
- Main
- Catalog
- Religion & Spirituality
- ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️
ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️
በዚህ channel ውስጥ መንፈሳዊ መጻሕፍትንና የየዕለቱን ስንክሳር ያገኛሉ።
Channel statistics
ግንቦት 5፣ 2018 ዓ.ም.
🗓️ ግሪጎሪያን: 13/05/2026
═══════════════════════════════════════════════════
💭 የዕለቱ ጥቅስ:
"እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፥ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።" 📖 1ኛ ዮሐንስ 4:16📖 ግጽዌ - የዕለቱ ንባብ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈ 📌 ዕብራውያን 11
³² እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶንም ስለ ዮፍታሔም ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና። ³³ እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ፥ ጽድቅን አደረጉ፥ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አገኙ፥ ³⁴ የአንበሶችን አፍ ዘጉ፥ የእሳትን ኃይል አጠፉ፥ ከሰይፍ ስለት አመለጡ፥ ከድካማቸው በረቱ፥ በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ። ³⁵ ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤ ³⁶ ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ፤ ³⁷ በድንጋይ ተወግረው ሞቱ፥ ተፈተኑ፥ በመጋዝ ተሰነጠቁ፥ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ፥ ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ ³⁸ ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ። ³⁹-⁴⁰ እነዚህም ሁሉ በእምነታቸው ተመስክሮላቸው ሳሉ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አላገኙም፥ ያለ እኛ ፍጹማን እንዳይሆኑ እግዚአብሔር ስለ እኛ አንዳች የሚበልጥ ነገርን አስቀድሞ አይቶ ነበርና።📌 1ኛ ጴጥሮስ 2
¹⁹ በግፍ መከራን የሚቀበል ሰው እግዚአብሔርን እያሰበ ኃዘንን ቢታገሥ ምስጋና ይገባዋልና። ²⁰ ኃጢአት አድርጋችሁ ስትጎሰሙ ብትታገሡ፥ ምን ክብር አለበት? ነገር ግን መልካም አድርጋችሁ መከራን ስትቀበሉ ብትታገሡ፥ ይህ ነገር በእግዚአብሔር ዘንድ ምስጋና ይገባዋል። ²¹ የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና። ²² እርሱም ኃጢአት አላደረገም፥ ተንኰልም በአፉ አልተገኘበትም፤ ²³ ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም መከራንም ሲቀበል አልዛተም፥ ነገር ግን በጽድቅ ለሚፈርደው ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ ²⁴ ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። ²⁵ እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና፥ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል።📌 ሐዋርያት 7
⁵¹ እናንተ አንገተ ደንዳኖች ልባችሁና ጆሮአችሁም ያልተገረዘ፥ እናንተ ሁልጊዜ መንፈስ ቅዱስን ትቃወማላችሁ፤ አባቶቻችሁ እንደ ተቃወሙት እናንተ ደግሞ። ⁵²-⁵³ ከነቢያትስ አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን ነው? የጻድቁንም መምጣት አስቀድሞ የተናገሩትን ገደሉአቸው፤ በመላእክት ሥርዓት ሕግን ተቀብላችሁ ያልጠበቃችሁት እናንተም አሁን እርሱን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት ገደላችሁትም። ⁵⁴ ይህንም በሰሙ ጊዜ በልባቸው በጣም ተቈጡ ጥርሳቸውንም አፋጩበት። ⁵⁵ መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፦📌 ምስባክ 👇
ላዕሌከ ተገደፍኩ እማኅፀን። እምከርሠ እምየ አንተ አምላኪየ። ኢትርኀቅ እምኔየ እስመ አልጸቁ እትመንደብ። መዝ 21፥10-11።📌 ትርጉም
ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ ከእናቴ ሆድ ጀምረህ አንተ አምላኬ ነህ። ጭንቀት ቀርባለችና የሚረዳኝም የለምና ከእኔ አትራቅ። መዝ 21፥10-11።📌 ወንጌል 📖ማቴዎስ 21
³³ ሌላ ምሳሌ ስሙ። የወይን አትክልት የተከለ ባለቤት ሰው ነበረ፤ ቅጥርም ቀጠረለት፥ መጥመቂያም ማሰለት፥ ግንብም ሠራና ለገበሬዎች አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ። ³⁴ የሚያፈራበትም ጊዜ ሲቀርብ፥ ፍሬውን ሊቀበሉ ባሮቹን ወደ ገበሬዎች ላከ። ³⁵ ገበሬዎቹም ባሮቹን ይዘው አንዱን ደበደቡት አንዱንም ገደሉት ሌላውንም ወገሩት። ³⁶ ደግሞ ከፊተኞች የሚበዙ ሌሎች ባሮችን ላከ፥ እንዲሁም አደረጉባቸው። ³⁷ በኋላ ግን፦ ልጄንስ ያፍሩታል ብሎ ልጁን ላከባቸው። ³⁸ ገበሬዎቹ ግን ልጁን ባዩ ጊዜ እርስ በርሳቸው፦ ወራሹ ይህ ነው፤ ኑ፥ እንግደለውና ርስቱን እናግኝ ተባባሉ። ³⁹ ይዘውም ከወይኑ አትክልት አወጡና ገደሉት። ⁴⁰ እንግዲህ የወይኑ አትክልት ጌታ በሚመጣ ጊዜ በእነዚህ ገበሬዎች ምን ያደርግባቸዋል? ⁴¹ እነርሱም፦ ክፉዎችን በክፉ ያጠፋቸዋል፥ የወይኑንም አትክልት ፍሬውን በየጊዜው ለሚያስረክቡ ለሌሎች ገበሬዎች ይሰጠዋል አሉት። ⁴² ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፤ ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ፥ ለዓይኖቻችንም ድንቅ ነው የሚለውን ከቶ በመጽሐፍ አላነበባችሁምን? ⁴³ ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰዳለች ፍሬዋንም ለሚያደርግ ሕዝብ ትሰጣለች። ⁴⁴ በዚህም ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ይቀጠቀጣል፤ ድንጋዩ ግን የሚወድቅበትን ሁሉ ይፈጨዋል። ⁴⁵ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያንም ምሳሌዎቹን ሰምተው ስለ እነርሱ እንደ ተናገረ አስተዋሉ፤ ⁴⁶ ሊይዙትም ሲፈልጉት ሳሉ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስላዩት ፈሩአቸው።✝️ ቅዳሴ
የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው።
1.📌 ወርኀዊ በዓላት
1.📖1ኛ ዼጥ 5፥3
✍️
ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀዪቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል። እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ። ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውና ያጻፈውም ከግዕዝ ወደ አማርኛ የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን።
አምላካችን ሆይ፣ በዚህ ቀን የምንነበውን ቃልህ በልባችን እንድናስቀምጥ እና በሕይወታችን እንድንተገብር እርዳን። አሜን አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ...።═══════════════════════════════════════════════════ 📱 ቦት: @gitsawebot 📺 ቻናል: https://t.me/religious_books_lover 🌐 ድህረ ገጽ: https://gitsawe-tailwind-2019.vercel.app/ 🕊️ ሰላም ይሁንላችሁ!
ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ። እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ። ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ። እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ። እምእለ አብኡ ብዑላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን። ሰማዕት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን። ደናግል ዓዲ ወመነኰሳት ኄራን። ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን። እስከ አረጋዊ ልሒቅ ወንኡስ ሕፃን። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ። ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ። ወለዘሰምዐ ቃሎ በዕዝነ መንፈስ። በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኵሉ እምባእስ። ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ።
ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀዪቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል። እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ። ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውና ያጻፈውም ከግዕዝ ወደ አማርኛ የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን።
አምላካችን ሆይ፣ በዚህ ቀን የምንነበውን ቃልህ በልባችን እንድናስቀምጥ እና በሕይወታችን እንድንተገብር እርዳን። አሜን አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ...።═══════════════════════════════════════════════════ 📱 ቦት: @gitsawebot 📺 ቻናል: https://t.me/religious_books_lover 🌐 ድህረ ገጽ: https://gitsawe-tailwind-2019.vercel.app/ 🕊️ ሰላም ይሁንላችሁ!
1.📌 ወርኀዊ በዓላት
1.📖1ኛ ዼጥ 5፥3
✍️
ግንቦት 4፣ 2018 ዓ.ም.
🗓️ ግሪጎሪያን: 12/05/2026
═══════════════════════════════════════════════════
💭 የዕለቱ ጥቅስ:
"እግዚአብሔር ፍቅር ነው፤ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፥ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።" 📖 1ኛ ዮሐንስ 4:16📖 ግጽዌ - የዕለቱ ንባብ ━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━ ┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈ 📌 የዕለቱ የወንጌል ክፍል - ማቴዎስ 25:14-31
“ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤ ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ፥ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ። አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ። አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ። “ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው።አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ፦ ‘ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት፡’ አለ። ጌታውም፦ ‘መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ፡’ አለው። ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ “ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት፡” አለ። ጌታውም፦ ‘መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ፡’ አለው። አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ‘ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ፡’ አለ። ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፦ ‘አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ፥ ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንሁባትም እንድሰበስብ ታውቃለህን ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፥ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር። ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል። የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል’።”📌 ምስባክ - መዝሙር 83:6
እስመ መምህረ ህግ ይሁብ በረከተ ወየኃውር እምኃይል ውስተ ኃይል ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን📌 ትርጉም
የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል📌 ማጠቃለያ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን ይቆየን።
ልሳንየ ላዕላዕ ይሴብሐኪ፤ እግዝእትየ እብለኪ፤ አዳም ንባብኪ፤ ወመሠረቱ ወመሠረቱ ለዓለም አንቲ፤ ዕጓለ አንበሳ ዕጓለ አንበሳ በከርሥኪ ፆርኪ፤ እምአንስት ቡርክት አንቲ፤ ለመሠረትኪ የኃትዎ ዕንቊ ክቡር፤ አንቲ ውእቱ መንፈሳዊት ሀገር ንጽሕት ፀምር፤ ዘኃረያ ጸባኦት አማኑኤል።አመላለስ አንቲ ውእቱ መንፈሳዊት ሀገር ንጽሕት ፀምር/፪/ ዘኃረያ ጸባኦት አማኑኤል/፬/ =>✍እመሒ ስሕተኩ አንትሙ እለ በመንፈስ አርትዕ(የተሳሳትኩት ቢኖር እናንተ በመንፈስ ያላችሁ አቃኑት)🙏🙏🙏
ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤አዳም ወሠናይት፤ፅዕዱት ወብርህት እኅቶሙ ለመላእክት፤ማርያምሰ ተሐቱ ውስተ ከርሡ ለአዳም፤ከመ ባሕርይ ፀዓዳ፤እንተ ሠረፀት እምሥርወ ዕሤይ ወተወልደት፤እምዘርዓ ዳዊት በምድረ ይሁዳ።ዋይዜማ
ሃሌ ሉያ ቆምኪ ርእየትኪ(ርእዮትኪ)ወክሣድኪ ከመ አርማስቆስ፤እኅትነ ይብልዋ መላእክት በሰማያት፤ስብሕት በሐዋርያት ኢያቄም ወለዳ፤ደብተራ ዘትዕይንት፤ጥዕምት በቃላ ወሠናይት በምግባራ፤እግዝእትነ ማርያም።ምልጣን፦ ስብሕት በሐዋርያት ኢያቄም ወለዳ ደብተራ ዘትዕይንት፤ኢያቄም ወለዳ ጥዕምት በቃላ ኢያቄም ወለዳ። አመላለስ ኢያቄም ወለዳ ኢያቄም ወለዳ/፪/ ጥዕምት በቃላ ኢያቄም ወለዳ/፬/ በ፭ ለእግዚአብሔር ምድር በምልዓ፦ ሰአሊ ለነ ማርያም እንተ እግዚእ ኀርያ፤ሰአሊ ለነ ማርያም። እግዚአብሔር ነግሠ፦ ኦ ማርያም መንክር ልደትኪ ወዕፁብ ግብርኪ፤ዓምደ እሳት ፆርኪ ወልድኪ መድኃኔ ዓለም ዲበ ዕፅ ተቀነወ፤ወዘተጼወወ ሕዝብ በደሙ ቤዘወ። ይትባረክ እግዚእትየ እብለኪ ወእሙ ለእግዚእየ እብለኪ፤ቃል ቅዱስ ኀደረ ላዕሌኪ። ፫ት ሥረዩ፦ ማርያምሰ እሙኒ ዐመቱኒ በትረ አሮን እንተ ሠረጸት እንበለ ተክል። ሰላም፦
አንጺሖ ሥጋሃ ኀደረ ላዕሌሃ ወተወልደ እምኔሃ ፍሥሐ፤እምሥርወ እሴይ እምዘርዓ ዳዊት እምዘመዶሙ ለካህናት እንተ ሠረፀት ለሕይወት ሰላማዊት ጽርሕ ንጽሕት ደብተራ ፍጽምት እኅቶሙ ለመላእክት።=>✍እመሒ ስሕተኩ አንትሙ እለ በመንፈስ አርትዕ(የተሳሳትኩት ቢኖር እናንተ በመንፈስ ያላችሁ አቃኑት)🙏🙏🙏 ☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️ ሥርዓተ ማኅሌት አመ ፩ ለግንቦት ልደታ ለእግዚእትነ ማርያም ❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ የልደታ ለማርያም #ሥርዓተ_ማኅሌት ከሊቃውንቱ ጋራ አብረን ለማመስገን ይረዳን ዘንድ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል። "ሥርዓተ ነግሥ" ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፤ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ ሃሌ ሉያ፤ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤ በአሐቲ ቃል። መልክአ ሥላሴ፦
ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ ለሣሕል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።ዚቅ ለማርያም ዘምሩ፤ ለማርያም ዘምሩ፤ መስቀሎ ለወልዳ እንዘ ትጸውሩ። መልክዐ ሚካኤል፦
ሰላም ለልሳንከ መዝሙረ ቅዳሴ ዘነበልባል፤ ወለድምጸ ቃልከ ሐዋዝ ቀርነ መንግሥቱ ለቃል፤ ሞገሰ ክብሩ ሚካኤል ለተላፊኖስ ባዕል፤ አልቦ ዘይትማሰለከ በልማደ ምሕረት ወሣህል፤ እንበለ ባሕቲታ እኅትከ ማርያም ድንግል።ዚቅ ተውህቦ ምሕረት ለሚካኤል፣ ወብሥራት ለገብርኤል፤ ወሀብተ ሰማያት ለማርያም ድንግል። ዘጣዕሙ፦
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ህይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።ዚቅ፦
ወመሠረቱ ወመሠረቱ ለዓለም አንቲ፤ ዕጓለ አንበሳ ዕጓለ አንበሳ በከርሥኪ ፆርኪ፤ እምአንስት ቡርክት አንቲ፤ ለመሠረትኪ የኃትዎ ዕንቊ ክቡር፤ አንቲ ውእቱ መንፈሳዊት ሀገር ንጽሕት ፀምር፤ ዘኃረያ ጸባኦት አማኑኤል።ነግሥ፦
፪ቱ አዕሩግ አመ በከዩ ብካየ፤ ረከቡ ወለተ ዘታስተሠሪ ጌጋየ፤ ለወንጌላውያን ኲልነ ዘኮነተነ ምጒያየ፤ ኢያቄም ወሐና ወለዱ ሰማየ፤ ሰማዮሙኒ አሥረቀት ፀሐየ።ዚቅ ምሥራቀ ምሥራቃት ሙፃአ ፀሐይ፤ እግዝእትየ ዘመና ሙዳይ፤ ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ። መልክአ ማርያም፦
ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤ እምነ ከልበኔ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ፤ ማርያም ድንግል ለባሲተ ዓቢይ ትእዛዝ፤ ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፤ ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ።ዚቅ በሐኪ ማርያም ዘገነት ኮል፤ ዕፀ ጳጦስ መዝገቡ ለቃል፤ ዕለተ ልደትኪ ዮም በጽድቅ ናብዕል። ወረብ በሐኪ ማርያም ዘገነት ኮል/፪/ 'ዕፀ ጳጦስ'/፪/ መዝገቡ ለቃል/፪/ መልክአ ማርያም፦
ሰላም ለልሳንኪ ሙኃዘ ኀሊብ ወመዓር፤ ዘተነብዮ ወፍቅር፤ ማርያም ድንግል ወለተ ድኁኃን አድባር፤ ኅብዕኒ እምአይነ ፀር ወአንጽሕኒ እምነውር፤ እስመ ተስፋየ አንቲ በሰማይ ወምድር።ዚቅ መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፤ ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ። ወረብ 'መሠረታቲሃ'/፪/ ውስተ አድባር ቅዱሳን/፪/ ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ ወብእሲ ተወልደ/፪/ መልክአ ማርያም፦
ሰላም ለአእዳውኪ እሳተ መለኮት እለ ገሠሣ፣ አውቃፈ ብሩር ወወርቅ ለሥርጋዌሆን ኢኃሠሣ፤ ማርያም ድንግል ለመካን ሕንባበ ከርሳ፤ አንጽሕኒ እግዝእትየ ለፍትወተ ዓለም እምርኲሳ፤ በዲበ ሥጋየ ኢትንብር ነጊሣ።ዚቅ ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ፤ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ። ወረብ 'እምሐና ወኢያቄም'/፪/ ተወለድኪ/፪/ አላ 'በሩካቤ'/፪/ ዘበሕግ/፪/ መልክአ ማርያም፦
ሰላም ዕብል ለድንግልናኪ ዕጽው፤ እንተ እምኔሁ ሠረቀ ፀሐየ መለኮት ኅትው፤ ማርያም ድንግል ዘስነ ንጽሕኪ ፍትው፤ ለኀዲር በበፍናው(በማኅደር ወበፍናው)በአሕጉር ወበድው፤ ዕቀብኒ ወለቶሙ ለኄራን አበው።ዚቅ
ወለቶሙ ለነቢያት ይእቲ ማርያም፤ እሞሙ ለሐዋርያት ይእቲ ማርያም፤ ደብተራ ፍጽምት እንተ ኢገብራ ዕደ ሰብእ፤ ዕጹበ ግብረ(ገብረ) መናሥግተ ሥጋ ኢያርኃወ ዕጹበ ገብረ።ወረብ ወለቶሙ ለነቢያት እሞሙ ለሐዋርያት ይእቲ ማርያም/፪/ ደብተራ ፍጽምት ደብተራ እንተ ኢገብራ ዕደ ሰብእ/፪/ መልክአ ማርያም፦
በዝንቱ ቃለ ማኅሌት ወበዝንቱ ይባቤ፤ ለዘይስዕለኪ ብእሲ ጊዜ ረከቦ ምንዳቤ፤ ብጽሒ ፍጡነ ትሰጠዊዮ ዘይቤ፤ ማርያም ዕንቊየ ክርስቲሎቤ ወምዕዝተ ምግባር እምከርቤ፤ ዘጸገየ ማኅጸንኪ አፈወ ነባቤ።ዚቅ ርግብ ፀዓዳ ዘዕንቊ ድዳ፤ ወዘጳዝዮን ማኅፈዳ፤ ተወልደት ዮም በምድረ ይሁዳ። ወረብ ርግብ ፀዓዳ ዘዕንቊ ድዳ ወዘጳዝዮን ማኅፈዳ ወዘጳዝዮን/፪/ ዮም ተወልደት በምድረ 'ይሁዳ'/፪/ በምድረ ይሁዳ ተወልደት። ማስረቂያ፦
ሰላም ለልደትኪ እማኅጸነ ድክምት ሥጋ፤ ድኅረ ኃለፋ ውርዙት ወድኅረ ትክቶ ኃደጋ፤ ማርያም ሥመሪ ወጸሐቂ እንበለ ንትጋ፤ ለማየ ንጽሕኪ ትረስዪኒ ፈለጋ፤ እስመ ንጽሕ ይሁብ ሞገስ ወጸጋ።ዚቅ ሐመልማላዊት ሐመልማላዊት ሐመልማላዊት ዕፅ ሙሴ ዘርእያ በደብረ ሲና፤ እግዝእትየ ሙዳዩ ለመና፤ ተወልደት ዮም እምነ ኢያቄም ወሐና። ወረብ 'ሐመልማላዊት'/፪/ ዕፅ ሙሴ ዘርእያ በደብረ ሲና/፪/ ተወልደት ዮም እምነኢያቄም ወሐና/፪/ ምልጣን፦ ዮም ፍሥሃ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም እምሐና ወኢያቄም፤ ከመ ትቤዙ ነቢያተ ወጻድቃነ፤ አማን ተወልደት እመብርሃን። ምልጣን ዘዜማ፦ ከመ ትቤዙ ነቢያተ ወጻድቃነ፤ አማን ተወልደት እመብርሃን። አመላለስ 'አማን በአማን'/፪/ ተወልደት 'አማን በአማን'/፪//፪/ ተወልደት እመብርሃን/፬/
Reviews channel
3 total reviews
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
ኦርቶዶክሳዊ 📖📖📖 መጻሕፍት ✝️✝️✝️ is a Telegram channel in the category «Религия и духовность», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 5.2K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 27.3, with 3 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.2 ₽, and with 6 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий