
- Main
- Catalog
- Religion & Spirituality
- ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️
ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️
በዚህ channel ውስጥ መንፈሳዊ መጻሕፍትንና የየዕለቱን ስንክሳር ያገኛሉ።
Channel statistics
⁹ ይህ ቃል የታመነ ሁሉም እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ¹⁰ ይህን ለማግኘት እንደክማለንና፥ ስለዚህም እንሰደባለን፤ ይህም ሰውን ሁሉ ይልቁንም የሚያምኑትን በሚያድን በሕያው አምላክ ተስፋ ስለምናደርግ ነው። ¹¹-¹² ይህን እዘዝና አስተምር። በቃልና በኑሮ በፍቅርም በእምነትም በንጽሕናም ለሚያምኑቱ ምሳሌ ሁን እንጂ፥ ማንም ታናሽነትህን አይናቀው። ¹³ እስክመጣ ድረስ ለማንበብና ለመምከር ለማስተማርም ተጠንቀቅ። ¹⁴ በትንቢት ከሽማግሌዎች እጅ መጫን ጋር የተሰጠህን፥ በአንተ ያለውን የጸጋ ስጦታ ቸል አትበል። ¹⁵ ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ፥ ይህንም አዘውትር። ¹⁶ ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ፥ በእነዚህም ጽና፤ ይህን ብታደርግ፥ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህና።1ኛ ጴጥሮስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ስለ ጌታ ብላችሁ ለሰው ሥርዓት ሁሉ ተገዙ፤ ለንጉሥም ቢሆን፥ ከሁሉ በላይ ነውና፤ ¹⁴ ለመኳንንትም ቢሆን፥ ክፉ የሚያደርጉትን ለመቅጣት በጎም የሚያደርጉትን ለማመስገን ከእርሱ ተልከዋልና ተገዙ። ¹⁵ በጎ እያደረጋችሁ፥ የማያውቁትን ሞኞች ዝም ታሰኙ ዘንድ እንዲህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነውና፤ ¹⁶ አርነት ወጥታችሁ እንደ እግዚአብሔር ባሪያዎች ሁኑ እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ። ¹⁷ ሁሉን አክብሩ፥ ወንድሞችን ውደዱ፥ እግዚአብሔርን ፍሩ፥ ንጉሥን አክብሩ። ሐዋርያት 24 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ነገር ግን ይህን እመሰክርልሃለሁ፤ በሕጉ ያለውን በነቢያትም የተጻፉትን ሁሉ አምኜ የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ፤ ¹⁵ እነዚህም ራሳቸው ደግሞ የሚጠብቁት፥ ጻድቃንም ዓመፀኞችም ከሙታን ይነሡ ዘንድ እንዳላቸው ተስፋ በእግዚአብሔር ዘንድ አለኝ። ¹⁶ ስለዚህ እኔ ደግሞ በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ሁልጊዜ ነውር የሌለባት ሕሊና ትኖረኝ ዘንድ እተጋለሁ። ¹⁷ ከብዙ ዓመትም በኋላ ለሕዝቤ ምጽዋትና መሥዋዕት አደርግ ዘንድ መጣሁ፤ ¹⁸ ይህንም ሳደርግ ሳለሁ ሕዝብ ሳይሰበሰብ ሁከትም ሳይሆን በመቅደስ ስነጻ አገኙኝ። ¹⁹ ነገር ግን በእኔ ላይ ነገር ያላቸው እንደ ሆነ፥ በፊትህ መጥተው ይከሱኝ ዘንድ የሚገባቸው ከእስያ የመጡ አንዳንድ አይሁድ አሉ። ²⁰-²¹ ወይም በመካከላቸው ቆሜ፦ ዛሬ ስለ ሙታን መነሣት በፊታችሁ በእኔ ይፈርዱብኛል ብዬ ከጮኽሁት ከዚህ ከአንድ ነገር በቀር፥ በሸንጎ ፊት ቆሜ ሳለሁ በእኔ አንድ ዓመፃ ያገኙ እንደ ሆን እነዚህ ራሳቸው ይናገሩ። ²² ፊልክስ ግን የመንገዱን ነገር አጥብቆ አውቆአልና፦ የሻለቃው ሉስዮስ በወረደ ጊዜ ነገራችሁን እቆርጣለሁ ብሎ ወደ ፊት አዘገያቸው።#ሚያዝያ_12_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበበው_የሚዜመው_የቅዳሴ_ምስባክ👇
አድኅነኒ እምእለ ሮዱኒ እስመ ይኄይሉኒ። ወአውፅአ እሞቅሕ ለነፍስየ። ከመ እግነይ ለስምከ እግዚኦ። {}
መዝ.141÷7-8
#ትርጉም፦
አቤቱ፥ ስምህን አመሰግን ዘንድ ነፍሴን ከወህኒ አውጣት፤ ዋጋዬን እስክትሰጠኝ ድረስ ጻድቃን እኔን ይጠብቃሉ።{}
መዝ.141÷7-8
#ወንጌል📖👇
ማቴዎስ 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ጌታችን ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፦ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። ¹⁴ እነርሱም፦ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት። ¹⁵ እርሱም፦ እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ¹⁶ ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ። ¹⁷ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ። ¹⁸ እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም። ¹⁹ የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል።✝️ ቅዳሴ #ሠለስቱ_ምዕት ቅዳሴ ነው።
ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀዪቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል። እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ። ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውና ያጻፈውም ከግዕዝ ወደ አማርኛ የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን።
አምላካችን ሆይ፣ በዚህ ቀን የምንነበውን ቃልህ በልባችን እንድናስቀምጥ እና በሕይወታችን እንድንተገብር እርዳን። አሜን አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ...።═══════════════════════════════════════════════════ 📱 ቦት: @gitsawebot 📺 ቻናል: https://t.me/religious_books_lover 🌐 ድህረ ገጽ: https://gitsawe-tailwind-2019.vercel.app/ 🕊️ ሰላም ይሁንላችሁ!
ሚያዝያ ዐሥራ ሁለት በዚህች ቀን ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ ሳሙኤል ዘቆየጻ ልደታቸው ነው፡፡ ሀገራቸው ትግራይ ቆየጻ ከተባለው ቦታ ነው፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ካመነኮሷቸው ከሰባቱ ከዋክብት ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ ይህ ጻድቅ በተለየ ሁኔታ በሊቅነታቸው ይታወቃሉ፡፡ ከ5 ሺህ በላይ ተከታይ መነኮሳት ነበሯቸው፡፡ 120 የሐረግ ሥዕላት ያሉት ትርጓሜ ወንጌል በ4 ዓምድ አድርገው በብራና ላይ ጽፈው እንደ አይሁድ 70ው ሊቃውንት እሳቸውም 70 እውቅ የሀገራችንን ሊቃውንት ሰብስበው እጅግ ትልቁን ትርጓሜ ወንጌል በጉባኤ አስወስነዋል፡፡ በጉባኤውም ካስወሰኑ በኋላ ወስደው ከሙታን መቃብር ላይ ቢጥሉት 211 ሙታን ተነሥተው ነአምን በአምላከ ጻድቃን ወሰማዕታት በጸሎተ ሳሙኤል ተንሣዕነ ብለው መስክረዋል። ወንጌላቸውንም በሊቃውንት ሲያጽፉ ቀለሙን ቅዱሳን መላእክት ያመጡላቸው ነበር፡፡ ጻድቁ ባረፉ ጊዜ 5 ነብሮች መጥተው መቃብራቸውን ቆፍረው ቀብረዋቸዋል፡፡ ትልቁ ገዳማቸው በትግራይ ክፍለ ሀገር እንዳ ሥላሴ ቆሪሮ ወረዳ ውስጥ ይገኛል፡፡ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን።📌 የካቲት_10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አቡነ ሳሙኤል ዘቆየጻ (ኢትዮዽያዊ) 2.ቅዱስ ኤርምያስ ነቢይ 3.ቅዱስ አቤሜሌክ ኢትዮዽያዊ 4.ቅዱስ ባሮክ 5.ቅዱስ እለእስክንድሮስ ዘኢየሩሳሌም📌 ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላዕክት 2.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ 3.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ 4.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት) 5.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ 6.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ 7.ቅዱስ ድሜጥሮስ📖 ማቴ 3፥37-39
✍️ ኢየሩሳሌም ሆይ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርሷ የተላኩትንም የምትወግር ዶሮ ጫጩቶቿን ከክንፎቿ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም፤ እነሆ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላቹሃል፤ እላችሁአለሁና በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ እንግዲህ ወዲህ አታዩኝም
አንድ_አምላክ_በሆነ_በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ_ስም ሚያዝያ ዐሥራ ሁለት በዚህችም ዕለት የመላእክት አለቃ ቅዱስ_ሚካኤልን እግዚአብሔር ወደ ነብዩ_ኤርምያስ ላከው፣ የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ አባ_እለእስክንድሮስ አረፈ፣ ዳግመኛ በዚህች ቀን ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ_ሳሙኤል_ዘቆየጻ ልደታቸው ነው፡፡ በተጨማሪም ጠመው የምትባለው አገር ኤጲስቆጶስ የሆነው የ አባ_እንጦንስና የ አውሳንዮስ መታሰቢያቸው እንዲሁም መጥምቁ_ዮሐንስ የተገለጠላቸው ጋይዮስና ኤስድሮስ ዕረፍታቸው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳቸዋል፡፡ አርኬ ✍️ሰላም ለጋይዮስ ወለኤስድሮስ ዓበሞ። ትእዛዘ ወንጌል ለፈጽሞ። ለረድኤተ ብእሲ ድውይ በጽሒቅ ወአስተሐምመ። አሐዱ ተሠይመ በፈቃዱ በዘይፌውስ ሕማሞ።ወካልኡ ተኀድገ ይትለአክ ድካሞ።✝️ ቅዱስ_ኤርምያስ_ነቢይ
ሚያዝያ ዐሥራ ሁለት በዚህችም ዕለት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን እግዚአብሔር ወደ ነብዩ ኤርምያስ ላከው፡፡ ጠባቡና ረግረግ ከሆነ እሥር ቤት ሴዴቅያስ ንጉሥ በአሠረው ጊዜ የንጉሡ ባለሟልና የጭፍራ አለቃ የሆነው አቤሜሌክ አወጣው። ያንጊዜም የኢየሩሳሌምን ጥፋት እንዲያይ መራራ ምርኮንም እንዳይቀምስ ኤርምያስ ነብይ መረቀው እንዲሁም ሆነ። ስሳ ስድስት ዓመትም ተኝቶ ኖረ ከእርሱ ጋራ ወይንና በለስ ነበረ አልተለወጠም የእስራኤል ልጆች ከምርኮ እስቲመለሱ በለሱንም ከደብዳቤ ጋራ ወደ ኤርምያስ ባቢሎን አገር ላከው። ስለዚህም የዚህን የከበረ መልአክ ሚካኤልን በየወሩ በዐሥራ ሁለት ቀን መታሰቢያውን እንድናደርግ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙን። አርኬ ✍️ሰላም ለከ ዘተፈሰይከ በክብር። መልአከ ኪዳኑ ወምክሩ ለእግዚአብሔር። ሚካኤል ረዳኢ ለእለ ውስተ የብስ ወባሕር። ለረድኤትከ ዘየዓዕቦ ነገር አልቦ በሰማይ ወአልቦ በምድር።✝️ ቅዱስ_እለእስክንድሮስ_ዘኢየሩሳሌም
በዚህች ቀን የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ አባ እለእስክንድሮስ አረፈ። ይህ ቅዱስም አስቀድሞ በቀጰዶቅያ አገር ኤጲስቆጶስነት ተሹሞ ነበር። እርሱም የከበሩ ቦታዎችን ተሳልሞ በረከት ተቀብሎ ወደ አገሩ ሊመለስ አስቦ ኢየሩሳሌም መጣ። በኢየሩሳሌምም ስሙ በርኪሶስ የሚባል መቶ ዐሥር ዓመት የሆነው ጻድቅ ሰው ነበረ ሹመቱንም ሊተው ይወድ ነበረ ወገኖቹ ግን አልለቀቁትም። ቅዱስ እለእስክንድሮስም ሥራውን ፈጽሞ ወደ አገሩ ቀጰዶቅያ ሊመለስ በፈለገ ጊዜ እግዚአብሔር እንዲህ የሚል ቃል እነሆ ከሰማይ አሰማ። ወደ እገሌ በርውጡ አስቀድሞ የሚገባውንም ይዛችሁ በላያችሁ ኤጲስቆጶስነት ሹሙት። ያን ጊዜም ሲወጡ አባ እለእስክንድሮስን አገኙትና ያዙት። እርሱም እኔ የቀጰዶቅያ ኤጲስቆጶስ ነኝ የክብር ባለቤት ክርስቶስ በእነርሱ ላይ የሾመኝን መንጋዎቼን ልተው አይቻለኝም አላቸው። እነርሱም ከሰማይ ስለሰሙት ስለዚያ ቃል ስለርሱም እንደአመለከታቸው ነገሩት። ይህ ነገር ከእግዚአብሔር እንደሆነ በተረዳ ጊዜ ለበዓሉም የተሰበሰቡ አባቶች መከሩት ቃላቸውንም ተቀበለ ወደ ሀገሩ ቀጰዶቅያም እንዲህ ብሎ መልእክት ጽፎ ላካት። ይቅርታ አድርጉልኝ በእኔ ላይ አትዘኑ በእናንተ ላይም ኤጲስቆጶስ በእኔ ፈንታ ሹሙ እናንተም የተፈታችሁ ናችሁ ያቺን መልእክትም ከእርሱ ጋራ አብረው ከመጡ ከቀጰዶቅያ ሰዎች ጋራ ላከ። ከዚህም በኃላ እየተራዳው አምስት ዓመት ያህል ከአባ በርኪሶስ ጋራ ኖረ። ከዚህም በኃላ ሽማግሌው አባ በርኪሶስ አረፈ። አባ እለእስክንድሮስም መንጋውን ተረክቦ እንደ ሐዋርያት በመልካም አጠባበቅ ጠበቃቸው። ከሀዲ መክስምያኖስም በነገሠ ጊዜ ይህን አባት ይዞ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ አሠቃየው። ከዚያም በላዩ የሚያደርግበትን እስከሚያስብ ድረስ አሠረው፡፡ ጌታችንም ይህን ከሀዲ ፈጥኖ አጠፋው፣ ወገኖቹም ይህን አባት እለእስክንድሮስን ከእሥር ቤት አወጡት። ገርድያኖስም በነገሠ ጊዜ ጸጥታና ሰላም ሆነ ከክርስቲያን ወገኖች ላይም ጥቂት ወራት መከራው ጸጥ አለ። ገርድያኖስም በሞተ ጊዜ በርሱ ፈንታ አማኒ የሆነ ፊልጶስ ነገሠ። እርሱም በክብር ባለቤት በጌታችን ስለሚአምን በክብር ባለቤት በጌታ ክርስቶስ ሰም የታሠሩትን ምእመናንን ፈታቸው እጅግም አከበራቸው ይህም አባት በጸጥታ ኖረ። ከዚህም በኃላ ከሀዲ ዳኬዎስ ተነሣ ፊልጶስንም ገድሎ መንግሥቱን ወሰደ ክርስቲያኖችንም እጅግ አሠቃያቸው ይህንንም አባት ያዘው ብዙዎችንም የቤተ ክርስተያን ሊቃውንት ጽኑ ሥቃይም አሠቃያቸው። ይልቁንም ይህን አባት አብዝቶ አሠቃየው ጽኑ ግርፋትንም ገርፎ ስለት በአላቸው በትሮች የጐኑ ዐጥንቶች ተሰብረው ወደሆዱ እስቲገቡ አስመታው። ከዚህም በኃላ እስከ እሥር ቤት ጐትተው በዚያ እንዲጥሉት አዘዘ እንዲሁም አደረጉበት። እግዚአብሔር ለመረጣቸው ያዘጋጀውን መንግሥተ ሰማይ እስከ ወረሰ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ እስከ ሰጠ ድረስ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እየታመነ በዚያ ወድቆ ኖረ በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። አርኬ ✍️ሰላም ዕብል ለዘበእንተ ጽድቅ ዘተዘብጠ። ዐፅመ ገቦሁ ዘውስጥ እስከ ተቀጥቀጠ። እለእስከንድሮስ ዘኮነ በኢየሩሳሌም ሥሉጡ። ይምጻእ ይእዜ ንርአዪ ኅዳጠ። ዘምስለ እንጦንስ ወሉቃስ ወአኮ ፍሉጠ።✝️ አቡነ_ሳሙኤል_ዘቆየጻ 📖 ቀጣይ ክፍል ይከተላል...
ሚያዝያ 12፣ 2018 ዓ.ም.
🗓️ ግሪጎሪያን: 20/04/2026
═══════════════════════════════════════════════════
💭 የዕለቱ ጥቅስ:
"እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፥ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።" 📖 1ኛ ዮሐንስ 4:16📖 ግጽዌ - የዕለቱ ንባብ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈ 📌 ▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ሐዋርያት ▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ምስባክ ▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ትርጉም ▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ወንጌል ▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ቅዳሴ
ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው።
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል።መልክአ ሥላሴ፦ ሰላም ለእንግድዓክሙ ትዕይንተ ንጉሥ ምክር፤ሥሉስ ቅዱስ መልህቃተ ሰማይ ሐመር፤ሶበ ይዴግነኒ ባዕስ መልአከ ቅንዓቱ ለፀር፤ምስለ ኃይል ይባልሐኒ ባሕረ ምሕረትክሙ ፍቅር፤ከመ ለእስራኤል ቀደምት ባልሖሙ ባሕር። ዚቅ፦ ሃሌ ሉያ ለአብ፤ሃሌ ሉያ ለወልድ፤ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ፤ይትባረክ እግዚአብሔር፤ይትነከር ውእቱ ይትነከር፤ፈረሰ ወዘይጼዓን ላዕሌሁ፤ወረወ ውስተ ባሕር። ነግስ በላይ ቤት:-
ሰላም ለቆምከ ሥርግወ ዋካ ወሞገስ፤ኀበ መቃብሩ ዘቆመ ለበኵረ ትንሣኤ ክርስቶስ፤ሚካኤል ሣዋዒ በግዓ ቅዳሴ ሠላስ፤ኢይኀልቅ ወርኃ ምግብየ ከመ ሕዝቅያስ ንጉሥ፤ፀሐየ ሕይወትየ በዘመን ሐዲስ።ዚቅ፦
ክብሮሙ ለመላእክት ከመ መንኰራኵር፤ወረደ መልአከ እግዚአብሔር በጽባሕ ኀበ መቃብር፤ወአንኰርኰራ ለይእቲ ዕብን ወነበረ ዲቤሃ፤ወርእየቱ ከመ መብረቅ፤ወአልባሲሁኒ ፀዓዳ ከመ በረድ፤ወበእኁድ ሰንበት ጌሠት ማርያም መግደላዊት፤በጽባሕ ኀበ መቃብር ተንሥአ ክርስቶስ እሙታን በሣልስት ዕለት፤ወይቤሎን ለአንስት፤ሑራ ንግራ ለአርዳዕየ፤ገሊላ እቀድሞሙ ተንሢዕየ እምነ ሙታን።በታች ቤት:- መልክአ ሚካኤል፦ ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ስመ ልዑል ዘተሳተፈ፤ ወልደ ያሬድ ሄኖክ በከመ ጸሐፈ፤ ሶበ እጼውዕ ስመከ ከሢትየ አፈ፤ ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ፤ ለረዲኦትየ ነዓ ሰፊሐከ ክንፈ። ዚቅ፦ ስማዕ ጸሎተነ ወስእለተነ፤ወሥረይ ኵሎ ኃጢአተነ፤ስማዕ ጸሎተነ ወስእለተነ። መልክአ ሚካኤል፦ ሰላም ለአዕናፊከ መዓዛ አርያም እለ ተመልዑ፤ሱራፌል ምስሌከ አመ ይሠውዑ፤ሚካኤል አንተ ለያዕቆብ ኖላዌ ዘርዑ፤በሎሙ ለአብያጺከ ለሐውፆ አርክየ ንዑ፤እስመ በ፩ዱ ፍቁር ይሰሐብ ካልዑ። ዚቅ በታች ቤት:- አጽነነ ሰማያተ ወወረደ፤አድለቅለቃ ለምድር ወሆካ ለቀላይ፤ወኀብሩ ፬ቱ አናቅጸ ስብሐቲከ፤ወደቂቀ ያዕቆብ ኅሩያኒከ፤እለ ዓቀቡ ሕገከ ወሥርዓተከ ለልዑል፤ኢየሐሙ ዘኢይመውቱ ይወርሱ ዓለመ፤ተስፋሆሙ ለጻድቃን። ዚቅ በላይ ቤት:- ኖላዊ ኄር ኖላዊሆሙ ለ፳ኤል፤ነዓ ርድዓነ፤አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ። በላይ ቤት:- መልክአ ሚካኤል፦
ሰላም ለጒርዔከ ንቃመ ቅዳሴ ዘረዓመ፤እስከ ይመልዕ አርያመ፤ሚካኤል ዘኮንከ ለደቂቀ ጼዋ ቃውመ፤ጊዜ ሰአልኩከ ሀበኒ ሰላመ፤ወኢትብለኒ ግባኦ ለአኀብከ ጌሠመ።ዚቅ፦ በእደ መልአኩ ይዕቀበነ፤ሰላመ ዚአሁ የሀበነ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤በእደ መልአኩ ይዕቀበነ፤ሰላመ ዚአሁ የሀበነ መልክአ ሚካኤል፦ ሰላም ለልብከ መዝገበ ርኅራኄ ወየዋሃት፤ኅሩመ በቀል ወቅንዓት፤ሚካኤል ሥዩም በዲበ ኃይላት፤ለደቂቀ ያዕቆብ ዘአሕለፍኮሙ በማዕከለ ባሕር ግርምት፤አኅልፈኒ ሊተ እምኅቡዕ መሥገርት። ዚቅ በታች ቤት:- ውእቱ መልአከ እግዚአብሔር መርሖሙ፤ወአሕለፎሙ ማዕከለ ቀላይ፤ወኢደክመ ሴስዮቶሙ፤፵ ዓመተ በገዳም። ዚቅ በላይ ቤት:- እምድረ ግብፅ አውጽኦሙ ወበመዝራዕቱ ረድዖሙ፤ወይቤሎሙ ግበሩ በዓለ በትፍሥሕት፤ዛቲ ፋሲካ ቀዳሚት ሕግ ወሥርዓት፤ዛቲ ፋሲካ ተዝካረ ትንሣኤው ለመድኃኒነ፤ዛቲ ፋሲካ ለኵልነ በዓል። ምልጣን ፦ አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ ሚካኤል ሰአለ ሥርየተ ወገብርኤል አዕረገ ጸሎተ ወሪዶ እመስቀሉ አብርሃ ለኲሉ። እስመ ለዓለም
ዘ፯ቱ ኃይለ ሰማያት ኀደረ ውስተ ልበ ምድር፤ወሀለዋ አንስትኒ እለ ተልዕካሁ ለክርስቶስ፤ወሖራ ኀበ ንጉሠ ስብሐት ወይቤላ፤ተንሥአ እግዚእነ እሙታን፤ወይቤሎሙ እግዚኦሙ ለመላእክት ኀበ ተሰቀልኩ ዕፅ ክቡረ ይኵን፤ተንሥአ በሉኒ፤ተንሥእ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ።
"እምሥራቀ ፀሐይ እስከነ ዓረብ። ይትአኰት ስሙ #እግዚአብሔር። ልዑል #እግዚአብሔር መልዕልተ ኵሉ አሕዛብ"።መዝ 112፥3-4። #ትርጉም፦
"ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም ድረስ የ #እግዚአብሔር ስም ቡሩክ ይሁን። ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያው ድረስ የ #እግዚአብሔር ስም ይመስገን"።መዝ 112፥3-4። #ወንጌል 📖 ዮሐንስ 17 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹-² ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ፦ አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው። ³ እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። ⁴ እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤ ⁵ አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ። ⁶ ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ ለእኔም ሰጠሃቸው፤ ቃልህንም ጠብቀዋል። ⁷ የሰጠኸኝ ሁሉ ከአንተ እንደ ሆነ አሁን ያውቃሉ፤ ⁸ የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ከአንተም ዘንድ እንደ ወጣሁ በእውነት አወቁ፥ አንተም እንደ ላክኸኝ አመኑ። ⁹ እኔ ስለ እነዚህ እለምናለሁ፤ ስለ ዓለም አልለምንም ስለ ሰጠኸኝ እንጂ፤ የአንተ ናቸውና፤ ¹⁰ የእኔም የሆነ ሁሉ የአንተ ነው የአንተውም የእኔ ነው፤ እኔም ስለ እነርሱ ከብሬአለሁ። ¹¹ ከዚህም በኋላ በዓለም አይደለሁም፥ እነርሱም በዓለም ናቸው፥ እኔም ወደ አንተ እመጣለሁ። ቅዱስ አባት ሆይ፥ እነዚህን የሰጠኸኝን እንደ እኛ አንድ እንዲሆኑ በስምህ ጠብቃቸው። ¹² ከእነርሱ ጋር በዓለም ሳለሁ የሰጠኸኝን በስምህ እኔ እጠብቃቸው ነበር፤ ጠበቅኋቸውም መጽሐፉም እንዲፈጸም ከጥፋት ልጅ በቀር ከእነርሱ ማንም አልጠፋም። ¹³ አሁንም ወደ አንተ እመጣለሁ፤ በእነርሱም ዘንድ ደስታዬ የተፈጸመ እንዲሆንላቸው ይህን በዓለም እናገራለሁ። ¹⁴ እኔ ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ፤ እኔም ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉምና ዓለም ጠላቸው። ¹⁵ ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ከዓለም እንድታወጣቸው አልለምንም። ¹⁶ እኔ ከዓለም እንዳይደለሁ ከዓለም አይደሉም። ¹⁷ በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው። ¹⁸ ወደ ዓለም እንደ ላክኸኝ እንዲሁ እኔ ወደ ዓለም ላክኋቸው፤ ¹⁹ እነርሱም ደግሞ በእውነት የተቀደሱ እንዲሆኑ እኔ ራሴን ስለ እነርሱ እቀድሳለሁ። ²⁰-²¹ ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልለምንም፤ አንተ እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፥ አንተ፥ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። ²²-²³ እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል። ²⁴ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር ስለ ወደድኸኝ የሰጠኸኝን ክብሬን እንዲያዩ እኔ ባለሁበት የሰጠኸኝ እነርሱ ደግሞ ከእኔ ጋር ይሆኑ ዘንድ እወዳለሁ። ²⁵ ጻድቅ አባት ሆይ፥ ዓለም አላወቀህም፥ እኔ ግን አወቅሁህ እነዚህም አንተ እንደ ላክኸኝ አወቁ፤ ²⁶ እኔንም የወደድህባት ፍቅር በእነርሱ እንድትሆን እኔም በእነርሱ፥ ስምህን አስታወቅኋቸው አስታውቃቸውማለሁ።
Reviews channel
3 total reviews
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️ is a Telegram channel in the category «Религия и духовность», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 5.2K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 27.3, with 3 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.2 ₽, and with 6 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий