎ ይህን ቃል ለጳውሎስ ነገረው።
³⁷ ጳውሎስ ግን፦ እኛ የሮሜ ሰዎች ስንሆን ያለ ፍርድ በሕዝብ ፊት ደብድበው በወኅኒ ጣሉን፤ አሁንም በስውር ይጥሉናልን? አይሆንም ራሳቸው ግን መጥተው ያውጡን አላቸው።
³⁸ ሎሌዎቹም ይህን ነገር ለገዢዎች ነገሩ። የሮሜ ሰዎችም እንደ ሆኑ በሰሙ ጊዜ ፈሩ፤
³⁹ መጥተውም ማለዱአቸው፥ አውጥተውም ከከተማ ይወጡ ዘንድ ለመኑአቸው።
⁴⁰ ከወኅኒውም ወጥተው ወደ ልድያ ቤት ገቡ፥ ወንድሞችንም ባዩ ጊዜ አጽናኑአቸውና ሄዱ።
#ምስባክ 👇
#እግዚአብሔር እሴብሕ ቃልየ። #እግዚአብሔር ይከብር ዘነበብኩ። ወበ #እግዚአብሔር ተወከልኩ ኢይፈርህ።#ትርጉም
በ #እግዚአብሔር ቃሉን አመሰግናለሁ፤ በ #እግዚአብሔር ቃሉን አከብራለሁ። በ #እግዚአብሔር ታመንሁ፥ አልፈራም ሰው ምን ያደርገኛል?#ወንጌል 📖👇 ማቴዎስ 27 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵⁰ ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ። ⁵¹ እነሆም፥ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፥ ምድርም ተናወጠች፥ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤ ⁵² መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤ ⁵³ ከትንሣኤውም በኋላ ከመቃብሮች ወጥተው ወደ ቅድስት ከተማ ገቡና ለብዙዎች ታዩ። ⁵⁴ የመቶ አለቃም ከእርሱም ጋር ኢየሱስን የሚጠብቁ መናወጡንና የሆነውን ነገር አይተው፦ ይህ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ ብለው እጅግ ፈሩ። ⁵⁵ ኢየሱስን እያገለገሉ ከገሊላ የተከተሉት ብዙ ሴቶች በሩቅ ሆነው ሲመለከቱ በዚያ ነበሩ፤ ✝️ ቅዳሴ #ማርያም ቅዳሴ ነው።
161
19:26
24.08.2025
139
19:33
25.08.2025
#ነሐሴ_20
1ኛ ቆሮንቶስ 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³¹ በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ባለኝ በእናንተ ትምክህት እየማልሁ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ዕለት ዕለት እሞታለሁ።
³² እንደ ሰው በኤፌሶን ከአውሬ ጋር ከታገልሁ፥ ሙታንስ የማይነሡ ከሆነ፥ ምን ይጠቅመኛል? ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ።
³³ አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።
³⁴ በጽድቅ ንቁ ኃጢአትንም አትሥሩ፤ እግዚአብሔርን የማያውቁ አሉና፤ አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ።
³⁵ ነገር ግን ሰው፦ ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።
³⁶ አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም፤
³⁷ የምትዘራውም፥ ስንዴ ቢሆን ከሌላም ዓይነት የአንዱ ቢሆን፥ ቅንጣት ብቻ ነው እንጂ የምትዘራው የሚሆነውን አካል አይደለም፤
³⁸ እግዚአብሔር ግን እንደ ወደደ አካልን ይሰጠዋል ከዘሮችም ለእያንዳንዱ የገዛ አካሉን ይሰጠዋል።
³⁹ ሥጋ ሁሉ አንድ አይደለም፥ የሰው ሥጋ ግን አንድ ነው፥ የእንስሳም ሥጋ ሌላ ነው፥ የወፎችም ሥጋ ሌላ ነው፥ የዓሣም ሥጋ ሌላ ነው።
⁴⁰ ደግሞ ሰማያዊ አካል አለ፥ ምድራዊም አካል አለ፤ ነገር ግን የሰማያዊ አካል ክብር ልዩ ነው፥ የምድራዊም አካል ክብር ልዩ ነው።
⁴¹ የፀሐይ ክብር አንድ ነው የጨረቃም ክብር ሌላ ነው የከዋክብትም ክብር ሌላ ነው፤ በክብር አንዱ ኮከብ ከሌላው ኮከብ ይለያልና።
⁴² የሙታን ትንሣኤ ደግሞ እንዲሁ ነው። በመበስበስ ይዘራል፥ ባለመበስበስ ይነሣል፤
⁴³ በውርደት ይዘራል፥ በክብር ይነሣል፤ በድካም ይዘራል፥ በኃይል ይነሣል፤
⁴⁴ ፍጥረታዊ አካል ይዘራል፥ መንፈሳዊ አካል ይነሣል። ፍጥረታዊ አካል ካለ መንፈሳዊ አካል ደግሞ አለ።
⁴⁵ እንዲሁ ደግሞ፦ ፊተኛው ሰው አዳም ሕያው ነፍስ ሆነ ተብሎ ተጽፎአል፤ ኋለኛው አዳም ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ሆነ።
⁴⁶ ነገር ግን አስቀድሞ ፍጥረታዊው ቀጥሎም መንፈሳዊው ነው እንጂ መንፈሳዊው መጀመሪያ አይደለም።
⁴⁷ የፊተኛው ሰው ከመሬት መሬታዊ ነው፤ ሁለተኛው ሰው ከሰማይ ነው።
⁴⁸ መሬታዊው እንደ ሆነ መሬታውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው፥ ሰማያዊው እንደ ሆነ ሰማያውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው።
⁴⁹ የዚያንም የመሬታዊውን መልክ እንደ ለበስን የሰማያዊውን መልክ ደግሞ እንለብሳለን።
⁵⁰ ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እላለሁ፦ ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርሱ አይችሉም፥ የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም።
ያዕቆብ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ወንድሞች ሆይ፥ እርስ በርሳችሁ አትተማሙ። ወንድሙን የሚያማ በወንድሙም የሚፈርድ ሕግን ያማል በሕግም ይፈርዳል፤ በሕግም ብትፈርድ ፈራጅ ነህ እንጂ ሕግን አድራጊ አይደለህም።
¹² ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ነው፤ እርሱም ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል ነው፤ በሌላው ግን የምትፈርድ አንተ ማን ነህ?
¹³ አሁንም፦ ዛሬ ወይም ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና።
¹⁴ ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና።
¹⁵ በዚህ ፈንታ። ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።
¹⁶ አሁን ግን በትዕቢታችሁ ትመካላችሁ፤ እንደዚህ ያለ ትምክህት ሁሉ ክፉ ነው።
¹⁷ እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው።
ሐዋርያት 23
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²² የሻለቃውም፦ ይህን ነገር ለእኔ ማመልከትህን ለማንም እንዳትገልጥ ብሎ ካዘዘ በኋላ ብላቴናውን አሰናበተው።
²³ ከመቶ አለቆቹም ሁለት ጠርቶ፦ ወደ ቂሣርያ ይሄዱ ዘንድ ሁለት መቶ ወታደሮችንና ሰባ ፈረሰኞችን ሁለት መቶም ባለ ጦር መሣሪያዎችን ከሌሊቱ በሦስተኛው ሰዓት አዘጋጁ አላቸው።
²⁴ ጳውሎስንም ወደ አገረ ገዡ ወደ ፊልክስ በደኅና እንዲያደርሱት የሚያስቀምጡበትን ከብት ያዘጋጁ ዘንድ አዘዛቸው።
²⁵ ደብዳቤም ጻፈ እንዲህ የሚል፦
²⁶ ከቀላውዴዎስ ሉስዮስ ወደ ክቡር አገረ ገዡ ወደ ፊልክስ፤ ሰላም ለአንተ ይሁን።
²⁷ ይህን ሰው አይሁድ ይዘው ሊገድሉት ባሰቡ ጊዜ ከጭፍሮቹ ጋር ደርሼ አዳንሁት፥ ሮማዊ እንደ ሆነ አውቄ ነበርና።
²⁸ የሚከሰስበትንም ምክንያት አውቅ ዘንድ አስቤ ወደ ሸንጎአቸው አወረድሁት፤
²⁹ በሕጋቸውም ስለ መከራከር እንደ ከሰሱት አገኘሁ እንጂ ለሞት ወይም ለእስራት የሚያደርስ ክስ አይደለም።
³⁰ በዚህም ሰው አይሁድ ሴራ እንዲያደርጉበት ባመለከቱኝ ጊዜ ያን ጊዜውን ወደ አንተ ሰደድሁት፥ ከሳሾቹንም ደግሞ በፊትህ ይከሱት ዘንድ አዘዝኋቸው። ደኅና ሁን።
³¹ ወታደሮቹም እንደ ታዘዙት ጳውሎስን ይዘው በሌሊት ወደ አንቲጳጥሪስ አደረሱት፤
³² በነገውም ከእርሱ ጋር ይሄዱ ዘንድ ፈረሰኞችን ትተው ወደ ሰፈር ተመለሱ።
³³ እነዚያም ወደ ቂሣርያ ገብተው ደብዳቤውን ለአገረ ገዡ በሰጡ ጊዜ ጳውሎስን ደግሞ በፊቱ አቆሙት።
³⁴ ካነበበውም በኋላ የወዴት አውራጃ እንደ ሆነ ጠየቀው፤ የኪልቅያ ሰው መሆኑንም ባወቀ ጊዜ፦
#ምስባክ👇
ነጽረኒ ወስምዐኒ እግዚኦ አምላኪየ። አብርሆን ለአዕይንትየ ከመ ኢይኑማ ለመዊት። ወከመ ኢይበሉኒ ጸላእትየ ሞዕናሁ።መዝ 12፥3 ወይም መዝ 44፥9-10። #ትርጉም
አቤቱ አምላኬ፥ እየኝ ስማኝም፤ ጠላቴ፦ አሸነፍሁት እንዳይል፥ የሚያስጨንቁኝም እኔ ብናወጥ ደስ እንዳይላቸው፥ ለሞትም እንዳልተኛ ዓይኖቼን አብራ። {}
መዝ 12፥3
#ወንጌል📖👇
ማቴዎስ 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²³ በዚያን ቀን፦ ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ ቀረቡ፥
²⁴ እንዲህም ብለው ጠየቁት፦ መምህር ሆይ፥ ሙሴ አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ሲሞት ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካ አለ።
²⁵ ሰባት ወንድማማች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ሞተ፥ ዘርም ስለሌለው ሚስቱን ለወንድሙ ተወለት፤
²⁶ እንዲሁ ደግሞ ሁለተኛው ሦስተኛውም፥ እስከ ሰባተኛው ድረስ።
²⁷ ከሁሉም በኋላ ሴቲቱ ሞተች።
²⁸ ሁሉ አግብተዋታልና በትንሣኤ ቀንስ፥ ከሰባቱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች?
²⁹ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።
³⁰ በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም።
³¹-³² ስለ ትንሣኤ ሙታን ግን፦ እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።
³³ ሕዝቡም ይህን ሰምተው በትምህርቱ ተገረሙ።
✝️ ቅዳሴ ማርያም ቅዳሴ ነው።135
19:54
25.08.2025
close
Reviews channel
keyboard_arrow_down
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
5.0
0 reviews over 6 months
c
**ffeenold@******.io
On the service since June 2022
15.12.202420:39
5
Everything is fine. Thank you!
Channel statistics
Rating
17.5
Rating reviews
5.0
Сhannel Rating
4
Subscribers:
5.4K
APV
lock_outline
ER
3.8%
Posts per day:
10.0
CPM
lock_outlineSelected
0
channels for:$0.00
Subscribers:
0
Views:
lock_outline
Add to CartBuy for:$0.00
Комментарий