
- Main
- Catalog
- Religion & Spirituality
- Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️»
Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️»
በዚህ channel ውስጥ መንፈሳዊ መጻሕፍትንና የየዕለቱን ስንክሳር ያገኛሉ።
Channel statistics
¹⁰ በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ። ¹¹ የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ። ¹² መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ። ¹³ ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ። ¹⁴-¹⁵ እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤ ¹⁶ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤ ¹⁷ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው። ¹⁸ በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤ይሁዳ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ቀድሞ የተነገረውን ቃል አስቡ፤ ¹⁸ እነርሱ፦ በመጨረሻው ዘመን በኃጢአተኝነት እንደ ገዛ ምኞታቸው እየሄዱ ዘባቾች ይሆናሉ ብለዋችኋልና። ¹⁹ እነዚህ የሚያለያዩ ሥጋውያንም የሆኑ መንፈስም የሌላቸው ሰዎች ናቸው። ²⁰ እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ፥ ²¹ ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ። ²² አንዳንዶች ተከራካሪዎችንም ውቀሱ፥ አንዳንዶችንም ከእሳት ነጥቃችሁ አድኑ፥ ²³ አንዳንዶችንም በሥጋ የረከሰውን ልብስ እንኳ እየጠላችሁ በፍርሃት ማሩ። ²⁴ ሳትሰናከሉም እንዲጠብቃችሁ፥ በክብሩም ፊት በደስታ ነውር የሌላችሁ አድርጎ እንዲያቆማችሁ ለሚችለው ²⁵ ብቻውን ለሆነ አምላክና መድኃኒታችን ከዘመን ሁሉ በፊት አሁንም እስከ ዘላለምም ድረስ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ግርማ ኃይልም ሥልጣንም ይሁን፤ አሜን።ሐዋርያት 28 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በደኅና ከደረስን በኋላ በዚያን ጊዜ ደሴቲቱ መላጥያ እንድትባል አወቅን። ² አረማውያንም የሚያስገርም ቸርነት አደረጉልን፤ ዝናብ ስለ ሆነም ስለ ብርዱም እሳት አንድደው ሁላችንን ተቀበሉን። ³ ጳውሎስ ግን ብዙ ጭራሮ አከማችቶ ወደ እሳት ሲጨምር እፉኝት ከሙቀት የተነሣ ወጥታ እጁን ነደፈችው። ⁴ አረማውያንም እባብ በእጁ ተንጠልጥላ ባዩ ጊዜ፥ እርስ በርሳቸው፦ ይህ ሰው በእርግጥ ነፍሰ ገዳይ ነው፥ ከባሕርም ስንኳ በደኅና ቢወጣ የእግዚአብሔር ፍርድ በሕይወት ይኖር ዘንድ አልተወውም አሉ። ⁵ እርሱ ግን እባቢቱን ወደ እሳት አራገፋት አንዳችም አልጐዳችውም፤ ⁶ እነርሱም፦ ሊያብጥ ወይም ወዲያው ሞቶ ሊወድቅ ነው ብለው ይጠባበቁት ነበር ብዙ ጊዜ ግን ሲጠባበቁ በእርሱ ላይ የሚያስገርም ነገር ምንም ባላዩ ጊዜ፦ ይህስ አምላክ ነው ብለው አሳባቸውን ለወጡ።#ምስባክ
አንተ አጽናዕካ ለባሕር ለኃይልከ። ወአንተ ሰበርከ ርእሰ ከይሲ በውስተ ማይ ወአንተ ቀጥቀጥከ አርእስቲሁ ለከይሲ።#ትርጉም፦
አንተ ባሕርን በኃይልህ አጸናሃት፤ አንተ የእባቦችን ራስ በውኃ ውስጥ ሰበርህ። አንተም የዘንዶውን ራሶች ቀጠቀጥህ፤ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው።መዝ.73÷13-14 #ወንጌል 📖👇 ማርቆስ 16 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ኋላም በማዕድ ተቀምጠው ሳሉ ለአሥራ አንዱ ተገለጠ፥ ተነሥቶም ያዩትን ስላላመኑአቸው አለማመናቸውንና የልባቸውን ጥንካሬ ነቀፈ። ¹⁵ እንዲህም አላቸው፦ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ¹⁶ ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። ¹⁷ ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥ ¹⁸ የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ። ¹⁹ ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ።✝️ ቅዳሴ #ዮሐንስ (ኀቤከ) ነው።
¹⁷ እንግዲህ አሕዛብ ደግሞ በአእምሮአቸው ከንቱነት እንደሚመላለሱ ከእንግዲህ ወዲህ እንዳትመላለሱ እላለሁ በጌታም ሆኜ እመሰክራለሁ። ¹⁸ እነርሱ ባለማወቃቸው ጠንቅ በልባቸውም ደንዳንነት ጠንቅ ልቡናቸው ጨለመ፥ ከእግዚአብሔርም ሕይወት ራቁ፤ ¹⁹ ደንዝዘውም በመመኘት ርኵሰትን ሁሉ ለማድረግ ራሳቸውን ወደ ሴሰኝነት አሳልፈው ሰጡ። ²⁰ እናንተ ግን ክርስቶስን እንደዚህ አልተማራችሁም፤ ²¹ በእርግጥ ሰምታችሁታልና፥ እውነትም በኢየሱስ እንዳለ በእርሱ ተምራችኋል፤ ²² ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥ ²³ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ ²⁴ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ። ²⁵ ስለዚህ ውሸትን አስወግዳችሁ፥ እርስ በርሳችን ብልቶች ሆነናልና እያንዳንዳችሁ ከባልንጀሮቻችሁ ጋር እውነትን ተነጋገሩ። ²⁶ ተቆጡ ኃጢአትንም አታድርጉ፤ ²⁷ በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፥ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት። ²⁸ የሰረቀ ከእንግዲህ ወዲህ አይስረቅ፥ ነገር ግን በዚያ ፈንታ ለጎደለው የሚያካፍለው እንዲኖርለት በገዛ እጆቹ መልካምን እየሠራ ይድከም። ²⁹ ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ። ³⁰ ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ። ³¹ መራርነትና ንዴት ቁጣም ጩኸትም መሳደብም ሁሉ ከክፋት ሁሉ ጋር ከእናንተ ዘንድ ይወገድ። ³² እርስ በርሳችሁም ቸሮችና ርኅሩኆች ሁኑ፥ እግዚአብሔርም ደግሞ በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ ይቅር ተባባሉ።ይሁዳ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያት ቀድሞ የተነገረውን ቃል አስቡ፤ ¹⁸ እነርሱ፦ በመጨረሻው ዘመን በኃጢአተኝነት እንደ ገዛ ምኞታቸው እየሄዱ ዘባቾች ይሆናሉ ብለዋችኋልና። ¹⁹ እነዚህ የሚያለያዩ ሥጋውያንም የሆኑ መንፈስም የሌላቸው ሰዎች ናቸው። ²⁰ እናንተ ግን፥ ወዳጆች ሆይ፥ ከሁሉ ይልቅ በተቀደሰ ሃይማኖታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ እየተጋችሁ በመንፈስ ቅዱስም እየጸለያችሁ፥ ²¹ ወደ ዘላለም ሕይወት የሚወስደውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት ስትጠባበቁ በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ። ²² አንዳንዶች ተከራካሪዎችንም ውቀሱ፥ አንዳንዶችንም ከእሳት ነጥቃችሁ አድኑ፥ ²³ አንዳንዶችንም በሥጋ የረከሰውን ልብስ እንኳ እየጠላችሁ በፍርሃት ማሩ።ሐዋርያት 20 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁸ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ²⁹-³⁰ ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ፥ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሡ እኔ አውቃለሁ። ³¹ ስለዚህ ሦስት ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሠጽ እንዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ።#ምስባክ 👇 ሣህሉ #ለእግዚአብሔር መልዐ ምድረ። ወበቃለ #እግዚአብሔር ጸንዐ ሰማያት። ወእምእስትንፋስ አፉሁ ኵሉ ኃይሎሙ።
ጽድቅንና ፍርድን ይወድዳል፤ የ #እግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች። በ #እግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ።መዝ.32÷5-6 #ወንጌል 📖👇 ዮሐንስ 15 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁶ ዳሩ ግን እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል፤ ²⁷ እናንተም ደግሞ ከመጀመሪያ ከእኔ ጋር ኖራችኋልና ትመሰክራላችሁ። #ቅዳሴ #ሠለስቱ_ምዕት_ቅዳሴ ነው።
ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀዪቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል። እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ። ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውና ያጻፈውም ከግዕዝ ወደ አማርኛ የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን።
አምላካችን ሆይ፣ በዚህ ቀን የምንነበውን ቃልህ በልባችን እንድናስቀምጥ እና በሕይወታችን እንድንተገብር እርዳን። አሜን አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ...።═══════════════════════════════════════════════════ 📱 ቦት: @gitsawebot 📺 ቻናል: https://t.me/religious_books_lover 🌐 ድህረ ገጽ: https://gitsawe-tailwind-2019.vercel.app/ 🕊️ ሰላም ይሁንላችሁ!
❖ በዚችም ዕለት ተገዳይ የሆነ መነኰስ የከበረ አክርስጥሮስ አረፈ፤ ይህም አባት በዮርዳኖስ ገዳም የሚኖር ነበር ከመነኰሳቱም አንዱ እየሰገደ እንዲህ ብሎ ጠየቀው አባቴ አክርስጥሮስ ሆይ ከእኔ ጋር ፍቅርን አደርግ እጠቀምበትም ዘንድ ሥራህን ሁሉ ንገረኝ አለው። ❖ ሽማግሌው አክርስጥሮስም እንዲህ ብሎ መለሰለት ልጄ ሆይ ግልማሳ ሆኜ ሳለ በመነኰስኩ ጊዜ በዚያ እጸልይ ዘንድ በሌሊት ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ መቅደስ እሔድ ነበር። ❖ ዐሥራ ሁሉት ደረጃዎችም አሏት በየአንዳንዱም ደረጃ መቶ መቶ ስግደቶችን እሰግዳለሁ ደወልንም በሚደውሉ ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመግባት ከወንድሞች ጋር የማኅበሩን የጸሎት ሥርዓት እፈጽማለሁ እንዲሁም በማድረግ ዐሥር ዓመት ኖርኩ። ❖ ከሌሊቶችም በአንዲቱ የተለመደ ጸሎቴን ከፈጸምኩ በኋላ ልቡናዬ በተመሥጦ ተማረከ ነጫጭ ልብሶችን የለበሱ ሁለት ሰዎች መቅረዞችን ሲያበሩ እኩሌቶቹ ሲበሩ እኩሌቶቹም ሲጠፉ አየሁ፤ እኔም ይህ ሥራ ምንድን ነው አልኳቸው እነዚያም አባቶች ባልንጀራውን የሚወድ መቅረዙ የበራለታል አሉኝ እኔም ደግሜ መቅረዜ የቱ ነው አልኋቸው እነርሱም ሒድ ከወንድሞችህ ጋር ተፋቀር እኛ እናበራልሃለን አሉኝ በነቃሁም ጊዜ ማንንም አላገኘሁም። ❖ ከዚህም በኋላ አባ አክርስጥሮስ ብቻውን ወደ ደብረ ሲና ሒዶ በዚያ እየተጋደለ ኀምሳ ዓመት ኖረ ወደርሱም እንዲህ የሚለው ቃል መጣ ከአባቶችህ ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ገዳምህ ተመለስ ከዚህም በኋላ በተመለሰ ጊዜ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።✝️ የመለኮትን ነገር የሚናገር አቡነ ጎርጎርዮስ
❖ በሌላም በኩል ‹‹ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ›› እየተባለም ይጠራል፤ ሀገሩ ቂሳርያ ነው፤ በመጀመሪያ የሕግ ባለሙያ የነበረ ሲሆን በኋላ ግን የቍስጥንጥንያ ሊቀጳጳስ ሆኖ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በሐዋርያነት አገልግሏል፡፡ ❖ በደራሲነቱ ምድራውያን መላእክት ከተሰኙት ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ነው፤ የአምላክን ሰው መሆንና ምሥጢረ ሥላሴን እጅግ አስፍቶና አራቆ ያስተማረ ከመሆኑም በላይ ‹‹ዳግማዊ ዮሐንስ ነባቤ መነኮት›› ተብሎ እስኪጠራ ድረስ በነገረ መለኮት የተራቀቀ ታላቅ ሊቅ መምህር ነው፡፡ ❖ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙን የማይጠቅስ መጽሐፍና መምህር የለም፤ ሃይማኖተ አበው አጥብቆ የሚጠራው የቤተ ክርስቲያናችን መመኪያ ነው፤ የአርመንን ኦርቶዶክስ ያቀና ሲሆን መንበሩን የኖኅ መርከብ ባረፈችበት አራራት ተራራ ላይ ነው የሠራው፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፤ በጸሎቱ ይማረን✝️
በዚችም ዕለት የቅድስት ኦርኒ ማኅበር የሆኑ ዐሥራ ሦስት ሺህ ሰዎች በሰማዕትነት ሞቱ። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። አርኬ ✍️ሰላም ለሚናስ ዘተኀርየ በድልው። ሊቀ ጳጳሳት ይኩን እምኁልቈ አበው። ዕጉሥ በምንዳቤ ወበመናስው። ይትኖለወኒ ትንባሌሁ በውስተ ኵሉ ፍናው። እምኃይለ ጋኔን ዘየሐውር በበድው። በጥር ወር የሚነበብ ምንባብ ደረሰ ተፈፀመ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።📌 ጥር 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ሶፍያና 3ቱ ሰማዕታት ልጆቿ (ጲስጢስ አላዺስና አጋዺስ) 2.ቅድስት ኦርኒ ሰማዕት (በ5 ነገሥታት እጅ የተሰቃየች የሐዋርያው ጢሞቴዎስ ተከታይና ወደ ብሔረ ሕያዋን የተነጠቀች እናት) 3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት 4.አባ አክርስጥሮስ 5.አምስቱ ደናግል ሰማዕታት (ጤቅላ ማርያ ማርታ አበያ ዓመታ) 6.ጻድቃነ ዴጌ (የተሠወሩበት) 7.አባ ሚናስ ሊቀ ዻዻሳት 8.130,000 ሰማዕታት (የቅድስት ኦርኒ ማሕበር)📌 ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ 2.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት 3.አባ ሣሉሲ ክቡር✝️ 📖1ኛ ጴጥ 3፥3
✍️ለእናንተም ጠጉርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጐናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ
❖ በዚችም ቀን ስሙ መርቅያኖስ የሚባል ለጣዖት የሚሰግድ የሮም ንጉሥ ልጅ የከበረች ኦርኒ በሰማዕትነት አረፈች፤ የዚችም ቅድስት እናቷ ክርስቲያናዊት ናት አባቷም እልፍኝ ሠርቶላት በወርቅና በብር ልብሶች ከአጌጡ ዐሥራ ሁለት ደናግል ጋር ወደዚያ አስገባት ከልጁ ጋር ይሰግዱላቸው ዘንድ ዐሥራ ሰባት ጣዖታትን አመጣላቸው በላይዋም በሩን ዘጋ በዚያም ሰባት ዓመት ከስድስት ወር ኖረች። ❖ በአንዲትም ዕለት ዐይኖቿን ወደ ምሥራቅ ቀና በአደረገች ጊዜ ርግብን አየች በአፏም የዘይት ቅጠል ይዛ ነበር ከማዕድዋም ላይ ጥላው ወጣች ዳግመኛም ወደ ምዕራብ ስትመለከት ቊራ መጣ በአፉም ከይሲ ይዞ ነበር ከማዕዷም ላይ ጥሎት ወጣ አደነቀችም። ❖ በዚያንም ጊዜ አባቷ የሰጣት መምህርዋ መጣ ያንንም ራእይ አወራችለት እርሱም ሲተረጉምላት ርግብ የጥበብ ነገር ነው የዘይቱም ቅርንጫፍ በጥምቀት የሚገኝ ክብር ነው ቊራም ንጉሥ ነው ከይሲውም መከራ ነው አንቺም በርቺ ጠንክሪ በክርስቶስ ስም መከራ ትቀበዪ ዘንድ አለሽና የሕይወት አክሊልንም ትቀበያለሽ አላት። ❖ ከዚህም በኋላ በአደገች ጊዜ አባቷና እናቷ ወደርሷ ወጥተው ስለ ጋብቻ ተናገርዋት የከበረች ኦርኒም እስከ ሰባት ቀን ታገሡኝ አለቻቸው ከዚህም በኋላ እርሱ የመረጠውን መንገድ ይመራት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየች። ❖ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ በርቺ ኃይልንም ልበሺ ሐዋርያው ጢሞቴዎስም ወዳንቺ መጥቶ የወንጌልን ትእዛዝ ያሰተምርሻል አላት፤ ወዲያውኑ ጢሞቴዎስ መጥቶ የቤቷን ግድግዳ ሠንጥቆ ወደርሷ ገባ ሁሉንም አስተማራት ከበታቹም ውኃ ፈለቀ በውኃውም ላይ ጸለየና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃትና ከእርሷ ዘንድ ሔደ። ❖ በዚያንም ጊዜ ቅድስት ኦርኒ ተነሥታ የአባቷን ጣዖቶች ሠበረች አባቷና እናቷም በመጡ ጊዜ እንደቀድሞው ስለ ጋብቻ ተናገርዋት እርሷም እኔስ ለሰማያዊ ሙሽራ ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠርቻለሁ በስሙም ተጠምቄአለሁ አለቻቸው። ❖ ንጉሥ አባቷም የልጁን ነገር በሰማ ጊዜ ታላቅ ቊጣን ተመላ ከአዳራሽዋም እየጎተተ አወረዳት እናቷም እያለቀሰች በራስዋም ላይ አመድ እየነሰነሰች ትከተላት ነበር በሰንሰለት ታሥረው የሚቀለቡ አራት ፈረሶችን አምጥተው ከጅራታቸው ላይ ቅድስት ኦርኒን በራስዋ ጠጉር አሥረው እንዲአስጎትቷት ንጉሥ አባቷ አዘዘ። ❖ አንዱ ፈረስም ስንሰለቱን በጥሶ ሲያመልጥ የንጉሡን ቀኝ እጅ ቆረጠውና ወዲያውኑ ወድቆ ሞተ የከበረች ኦርኒም ተነሥታ ጸሎት አደረገችና ንጉሥ አባቷን ከሞት አስነሣችው የተቆረጠ እጁንም እንደቀድሞው መለሰችው ሕዝቡም ይህን ድንቅ ሥራ አይተው ከንጉሥ አባቷ ጋር በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ በእጆቿም ሠላሳ ሽህ ያህል ሰዎች ተጠመቁ። ❖ ንጉሥ ዳኬዎስም ሰምቶ ወደዚያች አገር ገባ የከበረች ኦርኒንም ይዞ በራስዋ ጠጉር ይሰቅሏት ዘንድ አዘዘ ዳግመኛም እባቦችና ጊንጦች ወደ ተመሉበት ጉድጓድ እንዲጨምሩዋት አዘዘ በጨመሩዋትም ጊዜ ሁሉም በእግዚአብሔር ኃይል ሞቱ ደግሞ በመጋዝ እንዲሠነጥቋት አዘዘ መጋዙም ተሠበረ ንጉሡም ሞተ። ❖ የዳኬዎስም ልጁ ሰምቶ መጣ ያቺንም አገር ከበባት ቅድስት ኦርኒንም ይዞ የተሳሉ መርፌዎችንም በእጆቿና በእግሮቿ እንዲሰገስጉ በጀርባዋም ላይ አሻዋ የተመላ ዳውላ አድርገው ከአራት ፈረሶች ላይም አሥረው ሥጋዋ ተበጣጥሶ እስቲጠፋ ድረስ እንዲአስሮጧቸው አዘዘ በዚህም አልቻሏትም፤ ያንንም ከሀዲ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ጦር ወግቶ ገደለው የከበረች ኦርኒም ሃይማኖትን እያስተማረች በሽተኞችን እየፈወሰች ሙታንን እያስነሣች ተቀመጠች። ❖ አራተኛ ንጉሥም መጣ የቅድስት ኦርኒንም ዜና ሰምቶ ወደርሱ አስቀረባትና ለአማልክት ትሠዋ ዘንድ አስገደዳት እምቢ ባለችውም ጊዜ ከእሳት ውስጥ እንዲጨምሩዋት አዘዘ ከእሳትም ውስጥ በደኅና ወጥታ የረከሱ አማልክቶቹን ዘለፈች ንጉሡም ይህን ድንቅ ሥራ አይቶ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። ❖ አምስተኛው የፋርስ ንጉሥ መጣ የከበረች ኦርኒንም ይዞ በእጁ በያዘው ጦር ወጋትና ሞተች ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክም መጥቶ ከሞት አስነሣት በክብር ባለቤትም በክርስቶስ ስም እያስተማረች ወደ ከተማው ውስጥ ገባች ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ተነጥቃ ወጣች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
በዚችም ቀን የመለኮትን ነገር የሚናገር የጎርጎርዮስ መታሰቢያው ነው። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን። አርኬ ✍️ሰላም ለኦርኒ ሠናይተ ዝክር ወስም። ዘበትርጓሜሁ ሰላም። እስመ ኰነንዋ ላቲ በዘዚአሁ ሕማም። በእንተ አውስቦ ሥርዓተ ሥጋ ወደም። ውስተ ሕሊናሃ ኢሦጠት ምክረ አብ ወእም። ✍️ሰላም ለአክርስጥሮስ አመ ሕሊናሁ ተፄወወ። ርሱያነ ልብስ ፀዓዳ ረኪቦ ዕደወ። እምእሉ ዘይቤ ነገረ ምዕዳን ለበወ። በምልዐ ልብከ ተፋቀር አኃወ። ከመ ቀንዲልከ ያስተርኢ ኅትወ። ✍️ሰላም እብል ለብዙኃን አእላፋት። እለ ነጺሮሙ አምኑ ትንሣኤ ኦርኒ እሞት። ወእሉ አኃው ዘእምአሐቲ ጥምቀት። ይሠውሩኒ በጽድቆሙ እምጌጋይ ክሡት። ኃፍረተ ባዕል ፍጹመ ከመ ይሠውር ቤት።✝️ መነኰስ አክርስጥሮስ
❖ በዚችም ዕለት የከበረች ጤቀላ ከእርሷ ጋር ከሚኖሩ አራት ደናግል ጋር ፎላ በሚባል ኃጥእ ቄስ እጅ በሰማዕትነት ሞተች፤ ይህም ፎላ የሚባል ቄስ በዓመፅ የሰበሰበው ብዙ ገንዘብ እንዳለው በከሀዲ መኰንን ዘንድ ነገር ሠሩበት መኰንኑም ገንዘቡን ሁሉ እንዲወርሱት አዘዘ ፎላም ወደ መኰንኑ ሒዶ ገንዘቡን እንዲመልስለት ማለደው፤ መኰንኑም ስለ እነዚህ ደናግል ሰምቶ ወደርሱ እንዲአመጡአቸው አዘዘ በመጡም ጊዜ ፎላን መኰንኑ ለፀሐይ ይሰግዱ ዘንድ እሊህን ደናግል ብትሸነግላቸው ገንዘብህን እመልስልሃለሁ አለው። ❖ ፎላም ሊሸነግላቸው ጀመረ ደናግሉም አንተ የሰይጣን ልጅ የክብር ባለቤት ክርስቶስን እንክደው ዘንድ እንዴት ትፈትነናለህ አንተ ቀድሞ መምህራችን የነበርክ ስትሆን ብለው ዘለፉት፤ መኰንኑም ቃላቸውን በሰማ ጊዜ በጅራፍ እንዲገርፏቸው አዘዘ እነርሱ ግን መናገራቸውን አልተዉም ሥቃይንም አልፈሩም። ❖ መኰንኑም ፎላን የበከተ ብትበላ ደምንም ብትጠጣ ገንዘብህን እመልስልሃለሁ አለው ፎላም እንዳለው አደረገ፤ ዳግመኛም እሊህን ደናግል ብትገድላቸው ገንዘብህን እመልስልሃለሁ አለው በሰማም ጊዜ ልቡናውን አጽንቶ ሊገድላቸው ሔደ እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ልቡ በገንዘብ ፍቅር ተነድፎዋልና። ❖ ደናግሉም እንዲህ አሉት ከሀዲ ሆይ የመድኃኒታችንን ክርስቶስን ሥጋውንና ደሙን በእጅህ ተቀብለን አልነበረምን ስለ ገንዘብ ፍቅር እኛን የክርስቶስን በጎች ታጠፋ ዘንድ እንዴት መጣህ እንዲህም እያሉ ሰልፍ እንደተማረ አርበኛ ሰው በሰይፍ ራሶቻቸውን ቆረጠ። ❖ መኰንኑም የፎላን ብላሽነትና ድንቊርና አይቶ በሰይፍ ገደለው ነፍሱንም ገንዘቡንም ሃይማኖቱንም አጣ፤ የደናግሉም ስማቸው ጤቅላ ማርያ ማርታ አመታ ዓበያ ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። አርኬ ✍️ሰላም ለደናግል ማርያ ወማርታ። ጤቀላ አበያ ወአመታ። እንዘ ኢይትአንተላ ሕቀ ወኢይት አተታ። በሰይፈ ቀሲስ መምህሮን ዘተሴሰየ ማውታ። ተውላጠ ንዋዩ ኃላፊ ኅቡረ ዘሞታ።✝️ ቅድስት ኦርኒ ሰማዕት
Reviews channel
2 total reviews
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️» is a Telegram channel in the category «Религия и духовность», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 5.2K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 27.4, with 2 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.2 ₽, and with 5 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий