
- Main
- Catalog
- Religion & Spirituality
- Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️»
Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️»
በዚህ channel ውስጥ መንፈሳዊ መጻሕፍትንና የየዕለቱን ስንክሳር ያገኛሉ።
Channel statistics
አምላካችን ሆይ፣ በዚህ ቀን የምንነበውን ቃልህ በልባችን እንድናስቀምጥ እና በሕይወታችን እንድንተገብር እርዳን። አሜን።📱 ቦት: @gitsawebot 📺 ቻናል: https://t.me/religious_books_lover 🌐 ድህረ ገጽ: https://gitsawe-tailwind-2019.vercel.app/ 🕊️ ሰላም ይሁንላችሁ!
የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ወደ አንጾኪያ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ ጊዜ ሠራዊቱን ከከተማውጭ ትቶ ከሁለቱ ወዳጆቹ ከለውንድዮስና ከኒቆሮስ ጋር ገባ ንጉሥም በክብር ተቀበሎ ስለጦርነት ወሬ ስለ ሠራዊቱም ጠየቀው እርሱም የሆነውን ሁሉ ነገረው ። ከዚህም በኋላ ለአጵሎን ስለ መስገድ አወሳ የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ንጉሠን ገሠጸውዘለፈውም እንዲሁም ወዳጆቹ ለውንድዮስና ኒቆሮስ ንጉን ረገሙት እርሱም ተቆጣለውንድዮስንና ኒቆሮስን ወደ ሚዶን አገር ወስደው በዚያ ያሠቃዩአቸው ዘንድ አዘዘ ።ኒቆሮስ የፋርስ ሀገር የሠራዊት አለቃ መኩንን ስለነበረ ከፋርስ ሰዎች የተነሣ ዲዮቅልጥያኖስፈርቷልና በዚያም ለውንድዮስንና ኒቆሮስን በአሠቃዩአቸው ጊዜ በዚች ቀን ጥር ዐሥራ ሁለትየሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ ። የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስን ግን ኮሞል በሚባል ታላቅ እንጨት ላይ አስተኝተው ቀሩጥራቸውመቶ ኃምሳ ሦስት በሆኑ በረጃጅም የብረት ችንካሮች እንዲቸነክሩት አዘዘ ። እግዚአብሔርምመልአኩን ሚካኤልን ወደርሱ ልኮ በመከራው ሁሉ አጸናው ። በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸለትና የመረጥኩህ ቴዎድሮስ ሆይሰላም ይሁንልህ ይህን ሁሉ መከራ ስለ ስሜ ታግሠሃልና ብፁዕ ነህ ይህን ከሀዲ ንጉሥታሳፈረው ዘንድ እሊህን ብረቶች ከሥጋህ ውስጥ አውጥቼ እንዳድንህ ትሻለህን አለው ።ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ጌታችንን እንግዲህስ ስለ ከበረ ስምህ መሞት ይሻለኛል አለው ።ሁለተኛም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጄ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሆይ እነሆሦስት አክሊላትን አዘጋጅቼልሃለሁ አንደኛው ስለ ድንግልናህ ሁለተኛው የዚህን ዓለም ክብርትተህ መከራ ስለመቀበልህ ሦስተኛው ስለ ስሜ ደምህን ስለ አፈሰስክ ነው አለው ። እኔም ቃል ኪዳንን ሰጠሁህ ስምህን ለሚጠራና መታሰቢያህን ለሚያደርግ በሁሉ ቦታ ከመከራውሁሉ አድነው ዘንድ ለድኖችም ምጽዋት የሰጠውን ስለ አንተ በቤተ ክርስቲያን መባ ያገባውንየገድልህን መጽሐፍ የጻፈውንና ያጻፈውን ቤተ ክርስቲያንህንም የሠራውን ሁሉንም ኃጢአቱንይቅር ብዬ መንግሥተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ ። ጌታችንም ይህን ቃል ኪዳን ከሰጠው በኋላወደ ሰማይ ዐረገ ቴዎድሮስም ሦስቱን አክሊሎች ሲሰጡት ሦስቱን መላእክት አየ በዚያንም ጊዜየከበረች ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ ። ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ከአረፈ በኋላ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ለጣዖታት ያሰግዱአቸው ዘንድወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ ሠራዊት የጣዖታቱን ካህናት ላከ ሁለተኛም ንጉሥን የሚወድ ለአማልክትይስገድ እያለ የሚዞር ዓዋጅ ነጋሪ አዘዘ ። የቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሠራዊትም የነገሥታት ንጉሥየጌቶች ጌታ ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም ብለው ሁሉም ጮኹንጉሠሥም ሰምቶ ራሶቻቸውን በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ ። ቁጥራቸውም ሁለት መቶኃምሳ እልፍ ሆነ በሰማዕታት ራሶች ላይ አክሊልን የሚያኖሩ ብርሃናውያን መላእክት አየሩንመሉት ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታት ሁሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። አርኬ ሰላም ለከ ቴዎድሮስ ዐጽቅ ። ዘብሔረ ምሥራቅ ። በመንግሥተ ክርስቶስ ትትዓጸፍ አልባሰመብረቅ ። ዘኢተከድነ ቅንዋተ በአምሳለ ቄጽል ጽፉቅ ። እምውስተ ሥጋከ ኢሀሎ ዕሩቅ ። ሰላም ለክሙ አእላፈ ቴዎድሮስ አዕናቀ፡ ። ክልኤቱ ምእት እልፍ ወኃምሳ እልፍ ዘበጐልቀ* ።ኦ ሥርግዋን በጽጌ ሃይማኖት ሰንሰሪቀ ። አምሥጡኒ እምነ ፃማ አመ ትከውን ኩርያቀኑ ። ከመእማዕገት ያመሥጥ ምዳቀ፡ ። ሰላም ለለውንድዮስ ወለቢጹ ኒቆሮስ ። መኩንነ ፋርስ ። ምስለ ቴዎድሮስ ሰማዕት ወልደ ሲድራኮስ ። ዘአጥመቆሙ በእሳት ወበመንፈስ ቅዱስ ። ወኅቤ ሕይወት ኢየሱስ ክርስቶስ ።✝️ የሰማዕታቱ የዩልያኖስና የመነኩሴው የዳንኤል መታሰቢያ
በዚችም ቀን የቅዱሳን የሰማዕታቱ የዩልያኖስና የመነኩሴው የዳንኤል መታሰቢያቸው ነው ። የይስሐቅም ልጅ የያዕቆብ የልደቱ መታሰቢያ ነው ። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና አሜን ።📌 ጥር ፲፪ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1. ቃና ዘገሊላ 2. ቅዱስ ያዕቆብ እሥራኤል 3. ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ 4. የቅዱሳን ለውንድዮስ እና ኒቆሮስ 5.፪.5 ሚሊየን ሰማዕታት (የቅዱስ ቴዎድሮስ ማሕበር)📌 ወርኀዊ በዓላት 📖ዮሐ. ፪፥8
✍️ አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ አደነቀ ። ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም ። ውሃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር ። አሳዳሪውም ሙሽራውን ጠርቶ.:-'ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል ። ከሰከሩም በሁዋላ መናኛውን ። አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል' አለው ።
➛በጌርጌሴኖን አንድ አጋንንት ያደረበት ሰው ወደ ጌታችን ቀርቦ ‹‹የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ_ክርስቶስ_ሆይ ከአንተ ጋር ምን አለኝ?›› አለው፡፡ እውነት ይህ ቃል የንቀት ይመስላልን? የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ብሎ አምላክነቱን እየመሰከረ ሊያቃልለው ይችላልን? ደግሞስ ላለመጥፋት ፍፁም የሚፈልግ ሰው ሊያድነው ሥልጣን ያለውን ሊንቅ ይችላልን? አይችልም፡፡ ይህ ቃል የሚያመለክተው ምን አጠፋሁ ስለምን ልታጠፋኝ ወደድክ በማለት መፍራት መራዱን ነው፡፡ (ሉቃ 8÷28-29) ስለሆነም ‹‹አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?›› የሚለው የንቀት አለመሆኑን ከሁለቱ ጥቅሶች መረዳት እንችላለን፡፡ እመቤታችን እና ጌታ በንግግር አልተቃረኑም ንግግራቸው የፍቅር ነበር፡፡ ንግግራቸው የመግባባት ስለነበር ነው ‹‹አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?›› ካላት በኋላ ዘወር ብላ አገልጋዮቹን የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ ያለችው፡፡ ‹‹ጊዜዬ አልደረሰም›› ጌታ ይህን ቃል የተናገረው ስለ ብዙ ምክንያቶች ነው፡፡ ጊዜዬ አልደረሰም ማለቱ፡- ➛ እግዚአብሔር ነገሮችን የሚያከናውንበት የራሱ ጊዜ አለው፡፡ በመሆኑም ይህን ተአምር የምፈፅምበት ጊዜዬ አልደረሰም ሲል ነው፡፡ ➛አንድም ጋኖቹ ውስጥ የቀረ ወይን ስለነበረ ባለው ላይ አበርክቶ እንጂ ውኃውን ወደ ወይን አልለወጠውም እንዳይሉ ወይኑ ከጋኑ ተንጠፍጥፎ እስኪያልቅ ድረስ ጊዜዬ አልደረሰም አለ፡፡ ➛አንድም ይሁዳ ከሠርግ ቤት ወጣ ብሎ ነበርና ወደ ሠርግ ቤቱ እስኪመለስ ጊዜዬ አልደረሰም አለ፡፡ ይሁዳ በቃና የገለጠውን ምስጢር ለእኔ ስላላሣየኝ ተከፍቼበት ከተአምራቱ ቢያጎድለኝ በሞቱ ገባሁበት፤ ሸጥኩት እንዳይል ምክንያት ለማሳጣት እንዲህ አድርጓል፡፡ ➛አንድም እውነተኛ የሕይወት ወይን የሆነውን ደሜን የምሠጥበት ጊዜ ገና ነው ሲል፡፡ የድንግል ማርያም አማላጅነት በገሊላ ቃና ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በሠርግ ቤት ሣለ የወይኑን ማለቅ የማይመለከት ሆኖ አይደለም፡፡ ነገር ግን የእናቱን የድንግል ማርያምን አማላጅነት ሊገልጥ ስለወይኑ ማለቅ እስክትነግረው ድረስ አንዳች ነገር አላደረገም፡፡ ኋላ ግን የጭንቀት አማላጅ ድንግል ማርያም ስለ ወይኑ አሰበች ልጇ ወዳጇን ለመነች፡፡ እርሱም የእናቱን ልመና ተቀብሎ ተአምራቱን ፈፀመ፡፡ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሣይነግሯት በልብ ያለውን የምታውቅ የምትመረምር እናት ናትና የሠርጉ አስተናባሪዎች ይሄ ጎደለ ሣይሏት የልቦናቸውን ሐዘን ተመልክታ ከልጇ ከወዳጇ አማልዳ የጎደላቸውን ሞልታለች፡፡ያስጨነቃቸውንም አርቃለች፡፡ በችግራቸው ደርሳላቸዋለች፡፡ ታዲያ ሳይነግሯት የልቡናን አይታ ከማለደች ስሟን ጠርተው ለሚለምኗትማ እንዴት አብልጣ አታማልድ? ለእርሱም ከቸር አባቱ ሕይወት ከሆነ መንፈስ_ቅዱስም ጋር ክብር ምስጋና ስግደትም ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን። አምላከ ቅዱሳን ወይነ ቃና ፍቅሩን ያሳድርብን። ከድንግል ማርያም እናቱ ምልጃና ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን ለዘላለሙ አሜን።✝️ #ቅዱስ_ቴዎድሮስ_በናድሌዎስ
በዚችም ዕለት የምሥራቅ ሰው ጽኑዕ ኃይለኛ የሆነ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ በሰማዕትነት ሞተ ። ይህም ታላቅ ተጋዳይ ከአንጾኪያ አገር ሰዎች ከመንግሥት ወገን ነው የአባቱ ስም ሲድራኮስይባላል ለንጉሥም የጭፍራ አለቃ ነው የእናቱም ስም በጥሪቃ ይባላል ትርጓሜውም እመቤትማለት ነው ። ንጉሥ ኑማርያኖስም በጦርነት ውስጥ በሞተ ጊዜ ልጁ ዮስጦስም በጦርነት ውስጥ ነበርመንግሥትም ያለ ንጉሥ ነበረች የቴዎድሮስ አባት ሲድራኮስና ፋሲለደስ ዲዮቅልጥያኖስ ነግሦሃይማኖቱን እስከ ካደ ድረስ የመንግሥቱን አስተዳደር ይመሩ ነበር ። እርሱም ዲዮቅልጥያኖስ አስቀድሞ ከላየኛው ግብጽ የሆነ የዮስጦስ እኅት የንጉሥ ኑማርዮስ ልጅሚስት ሆነችውና አነገሰችው ። ቅዱስ ቴዎድሮስም በአደገ ጊዜ በጦርነት ውስጥ ፈጽሞ ኃይለኛሆነ እርሱ ቅዱስ ቴዎድሮስ በሚሔድበት ጦርነት ሁሉ ጠላቶቹን ድል አድርጎ ያሳድዳቸዋልየፋርስ ሰዎችም ቴዎድሮስ ወደእናንተ መጣ ሲሏቸው ልባቸው ይሰበራል ይገዙለታልምከእነርሱም ውስጥ ቴዎድሮስ የሮማውያን አምላክ ነው የሚሉ አሉ ። ለዲዮቅልጥያኖስ ክህደት ምክንያት የሆነ የ ዝ ንጉሥን ልጅ ኒጎሚዶስን ሁለት ጊዜ የማረከውእርሱ ነው ከአባ አጋግዮስም ዘንድ በአኖረው ጊዜ አጋግዮስ በኒጎሚዶስ ክብደት ልክ ወርቅአስመዝኖ ከቀ-ዝ ንጉሥ ተቀብሎ ወደ አባቱ መልሶታልና ። የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም በጦርነት ቦታ ቡናቢስ በሚባል ወንዝ አጠገብ ሳለ ስሙለውንድዮስ የሚባል ወዳጁም ሳለ ከዚህም በኋላ በአንዲት ሌሊት ራእይን አየ ከምድር እስከሰማይ የሚደርስ መሰላል አለ ። በላዩም በታላቅ ዙፋን ጌታችን ተቀምጧል በዙሪያውም የብዙብዙ አእላፍ መላእክት ያመሰግናሉ ከበታቹም ታላቅ ከይሲ ነበረ በዙፋኑ ላይ የተተመጠውምቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሆይ ለኔ ልጄ ልትሆነኝ ትወዳለህን አለው ። ቴዎድሮስም አቤቱ አንተ ማነህ አለ ጌታችንም እኔ የአብ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ነኝ ለአንተም ስለስሜ ደምህ ይፈስ ዘንድ አለህ አለው ። በዚያንም ጊዜ ከቆሙት አንዱ ወሰደውና በእሳት ባሕርሦስት ጊዜ አጠመቀው ሁለመናውም በመንበሩ ዙሪያ እንደቆሙት ሆነ ። ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ጌታችንን ከወዳጄ ከለውንድዮስ መለየት አልሻም አለው ጌታም እንዲህብሎ መለሰለት እርሱ ብቻ አይደለም ለቀቶ*ዝ ሰራዊት መኮነን የሆነ ኒቆሮስም ነው እንጂ ።ከዚህም በኋላ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ አየ እነዚያ መላእክትም ለውንድዮስንና ኒቆሮስንአጠመቋቸው ከእሳት ባሕር ውስጥ አጠመቋቸውና እነርሱን ለቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሰጡትከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ራእይን እንዳየ ለለውንድዮስ ነገረው ፈጽሞ ደስ ብሏቸው እርስበርሳቸው ተሳሳሙ ። ከዚህም በኋላ የቁዝ የሠራዊት አለቃ ኒቆሮስ ወዳለበት የእግዚአብሔር ኃይል ተሸከመቻቸውእርሱም በደስታ ተቀብሎ አስቀድሞ እንደሚያውቃቸው አቅፎ ሳማቸው እነርሱም እንዳዩትያንን ራእይ ነገራቸው እጅግም አደነቁ ኒቆሮስም ቴዎድሮስ በናድሌዎስን እኔንና ወንድሜለወንድዮስን ለአንተ በእጅህ እንደሰጡን ወንድሜ ሆይ ዕወቅ አለው ። ከዚህም በኋላ በዚያን ጊዜ ወደ ሠራዊቶቻቸው መጡ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስክርስቶስ ስለ ስሙ ደማቸውን ሊአፈሱ ተስማሙ ። ከንጉሠ ቁዝ እንዴት ዕርቅ እንዳደረገሊጠይቀው ያን ጊዜ ንጉሥ ወደ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ላከ ዲዮቅልጥያኖስ ጌታን ኢየሱስክርስቶስን ክዶ ጣዖታትን በአመለከ ጊዜ ስለዚህ የጐ-ዝ ሰዎች እጅግ ደስ ብሏቸዋልና ።የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ሠራዊቱን ነፍሱን ከሰይፍ ሊያድን የሚወድ ወደ ፈለገው ይሒድየክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ግን መጋደልን የሚሻ ከእኛ ጋር ይኑርአላቸው ። ሁሉም በታላቅ ድምፅ አንተ የምትሞትበትን ሞት እኛ ከአንተ ጋራ እንሞታለንአምላክህም አምላካችን ነው ብለው ጮኹ የተመሰገነ ቴዎድሮስም ዳግመኛ ነገራችሁ እውነትከሆነ ሁላችሁም ወደዚህ ወንዝ ወርዳችሁ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሦስት ጊዜተጠመቁ አላቸው ። በዚያንም ጊዜ ልብሳቸውን አውልቀው ወደ ወንዙ ወርደው እንዳላቸውም ተጠመቁ ከውኃውምሲወጡ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃልን ሰሙ ምስክሮቼ በርቱ ጽኑ አሸናፊዎችም ሁኑ እኔከእናንተ ጋር እኖራለሁና ።
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው በዚች ቀን እስራኤል ወደ ተባለ ያዕቆብ እግዚአብሔር ልኮታልና ከወንድሙ ከኤሳውም ፈርቶ ሳለ አዳነው ። ዮርዳኖስንም አሻግሮት ወደ እናቱ ወንድም ወደ ላባ ሔደ ። እርሱም ሁለቱን ልጆቹን ልያንና ራጌልን አጋባው ከዚህም በኋላ ከብዙ ገንዘቡና ከልጆቹ ጋር መንገዱን እየጠረገና እያቀና በሰላም በጤና ወደ አገሩ መለሰው ወንድሙ ኤሳውም በፍቅር በሰላም ተቀበለው ስለዚህም የሊቀ መላእክት ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ሆነ ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ መልአክ አማላጅነት ይማረን ለዘላለሙ አሜን ። አርኬ ሰላም ለከ ሚካኤል አሐዱ ። እምነ ሊቃናት ልዑላን ለእግዚአብሔር ጸማዱ ። አመ ተፈኖከ ትኩን ረድኤተ ቴዎድሮስ ጊዜ መራዱ ። ከመ ቄጽል እምነፋስ ሰብአ ሞዝ ርዕዱ ። ሶበ መጥባሕተከ ነጸሩ በእዱ ።✝️ ቃና_ዘገሊላ
በዚችም ቀን የክብር ባለቤት ጌታችንና ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በሆነች በቃና በሠርግ ቤት የሠራው የተአምራቱ መታሰቢያ ይደረግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሠሩ ። ቅዱስ ወንጌል እንደ ተናገረ ይህች የተአምራቱ መጀመሪያ ናት ውኃውን ለውጦ መዓዛው የሚጥም ጣፋጭ ወይን አድርጎታልና ። በዚህም አሳዳሪው ምስክር ሆነ ሙሽራውን በጠራው ጊዜ ሰው ሁሉ መልካሙን ጠጅ አስቀድሞ ያጠጣል ከሰከሩም በኋላ ዝቅተኛውን ያጠጣል ። አንተ ግን የተሻለውን ጠጅ ወደ ኋላ አቆይተህ አጠጣህ አለው ። ጌትነቱንም ገለጠ ደቀ መዛሙርቱም አመኑበት ። ለርሱም ከቸር አባቱ መሐሪና ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን ። አምላከ ቅዱሳን ወይነ ቃና ፍቅሩን ያሳድርብን ። ከድንግል እናቱ ምልጃና ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን። አርኬ ሰላም ለሑረትከ ውስተ ቤተ ከብካብ በፍቅር ። ከመ ታውይን ማየ እግዚአብሔር ። ዝንቱ ኃይልከ ዘበኅቤነ መንክር ። ለከሰ አልቦ ዘይሰአነከ ግብር ። እስመ ገባሪሆሙ አንተ ለሰማይ ወምድር ። ቃና ዘገሊላ በቀጥታ ትርጉም የገሊላዋ ቃና ማለት ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስተምህሮ በጥምቀት በዓል ማግስት(ጥር 12) ቀን የቃና ዘገሊላ በዓል ይከበራል፡፡ ይህ በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ በድምቀት የሚከበር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዳራ ያለው በዓል ነው፡፡ በዓሉ ቃና ዘገሊላ የሚል ስያሜ ያገኘው ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ የገሊላ ሀገር ክፍል በምትሆን ቃና በተባለችው ቦታ በፈፀመው ተአምር መነሻነት ነው፡፡ የቃና ዘገሊላ ጥንተ ነገሩ ወይም ታሪኩ የተፈፀመው የካቲት 23 ቀን ነው፡፡ ነገር ግን አባቶቻችን የውኃን በዓል ከውኃ በዓል ጋር ለማክበር ብለው የየካቲቱን በዓል ወደ ጥር 12 አምጥተውታል፡፡ ይህም ውኃ ወደ ወይን የተለወጠበትን በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ለማስተሣሠር ለማስኬድ ነው፡፡ በመሆኑም የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር 12 ቀን ይከበራል፡፡ በቃና_ዘገሊላ_ምን_ተፈፀመ? ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በምትሆን በቃና በተደረገ ሠርግ ላይ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር ተገኝቶ ነበር፡፡ ‹‹ወሀለወት ህየ እሙ ለእግዚእ ኢየሱስ›› ‹‹የ ጌታ_የኢየሱስ እናትም በዚያ ነበረች›› እንዳለ ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ (ዮሐ 2÷1) እመቤታችን ለሠርገኞቹ ዘመድ ነበረችና ከልጇ ከወዳጇ ከ ኢየሱስ_ክርስቶስ በሰርጉ ላይ ታድማ ነበር፡፡ እናትን ጠርቶ ልጅን መተው ሥርዓት ስላልሆነ፤ በተጨማሪ ደግሞ ደቀ መዛሙርቱ ከ ጌታ ጋር በሰርጉ ታድመዋል፡፡ ይህም መምህርን ጠርቶ ደቀ መዛሙርቱን መተው ሥርዓት ስላልሆነ (ተገቢ ስላልሆነ) ነው፡፡ የሠርጉ ሥነ-ሥርዓት በሠመረ ባማረ ሁኔታ እየተከናወነ ሳለ ድንገት የወይን ጠጅ አለቀ፡፡ አስተናባሪዎቹ በጭንቀት ባሕር ሰጥመው ምን እንደሚያደርጉ ግራ በገባቸው በጠበባቸው ጊዜ የችግር ጊዜ ደራሽ የኃዘን ጊዜ አፅናኝ የሆነችው የአምላክ እናት ድንግል ማርያም ቅዱስ ገብርኤል እንደተናገረ በፀጋ የተሞላች ናትና (ሉቃ 1÷28) ማንም ሳይነግራት የልቦናቸውን ጭንቀት አይታ፣ ጎዶሎአቸውን ተመልክታ ወደ ልጇ ወደ ወዳጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘወር ብላ ‹‹ወይንኬ አልቦሙ›› ‹‹ወይን ጠጅ እኮ አልቆባቸዋል›› አለችው፡፡ እርሱም መልሶ ‹‹አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?›› ‹‹ጊዜዬ ገና አልደረሰም›› አላት፡፡ እመቤታችንም ለአገልጋዮቹ ‹‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ›› አለቻቸው፡፡ ጌታም በቦታው የነበሩ ስድስት ጋኖች ውኃ ሞልተው እንዲያመጡ አዘዛቸው፡፡ ውኃውንም ወደ ወይን ለውጦ ለሊቀ ምርፋቅ (ለአሳዳሪው) እንዲሠጡት አዘዘ፡፡ አሳዳሪውም ወደ ወይን የተለወጠውን ውኃ በቀመሰ ጊዜ አደነቀ፡፡ ከወዴት እንደመጣ ስላላወቀ ሙሽራውን ‹‹ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል ከሰከሩም በኋላ መናኛውን ያቀርባል አንተ ግን መልካሙን እስከ አሁን አቆይተሃል›› አለው፡፡ ወይኑም በሰው እጅ ያይደለ በሠማያዊው አባት የተዘጋጀ ስለነበር ጣፋጭ እና ልብን የሚያስደስት ነበር፡፡ ‹‹አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?›› ይህንን የ ጌታችንን ንግግር ብዙዎች በዘመናችን ሲሣሣቱበት ይታያል ፡፡ ክብር ይግባውና አምላካችን ይህንን የተናገረው እናቱን ሊያቃልል ሽቶ አይደለም፡፡ ስለሆነም ከመጽሐፍ ቅዱስ አንፃር ይህን አረፍተ ነገር መመልከቱ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ በተናጠል ስንመለከት ‹‹አንቺ ሴት›› ሴት የሚል ቃል የፆታ መጠሪያ ነውና በፆታዋ አክብሮ ሲጠራት ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሔዋን ከአዳም በተፈጠረች ጊዜ አዳም እንዲህ ሲል ተናግሮ ነበር ‹‹ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት ሥጋም ከሥጋዬ ናት እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል›› (ዘፍ 2÷23) በመሆኑም ጌታ አንቺ ሴት ማለቱ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋ ነፍስ መንሣቱን ለማጠየቅ ነው፡፡ ‹‹ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?›› የሚለውን ዐረፍተ ነገር የንቀት ስለመሰለን ብቻ ‘ የዳቦ መልክ የያዘ ድንጋይ፤ ዳቦ ነው እንደማይባል’ የንቀት ንግግር ነው ልንል አይገባም፡፡ ጌታም እንዲህ ሲል ውኃውን ወይን አድርግላቸው ብትይኝ አላደርግም እልሽ ዘንድ ከአንቺ ጋር ምን ፀብ አለኝ ማለቱ ነው፡፡ ይህ ንግግር በመጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ቦታ ተጽፎ እንደሚገኘው በዕብራውያን ዘንድ የተለመደ የአነጋገር ዘይቤ ነው፡፡ ለአብነት ይሆን ዘንድ ጥቂት ጥቅሶችን ከመጽሐፍ ቅዱስ እንመልከት፡- ➛የሰራፕታዋ ሴት በ 1ነገ 17÷18 ላይ እንደምናገኘው ልጇ በሞተባት ጊዜ ቅዱስ ኤልያስን በሐዘን በለቅሶ እንዲህ ብላ ነበር ‹‹የ እግዚአብሔር ሰው ሆይ ከአንተ ጋር ምን አለኝ?›› ትወልጃለሽ ብለህ የወለድኩት ልጅ ምን በድዬህ ምንስ አስከፍቼህ ሞተብኝ? ስትል ነው እንጂ አባባሏ የንቀት ወይም የማቃለል አይደለም፡፡📖 ቀጣይ ክፍል ይከተላል...
ጥር 12፣ 2018 ዓ.ም.
🗓️ ግሪጎሪያን: 19/01/2026
═══════════════════════════════
💭 የዕለቱ ጥቅስ:
"እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፥ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።" 📖 1ኛ ዮሐንስ 4:16📖 ግጽዌ - የዕለቱ ንባብ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌 ሮሜ 9
¹-² ብዙ ኀዘን የማያቋርጥም ጭንቀት በልቤ አለብኝ ስል በክርስቶስ ሆኜ እውነትን እናገራለሁ፤ አልዋሽምም፤ ሕሊናዬም በመንፈስ ቅዱስ ይመሰክርልኛል።³ በሥጋ ዘመዶቼ ስለ ሆኑ ስለ ወንድሞቼ ከክርስቶስ ተለይቼ እኔ ራሴ የተረገምሁ እንድሆን እጸልይ ነበርና።⁴ እነርሱ እስራኤላውያን ናቸውና፥ ልጅነትና ክብር ኪዳንም የሕግም መሰጠት የመቅደስም ሥርዓት የተስፋውም ቃላት ለእነርሱ ናቸውና፤⁵ አባቶችም ለእነርሱ ናቸውና፤ ከእነርሱም ክርስቶስ በሥጋ መጣ፥ እርሱም ከሁሉ በላይ ሆኖ ለዘላለም የተባረከ አምላክ ነው፤ አሜን።⁶ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል የተሻረ አይደለም። እነዚህ ከእስራኤል የሚወለዱ ሁሉ እስራኤል አይደሉምና፤ የአብርሃምም ዘር ስለሆኑ ሁላቸው ልጆች አይደሉም፥⁷ ነገር ግን፦ በይስሐቅ ዘር ይጠራልሃል ተባለ።⁸ ይህም፥ የተስፋ ቃል ልጆች ዘር ሆነው ይቆጠራሉ እንጂ እነዚህ የሥጋ ልጆች የሆኑ የእግዚአብሔር ልጆች አይደሉም ማለት ነው።⁹ ይህ፦ በዚህ ጊዜ እመጣለሁ ለሳራም ልጅ ይሆንላታል የሚል የተስፋ ቃል ነውና።¹⁰ ይህ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ርብቃ ደግሞ ከአንዱ ከአባታችን ከይስሐቅ በፀነሰች ጊዜ፥¹¹ ልጆቹ ገና ሳይወለዱ፥ በጎ ወይም ክፉ ምንም ሳያደርጉ፥ ከጠሪው እንጂ ከሥራ ሳይሆን በምርጫ የሚሆን የእግዚአብሔር አሳብ ይጸና ዘንድ፥¹² ለእርስዋ፦ ታላቁ ለታናሹ ይገዛል ተባለላት።¹³ ያዕቆብን ወደድሁ ኤሳውን ግን ጠላሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።¹⁴ እንግዲህ ምን እንላለን? በእግዚአብሔር ዘንድ ዓመፃ አለ ወይ? አይደለም።¹⁵ ለሙሴ፦ የምምረውን ሁሉ እምረዋለሁ ለምራራለትም ሁሉ እራራለታለሁ ይላልና።¹⁶ እንግዲህ ምሕረት ለወደደ ወይም ለሮጠ አይደለም፥ ከሚምር ከእግዚአብሔር ነው እንጂ።¹⁷ መጽሐፍ ፈርዖንን፦ ኃይሌን በአንተ አሳይ ዘንድ ስሜም በምድር ሁሉ ይነገር ዘንድ ለዚህ አስነሣሁህ ይላልና።📌 ይሁዳ 1
⁹ የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር፦ ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።¹⁰ እነዚህ ግን የማያውቁትን ሁሉ ይሳደባሉ፥ አእምሮም እንደሌላቸው እንስሶች በፍጥረታቸው በሚያውቁት ሁሉ በእርሱ ይጠፋሉ።¹¹ ወዮላቸው፥ በቃየል መንገድ ሄደዋልና ስለ ደመወዝም ለበለዓም ስሕተት ራሳቸውን አሳልፈው ሰጥተዋል በቆሬም መቃወም ጠፍተዋል።¹² እነዚህ ከእናንተ ጋር ሲጋበዙ በፍቅር ግብዣችሁ እንደ እድፍ ናቸው፤ እንደ እረኞች ያለ ፍርሃት ራሳቸውን ይጠብቃሉ፤ በነፋስ የተወሰዱ ውኃ የሌለባቸው ደመናዎች፥ ፍሬ የማያፈሩ ሁለት ጊዜ የሞቱ ከነሥራቸው የተነቀሉ በበጋ የደረቁ ዛፎች፥¹³ የገዛ ነውራቸውን አረፋ እየደፈቁ ጨካኝ የባሕር ማዕበል፥ ድቅድቅ ጨለማ ለዘላለም የተጠበቀላቸው የሚንከራተቱ ከዋክብት ናቸው።📌 ሐዋርያት 10
³⁴-³⁵ ጴጥሮስም አፉን ከፍቶ እንዲህ አለ፦ እግዚአብሔር ለሰው ፊት እንዳያደላ ነገር ግን በአሕዛብ ሁሉ እርሱን የሚፈራና ጽድቅን የሚያደርግ በእርሱ የተወደደ እንደ ሆነ በእውነት አስተዋልሁ።³⁶ የሁሉ ጌታ በሚሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እየሰበከ ይህን ቃል ወደ እስራኤል ልጆች ላከ።³⁷ ዮሐንስ ከሰበከው ጥምቀት በኋላ ከገሊላ ጀምሮ በይሁዳ ሁሉ የሆነውን ነገር እናንተ ታውቃላችሁ።³⁸ እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤³⁹ እኛም በአይሁድ አገርና በኢየሩሳሌም ባደረገው ነገር ሁሉ ምስክሮች ነን፤ እርሱንም በእንጨት ላይ ሰቅለው ገደሉት።📌 ምስባክ
ወምስካይነ አምላኩ ለያዕቆብ። ንዑ ትርእዩ ግብሮ ለእግዚአብሔር። ዘገብረ መንክር ወዲበ ምድር።📌 ትርጉም
የሠራዊት ጌታ ከእኛ ጋር ነው፤ የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። የእግዚአብሔርን ሥራ፥ በምድር ያደረገውንም ተኣምራት እንድታዩ ኑ። መዝ.45÷7-8📌 ወንጌል ዮሐንስ 1
⁴⁴ በነገው ኢየሱስ ወደ ገሊላ ሊወጣ ወደደ፥ ፊልጶስንም አገኘና፦ ተከተለኝ አለው።⁴⁵ ፊልጶስም ከእንድርያስና ከጴጥሮስ ከተማ ከቤተ ሳይዳ ነበረ።⁴⁶ ፊልጶስ ናትናኤልን አግኝቶ፦ ሙሴ በሕግ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል አለው።⁴⁷ ናትናኤልም፦ ከናዝሬት መልካም ነገር ሊወጣ ይችላልን? አለው። ፊልጶስ፦ መጥተህ እይ አለው።⁴⁸ ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ፦ ተንኰል የሌለበት በእውነት የእስራኤል ሰው እነሆ አለ።⁴⁹ ናትናኤልም፦ ከወዴት ታውቀኛለህ? አለው። ኢየሱስም መልሶ፦ ፊልጶስ ሳይጠራህ፥ ከበለስ በታች ሳለህ፥ አየሁህ አለው።⁵⁰ ናትናኤልም መልሶ፦ መምህር ሆይ፥ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ፤ አንተ የእስራኤል ንጉሥ ነህ አለው።⁵¹ ኢየሱስም መልሶ፦ ከበለስ በታች አየሁህ ስላልሁህ አመንህን? ከዚህ የሚበልጥ ነገር ታያለህ አለው።⁵² እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው።📌 ቅዳሴ
ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ ነው።
አምላካችን ሆይ፣ በዚህ ቀን የምንነበውን ቃልህ በልባችን እንድናስቀምጥ እና በሕይወታችን እንድንተገብር እርዳን። አሜን።📱 ቦት: @gitsawebot 📺 ቻናል: https://t.me/religious_books_lover 🌐 ድህረ ገጽ: https://gitsawe-tailwind-2019.vercel.app/ 🕊️ ሰላም ይሁንላችሁ!
1. ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ (ፍልሠቱ)📌 ወርኀዊ በዓላት
1. የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት 2. ቅድስት አርሴማ ድንግል📖1ኛ ዼጥ 5፥3
✍️ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማሕበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ፤ እንዲሁም ጐበዞች ሆይ! ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል
ጥር 11፣ 2018 ዓ.ም.
🗓️ ግሪጎሪያን: 18/01/2026
═══════════════════════════════
💭 የዕለቱ ጥቅስ:
"እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፥ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።" 📖 1ኛ ዮሐንስ 4:16📖 ግጽዌ - የዕለቱ ንባብ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌 ቲቶ 3
⁴ ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥⁵ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤⁶-⁷ ያን መንፈስም፥ በጸጋው ጸድቀን በዘላለም ሕይወት ተስፋ ወራሾች እንድንሆን፥ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በእኛ ላይ አትርፎ አፈሰሰው።⁸ ቃሉ የታመነ ነው። እግዚአብሔርንም የሚያምኑት በመልካም ሥራ በጥንቃቄ እንዲጸኑ፥ እነዚህን አስረግጠህ እንድትናገር እፈቅዳለሁ። ይህ መልካምና ለሰዎች የሚጠቅም ነው፤📌 1ኛ ዮሐንስ 5
⁵ ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው?⁶ በውኃና በደም የመጣ ይህ ነው እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ፤ በውኃውና በደሙ እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም።⁷ መንፈስም እውነት ነውና የሚመሰክረው መንፈስ ነው።⁸ የሚመሰክሩት መንፈሱና ውኃው ደሙም ሦስት ናቸውና፤ ሦስቱም በአንድ ይስማማሉ።⁹ የሰውን ምስክር ብንቀበል የእግዚአብሔር ምስክር ከእርሱ ይልቅ ይበልጣል፤ ስለ ልጁ የመሰከረው የእግዚአብሔር ምስክር ይህ ነውና።¹⁰ በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን በነፍሱ ምስክር አለው፤ በእግዚአብሔር የማያምን እግዚአብሔር ስለ ልጁ የመሰከረውን ምስክር ስላላመነ ሐሰተኛ አድርጎታል።¹¹ እግዚአብሔርም የዘላለምን ሕይወት እንደ ሰጠን ይህም ሕይወት በልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው።¹² ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።¹³ የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ።📌 ሐዋርያት 10
³⁴-³⁵ ጴጥሮስም አፉን ከፍቶ እንዲህ አለ፦ እግዚአብሔር ለሰው ፊት እንዳያደላ ነገር ግን በአሕዛብ ሁሉ እርሱን የሚፈራና ጽድቅን የሚያደርግ በእርሱ የተወደደ እንደ ሆነ በእውነት አስተዋልሁ።³⁶ የሁሉ ጌታ በሚሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እየሰበከ ይህን ቃል ወደ እስራኤል ልጆች ላከ።³⁷ ዮሐንስ ከሰበከው ጥምቀት በኋላ ከገሊላ ጀምሮ በይሁዳ ሁሉ የሆነውን ነገር እናንተ ታውቃላችሁ።³⁸ እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤³⁹ እኛም በአይሁድ አገርና በኢየሩሳሌም ባደረገው ነገር ሁሉ ምስክሮች ነን፤ እርሱንም በእንጨት ላይ ሰቅለው ገደሉት።📌 ምስባክ
ርእዩከ ማያት እግዚኦ። ርእዩከ ማያት ወፈርሁ። ደንገፁ ቀላያተ ማያት ወደምፀ ማያቲሆሙ።📌 ትርጉም
አቤቱ፥ ውኆች አዩህ፥ ውኆችም አይተውህ ፈሩ፤ ጥልቆች ተነዋወጡ፥ ውኆችም ጮኹ። ደመኖች ድምፅን ሰጡ፥ ፍላጾችህም ወጡ። መዝ.76÷16-17📌 ወንጌል ሉቃስ 3
²¹ ሕዝቡም ሁሉ ከተጠመቁ በኋላ ኢየሱስ ደግሞ ተጠመቀ። ሲጸልይም ሰማይ ተከፈተ፥²² መንፈስ ቅዱስም በአካል መልክ እንደ ርግብ በእርሱ ላይ ወረደ፤ የምወድህ ልጄ አንተ ነህ፥ በአንተ ደስ ይለኛል የሚል ድምፅም ከሰማይ መጣ።²³ ኢየሱስም ሊያስተምር ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ያህል ሆኖት ነበር እንደመሰላቸው የዮሴፍ ልጅ ሆኖ፥ የኤሊ ልጅ፥²⁴ የማቲ ልጅ፥ የሌዊ ልጅ፥ የሚልኪ ልጅ፥²⁵ የዮና ልጅ፥ የዮሴፍ ልጅ፥ የማታትዩ ልጅ፥ የአሞጽ ልጅ፥ የናሆም ልጅ፥ የኤሲሊም ልጅ²⁶ የናጌ ልጅ፥ የማአት ልጅ፥ የማታትዩ ልጅ የሴሜይ ልጅ፥ የዮሴፍ ልጅ፥²⁷ የዮዳ ልጅ፥ የዮናን ልጅ፥ የሬስ ልጅ፥ የዘሩባቤል ልጅ፥ የሰላትያል ልጅ፥ የኔሪ ልጅ፥²⁸ የሚልኪ ልጅ፥ የሐዲ ልጅ፥ የዮሳስ ልጅ፥ የቆሳም ልጅ፥ የኤልሞዳም ልጅ፥ የኤር ልጅ፥²⁹ የዮሴዕ ልጅ፥ የኤልዓዘር ልጅ የዮራም ልጅ፥ የማጣት ልጅ፥ የሌዊ ልጅ፥³⁰ የስምዖን ልጅ፥ የይሁዳ ልጅ፥ የዮሴፍ ልጅ፥³¹ የዮናን ልጅ፥ የኤልያቄም ልጅ፥ የሜልያ ልጅ፥ የማይናን ልጅ፥ የማጣት ልጅ፥ የናታን ልጅ³² የዳዊት ልጅ፥ የእሴይ ልጅ፥ የኢዮቤድ ልጅ፥ የቦዔዝ ልጅ፥ የሰልሞን ልጅ፥³³ የነአሶን ልጅ፥ የአሚናዳብ ልጅ፥ የአራም ልጅ፥ የአሮኒ ልጅ፥ የኤስሮም ልጅ፥³⁴ የፋሬስ ልጅ፥ የይሁዳ ልጅ፥ የያዕቆብ ልጅ፥ የይስሐቅ ልጅ፥ የአብርሃም ልጅ፥ የታራ ልጅ፥³⁵ የናኮር ልጅ፥ የሴሮህ ልጅ፥ የራጋው ልጅ፥ የፋሌቅ ልጅ፥ የአቤር ልጅ፥ የሳላ ልጅ፥³⁶ የቃይንም ልጅ፥ የአርፋክስድ ልጅ፥ የሴም ልጅ፥ የኖኅ ልጅ፥ የላሜህ ልጅ፥³⁷ የማቱሳላ ልጅ፥ የሄኖክ ልጅ፥ የያሬድ ልጅ፥³⁸ የመላልኤል ልጅ፥ የቃይናን ልጅ፥ የሄኖስ ልጅ፥ የሴት ልጅ፥ የአዳም ልጅ፥ የእግዚአብሔር ልጅ።📌 ቅዳሴ
ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው።
Reviews channel
2 total reviews
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️» is a Telegram channel in the category «Религия и духовность», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 5.2K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 27.4, with 2 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.2 ₽, and with 5 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий