
- Main
- Catalog
- Religion & Spirituality
- Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️»
Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️»
በዚህ channel ውስጥ መንፈሳዊ መጻሕፍትንና የየዕለቱን ስንክሳር ያገኛሉ።
Channel statistics
❖ ቅዱስ ጳውሎስም በጌታችን አምኖ ወደ ሐዋርያት በመጣ ጊዜ ክብር ይግባውና ለክርስቶስ እርሱ ደቀ መዝሙሩ እንደሆነ ሐዋርያት አላመኑትም ነበር፤ ይህ በርናባስ ጌታችን በመንገድ እንደ ተገለጸለትና እንደአነጋገረው እርሱም በጌታ ኢየሱስ ስም በደማስቆ እንደ አስተማረ ነገራቸው፤ ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔርን ሥራ ሲሠሩ ሲጾሙ ሲጸልዩ መንፈስ ቅዱስ ሳውልንና በርናባስን እኔ እነርሱን ለመረጥኩለት ሥራ ለዩልኝ አላቸው። ❖ ከዚህም በኋላ ጹመው ጸልየው እጆቻቸውን በራሳቸው ላይ ጭነው ሾሟቸው። ከመንፈስ ቅዱስም ተሹመው ወደ ሴሌውቅያ ወረዱ ከዚያም ወደ ቆጵሮስ ሔዱ የእግዚአብሔርንም ቃል በሀገሩ ሁሉ አስተማሩ፤ ልስጥራን በተባለ አገርም ልምሾ የነበረውን ሰው በአዳኑት ጊዜ የልስጥራን ሰዎች መሥዋዕትን ሊሠዉላቸው ወደዱ። ❖ ሐዋርያት ጳውሎስና በርናባስም በሰሙ ጊዜ ልብሳቸውን ቀደው ወደ ሕዝቡ ሔዱ ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው እንዲህ አሏቸው እናንት ሰዎች ይህ ነገር ምንድን ነው እኛማ እንደናንተ የምንሞት ሰዎች አይደለንምን ይህን ከንቱ ነገር ትታችሁ ሰማይና ምድርን ባሕርንም በውስጣቸው ያለውን ሁሉ ወደ ፈጠረ ወደ ሕያው እግዚአብሔር ትመለሱ ዘንድ እናስተምራችኋለን አሏቸው እንዲህም ብለው መሠዋትን በጭንቅ አስተዋቸው። ❖ ከዚያም ብዙ ሀገሮችን ከአስተማሩ በኋላ ቅዱስ በርናባስ ከቅዱስ ጳውሎስ ተለይቶ ማርቆስን ይዞ ወደ ቆጵሮስ ሔደ በዚያም አስተማረ ብዙዎችን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን መለሳቸውና የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። ❖ በቆጵሮስ አገር የሚኖሩ አይሁድም ቀኑበት በመኳንንትም ዘንድ ወነጀሉት በእግር ብረትም አሥራው ጽኑ ግርፋትን ገረፉት ከዚህም በኋላ በደንጊያ ወገሩት ዳግመኛም ወስደው ከእሳት ጨመሩት ምስክርነቱንም ፈጸመ ማርቆስም ከርሱ ጋር አለ ግን እግዚአብሔር ጠብቆ አተረፈው። እርሱም ቅዱስ በርናባስን ከእሳት ውስጥ አወጣው ሥጋውንም እሳት ከቶ አልነካውም በአማሩ ልብሶችም ገነዘውና ተሸክሞ ወስዶ ከቆጵሮስ ከተማ ውጭ በዋሻ ውስጥ አኖረው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። አርኬ ✍️ሰላም ለበርናባስ በማእሠረ ጌጋይ ዘኢተእኀዘ። ከመ መንፈስ ቅዱስ አዘዘ። ሥርዓተ ፈጺሞ ወመልእክተ ቃሉ አዚዘ። በዋዕየ እሳት ሶበ እምዓለም ግዕዘ። ለወንጌላዊ ማርቆስ በእዱ ተገንዘ።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ ✝️ አባ ይስሐቅ ጻድቅ ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
❖ ይህ ቅዱስ በመካከለኛው ዘመን በምድረ ግብጽ የነበረ ገዳማዊ ነው፤ መንኖ ለብዙ ዘመናት በገዳም ሲኖር ምኞቱ አንዲት ብቻ ነበረች፤ እመቤታችንን በአካል መመልከትን ይፈልግ ነበር:: ❖ የገዳሙ ጠባቂ በመሆኑ መነኮሳት ሲተኙ መቅደሱን ከፍቶ በድንግል ማርያም ስዕል ፊት ይጸልይ: ይሰግድ ያነባ ነበር፤ እንዲህ ለ7 ዓመታት ስለ ተጋ ድንግል እመ ብርሃን ልመናውን ሰማች:: ❖ በዚህ ዕለትም ከፀሐይ 7 እጅ ደምቃ ወደ እርሱ መጣች፤ ደንግጦ ሲወድቅ አነሳችው፤ ከ3 ቀናት በሁዋላ እመለሳለሁ ብላም ተሠወረችው፤ በ23ም ዐረፈ:: በረከቱ ረድኤቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን። አርኬ ✍በዛቲ ዕለት ሶበ ጸለየ ጥቡዐ። ለይስሐቅ አስተርዓየቶ እም አይቆናሃ ወጺአ። እምጸዳለ መብረቅ ጥቀ እንዘ ትጸድል ስብአ።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ታኅሣሥ 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
1.ኖላዊ ሔር 2.ቅዱስ በርናባስ ሐዋርያ 3.አባ ይስሐቅ ጻድቅ▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ወርኀዊ በዓላት ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
1.ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም 2.አበው ጎርጎርዮሳት 3.አቡነ ምዕመነ ድንግል 4.አቡነ አምደ ሥላሴ 5.አባ አሮን ሶርያዊ 6.አባ መርትያኖስ ጻድቅ▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📖ዮሐ 10፥14-16 ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
✍️ መልካም እረኛ እኔ ነኝ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጐች አውቃለሁ፤ የራሴም በጐች ያውቁኛ ፤ ነፍሴንም ስለ በጐች አኖራለሁ፤ ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጐች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምጼንም ይሰማሉ፤ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ
ወትቀውም ንግሥት በየማንከ። በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኊብርት። ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ ዕዝነኪ።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ትርጉም ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች። ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ መዝ 44፥9-10።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ወንጌል ሉቃስ 1 ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
¹⁷ እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል። ¹⁸ ዘካርያስም መልአኩን፦ እኔ ሽማግሌ ነኝ ምስቴም በዕድሜዋ አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ? አለው። ¹⁹ መልአኩም መልሶ፦ እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፤ ²⁰ እነሆም፥ በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ፥ ይህ ነገር እስከሚሆን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ መናገርም አትችልም አለው። ²¹ ሕዝቡም ዘካርያስን ይጠብቁት ነበር፤ በቤተ መቅደስም ውስጥ ስለ ዘገየ ይደነቁ ነበር። ²² በወጣም ጊዜ ሊነግራቸው አልቻለም፥ በቤተ መቅደስም ራእይ እንዳየ አስተዋሉ፤ እርሱም ይጠቅሳቸው ነበር፤ ድዳም ሆኖ ኖረ። ²³ የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሄደ። ²⁴-²⁵ ከዚህም ወራት በኋላ ሚስቱ ኤልሳቤጥ ፀነሰችና፦ ነቀፌታዬን ከሰው መካከል ያስወግድልኝ ዘንድ ጌታ በተመለከተበት ወራት እንዲህ አድርጎልኛል ስትል ራስዋን አምስት ወር ሰወረች። ²⁶ በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥ ²⁷ ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ። ²⁸ መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት። ²⁹ እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና፦ ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው? ብላ አሰበች። ³⁰ መልአኩም እንዲህ አላት፦ ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ። ³¹ እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ። ³² እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤ ³³ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም። ³⁴ ማርያምም መልአኩን፦ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል? አለችው።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ቅዳሴ ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
ማርያም ቅዳሴ ነው።
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን አምላክን የወለደች የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓልዋ መታሰቢያ ነው። እርሷ የባህርያችን መመኪያ ናትና በእርሷ በእናቱ አማላጅነት ጌታችን ይጠብቀንና ያድነን ዘንድ መታሰቢያዋን እያደረግን ወደርሷ እንለምን ዘንድ ይገባናል፤ እርሷን ሕይወትን መድኃኒትን አድርጎ ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። አርኬ ✍️ሰላም ለማርያም ዘረከበት ዘርዐ። እንበለ ትሰቀይ ጠለ ወእንበለ ትስተይ ነቅዐ። በዛቲ ዕለት ሶበ ጸለየ ጥቡዐ። ለይስሐቅ አስተርአየቶ እምአይቆናሃ ወጺኣ። እምጸዳለ መብረቅ ጥቀ እንዘ ትጸድል ስብዐ።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ ✝️ ኖላዊ ሔር ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
❖ በዚችም ቀን በበግ እረኛ አምሳል መድኃኒታችን የተገለጸበት ነው፤ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በበግ እረኛ ተመስሎ የተገለጠበት ዕለት ነው፤ እግዚአብሔር አዳምን በ7 ሃብታት አክብሮ በገነት ቢያኖረው አትብላ የተባለውን ዕፀ በለስ በላ፤ በዚህም ከፈጣሪው ተጣልቶ በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ በርደተ መቃብር ርደተ ገሃነም ተፈረደበት፤ በሁዋላ ግን ንስሃ ስለ ገባ ከ5 ቀን ተኩል (5,500 ዘመን) በሁዋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ የሚል ቃል ኪዳንን ሰጠው:: ❖ ከዚህ በሁዋላ ለ5,500 ዘመናት ጊዜ ወደ ታች ይቆጠር ጀመር፤ ስለ እግዚአብሔር ሰው መሆንና ዓለምን ማዳንም ትንቢት ይነገር ሱባኤ ይቆጠር ምሳሌም ይመሰል ገባ፤ ከአዳም እስከ ሙሴ (ዘመነ አበው) ምሳሌያት ይበዛሉ:: ❖ ከሙሴ እስከ ዳዊት (ዘመነ መሣፍንት) ምሳሌያቱ እየጐሉ መጥተዋል፤ ከልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እስከ ቅዱስ ሚልክያስ ድረስ (በዘመነ ነቢያት / ነገሥት) ግን ትንቢቶች ስለ ክርስቶስና ስለ ማደሪያ እናቱ እንደ ጐርፍ ፈሰዋል:: ❖ ነቢያትም የመሲህን መምጣት እየጠበቁ በጾም በጸሎትና በትሕርምት ኑረዋል፤ እንባቸውንም አፍሰው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶላቸዋል፤ ቅድስት ቤተክርስቲያን ይህችን ዕለት ኖላዊ ሔር ብላ ታከብራለች፤ ይሕንንም ለሳምንት ያህል ታዘክራለች፤ መሠረታዊ መነሻዋም ነው። 📖ዮሐ 10፥1 <b>❓ኖላዊ ማለት</b> ❖ በቁሙ እረኛ ማለት ሲሆን ሔር ደግሞ ቸር-ርሕሩሕ-አዛኝ እንደ ማለት ነው፤ ገጥመን ብንተረጉመው ደግሞ ቸር እረኛ የሚል ትርጉምን ይሰጠናል፤ ከአባታችን አዳም ስህተት በሁዋላ ተፈጥረው ከነበሩ ችግሮች አንዱ ቸር እረኛ ማጣት ነው፤ እግዚአብሔር አዳምን ፈጥሮ ቸር እረኛ ሆኖ በገነት አሰማርቶት ነበር:: ❖ ኤዶም ገነት የለመለመች ፈሳሾች የሞሉባት መልካም መስክ ናትና፤ አባታችን ቅዱስ አዳም ደግሞ እንደ አቅሙ የጸጋ እረኝነት ተሰጥቶት ነበር፤ ድቀት ካገኘው በሁዋላ ግን ከነፍስ እረኛው ጋር ተጣልቶ ከመልካሟ መስክ ገነት ወጣ፤ እርሷንና የነፍሱን እረኛ ሲሻም አለቀሰ ተስፋ ድኅነት ሲሰጠውም ለልጆቹ ነገራቸው:: ❖ ከዚያም በመንጋው ላይ በአዳም ሴት ተተካ ከሴት ኄኖስ ከኄኖስ ቃይናን . . . እያለ ከኖኅ ደረሰ፤ ከኖኅም በሴም ከአብርሃም ከአብርሃምም በይስሐቅና በያዕቆብ ወርዶ ከሙሴ ደረሰ፤ ከሙሴም በኢያሱ አልፎ ከነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ደረሰ፤ እነዚህ ሁሉ እረኞች ምንም እንኩዋ ለእግዚአብሔር ሕዝብ በትጋት ቢሠሩም ሕዝቡን ከሲዖል ማዳን አልቻሉም፤ ከሲዖል የሚያድን የነፍስ እረኛ ነውና ያን ጊዜ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት የራሱን የአባቶቹንና የልጆቹን ጩኸት ባንድ አድርጐ ጮኸላቸው:: ✍ኖላዊሆሙ ለእሥራኤል አጽምዕ 👉የእሥራኤል እረኛ ሆይ ስማን አለ:: 📖መዝ 79፥1 ❖ ጩኸቱም ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰ፤ ይህንን የሰማ ጌታም በጊዜው ከድንግል ማርያም ተወለደ፤ በየጥቂቱ አድጐ ቸር እረኝነቱን ገለጠ፤ መድኃኒታችን እንዳስተማረን እርሱ ቸር እረኛ ነው፤ ከእርሱ በፊት የተነሱት ቴዎዳስ ዘግብጽና ይሁዳ ዘገሊላ 📖ሐዋ 5፥36 📖ዮሐ 10፥8 ❖ ሐሰተኛ እረኞች ነበሩ እርሱ ግን እውነተኛው የበጐች በር ነውና፤በእርሱ የሚገቡ ሁሉ የዘለዓለም ሕይወትን ያገኛሉ:: 📖ዮሐ 10፥7 ❖ እርሱ እውነተኛ እረኛ ነውና፤ ለመንጋው ራሱን አሳልፎ ይሰጣል፤ በእሥራኤል ባሕል እረኞች ከፊት መንጋው (በጐቹ) ከሁዋላ ሆነው ይሔዳሉና ገዳይ ቢመጣ መጀመሪያ የሚገድለው እረኛውን ነው:: 📖ዮሐ 10፥11 ❖ መድኃኒታችን ክርስቶስ በሞቱ ሕይወትን በመራቆቱ የጸጋ ልብስን በውርደቱ ክብርን በድካሙ ኃይልን ይሰጠን ዘንድ ስለ እኛ ራሱን አሳልፎ ሰጠ የማይሞት ንጉሥ ስለ መንጋው ሞተ፤ ሰማይን ከነግሡ ምድርንም ከነልብሱ የፈጠረ ጌታ 📖ዮሐ 1፥2 ❖ ስለ በጐቹ ይህንን ሁሉ ታግሦ ከሲዖል አዳነን፤ በሚያርግ ጊዜም በእርሱ ፈንታ ባለ ሙሉ ስልጣን እረኞችን ሐዋርያትን 📖ዮሐ 21፥15 ❖ ሊቃነ ዻዻሳትን 📖ሐዋ 20፥28 ❖ ካህናትን ሾመልን፤ እነርሱን እረኞች አሰኝቶ እርሱ ሊቀ ኖሎት የእረኞች አለቃ ተባለ፤ እነርሱም እስከ ዓለም ፍጻም የክርስቶስን መንጋ ሊጠብቁ ስልጣኑም ኃላፊነቱም አለባቸው:: 📖ማቴ 28፥19 📖ማቴ 18፥18 የመድኃኔዓለም ቸርነቱ የድንግል እናቱ ምልጃዋ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ ሀገራችን ሰላም ፍቅር ያድርግልን። አርኬ ✍️ ሰላም ለርደትከ ዘእምቅድመ ዓለም ሀላዊ። ነበልባለ እሳት ውዑይ ለተዓጽፎ አባል ምድራዊ። ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ አብ መለኮታዊ። ይሴፈውከ መርዔትከ ለዘተዓቅብ ኖላዊ። ትቤዝዎሙ እምአርዌ ነዓዊ። ✍️ ሰላም ለኖላዊ አልቦ ዘይመስሎ። ዘመጽአ ይእዜ ወእምቅድመ ዓለም ዘሀሎ። መራዕየ ይዕቀብ እሙስና ወእምተሀጒሎ። መንገለ ወፈረ ያወፍር መትሎ። አባግዕኒ ይሰምዓ ቃሎ።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ ✝️ ሐዋርያ ቅዱስ በርናባስ ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
❖ በዚችም ቀን የስሙ ትርጓሜ የመረጋጋት ልጅ የሆነ ቅዱስ ሐዋርያ በርናባስ በሰማዕትነት አረፈ፤ ይህም ቅዱስ ሐዋርያ ከሌዊ ነገድ የሆነ ሀገሩ ቆጵሮስ ነው የቀድሞ ስሙ ዮሴፍ ነው ክብር ይግባውና ጌታችን ከመከራው በፊት ይሰብኩ ዘንድ ከላካቸው ከሰባ ሁለት አርድእት ጋር መረጠው ስሙንም በርናባስ ብሎ ጠራው። ❖ ከጌታ ዕርገትም በኋላ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ እርሱም ከሐዋርያት ጋር የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ተቀብሎ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አስተማረ። የእርሻ ቦታ ነበረውና ሽጦ ዋጋውን አምጥቶ ከሐዋርያት እግር በታች አኖረው።
ታኅሳስ 21፣ 2018 ዓ.ም.
🗓️ ግሪጎሪያን: 29/12/2025
═══════════════════════════════════════════════════
💭 የዕለቱ ጥቅስ:
"እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፥ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።" 📖 1ኛ ዮሐንስ 4:16📖 ግጽዌ - የዕለቱ ንባብ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌 ገላትያ 2 ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
¹ ከዚያ ወዲያ ከአሥራ አራት ዓመት በኋላ ከበርናባስ ጋር ቲቶን ደግሞ ይዤ ወደ ኢየሩሳሌም ሁለተኛ ወጣሁ፤ ² እንደ ተገለጠልኝም ወጣሁ፤ ምናልባትም በከንቱ እንዳልሮጥ ወይም በከንቱ ሮጬ እንዳልሆን በአሕዛብ መካከል የምሰብከውን ወንጌል አስታወቅኋቸው፤ ዋኖች ግን መስለው ለሚታዩ ለብቻቸው አስታወቅኋቸው። ³ ነገር ግን ከእኔ ጋር የነበረ ቲቶ እንኳ የግሪክ ሰው ሲሆን ይገረዝ ዘንድ ግድ አላሉትም፤ ⁴ ነገር ግን ባሪያዎች ሊያደርጉን በክርስቶስ ኢየሱስ ያለንን አርነታችንን ይሰልሉ ዘንድ ሾልከው በስውር ስለ ገቡ ስለ ሐሰተኞች ወንድሞች ነበረ። ⁵ የወንጌልም እውነት በእናንተ ዘንድ ጸንቶ እንዲኖር ለአንድ ሰዓት እንኳ ለቅቀን አልተገዛንላቸውም። ⁶ አለቆች የመሰሉት ግን፥ በፊት ማን እንደ ነበሩ አይገደኝም፤ እግዚአብሔር የሰውን ፊት አይቶ አያደላም፤ አለቆች የመሰሉት አንዳች እንኳ አልጨመሩልኝምና፥ ⁷ ተመልሰው ግን ጴጥሮስ ለተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠው እንዲሁ ለእኔ ላልተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠኝ አዩ፤ ⁸ ለተገረዙት ሐዋርያ እንዲሆን ለጴጥሮስ የሠራለት፥ ለእኔ ደግሞ ለአሕዛብ ሐዋርያ እንድሆን ሠርቶአልና። ⁹ ደግሞ የተሰጠኝን ጸጋ አውቀው፥ አዕማድ መስለው የሚታዩ ያዕቆብና ኬፋ ዮሐንስም እኛ ወደ አሕዛብ እነርሱም ወደ ተገረዙት ይሄዱ ዘንድ ለእኔና ለበርናባስ ቀኝ እጃቸውን ሰጡን፤ ¹⁰ ድሆችን እናስብ ዘንድ ብቻ ለመኑን፥ ይህንም ደግሞ ላደርግ ተጋሁ። ¹¹ ነገር ግን ኬፋ ወደ አንጾኪያ በመጣ ጊዜ ፊት ለፊት ተቃወምሁት፥ ይፈረድበት ዘንድ ይገባ ነበርና። ¹² አንዳንድ ከያዕቆብ ዘንድ ሳይመጡ ከአሕዛብ ጋር አብሮ ይበላ ነበርና፤ በመጡ ጊዜ ግን ከተገረዙት ወገን ያሉትን ፈርቶ ያፈገፍግ ነበርና ከእነርሱ ተለየ። ¹³ የቀሩትም አይሁድ ደግሞ፥ በርናባስ ስንኳ በግብዝነታቸው እስከ ተሳበ ድረስ፥ ከእርሱ ጋር አብረው ግብዞች ሆኑ።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ቆላስይስ 4 ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
¹ ጌቶች ሆይ፥ እናንተ ደግሞ በሰማይ ጌታ እንዳላችሁ ታውቃላችሁና ለባሪያዎቻችሁ በጽድቅና በቅንነት አድርጉላቸው። ² ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ፤ ³ በዚያን ጊዜም ስለ እርሱ ደግሞ የታሰርሁበትን የክርስቶስን ምሥጢር እንድንነግር እግዚአብሔር የቃሉን ደጅ ይከፍትልን ዘንድ ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ፤ ⁴ ልናገር እንደሚገባኝ ያህል እገልጠው ዘንድ ጸልዩልኝ። ⁵ ዘመኑን እየዋጃችሁ፥ በውጭ ባሉቱ ዘንድ በጥበብ ተመላለሱ። ⁶ ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን። ⁷ የተወደደ ወንድምና የታመነ አገልጋይ በጌታም አብሮኝ ባሪያ የሆነ ቲኪቆስ ኑሮዬን ሁሉ ያስታውቃችኋል፤ ⁸-⁹ ወሬያችንን እንድታውቁና ልባችሁን እንዲያጽናና፥ ከእናንተ ከሆነውና ከታመነው ከተወደደውም ወንድም ከአናሲሞስ ጋር ወደ እናንተ የምልከው ስለዚህ ምክንያት ነው፤ የዚህን ስፍራ ወሬ ሁሉ ያስታውቁአችኋል። ¹⁰-¹¹ ከተገረዙት ወገን ያሉት፥ አብሮ ከእኔ ጋር የታሰረ አርስጥሮኮስ የበርናባስም የወንድሙ ልጅ ማርቆስ ኢዮስጦስም የተባለ ኢያሱ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል፤ ስለ ማርቆስ፦ ወደ እናንተ ቢመጣ፥ ተቀበሉት የሚል ትእዛዝ ተቀበላችሁ፤ በእግዚአብሔር መንግሥት ከእኔ ጋር አብረው የሚሠሩት እነዚህ ብቻ ናቸው፥ እኔንም አጽናንተውኛል። ¹² ከእናንተ የሆነ የክርስቶስ ባሪያ ኤጳፍራ ሰላምታ ያቀርብላችኋል፤ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሁሉ ተረድታችሁና ፍጹማን ሆናችሁ እንድትቆሙ፥ ሁልጊዜ ስለ እናንተ በጸሎቱ ይጋደላል። ¹³ ስለ እናንተ በሎዶቅያም በኢያራ ከተማም ስላሉቱ እጅግ እንዲቀና እመሰክርለታለሁና። ¹⁴ የተወደደው ባለ መድኃኒቱ ሉቃስ ዴማስም ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። ¹⁵ በሎዶቅያ ላሉቱ ወንድሞችና ለንምፉን በቤቱም ላለች ቤተ ክርስቲያን ሰላምታ አቅርቡልን። ¹⁶ ይህችም መልእክት በእናንተ ዘንድ ከተነበበች በኋላ፥ በሎዶቅያ ሰዎች ማኅበር ደግሞ እንድትነበብ አድርጉ፤ ከሎዶቅያም የምትገኘውን መልእክት እናንተ ደግሞ አንብቡ። ¹⁷ ለአክሪጳም፦ በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ በሉልኝ። ¹⁸ በገዛ እጄ የተጻፈ የእኔ የጳውሎስ ሰላምታ ይህ ነው። እስራቴን አስቡ። ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ሐዋርያት 11 ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
²³ እርሱም መጥቶ የእግዚአብሔርን ጸጋ ባየ ጊዜ ደስ አለው፥ ሁሉንም በልባቸው ፈቃድ በጌታ ጸንተው ይኖሩ ዘንድ መከራቸው፤ ²⁴ ደግ ሰውና መንፈስ ቅዱስ እምነትም የሞላበት ነበረና። ብዙ ሕዝብም ወደ ጌታ ተጨመሩ። ²⁵ በርናባስም ሳውልን ሊፈልግ ወደ ጠርሴስ መጣ፤ ²⁶ ባገኘውም ጊዜ ወደ አንጾኪያ አመጣው። በቤተ ክርስቲያንም አንድ ዓመት ሙሉ ተሰበሰቡ፥ ብዙ ሕዝብንም አስተማሩ፤ ደቀ መዛሙርትም መጀመሪያ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ። ²⁷ በዚያም ወራት ነቢያት ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ወረዱ፤ ²⁸ ከእነርሱም አጋቦስ የሚሉት አንድ ሰው ተነሥቶ በዓለም ሁሉ ታላቅ ራብ ሊሆን እንዳለው በመንፈስ አመለከተ፤ ይህም በቀላውዴዎስ ቄሣር ዘመን ሆነ። ²⁹ ደቀ መዛሙርትም እያንዳንዳቸው እንደ ችሎታቸው መጠን አዋጥተው በይሁዳ ለሚኖሩት ወንድሞች እርዳታን ይልኩ ዘንድ ወሰኑ፤ ³⁰ እንዲህም ደግሞ አደረጉ፥ በበርናባስና በሳውልም እጅ ወደ ሽማግሌዎቹ ሰደዱት።▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ 📌 ምስባክ ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈ 📖 ቀጣይ ክፍል ይከተላል...
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፤በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤በአሐቲ ቃል።መልክአ ሥላሴ፦ ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ ለሣሕል፤እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል። ዚቅ፦ ሃሌ ሉያ ለአብ ንሴብሕ፤ለዘገብርኤል መልአክ አብሠራ፤ሃሌ ሉያ ለወልድ ወለመንፈስ ቅዱስ፤ተፈሥሒ ፍሥሕት ይቤላ፤አብሠራ አልሆሲሶ በዕዝና፤ኵሎ ዘለአኮ ነገራ። ነግሥ፦ ማኅፀንኪ እግዚእትየ ማርያም ይከብር ምስብዒተ፤እምጽርሐ አርያም ዘላዕሉ ወእምኪሩቤል ትርብዒተ፤ተስዓተ አዉራኀ ወኀምስተ ዕለተ፤ፆረ ዘኢይፀወር መለኮተ፤አግመረ ዘኢይትገመር እሳተ። ዚቅ፦ ዕፎ ፆርኪዮ ለዘኢይፀወር ተፀውሮ፤ዕፎ አግመርኪዮ ለዘኢይትከሃል ተገምሮ፤ወትቤሎሙ ማርያም ለሐዋርያት፤እስኩ ጠይቊ እመ ነገርኵክሙ ይወጽእ እሳት እምአፉየ፤ወያውዒ ኵሎ ዓለመ። መልክዓ ማርያም፦ ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤እምነ ከልበኔ ወቍስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ፤ማርያም ድንግል ለባሲተ ዐቢይ ትዕዛዝ፤ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፤ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ፡፡ ዚቅ፦ ወይቤላ ውእቱ መልአክ ሰላም ለኪ፤ሰላመ ዚአየ የሃሉ ምስሌኪ፤ተፈሥሒ ፍሥሕት። መልክዓ ማርያም፦ ሰላም ለአዕዛንኪ እለ ሰምዓ ቃሎ፤እግዚአብሔር እግዚእ ሶበ ለገብርኤል ተመሰሎ፤ማርያም ድንግል ጽሕቅት ለተሣሕሎ፤ሶበ ለልብየ እሳተ ኀዘን አሕለሎ፤ያፅምአኒ እላ ነገርየ ኵሎ። ዚቅ፦ አስተርአያ ለማርያም በአምሳለ ገብርኤል መልአክ፤ቃል በቃሉ ተናገራ፤ውእቱ ቃል ሥጋ ኮነ። መልክዓ ማርያም ፦ ሰላም ለእመታትኪ እለ ጸንዓ ይፍትላ፤ሜላተ ወወርቀ በናዝሬት ወበገሊላ፤ማርያም ድንግል ለዮዲት ጥበበ ቃላ፤ብጽሒ በሠረገላ ንትመሐል መሐላ፤ከመ ታኅድርኒ በብሔር ዘተድላ። ዚቅ፦ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤በናዝሬት ዘገሊላ መልአክ ለማርያም፤ተፈሥሒ ይቤላ፤ደንገፀ ወፈርሐ ይኅድጋ ለዘፈቀደ ለድንግልናሃ ዮሴፍ ሰገደ፤ናዝሬት እምገሊላ ትንዕስ ዓፀደ፤ወበጸጋ ትትሌዓል ፈድፋደ። መልክዓ ማርያም ፦ ሰላም ለንዋየ ውስጥኪ አምሳለ ንዋያ ለደብተራ፤ስብሐተ ልዑል ዘይሤውራ፤ማርያም ድንግል ትምክሕተ ደቂቃ ለሣራ፤ባልሕኒ ወለተ ቅስራ ለዓለመ ጽልመት እምፃዕራ፤እስመ መቅዓን ወጠዋይ ምሕዋራ። ዚቅ፦ ወለቱ ለቅስራ እንዘ ትፈትል ወርቀ በደብተራ፤ሊቀ ትጉሃን ገብርኤል አብሠራ። መልክዓ ማርያም፦ በዝንቱ ቃለ ማኅሌት ወበዝንቱ ይባቤ፤ለዘይስእለኪ ብእሲ ጊዜ ረከቦ ምንዳቤ፤ብጽሒ ፍጡነ ትሰጠዊዮ ዘይቤ፤ማርያም ዕንቍየ ክርስቲሎቤ ወምዕዝተ ምግባር እምከርቤ፤ዘጸገየ ማኅጸንኪ አፈወ ነባቤ፡፡ ዚቅ፦ ይቤላ መልአክ ለማርያም፤ተወከፊዮ ለቃል፤ኀቤኪ ይመጽእ፤ወበማኅፀነ ዚአኪ የኃድር። ማኅሌተ ጽጌ፦ ፈትለ ወርቅ ወፈትለ ሜላት አመ በአጽባዕትኪ ተባየጹ፤አምሳለ መለኮት ወትስብዕት እንዘ ኢየሐፁ፤ተአምረ ብርሃን ማርያም ለፀሐየ ጽድቅ አንቀጹ፤ጸገይኪዮ እንበለ አብ በሰሚዓ ቃሉ ወድምፁ፤ለገብርኤል መልአክኪ ዘፍሡሕ ገጹ። ዚቅ፦ መልአከ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል፤መልአከ ፍሥሐ በእሳት ሥዑል፤ሰበካ ለድንግል ምጽአቶ ለቃል፤ወርቀ ወሜላተ እንዘ ትፈትል። አመላለስ፦ መልአከ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል መልአከ ኃይል/፪/ መልአከ ፍሥሐ በእሳት ሥዑል/፬/ ወረብ፦ ቅዱስ ገብርኤል መልአከ ኃይል መልአከ ፍሥሐ በእሳት ሥዑል/፪/ ሰበካ ለድንግል ምጽአቶ ለቃል ወርቀ ወሜላተ እንዘ ትፈትል/፪/ አንገርጋሪ ወእንዘ ትፈትል ወርቀ ወሜላተ አስተርአያ ገብርኤል ግብተ፤ ወይቤላ እስመ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፤ ወትቤሎ ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ። አመላለስ ወትቤሎ ይኩነኒ/፪/ በከመ ትቤለኒ ይኩነኒ/፬/ እስመ ለዓለም፦ ጠባብ ወትሕት በቤተ መቅደስ ዘልህቃት ወለተ ዳዊት፤ ቀፀበቶ በትእምርት ለዘወረደ እመልዕልት፤ ዕፎ ኢያፍርሃ ገብርኤል ዘዜነዋ፤ በሐዳስ ስብከት ዘዘርዓ ውስተ ዕዝና፤እምቃሉ ሰሚዓ ተወከፈት በልባ፤ ለሐዲር ውስተ ከርሣ ደብተራሁ ሰመያ።
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ሃያ በዚች ቀን ከሌዊ ነገድ ከአሮን ትውልድ የሆነ ነቢይ ሐጌ አረፈ።✝️ ነቢይ ሐጌ
❖ እርሱም ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ነው ናቡከደነጾርም የኢየሩሳሌምን ሕዝብ በማረከ ጊዜ የዚህ ጻድቅ ነቢይ ወላጆች ከእስራኤል ልጆች ጋር ወደ ባቢሎን አገር ተማርከው ሔዱ ዳርዮስ የተባለውም ኵርዝ በነገሠ ጊዜ በሁለተኛው ዘመነ መንግሥቱ ይህ ነቢይ ትንቢት ተናገረ። ❖ የእስራኤልን ልጆች ወደ አገራቸው ይገቡ ዘንድ ኵርዝ ዳርዮስ በአሰናበታቸው ጊዜ እነርሱም ከገቡ በኋላ ቤተ መቅደስን ከመሥራት ቸለል በአሉ ጊዜ እነርሱ ግን በአማሩና በተሸለሙ ቤቶች ውስጥ ይኖሩ ነበርና እንዲህ አላቸው። ❖ ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር እንዲህ አለ የኔ ቤት ፈርሷል እናንተ ግን ሁላችሁም ቤታችሁን ታጸናላችሁ አላቸው፤ ስለዚህ ከምድር በላይ ያለች ሰማይ ዝናም ለዘር ትነሣለች ምድርም ፍሬዋን አትሰጥም አላቸው። ❖ ከሕዝቡም ደጋጎቻቸው ሰምተው እጅግ ፈሩ የእግዚአብሔርንም መመስገኛ ቤት እንደሚገባ መሥራት ጀመሩ፤ ይህም ጻድቅ ነቢይ ሰባ ዓመት ያህል ኖረ የትንቢቱም ወራት ክብር ይግባውና ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት በአራት መቶ ሠላሳ ዓመት ነው፤ ከዚህ በኋላም በሰላም በፍርቅ አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። አርኬ ✍️ ሰላም ለሐጌ ዘተነበየ በዖታ። ሚጠተ ፂውዋን ሕዝብ ወሕንፀተ መቅደስ ድኅረ ንስተታ። በእንተ ማርያምኒ ዘተደንገለት በመንታ። ለቤት ደኀሪት እንተ ትነብር ድሉታ። እምነ ቀዳሚት ይቤ ይኄይስ ትርሲታ።✝️
በዚችን ዕለት የንግሥት ታውፊና መታሰቢያዋ ሆነ የአውጋንዮስን የማድዮስም መታሰቢያቸው ነው በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። አርኬ ✍️ ሰላም ለክሙ አውጋንዮስ ወማድዮስ ጻድቃን። ወታውፊና ንግሥት ሥርጉተ ብርሃን። አመ ይመጽእ ክርስቶስ በዕለተ ፍዳ ወደይን። አመክንዩ አጋእዝትየ በዘእትባላሕ ምስኪን። እንበለ ምግባር ሊተ አልብየ ድኂን።📌 ታኅሣሥ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ሐጌ ነቢይ 2.አባ አውጋንዮስ 3.ታውፊና ንግሥት📌 ወርኀዊ በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር 2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ 3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ) 4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና 5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት 6.ማር ቴዎድሮስ ኃያል ሰማዕት📖ሐጌ 2፥9
✍️ብሩ የእኔ ነው፤ ወርቁም የእኔ ነው፤ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ከፊተኛው ይልቅ የዚህ የሁለተኛው ቤት ክብር ይበልጣል ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ በዚህም ሥፍራ ሰላምን እሰጣለሁ ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር
ታኅሳስ 20፣ 2018 ዓ.ም.
🗓️ ግሪጎሪያን: 29/12/2025
═══════════════════════════════
💭 የዕለቱ ጥቅስ:
"እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፥ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል।"
1ኛ ዮሐንስ 4:16
📖 ግጽዌ - የዕለቱ ንባብ
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌 ሮሜ 13
¹¹ ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና። ¹² ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል። እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ። ¹³ በቀን እንደምንሆን በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን፤ ¹⁴ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ።📌 1ኛ ዮሐንስ 1
¹ ስለ ሕይወት ቃል ከመጀመሪያው የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውንም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፤ ² ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤ ³ እናንተ ደግሞ ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተ ደግሞ እናወራላችኋለን። ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው። ⁴ ደስታችሁም እንዲፈጸም ይህን እንጽፍላችኋለን። ⁵ ከእርሱም የሰማናት ለእናንተም የምናወራላችሁ መልእክት፦ እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም የምትል ይህች ናት። ⁶ ከእርሱ ጋር ኅብረት አለን ብንል በጨለማም ብንመላለስ እንዋሻለን እውነትንም አናደርግም፤ ⁷ ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል። ⁸ ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም። ⁹ በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። ¹⁰ ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም።📌 ሐዋርያት 26
¹² ስለዚህም ነገ ከካህናት አለቆች ሥልጣንና ትእዛዝ ተቀብዬ ወደ ደማስቆ ስሄድ፥ ¹³ ንጉሥ ሆይ፥ በመንገድ ሳለሁ እኩል ቀን ሲሆን በዙሪያዬና ከእኔ ጋር በሄዱት ዙሪያ ከፀሐይ ብሩህነት የበለጠ ብርሃን ከሰማይ ሲበራ አየሁ፤ ¹⁴ ሁላችንም በምድር ላይ በወደቅን ጊዜ፦ ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል የሚል ድምፅ በዕብራይስጥ ቋንቋ ሲናገረኝ ሰማሁ። ¹⁵ እኔም፦ ጌታ ሆይ፥ ማንነህ? አልሁ። እርሱም አለኝ፦ አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ። ¹⁶ ነገር ግን ተነሣና በእግርህ ቁም፤ ስለዚህ እኔን ባየህበት ነገር ለአንተም በምታይበት ነገር አገልጋይና ምስክር ትሆን ዘንድ ልሾምህ ታይቼልሃለሁና። ¹⁷-¹⁸ የኃጢአትንም ስርየት በእኔም በማመን በተቀደሱት መካከል ርስትን ያገኙ ዘንድ፥ ከጨለማ ወደ ብርሃን ከሰይጣንም ሥልጣን ወደ እግዚአብሔር ዘወር እንዲሉ ዓይናቸውን ትከፍት ዘንድ፥ ከሕዝቡና ወደ እነርሱ ከምልክህ ከአሕዛብ አድንሃለሁ።📌 ምስባክ
ፈኑ ብርሃነከ ወጽድቀከ። እማንቱ ይምርሓኒ ወይሰዳኒ ደብረ መቅደስከ ወውስተ አብያቲከ እግዚኦ።📌 ትርጉም
“ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እነርሱ ይምሩኝ፥ ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ።” መዝ. 42÷3-4📌 ወንጌል ዮሐንስ 1
¹ በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ² ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። ³ ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። ⁴ በእርሱ ሕይወት ነበረች፥ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረች። ⁵ ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም። ⁶ ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ ⁷ ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምኑ ይህ ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክር መጣ። ⁸ ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ፥ እርሱ ብርሃን አልነበረም። ⁹ ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣ ነበር። ¹⁰ በዓለም ነበረ፥ ዓለሙም በእርሱ ሆነ፥ ዓለሙም አላወቀውም። ¹¹ የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም። ¹² ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ¹³ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም። ¹⁴ ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። ¹⁵ ዮሐንስ ስለ እርሱ መሰከረ እንዲህም ብሎ ጮኸ፦ ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ከእኔ በፊት ነበረና ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል፤ ስለ እርሱ ያልሁት ይህ ነበረ። ¹⁶ እኛ ሁላችን ከሙላቱ ተቀብለን በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጥቶናልና ሕግ በሙሴ ተሰጥቶ ነበርና፤ ¹⁷ ጸጋና እውነት ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ሆነ። ¹⁸ መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው። ¹⁹ አይሁድም፦ አንተ ማን ነህ? ብለው ይጠይቁት ዘንድ ከኢየሩሳሌም ካህናትንና ሌዋውያንን በላኩበት ጊዜ፥ የዮሐንስ ምስክርነት ይህ ነው።📌 ቅዳሴ
አትናቴዎስ ቅዳሴ ነው።
❖ በዚችም ቀን ከካህናት ወገን የሆነ የሀገረ ቡርልስ ኤጲስቆጶስ ቅዱስ አባት አባ ዮሐንስ አረፈ፤ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ የከበሩ ናቸው እነርሱም ከገንዘባቸው ለድኆችና ለችግረኞች ይሰጡ ነበር ወላጆቹም በአረፉ ጊዜ የተዉለትን ገንዘብ ወስዶ ቤተ ክርስቲያን ሠራ ዳግመኛም የእንግዳ ቤት ሠራ በውስጡም መጻተኞችንና በሽተኞችን ሰብስቦ የሚያገለግላቸው ሆነ የሚሹትንም ሁሉ ያቀርብላቸዋል። ❖ በዚያም ወራት ወደርሱ አንድ መነኵሴ መጣ የምንኲስናንም ሥራ አመሰገነለት ክብሩንም ገለጠለት ያ መነኲሴም ከሔደ በኋላ ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች ሰጥቶ አባ ዳንኤል ለአስቄጥስ ገዳም አበ ምኔት ሁኖ በነበረበት ወራት ወደ አስቄጥስ ሒዶ በአባ ዳንኤል ዘንድ መነኰሰ በዋሻ ውስጥም ብቻውን ሁኖ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ፤ ስለ መልካም ተጋድሎውም ሰይጣናት ቀኑበት ብዙ ዘመንም ታሞ ከኖረ በኋላ በደዌ መቅሠፍት ቀሠፉት። ❖ ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈወሰውና ኃይለኛ ጽኑዕ አደረገው በእግዚአብሔርም ፈቃድ ቡርልስ በሚባል አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ተሾመ በዘመኑም በሀገሮች ውስጥ ብዙ ኑፋቄ ነበረ እርሱም እንክርዳዱን ከሥንዴ መካከል ይነቅል ዘንድ ብዙ ድካምን ደከመ ከላይኛው ግብጽ የሆነ አንድ ሰው ነበረ ብዙ ነገርንም ይቀባጥር ነበር የመላእክት አለቃ ሚካኤል ምሥጢር ይገልጥልኛል በማለት እርሱ ብዙ ሰዎችን አሳታቸው ይህንንም በአወቀ ጊዜ ይዘው ይገርፉት ዘንድ አዘዘ ስሕተቱንም አመነ ከሀገርም አሳደዱት። ❖ ነቢይ ዕንባቆም ይታየኛል ብዙ ምሥጢራትንም ይገልጥልኛል የሚል ሌላ ሰው ነበረ ብዙዎችም ተከተሉት እርሱንም አሳደደው ትምህርቱንም አጠፋ መጻሕፍቱንም ቀደደ የሳቱትንም ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው። ❖ ይህ አባ ዮሐንስም መሥዋዕትን ለማሳረግ በሚቀድስ ጊዜ ፊቱ እሳት ይሆናል ሥጋውም ከእሳት ማንደጃ ውስጥ እንደ ወጣ ይሆናል ዕንባውም እንደ ዝናብ ይዘንባል የመላእክትን ሠራዊት በመሠዊያው ዙሪያ በግልጥ ያያቸዋልና፤ ኅብስቱ በሚፈተት ጊዜ ሦስቱን የመፈተቻ ምስጋናዎች አንብቦ ጽዋውን ሲባርከው እንደ ፍም የጋለ ሁኖ ጽዋውን ያገኘዋል። ❖ ከዚህም በኋላ በዘመኑ በቀን ከበሉ በኋላ በአንድ ቀን ሁለተኛ የሚቆርቡ ክፉዎች ሰዎች ተነሡ አስተማራቸው ገሠጻቸውም ግን አልተመለሱም ዳግመኛም አወገዛቸው ባልተመለሱም ጊዜ ስለ እሳቸው ጌታን ለመነው እሳትም ከሰማይ ወርዶ አለቃቸውን አቃጠለው የቀሩትም ይህን አይተው እጅግ ፈሩ ተጸጽተውም ወደ ቀናች ሃይማኖት ተመለሱ። ❖ ከዚህም በኋላ ከዚህ ከኃላፊው ዓለም እግዚአብሔር ሊአሳርፈው በወደደ ጊዜ ቅዱሳን አባ እንጦንስንና አባ መቃርስን ወደርሱ ላካቸው እነርሱም ዕረፍቱ እንደ ደረሰ አስረዱት ሕዝቡንም ሰብስቦ ሕግና ሥርዓትን እንዲጠብቁ እርስ በርሳቸውም ይፋቀሩ ዘንድ በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አዘዛቸው ከዚህም በኋላ በመኝታው ላይ ጋደም ብሎ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። አርኬ ✍️ ሰላም ለዮሐንስ እንተ ፃመወ ፈድፋደ። ከመ ይምላሕ ነግሀ እማዕከለ ሥርናይ ክርዳደ። ዝንቱ ካህን ተመሊዖ ረዓደ። በጊዜ ቅዳሴ እንዘ ያመዓትብ እደ። በአምሳለ እሳት ይረክቦ ለጽዋዕ ንዱደ።✝️ አቡነ ስነ ኢየሱስ ጻድቅ
❖ ጻድቁ በመካከለኛው (የብርሃን) ዘመን የነበሩ ኢትዮጵያዊ፤ ከምድረ ሽዋ ወደ ታች አርማጭሆ የሔዱ መናኝ ጭው ባለ በርሃ ለቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ ገዳምን ያነጹ አባት ብዙ አርድእትን ያፈሩ መናኝ ብዙ ተአምራትን የሠሩና ወንጌልን ያስተማሩ መነኮስ ናቸው:: ❖ በደመናም ይጫኑ ነበር ገዳማቸውም (ታች አርማጭሆ ከሳንጃ ከተማ የ3 ሰዓት መንገድ ይወስዳል) ድንቅና ባለ ብዙ ቃል ኪዳን ነው፤ መልአከ ሞት መስከረም 1 ቀን ቢመጣ የቅዱስ ገብርኤልን በዓል ሳላከብር አይሆንም ብለው ለ3 ወራት በበራቸው አቁመውታል፤ ታህሳስ 19 ቀንም አርፈዋል:: አምላከ ቅዱሳን ረድኤቱ በረከቱ ያሳድርብን፤ በጸሎታቸው ይማረን።📌 ታኅሣሥ 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት 2.ቅዱስ ዮሐንስ ዘቡርልስ 3.አቡነ ስነ ኢየሱስ ጻድቅ📌 ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት 2.አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ 3.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም 4.ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ📖ዳን 9፥20-22
✍️እኔም ገና ስናገርና ስጸልይ ፥ በኃጢአቴና በሕዝቤም በእስራኤል ኃጢአት ስናዘዝ ፥ በአምላኬም በእግዚአብሔር ፊት ስለ ተቀደሰው ስለ አምላኬ ተራራ ስለምን ፥ ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው የነበረው ሰው ገብርኤል እነሆ እየበረረ መጣ ፤ በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ፤ አስተማረኝም ፥ ተናገረኝም እንዲህም አለ፤ ዳንኤል ሆይ ጥበብንና ማስተዋልን እሰጥህ ዘንድ አሁን መጥቻለሁ
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐሥራ ዘጠኝ በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው እርሱም በባቢሎን አገር ከነደደ እሳት ውስጥ በጨመሩአቸው ጊዜ አናንያን አዛርያን ሚሳኤልን ያዳናቸው ነው።✝️ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅ
❖ ንጉሥ ናቡከደነፆር ከአባታቸው ከይሁዳው ንጉሥ ከኢዮአቄም ጋር የማረካቸው አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ እግዚአብሔር በዚህች ዕለት መልአኩን ልኮ ታላቅ ተአምር አድርጎላቸዋል፤ ንጉሥ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ጥበብን እያስተማረ ካሳደጋቸው በኋላ በባቢሎን ሀገሮች ሁሉ ውስጥ ሾማቸው፡፡ ❖ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ ለዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ፤ በዚህም ጊዜ ለጣዖቱ ባለመስገድ እግዚአብሔርን ብቻ በማምለክ የጸኑት እነዚህ ሦስት ወጣቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ❖ ስለ እነርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው ✍‹‹ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር መኳንንትንና ሹማምቶችን አዛዦችንና አዛውንቶችን በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን መጋቢዎችንም፣ አውራጃ ገዦችንም ሁሉ ይሰበስቡ ዘንድ፣ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፤ በዚያን ጊዜም መኳንንቱና ሹማምቶቹ፣ አዛዦቹና አዛውንቶቹ፣ በጅሮንዶቹና አማካሪዎቹ፣ መጋቢዎቹና አውራጃ ገዦቹ ሁሉ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ተሰበሰቡ፤ ናቡከደነፆርም ባቆመው ምስል ፊት ቆሙ፤ አዋጅ ነጋሪውም እየጮኸ እንዲህ አለ ‹ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፣ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል› ❖ ስለዚህ በዚያን ጊዜ አሕዛብ ሁሉ የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ፣ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የተናገሩ ሁሉ ተደፉ፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ሰገዱ፡፡ ❖ በዚያን ጊዜም ከለዳውያን ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፤ ለንጉሡም ለናቡከደነፆር ተናገሩ እንዲህም አሉ ‹ንጉሥ ሆይ ሺህ ዓመት ንገሥ፤ አንተ ንጉሥ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ የሚሰማ ሰው ሁሉ ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ይስገድ፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል ብለህ አዘዝህ፤ በባቢሎን አውራጃ ሥራ ላይ የሾምሃቸው ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም የሚባሉ አይሁድ አሉ፤ ንጉሥ ሆይ እነዚህ ሰዎች ትእዛዝህን እንቢ ብለዋል፤ አማልክትህን አያመልኩም፥ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል አይሰግዱም› ❖ ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ያመጡ ዘንድ አዘዘ፤ እነዚህንም ሰዎች ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው፤ ናቡከደነፆርም ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ሆይ አምላኬን አለማምለካችሁ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን፤ አሁንም የመለከቱንና የእንቢልታውን የመሰንቆውንና የክራሩን የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ ተደፍታችሁ ላሠራሁት ምስል ብትሰግዱ መልካም ነው፤ ባትሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው›› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ❖ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡን ‹ናቡከደነፆር ሆይ በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም፤ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፤ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ› አሉት፡፡ ❖ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፤ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፤ እርሱም ተናገረ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት አዘዘ፤ ሲድራቅንና ሚሳቅንም አብደናጎንም ያስሩ ዘንድ ወደ ሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ፤ የዚያን ጊዜም እነዚህ ሰዎች ከሰናፊላቸውና ከቀሚሳቸው ከመጐናጸፊያቸውም ከቀረውም ልብሳቸው ጋር ታስረው በሚነድድ በእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ፡፡ ❖ የንጉሡም ትእዛዝ አስቸኳይ ስለሆነ የእቶኑም እሳት እጅግ ስለሚነድድ፣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም የጣሉአቸውን ሰዎች የእሳቱ ወላፈን ገደላቸው፤ እነዚህም ሦስቱ ሰዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ታስረው በሚነድደው በእቶኑ እሳት ውስጥ ወደቁ፡፡ ❖ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም ‹ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን› ብሎ ተናገራቸው፤ እነርሱም ‹ንጉሥ ሆይ እውነት ነው› ብለው ለንጉሡ መለሱለት፤ እርሱም ‹እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል› ብሎ መለሰ፡፡ ❖ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደ ሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ ‹እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ኑ ውጡ› ብሎ ተናገራቸው፤ ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ፤ መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፣ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፣ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ፡፡ ❖ ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ› አለ›› 📖 ዳን 3፥1-30 የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ አማላጂነት፣ የሊቃነ መላእክቱ ጥበቃና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃ አይለየን፤ ሀገራችን ሰላም ፍቅር ያድርግልን አርኬ ✍️ሰላም እብል ኪያከ ክቡረ። ለስመ ዚአከ ገብርኤል እንዘ አነሥእ መዝሙረ። እግዚአብሔር መንበሮ ሰማየ ሰማያት ዘገብረ። ይትመሰል በአርአያከ አመ ጊዜ ሐወጸ ምድረ። እምነ መላእክት ኲሉ ስነከ አፍቀረ።✝️ አባ ዮሐንስ (ቡርልስ) 📖 ቀጣይ ክፍል ይከተላል...
ታኅሳስ 19፣ 2018 ዓ.ም.
🗓️ ግሪጎሪያን: 28/12/2025
═══════════════════════════════
💭 የዕለቱ ጥቅስ:
"እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፥ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል।"
1ኛ ዮሐንስ 4:16
📖 ግጽዌ - የዕለቱ ንባብ
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌 2ኛ ተሰሎንቄ 1
⁶-⁷ ጌታ ኢየሱስ ከሥልጣኑ መላእክት ጋር ከሰማይ በእሳት ነበልባል ሲገለጥ፥ መከራን ለሚያሳዩአችሁ መከራን፥ መከራንም ለምትቀበሉ ከእኛ ጋር ዕረፍትን ብድራት አድርጎ እንዲመልስ በእግዚአብሔር ፊት በእርግጥ ጽድቅ ነውና። ⁸ እግዚአብሔርን የማያውቁትን፥ ለጌታችንም ለኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል የማይታዘዙትን ይበቀላል፤ ⁹-¹⁰ በዚያም ቀን በቅዱሳኑ ሊከብር፥ ምስክርነታችንንም አምናችኋልና በሚያምኑት ሁሉ ዘንድ ሊገረም ሲመጣ፥ ከጌታ ፊት ከኃይሉም ክብር ርቀው በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ። ¹¹-¹² ስለዚህም ደግሞ እንደ አምላካችን እንደ ጌታም እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስም በእናንተ ዘንድ ሊከብር እናንተም በእርሱ ዘንድ ልትከብሩ፥ አምላካችን ለመጥራቱ የምትበቁ አድርጎ ይቈጥራችሁ ዘንድ፥ የበጎነትንም ፈቃድ ሁሉ የእምነትንም ሥራ በኃይል ይፈጽም ዘንድ ስለ እናንተ ሁልጊዜ እንጸልያለን።📌 ይሁዳ 1
²⁰ እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ፥ ²¹ ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ። ²² አንዳንዶች ተከራካሪዎችንም ውቀሱ፥ አንዳንዶችንም ከእሳት ነጥቃችሁ አድኑ፥ ²³ አንዳንዶችንም በሥጋ የረከሰውን ልብስ እንኳ እየጠላችሁ በፍርሃት ማሩ። ²⁴ ሳትሰናከሉም እንዲጠብቃችሁ፥ በክብሩም ፊት በደስታ ነውር የሌላችሁ አድርጎ እንዲያቆማችሁ ለሚችለው ²⁵ ብቻውን ለሆነ አምላክና መድኃኒታችን ከዘመን ሁሉ በፊት አሁንም እስከ ዘላለምም ድረስ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ግርማ ኃይልም ሥልጣንም ይሁን፤ አሜን።📌 ሐዋርያት 7
³⁰ አርባ ዓመትም ሲሞላ የጌታ መልአክ በሲና ተራራ ምድረ በዳ በቍጥቋጦ መካከል በእሳት ነበልባል ታየው። ³¹-³² ሙሴም አይቶ ባየው ተደነቀ፤ ሊመለከትም ሲቀርብ የጌታ ቃል፦ እኔ የአባቶችህ አምላክ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ ብሎ ወደ እርሱ መጣ። ሙሴም ተንቀጥቅጦ ሊመለከት አልደፈረም። ³³ ጌታም፦ የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች ምድር ናትና የእግርህን ጫማ አውልቅ። ³⁴ በግብፅ ያሉትን የሕዝቤን መከራ ፈጽሜ አይቼ መቃተታቸውንም ሰምቼ ላድናቸው ወረድሁ፤ አሁንም ና፥ ወደ ግብፅ እልክሃለሁ አለው። ³⁵ ሹምና ፈራጅ እንድትሆን የሾመህ ማን ነው? ብለው የካዱትን፥ ይህን ሙሴን በቍጥቋጦው በታየው በመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው።📌 ምስባክ
በቅድመ መላእክቲከ እዜምር ለከ። ወእሰግድ ውስተ ጽርሐ መቅደስከ። ወእገኒ ለስምከ።📌 ትርጉም
አቤቱ፥ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፥ የአፌን ነገር ሰምተኸኛልና፤ በመላእክት ፊት እዘምርልሃለሁ። ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤ ስለ ምሕረትህና ስለ እውነትህ ስምህንም አመሰግናለሁ፥ በሁሉ ላይ ቅዱስ ስምህን ከፍ ከፍ አድርገሃልና። መዝ 137፥1-2።📌 ወንጌል ሉቃስ 1
¹¹ የጌታም መልአክ በዕጣኑ መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ታየው። ¹² ዘካርያስም ባየው ጊዜ ደነገጠ፥ ፍርሃትም ወደቀበት። ¹³ መልአኩም እንዲህ አለው፦ ዘካርያስ ሆይ፥ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ¹⁴ ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። ¹⁵ በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤ ¹⁶ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመልሳል። ¹⁷ እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ፥ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ መንፈስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል። ¹⁸ ዘካርያስም መልአኩን፦ እኔ ሽማግሌ ነኝ ምስቴም በዕድሜዋ አርጅታለችና ይህን በምን አውቃለሁ? አለው። ¹⁹ መልአኩም መልሶ፦ እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፤ ²⁰ እነሆም፥ በጊዜው የሚፈጸመውን ቃሌን ስላላመንህ፥ ይህ ነገር እስከሚሆን ቀን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ መናገርም አትችልም አለው።📌 ቅዳሴ
ማርያም ቅዳሴ ነው።
Reviews channel
2 total reviews
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️» is a Telegram channel in the category «Религия и духовность», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 5.2K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 27.4, with 2 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.2 ₽, and with 5 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий