
Get clients in any niche!
Delegate the launch of advertising to us — for free
Learn more
17.6

Advertising on the Telegram channel «አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center»
5.0
Share
Add to favorite
Buy advertising in this channel
Placement Format:
keyboard_arrow_down
- 1/24
- 2/48
- 3/72
- Native
- 7 days
- Forwards
1 hour in the top / 24 hours in the feed
Quantity
%keyboard_arrow_down
- 1
- 2
- 3
- 4
- 5
- 8
- 10
- 15
Advertising publication cost
local_activity
$4.80$4.80local_mall
0.0%
Remaining at this price:0
Recent Channel Posts
ፖሊስ ጣብያዎች ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ገንዘብ በመቅጣት ገቢ እንዲያስገቡ መታዘዛቸው ተሰማ
- "እያንዳንዱ የፖሊስ ጣብያ በቅጣት የሚያስገባው የገንዘብ ኮቴ ተጥሎበታል፣ በዛሬው እለት ብቻ 4.2 ሚልየን ብር ተሰብስቧል"
(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የፖሊስ አባላት ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን ገንዘብ በመቅጣት ገቢ እንዲያስገቡ መታዘዛቸው ታውቋል።
ለመሠረት ሚድያ የደረሰው ጥቆማ እንደሚያሳየው የየክፍለ ከተማው ስራ አስፈፃሚዎች በየጊዜው የፖሊስ አዛዦችን እየሰበሰቡ ገንዘብ በተለይ ከነጋዴዎች እና ድርጅቶች በአስገዳጅ ሁኔታ እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ተላልፎላቸዋል።
"በእያንዳንዱ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ከላይ የተወሰነ ኮታ አለ፣ ያንን በተሰጠን ጊዜ ገደብ ሰብስበን ማስገባት ግዴታችን ነው" ብለው ቃላቸውን የሰጡ አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር በዚህ ምክንያት ፖሊስ መደበኛ ስራውን ጥሎ ቤት ለቤት እና በየድርጅቱ ገንዘብ ሲጠይቅ ይውላል ብለዋል።
ሌላኛው ደግሞ "ገንዘብ ከምንሰበስብባቸው መንገዶች መሃከል ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ገንዘብ መቅጣት፣ አስገዳጅ የህዳሴ ኩፖን ማስገዛት፣ ለኮሪደር ልማት በሚል ከነጋዴዎች መዋጮ መጠየቅ ናቸው ያልተስማማ ካለ የንግድ ፈቃድ እስከመታገድ ይደርሳል" በማለት ሁኔታውን አስረድተዋል።
ከሰሞኑ በርካታ የመንግስት ሚድያዎች ፍሳሽ የለቀቁ፣ መንገድ ያበላሹ፣ እና ያልተፈቀደ ስራ የሰሩ በማለት ድርጅቶች ከአስር ሺዎች እስከ መቶ ሺህ ብሮች እንደተቀጡ መዘገባቸው ይታወሳል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዛሬ ባወጣው አንድ መግለጫ በዛሬው ቀን ብቻ ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን 4.2 ሚልዮን ብር እንደቀጣ አስታውቋል።
ባለስልጣኑ እንዳለው በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 1.3 ሚልዮን ብር፣ በአቃቂ ክ/ከተማ 800 ሺህ ብር፣ በየካ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 500 ሺህ ብር በዛሬው እለት ብቻ ከቅጣት ተሰብስቧል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- "እያንዳንዱ የፖሊስ ጣብያ በቅጣት የሚያስገባው የገንዘብ ኮቴ ተጥሎበታል፣ በዛሬው እለት ብቻ 4.2 ሚልየን ብር ተሰብስቧል"
(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የፖሊስ አባላት ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን ገንዘብ በመቅጣት ገቢ እንዲያስገቡ መታዘዛቸው ታውቋል።
ለመሠረት ሚድያ የደረሰው ጥቆማ እንደሚያሳየው የየክፍለ ከተማው ስራ አስፈፃሚዎች በየጊዜው የፖሊስ አዛዦችን እየሰበሰቡ ገንዘብ በተለይ ከነጋዴዎች እና ድርጅቶች በአስገዳጅ ሁኔታ እንዲሰበስቡ ትዕዛዝ ተላልፎላቸዋል።
"በእያንዳንዱ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ከላይ የተወሰነ ኮታ አለ፣ ያንን በተሰጠን ጊዜ ገደብ ሰብስበን ማስገባት ግዴታችን ነው" ብለው ቃላቸውን የሰጡ አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር በዚህ ምክንያት ፖሊስ መደበኛ ስራውን ጥሎ ቤት ለቤት እና በየድርጅቱ ገንዘብ ሲጠይቅ ይውላል ብለዋል።
ሌላኛው ደግሞ "ገንዘብ ከምንሰበስብባቸው መንገዶች መሃከል ከደንብ ማስከበር ጋር በመሆን ገንዘብ መቅጣት፣ አስገዳጅ የህዳሴ ኩፖን ማስገዛት፣ ለኮሪደር ልማት በሚል ከነጋዴዎች መዋጮ መጠየቅ ናቸው ያልተስማማ ካለ የንግድ ፈቃድ እስከመታገድ ይደርሳል" በማለት ሁኔታውን አስረድተዋል።
ከሰሞኑ በርካታ የመንግስት ሚድያዎች ፍሳሽ የለቀቁ፣ መንገድ ያበላሹ፣ እና ያልተፈቀደ ስራ የሰሩ በማለት ድርጅቶች ከአስር ሺዎች እስከ መቶ ሺህ ብሮች እንደተቀጡ መዘገባቸው ይታወሳል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዛሬ ባወጣው አንድ መግለጫ በዛሬው ቀን ብቻ ድርጅቶችን እና ግለሰቦችን 4.2 ሚልዮን ብር እንደቀጣ አስታውቋል።
ባለስልጣኑ እንዳለው በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 1.3 ሚልዮን ብር፣ በአቃቂ ክ/ከተማ 800 ሺህ ብር፣ በየካ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ 600 ሺህ ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 500 ሺህ ብር በዛሬው እለት ብቻ ከቅጣት ተሰብስቧል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
1600
19:18
20.03.2025
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በፀደቁ ሁለት አዳዲስ አዋጆች ዙርያ ቅሬታ ያቀረቡ ፖለቲከኛ ዛሬ ጠዋት ታሰሩ
(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በነበረ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ ቀርቦ የፀደቀውን የየእርከኑ የምክር ቤት ተወካዮች ብዛት ለመወሰን የወጣ አዋጅ እንዲሁም የክልሉ ህገ መንግስትን እንደገና ለማሻሻል የወጣውን አዋጅ ተቃውመው ቅሬታ ያስገቡት ፖለቲከኛ ዛሬ ጠዋት ለእስር ተዳርገዋል።
መሠረት ሚድያ እንዳረጋገጠው የቦሮ ዲሞክራያዊ ፓርቲ የፖለቲካ አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ እና የክልሉ የምክር ቤት ተመራጭ የሆኑን አቶ ዮሐንስ ተሰማ በፀጥታ ሀይሎች ተወስደዋል።
የቦሮ ዲሞክራያዊ ፓርቲ በውሳኔዎቹ ላይ ቅሬታ የነበረው ሲሆን ሶስቱ የምክር ቤቱ አባላት በወቅቱ ተቃውሞ አቅርበው ውሳኔውንም 'የህገ መንግስት አተረጓጎም ላይ የቀረበ ቅሬታ' በሚል ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ከተጨማሪ ጥያቄዎች ጋር አቅርበው ነበር።
"በዚህ ሁኔታ ያቀረቡትን ጥያቄ የተለያዩ አንድምታ እየሰጡ ይባስ ብለው ዛሬ አቶ ዮሀንስን አስረውታል" ብለው የክልሉ የመረጃ ምንጫችን ለሚድያችን ተናግረዋል።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ከየካቲት 10 እስከ 11 2017 ዓ/ም በአሶሳ ከተማ ባካሄደው መደበኛ ጉባዔ በስራ ላይ የሚገኘውን የክልሉን የምክር ቤት የመቀመጫ ቁጥር ከ99 ወደ 165 አሻሽሏል፡፡
የቦሮ ዲሞክራያዊ ፓርቲ ግን የህዝብና ቤቶች ቆጠራ ሳይደረግ 165ቱ የመቀመጫ ብዛት አሁን በስራ ላይ ለሚገኙ የምርጫ ክልሎች የተከፋፈለበት መንገድ የህዝብ ብዛትን ያማከለ አለመሆኑን እና ነባር የምርጫ ክልሎች የፈረሱበትና አዳዲስ ምርጫ ክልሎች የተቋቋሙበት ሂደት ህገ መንግስቱን የጣሰ በመሆኑን እንዲሁም በቂ ውይይትና ክርክር ያልተደረገበት መሆኑን በመግለፅ ቅሬታውን ገልፆ ነበር።
ፓርቲው በመግለጫው የክልሉ መንግስት "በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ያቀረብነዉን ጥያቄና ቅሬታ በሃይል ለመደፍጠጥ በፓርቲያችንና ፓርቲያችንን ወክለዉ የክልል ምክር ቤት አባል በሆኑ አመራሮቻችን ላይ የጀመረው ዛቻ፣ ማስፈራሪያና ወከባ የተጀመረዉን የመደብለ ፓርቲ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ላይ አደጋ የሚጥል በመሆኑ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ እናሳስባለን" በማለት የካቲት 28/ 2017 ዓ/ም አሳስበው ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በነበረ የምክር ቤት ስብሰባ ላይ ቀርቦ የፀደቀውን የየእርከኑ የምክር ቤት ተወካዮች ብዛት ለመወሰን የወጣ አዋጅ እንዲሁም የክልሉ ህገ መንግስትን እንደገና ለማሻሻል የወጣውን አዋጅ ተቃውመው ቅሬታ ያስገቡት ፖለቲከኛ ዛሬ ጠዋት ለእስር ተዳርገዋል።
መሠረት ሚድያ እንዳረጋገጠው የቦሮ ዲሞክራያዊ ፓርቲ የፖለቲካ አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ እና የክልሉ የምክር ቤት ተመራጭ የሆኑን አቶ ዮሐንስ ተሰማ በፀጥታ ሀይሎች ተወስደዋል።
የቦሮ ዲሞክራያዊ ፓርቲ በውሳኔዎቹ ላይ ቅሬታ የነበረው ሲሆን ሶስቱ የምክር ቤቱ አባላት በወቅቱ ተቃውሞ አቅርበው ውሳኔውንም 'የህገ መንግስት አተረጓጎም ላይ የቀረበ ቅሬታ' በሚል ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ከተጨማሪ ጥያቄዎች ጋር አቅርበው ነበር።
"በዚህ ሁኔታ ያቀረቡትን ጥያቄ የተለያዩ አንድምታ እየሰጡ ይባስ ብለው ዛሬ አቶ ዮሀንስን አስረውታል" ብለው የክልሉ የመረጃ ምንጫችን ለሚድያችን ተናግረዋል።
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ከየካቲት 10 እስከ 11 2017 ዓ/ም በአሶሳ ከተማ ባካሄደው መደበኛ ጉባዔ በስራ ላይ የሚገኘውን የክልሉን የምክር ቤት የመቀመጫ ቁጥር ከ99 ወደ 165 አሻሽሏል፡፡
የቦሮ ዲሞክራያዊ ፓርቲ ግን የህዝብና ቤቶች ቆጠራ ሳይደረግ 165ቱ የመቀመጫ ብዛት አሁን በስራ ላይ ለሚገኙ የምርጫ ክልሎች የተከፋፈለበት መንገድ የህዝብ ብዛትን ያማከለ አለመሆኑን እና ነባር የምርጫ ክልሎች የፈረሱበትና አዳዲስ ምርጫ ክልሎች የተቋቋሙበት ሂደት ህገ መንግስቱን የጣሰ በመሆኑን እንዲሁም በቂ ውይይትና ክርክር ያልተደረገበት መሆኑን በመግለፅ ቅሬታውን ገልፆ ነበር።
ፓርቲው በመግለጫው የክልሉ መንግስት "በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ያቀረብነዉን ጥያቄና ቅሬታ በሃይል ለመደፍጠጥ በፓርቲያችንና ፓርቲያችንን ወክለዉ የክልል ምክር ቤት አባል በሆኑ አመራሮቻችን ላይ የጀመረው ዛቻ፣ ማስፈራሪያና ወከባ የተጀመረዉን የመደብለ ፓርቲ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ላይ አደጋ የሚጥል በመሆኑ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ እናሳስባለን" በማለት የካቲት 28/ 2017 ዓ/ም አሳስበው ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
3000
15:37
10.03.2025
'GTNA' ለሚድያ መገንቢያ የተሰጠውን 5 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ በ1 ቢልዮን ብር ሊሸጥ እያስማማ መሆኑ ታወቀ
- ቦታው ለጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ማስፋፊያ ተብሎ የተያዘ ነበር
(መሠረት ሚድያ)- ግሎባል ቴሌቭዥን ኔትዎርክ ኦፍ አፍሪካ (GTNA) በሚል ስያሜ የተቋቋመው እና በአፍሪካ ግዙፉ የሚድያ ተቋም ይሆናል የተባለለት ድርጅት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሊዝ የተረከበውን 5ሺ ካሬ ሜትር ቦታ በደላሎች አማካኝነት ሊሸጥ መሆኑ ታውቋል።
GTNA መሬቱን ከተረከበ ሶስት አመት እንዳለፈው የጠቆሙት ምንጮቻችን አሁን ላይ ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኘው ቦታው ታጥሮ ለመኪና ፓርኪንግ አገልግሎት ብቻ እየዋለ መሆኑን ከምስሎች እና ቪድዮዎች ጋር አያይዘው ለመሠረት ሚድያ ልከዋል።
"በመጀመርያ በደላሎች አማካኝነት ለሽያጭ የቀረበው በ1.4 ቢልዮን ብር ነበር፣ ገዢ ስላልተገኘ አሁን ላይ እስከ 1 ቢልዮን ብር እየተጠራበት ነው" የሚሉት ምንጮች አፍሪካን ማዕከል አድርጎ የአፍሪካን እውነት ለአለም ያሳውቃል የተባለለት ተቋም መሬቱን ለምን እንደሚሸጥ እንደማያውቁ ተናግረዋል።
አንድ የከተማ አስተዳደሩ ባልደረባ ግን መሬቱ ለሽያጭ መቅረቡን እንደሚያውቁ ለሚድያችን ገልፀው "በዲዛይኑ ላይ የተቀመጠውን ግዙፍ መንትያ ህንፃዎች ለመገንባት አበዳሪ ባንክ አልተገኘም፣ ምናልባት ሀብት ለማሰባሰብ ይሆናል" ብለዋል።
ግሩም ጫላ በተባለ ግለሰብ አማካኝነት በአፍሪካ ትልቅ ሚዲያ ሊገነባ እንደሆነ በርካታ ሚድያዎች ከሶስት አመት በፊት መዘገባቸው ይታወሳል። ለሚድያው ዋና መስሪያ ቤት የሚውለው ቁልፍ ቦታ ከጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ይዞታ ጭምር ተወስዶ እንደተሰጠ ምንጮቻችን ጠቁመዋል።
"መንግሥት ለጋንዲ መታሠቢያ ሆስፒታል የማስፋፊያ ህንፃዎች ግንባታ የሚሆን ሰፊ ቦታ አዘጋጅቶ ነበር፣ ይሁንና ከሆስፒታሉ ይዞታ ላይ 5,000 ካሬ ሜትር የሚሆን ቦታ በቂርቆስ ወረዳ 07 የግንባታ ፈቃድ ከሚሰጡ ሰዎች ጋር በተደረገ ውል በሆስፒታሉ ካርታ ላይ ሌላ አዲስ ካርታ ተሰርቷል" የሚሉት እኚህ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኛ በአንድ አጋጣሚ ለምን ብለው በጠየቁ የሆስፒታሉ ሰራተኞች ላይ ማስፈራራት ደርሶባቸው ነበርም ብለዋል።
ከጋንዲ ሆስፒታል ያገኘነው ተጨማሪ መረጃ እንደሚጠቁመው ሆስፒታሉ ለወላድ እናቶች አገልግሎት የሚውል የከርሰ ምድር ውሃ አስቆፍሮ የነበረ ሲሆን እሱም በGTNA ይዞታ ስር ሊሆን ይገባል የሚል አምባጓሮ ተነስቶ በመጨረሻም በ GTNA ይዞታ ስር እንደተጠቃለለ ታውቋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- ቦታው ለጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ማስፋፊያ ተብሎ የተያዘ ነበር
(መሠረት ሚድያ)- ግሎባል ቴሌቭዥን ኔትዎርክ ኦፍ አፍሪካ (GTNA) በሚል ስያሜ የተቋቋመው እና በአፍሪካ ግዙፉ የሚድያ ተቋም ይሆናል የተባለለት ድርጅት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሊዝ የተረከበውን 5ሺ ካሬ ሜትር ቦታ በደላሎች አማካኝነት ሊሸጥ መሆኑ ታውቋል።
GTNA መሬቱን ከተረከበ ሶስት አመት እንዳለፈው የጠቆሙት ምንጮቻችን አሁን ላይ ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኘው ቦታው ታጥሮ ለመኪና ፓርኪንግ አገልግሎት ብቻ እየዋለ መሆኑን ከምስሎች እና ቪድዮዎች ጋር አያይዘው ለመሠረት ሚድያ ልከዋል።
"በመጀመርያ በደላሎች አማካኝነት ለሽያጭ የቀረበው በ1.4 ቢልዮን ብር ነበር፣ ገዢ ስላልተገኘ አሁን ላይ እስከ 1 ቢልዮን ብር እየተጠራበት ነው" የሚሉት ምንጮች አፍሪካን ማዕከል አድርጎ የአፍሪካን እውነት ለአለም ያሳውቃል የተባለለት ተቋም መሬቱን ለምን እንደሚሸጥ እንደማያውቁ ተናግረዋል።
አንድ የከተማ አስተዳደሩ ባልደረባ ግን መሬቱ ለሽያጭ መቅረቡን እንደሚያውቁ ለሚድያችን ገልፀው "በዲዛይኑ ላይ የተቀመጠውን ግዙፍ መንትያ ህንፃዎች ለመገንባት አበዳሪ ባንክ አልተገኘም፣ ምናልባት ሀብት ለማሰባሰብ ይሆናል" ብለዋል።
ግሩም ጫላ በተባለ ግለሰብ አማካኝነት በአፍሪካ ትልቅ ሚዲያ ሊገነባ እንደሆነ በርካታ ሚድያዎች ከሶስት አመት በፊት መዘገባቸው ይታወሳል። ለሚድያው ዋና መስሪያ ቤት የሚውለው ቁልፍ ቦታ ከጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ይዞታ ጭምር ተወስዶ እንደተሰጠ ምንጮቻችን ጠቁመዋል።
"መንግሥት ለጋንዲ መታሠቢያ ሆስፒታል የማስፋፊያ ህንፃዎች ግንባታ የሚሆን ሰፊ ቦታ አዘጋጅቶ ነበር፣ ይሁንና ከሆስፒታሉ ይዞታ ላይ 5,000 ካሬ ሜትር የሚሆን ቦታ በቂርቆስ ወረዳ 07 የግንባታ ፈቃድ ከሚሰጡ ሰዎች ጋር በተደረገ ውል በሆስፒታሉ ካርታ ላይ ሌላ አዲስ ካርታ ተሰርቷል" የሚሉት እኚህ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኛ በአንድ አጋጣሚ ለምን ብለው በጠየቁ የሆስፒታሉ ሰራተኞች ላይ ማስፈራራት ደርሶባቸው ነበርም ብለዋል።
ከጋንዲ ሆስፒታል ያገኘነው ተጨማሪ መረጃ እንደሚጠቁመው ሆስፒታሉ ለወላድ እናቶች አገልግሎት የሚውል የከርሰ ምድር ውሃ አስቆፍሮ የነበረ ሲሆን እሱም በGTNA ይዞታ ስር ሊሆን ይገባል የሚል አምባጓሮ ተነስቶ በመጨረሻም በ GTNA ይዞታ ስር እንደተጠቃለለ ታውቋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
3000
17:55
07.03.2025
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የስራ ሀላፊ የነበሩት ግለሰብ በኬንያ አየር መንገድ የካርጎ ማናጀር ሆነው ተቀጠሩ
- የኬንያ አየር መንገድ ልምድ ያላቸውን ኢትዮጵያውያን እያፈላለገ በከፍተኛ ደሞዝ እየቀጠረ ነው
(መሠረት ሚድያ)- የኬንያ አየር መንገድ (ኬንያ ኤርዌይስ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት (ካርጎ) እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ማኔጂንግ ዳይሬክተር የነበሩትን አቶ ፍፁም አባዲን መቅጠሩ ተሰማ።
ኬንያ ኤርዌይስ አቶ ፍፁምን የካርጎ ክፍል ዳይሬክተር አድርጎ ከትናንት የካቲት 24/2017 ዓ/ም ጀምሮ በሃላፊነት እንደሾማቸው የመሠረት ሚድያ ምንጮች ጠቁመዋል።
አቶ ፍፁም በኢቪዬሽን ኢንደስትሪ ውስጥ ከ23 አመት በላይ የዘለቀ የስራ ልምድ ያላቸው ሲሆን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በካርጎ አገልግሎት ዘርፍ በርካታ እውቀት እንዳላቸው ይነገርላቸዋል።
በተለይ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት የአቪዬሽን ኢንዱስትሪው በከፍኛ ደረጃ በተጎዳበት ወቅት እና የኢትዮጵያ አየር መንገድም የመንገደኞች በረራ በተቀዛቀዘበት ወቅት ማኔጅመንቱ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የካርጎ ክፍሉ ከፍተኛ እንስቃሴ በማድረግ አየር መንገዱን ከኪሳራ መታደጉ ይታወሳል።
በዚህ አስቸጋሪ ወቅት አቶ ፍፁም የስራ ባልደረቦቻቸውን በማስተባበር ቀን ከሌሊት በመስራት ብቃታቸውን እንዳስመሰከሩ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
አቶ ፍፁም በትምህርት ዝግጅታቸው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆን ከአሜሪካው ኒው ሃምፕሻየር ዩኒቨርስቲ እና ከእንግሊዙ ኦፕን ዩኒቨርስቲ ሁለት የማስተርስ ዲግሪ ወስደዋል።
አቶ ፍፁም የዛሬ ሁለት አመት ገደማ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ከለቀቁ በኋላ ኑሮዋቸውን ከቤተሰባቸው ጋር በአሜሪካ አድርገው የነበረ ሲሆን በቅርብ ቀን ግን ወደ ኬንያ፣ ናይሮቢ እንደሚያቀኑ ታውቋል።
ግለሰቡ በትግራይ ጦርነት ወቅት በአንዳንድ አክቲቪስቶች ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶባቸው የነበረ ሲሆን ይህ ስም የማጠልሸት ዘመቻ በተመሳሳይ የደረሰባቸው የአየር መንገዱ የቀድሞ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንዲሁ በተመሳሳይ ስራቸውን በመቀየር ለግዙፉ ደልታ አየር መንገድ በአማካሪነት መስራት መጀመራቸው ይታወሳል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተፎካካሪ የሆነው ኬንያ ኤርዌይስ ልምድ ያላቸውን ኢትዮጵያውያን እያፈላለገ በከፍተኛ ደሞዝ እየቀጠረ እንደሆነ ምንጮች ለመሠረት ሚዲያ ገልፀዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- የኬንያ አየር መንገድ ልምድ ያላቸውን ኢትዮጵያውያን እያፈላለገ በከፍተኛ ደሞዝ እየቀጠረ ነው
(መሠረት ሚድያ)- የኬንያ አየር መንገድ (ኬንያ ኤርዌይስ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት (ካርጎ) እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ማኔጂንግ ዳይሬክተር የነበሩትን አቶ ፍፁም አባዲን መቅጠሩ ተሰማ።
ኬንያ ኤርዌይስ አቶ ፍፁምን የካርጎ ክፍል ዳይሬክተር አድርጎ ከትናንት የካቲት 24/2017 ዓ/ም ጀምሮ በሃላፊነት እንደሾማቸው የመሠረት ሚድያ ምንጮች ጠቁመዋል።
አቶ ፍፁም በኢቪዬሽን ኢንደስትሪ ውስጥ ከ23 አመት በላይ የዘለቀ የስራ ልምድ ያላቸው ሲሆን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በካርጎ አገልግሎት ዘርፍ በርካታ እውቀት እንዳላቸው ይነገርላቸዋል።
በተለይ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት የአቪዬሽን ኢንዱስትሪው በከፍኛ ደረጃ በተጎዳበት ወቅት እና የኢትዮጵያ አየር መንገድም የመንገደኞች በረራ በተቀዛቀዘበት ወቅት ማኔጅመንቱ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የካርጎ ክፍሉ ከፍተኛ እንስቃሴ በማድረግ አየር መንገዱን ከኪሳራ መታደጉ ይታወሳል።
በዚህ አስቸጋሪ ወቅት አቶ ፍፁም የስራ ባልደረቦቻቸውን በማስተባበር ቀን ከሌሊት በመስራት ብቃታቸውን እንዳስመሰከሩ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
አቶ ፍፁም በትምህርት ዝግጅታቸው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆን ከአሜሪካው ኒው ሃምፕሻየር ዩኒቨርስቲ እና ከእንግሊዙ ኦፕን ዩኒቨርስቲ ሁለት የማስተርስ ዲግሪ ወስደዋል።
አቶ ፍፁም የዛሬ ሁለት አመት ገደማ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ከለቀቁ በኋላ ኑሮዋቸውን ከቤተሰባቸው ጋር በአሜሪካ አድርገው የነበረ ሲሆን በቅርብ ቀን ግን ወደ ኬንያ፣ ናይሮቢ እንደሚያቀኑ ታውቋል።
ግለሰቡ በትግራይ ጦርነት ወቅት በአንዳንድ አክቲቪስቶች ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶባቸው የነበረ ሲሆን ይህ ስም የማጠልሸት ዘመቻ በተመሳሳይ የደረሰባቸው የአየር መንገዱ የቀድሞ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንዲሁ በተመሳሳይ ስራቸውን በመቀየር ለግዙፉ ደልታ አየር መንገድ በአማካሪነት መስራት መጀመራቸው ይታወሳል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተፎካካሪ የሆነው ኬንያ ኤርዌይስ ልምድ ያላቸውን ኢትዮጵያውያን እያፈላለገ በከፍተኛ ደሞዝ እየቀጠረ እንደሆነ ምንጮች ለመሠረት ሚዲያ ገልፀዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
3000
10:26
04.03.2025
imageImage preview is unavailable
የዲጂታል ካርታ ጥያቄ ያቀረቡ ተገልጋዮች ይዞታቸውን መነጠቃቸውን ተናገሩ
(መሠረት ሚድያ)- በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የዲጂታል ካርታ ጥያቄ ያቀረቡ ተገልጋዮች ይዞታቸው ለካራ ቆሬ አፓርታማ እንደተሰጠባቸው ተናገሩ።
ለመሠረት ሚዲያ አስተያየታቸውን የሰጡ ባለጉዳዮች እንዳሉት ለመኖሪያ ቤት የዲጂታል ካርታ ጥያቄ በኦላይን ካቀረቡና የአገልግሎት ክፍያ በቴሌ ብር በኩሉ እንዲከፍሉ ከተደረገ በኋላ የኦላይን አገልግሎቱ መቋረጡን እና ሰነዳችሁ አልተሟላም ተብለው በኦላይን መልስ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።
አገልግሎቱ ለምን እንደተቋረጠባቸው ለመጠየቅ ወደ ክፍለ ከተማው ባቀኑበት ጊዜ ደግሞ ይዞታቸው ለካራ ቆሬ አፓርታማ እንደተሰጠባቸው በመሃንዲሶች በኩል መገለጹን እንደሰሙ አስረድተዋል።
"መፍትሄ የሚሰጠን አካል የለም" የሚሉት የክፍለ ከተማው የዲጂታል ካርታ ተገልጋዮች "ለበርካታ አመታት ለፍተን የሰራነውን ቤትና ይዞታ በቀላሉ ለካራ ቆሬ አፓርታማ ተሰጥቷል መባሉን አንቀበልም" ብለዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የዲጂታል ካርታ ጥያቄ ያቀረቡ ተገልጋዮች ይዞታቸው ለካራ ቆሬ አፓርታማ እንደተሰጠባቸው ተናገሩ።
ለመሠረት ሚዲያ አስተያየታቸውን የሰጡ ባለጉዳዮች እንዳሉት ለመኖሪያ ቤት የዲጂታል ካርታ ጥያቄ በኦላይን ካቀረቡና የአገልግሎት ክፍያ በቴሌ ብር በኩሉ እንዲከፍሉ ከተደረገ በኋላ የኦላይን አገልግሎቱ መቋረጡን እና ሰነዳችሁ አልተሟላም ተብለው በኦላይን መልስ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።
አገልግሎቱ ለምን እንደተቋረጠባቸው ለመጠየቅ ወደ ክፍለ ከተማው ባቀኑበት ጊዜ ደግሞ ይዞታቸው ለካራ ቆሬ አፓርታማ እንደተሰጠባቸው በመሃንዲሶች በኩል መገለጹን እንደሰሙ አስረድተዋል።
"መፍትሄ የሚሰጠን አካል የለም" የሚሉት የክፍለ ከተማው የዲጂታል ካርታ ተገልጋዮች "ለበርካታ አመታት ለፍተን የሰራነውን ቤትና ይዞታ በቀላሉ ለካራ ቆሬ አፓርታማ ተሰጥቷል መባሉን አንቀበልም" ብለዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
2900
17:35
03.03.2025
imageImage preview is unavailable
የማስታወቂያ እድል ከመሠረት ሚድያ ጋር!
መሠረት ሚድያ በሶሻል ሚድያ አካውንቶቹ ላይ ውስን የማስታወቂያ እድሎችን ይዞ ቀርቧል፣ በዚህም መሠረት ማስታወቂያ ማሰራት የምትፈልጉ እና ተገቢውን ምዝገባ ያደረጋችሁ ድርጅቶች ልታነጋግሩን ትችላላችሁ።
ኢሜይል: [email protected]
*የምዝገባ ፈቃዳቸውን እና አድራሻቸውን የሚያቀርቡ አስተዋዋቂዎችን ብቻ እንቀበላለን
*ለግዜው የሪል እስቴት ማስታወቂያዎችን አንቀበልም
መሠረት ሚድያ
@MeseretMedia
መሠረት ሚድያ በሶሻል ሚድያ አካውንቶቹ ላይ ውስን የማስታወቂያ እድሎችን ይዞ ቀርቧል፣ በዚህም መሠረት ማስታወቂያ ማሰራት የምትፈልጉ እና ተገቢውን ምዝገባ ያደረጋችሁ ድርጅቶች ልታነጋግሩን ትችላላችሁ።
ኢሜይል: [email protected]
*የምዝገባ ፈቃዳቸውን እና አድራሻቸውን የሚያቀርቡ አስተዋዋቂዎችን ብቻ እንቀበላለን
*ለግዜው የሪል እስቴት ማስታወቂያዎችን አንቀበልም
መሠረት ሚድያ
@MeseretMedia
3000
16:41
28.02.2025
imageImage preview is unavailable
በአዲስ አበባ ከተማ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ መከሰቱን የጤና ባለሙያዎች ጠቆሙ
(መሠረት ሚድያ)- በመዲናዋ ውስጥ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) በሽታ እንደተከሰተ የጤና ባለሙያዎች ለሚድያችን በሰጡት ቃል አሳወቁ።
የበሽታው መከሰትን ለመሠረት ሚድያ ያረጋገጡት እነዚህ በአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ስር ባሉ ጤና ጣቢያ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ስጋቱ ለህዝብ ይፋ ሆኖ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በተመለከተ መልዕክት አለመተላለፉ የበለጠ ጉዳት እንዳያስከትል ስጋታቸውን ገልፀዋል።
"ሰሞኑ ከፍተኛ የአተት በሽታ ተከስቷል፣ ነገር ግን ምንም እየተባለ አይደለም። እኛም በየጤና ጣቢያ ሸራ ወጥራቹ ዝም ብላችሁ ስሩ እየተባልን ነው" ያለው አንድ የጤና ባለሙያ በአስደንጋጭ መልኩ 'vibrio cholerae' የተባለው የኮሌራ አምጪ ተህዋስም በምርመራ ወቅት በከተማው ውስጥ መገኘቱን ተናግሯል።
"እንደምናውቀው አተትም ሆነ ኮሌራ በጣም ተላላፊ ነው፣ ነገር ግን እየሆነ ያለው ነገር ፍፁም ተቃራኒ ነው" የሚሉት የጤና ባለሙያዎቹ ከ100 በላይ የበሽታው ተጠቂዎች አሁን ላይ ባሻ ወልዴ ተብሎ በሚጠራው የአራዳ ክፍለ ከተማ ጤና ማዕከል ገብተው እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።
"አሁን በዚህ ሰአት በርካታ ታማሚዎችን ካለ በቂ መከላከያ እና መሸፈኛ እያከምን ነው፣ አስቸኳይ መፍትሄ እንሻለን" ያሉን ሌላኛው የጤና ባለሙያ ናቸው።
ከሰሞኑ በጋምቤላ ክልል ኑዌር ብሔረሰብ ዞን አራት ወረዳዎች የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ ተከስቶ የዘጠኝ ሰዎችን ሕይወት መንጠቁ ታውቋል።
በዚህ ዙርያ ከጤና ሚኒስቴር ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በመሞከር ማብራርያ እናቀርባለን።
ፎቶ: ፋይል
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- በመዲናዋ ውስጥ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት (አተት) በሽታ እንደተከሰተ የጤና ባለሙያዎች ለሚድያችን በሰጡት ቃል አሳወቁ።
የበሽታው መከሰትን ለመሠረት ሚድያ ያረጋገጡት እነዚህ በአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ስር ባሉ ጤና ጣቢያ የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ስጋቱ ለህዝብ ይፋ ሆኖ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በተመለከተ መልዕክት አለመተላለፉ የበለጠ ጉዳት እንዳያስከትል ስጋታቸውን ገልፀዋል።
"ሰሞኑ ከፍተኛ የአተት በሽታ ተከስቷል፣ ነገር ግን ምንም እየተባለ አይደለም። እኛም በየጤና ጣቢያ ሸራ ወጥራቹ ዝም ብላችሁ ስሩ እየተባልን ነው" ያለው አንድ የጤና ባለሙያ በአስደንጋጭ መልኩ 'vibrio cholerae' የተባለው የኮሌራ አምጪ ተህዋስም በምርመራ ወቅት በከተማው ውስጥ መገኘቱን ተናግሯል።
"እንደምናውቀው አተትም ሆነ ኮሌራ በጣም ተላላፊ ነው፣ ነገር ግን እየሆነ ያለው ነገር ፍፁም ተቃራኒ ነው" የሚሉት የጤና ባለሙያዎቹ ከ100 በላይ የበሽታው ተጠቂዎች አሁን ላይ ባሻ ወልዴ ተብሎ በሚጠራው የአራዳ ክፍለ ከተማ ጤና ማዕከል ገብተው እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።
"አሁን በዚህ ሰአት በርካታ ታማሚዎችን ካለ በቂ መከላከያ እና መሸፈኛ እያከምን ነው፣ አስቸኳይ መፍትሄ እንሻለን" ያሉን ሌላኛው የጤና ባለሙያ ናቸው።
ከሰሞኑ በጋምቤላ ክልል ኑዌር ብሔረሰብ ዞን አራት ወረዳዎች የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት በሽታ ተከስቶ የዘጠኝ ሰዎችን ሕይወት መንጠቁ ታውቋል።
በዚህ ዙርያ ከጤና ሚኒስቴር ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በመሞከር ማብራርያ እናቀርባለን።
ፎቶ: ፋይል
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
2700
16:41
28.02.2025
imageImage preview is unavailable
የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት ቦታው ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያ ስለሚፈለግ እንዲነሳ ታዘዘ
(መሠረት ሚድያ)- እድሜ ጠገቡ የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት እና የግሪክ ክበብ አሁን ላይ የሚገኙበት ቦታ ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያነት ስለሚፈለግ እንዲነሱ እንደተነገራቸው ማረጋገጥ ችለናል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 የመሬት ልማት እና አስተዳደር ፅ/ቤት በቅርቡ ለትምህርት ቤቱ እና ክበቡ በፃፈው ደብዳቤ ይዞታው ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያነት እንደሚፈለግ ገልጿል።
ትምህርት ቤቱ ደብዳቤው እንደደረሰው ለቦርዱ እንዲሁም ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ለትምህርት ሚኒስቴር እና ሌሎች ለሚመለከታቸው አካላት ማሳወቁን እና መልካም ምላሽ እየጠበቀ መሆኑን መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ይጠቁማል።
ከአንድ አመት ተኩል በፊት የግሪክ ኮሚኒቲ ት/ቤት ከፍርድ ቤት የእግድ ትዕዛዝ ውጪ ግቢው በፖሊስ እንደተያዘበት ለህዝብ አሳውቆ ነበር። በወቅቱ ጉዳዩን ሰምተው ለማብረድ ወደ ስፍራው ያቀኑት በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር እንደተገፈተሩ እና ከግቢው ለቀው እንዲወጡ እንደተደረጉ ይታወሳል።
"አምና ትምህርት ቤቱ ላይ ያ ሁሉ ወከባ እና የስም ማጥፋት ሲደርስ ለምን እንደነበር የገባን አሁን ነው፣ መሬቱን ለመንጠቅ የተጠነሰሰ ሴራ ነበር" በማለት አስተያየታቸውን የሰጡ አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ የኮሚኒቲው አባል ደብዳቤው ለብዙዎች አስደንጋጭ እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል።
የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት ለበርካታ አስርት አመታት ተማሪዎችን ተቀብሎ ሲያስተምር የቆየ ሲሆን የግሪክ ኮሚኒቲ በኢትዮጵያ ያለውን ከ200 አመት በላይ ታሪክ ይዞ የቆየ መሆኑ ይነገርለታል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- እድሜ ጠገቡ የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት እና የግሪክ ክበብ አሁን ላይ የሚገኙበት ቦታ ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያነት ስለሚፈለግ እንዲነሱ እንደተነገራቸው ማረጋገጥ ችለናል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 የመሬት ልማት እና አስተዳደር ፅ/ቤት በቅርቡ ለትምህርት ቤቱ እና ክበቡ በፃፈው ደብዳቤ ይዞታው ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያነት እንደሚፈለግ ገልጿል።
ትምህርት ቤቱ ደብዳቤው እንደደረሰው ለቦርዱ እንዲሁም ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ለትምህርት ሚኒስቴር እና ሌሎች ለሚመለከታቸው አካላት ማሳወቁን እና መልካም ምላሽ እየጠበቀ መሆኑን መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ይጠቁማል።
ከአንድ አመት ተኩል በፊት የግሪክ ኮሚኒቲ ት/ቤት ከፍርድ ቤት የእግድ ትዕዛዝ ውጪ ግቢው በፖሊስ እንደተያዘበት ለህዝብ አሳውቆ ነበር። በወቅቱ ጉዳዩን ሰምተው ለማብረድ ወደ ስፍራው ያቀኑት በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር እንደተገፈተሩ እና ከግቢው ለቀው እንዲወጡ እንደተደረጉ ይታወሳል።
"አምና ትምህርት ቤቱ ላይ ያ ሁሉ ወከባ እና የስም ማጥፋት ሲደርስ ለምን እንደነበር የገባን አሁን ነው፣ መሬቱን ለመንጠቅ የተጠነሰሰ ሴራ ነበር" በማለት አስተያየታቸውን የሰጡ አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ የኮሚኒቲው አባል ደብዳቤው ለብዙዎች አስደንጋጭ እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል።
የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት ለበርካታ አስርት አመታት ተማሪዎችን ተቀብሎ ሲያስተምር የቆየ ሲሆን የግሪክ ኮሚኒቲ በኢትዮጵያ ያለውን ከ200 አመት በላይ ታሪክ ይዞ የቆየ መሆኑ ይነገርለታል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
1800
16:41
28.02.2025
ዋልታ ከፋና ጋር ከተዋሀደ በኋላ በርካታ የስራ ቅጥሮች በትውውቅ እየተፈፀሙ እንደሚገኙ ሰራተኞች ተናገሩ
(መሠረት ሚድያ)- ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በቅርቡ ከዋልታ ሚድያ እና ኮሙኒኬሽን ማዕከል ጋር ውህደት መፈፀሙን ተከትሎ በርካታ ህገወጥ የሆኑ የትውውቅ የስራ ቅጥሮች እንደተፈፀሙ ሰራተኞች ተናግረዋል።
እነዚህ ሰራተኞች ለመሠረት ሚድያ በሰጡት ጥቆማ ፋና ውህደቱን ተከትሎ አብዛኛውን ነባር፣ ጠንካራ እና ታታሪ የሚባሉ ሰራተኞቹን ያገለለ የደረጃ ሹመት ሰጥቷል ብለዋል።
"በሹመቱ 95 ፐርሰንት የሚሆነውን ቦታ ያገኙት የቀድሞዋ የፋና ብሮድካስቲንግ ባልደረባ፣ የአሁኗ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ የቅርብ ወዳጆች ናቸው" የሚሉት ሰራተኞቹ ከዳይሬክተር እስከ ስራ አስፈጻሚነት ደረጃ እንዲሾሙ የተደረጉት በዚህ መልኩ መሆኑን አስረድተዋል።
ቀደም ሲል ለሀገርና ለተቋሙ በታታሪነት የሚሰሩ ሰዎች እንዲገፉ ምክንያት ሆኗል በተባለው አካሄድ ዙርያ አስተያየት የሰጡን አንድ የተቋሙ ሰራተኛ "እንደበቀል እንዳያድጉ እና እንዲገፉ የተደረጉ በርካቶች ናቸው" ብለዋል። በሌላ በኩል ካለምንም መስፈርት፣ ብቃትና ለዘርፉ ልምድ ሳይኖራቸው በስራ አስፈጻሚነት እና በዳይሬክተርነት እንዲሾሙ የተደረጉ በርካቶች እንዳሉ ከነማስረጃው ለሚድያችን ሰጥተዋል።
መሠረት ሚድያ የተመለከተው አንድ የተቋሙ የቅርብ የቅጥር አካሄድ ከዳይሬክተር በታች ያሉት ብቻ ለውድድር ክፍት ሆነው ሌላውን በሹመት መፈፀሙን ያመላክታሉ። በዋልታ ይሰሩ የነበሩ በርካታ አንጋፋ ባለሙያዎችም ከስራ እንደተገለሉ ወይም ዝቅ ብለው እንዲሰሩ እንደተደረጉ በተጨማሪ ታውቋል።
ሚድያውን በዚህ ዙርያ ለማነጋገር የሞከርን ቢሆንም ምላሽ አላገኘንም፣ ወደፊት ተጨማሪ ማብራርያ ካገኘን በዜናው ዙርያ እንመለስበታለን።
ከፋና በተጨማሪ በሌላኛው የመንግስት ሚድያ ኢቢሲ ውስጥ 400 ሰራተኞች በሀሰተኛ ወይም ፎርጅድ ዶክመንት ተቀጥረው መገኘታቸውን መሠረት ሚድያ በቅርቡ መዘገቡ ይታወሳል። ይህን የኢቢሲ ድርጊት ያጋለጠው የተቋሙ ሰራተኛ የሽብር ክስ ቀርቦበት ለእስር ተዳርጎ እንደነበር መረጃ አቅርበን ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በቅርቡ ከዋልታ ሚድያ እና ኮሙኒኬሽን ማዕከል ጋር ውህደት መፈፀሙን ተከትሎ በርካታ ህገወጥ የሆኑ የትውውቅ የስራ ቅጥሮች እንደተፈፀሙ ሰራተኞች ተናግረዋል።
እነዚህ ሰራተኞች ለመሠረት ሚድያ በሰጡት ጥቆማ ፋና ውህደቱን ተከትሎ አብዛኛውን ነባር፣ ጠንካራ እና ታታሪ የሚባሉ ሰራተኞቹን ያገለለ የደረጃ ሹመት ሰጥቷል ብለዋል።
"በሹመቱ 95 ፐርሰንት የሚሆነውን ቦታ ያገኙት የቀድሞዋ የፋና ብሮድካስቲንግ ባልደረባ፣ የአሁኗ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ የቅርብ ወዳጆች ናቸው" የሚሉት ሰራተኞቹ ከዳይሬክተር እስከ ስራ አስፈጻሚነት ደረጃ እንዲሾሙ የተደረጉት በዚህ መልኩ መሆኑን አስረድተዋል።
ቀደም ሲል ለሀገርና ለተቋሙ በታታሪነት የሚሰሩ ሰዎች እንዲገፉ ምክንያት ሆኗል በተባለው አካሄድ ዙርያ አስተያየት የሰጡን አንድ የተቋሙ ሰራተኛ "እንደበቀል እንዳያድጉ እና እንዲገፉ የተደረጉ በርካቶች ናቸው" ብለዋል። በሌላ በኩል ካለምንም መስፈርት፣ ብቃትና ለዘርፉ ልምድ ሳይኖራቸው በስራ አስፈጻሚነት እና በዳይሬክተርነት እንዲሾሙ የተደረጉ በርካቶች እንዳሉ ከነማስረጃው ለሚድያችን ሰጥተዋል።
መሠረት ሚድያ የተመለከተው አንድ የተቋሙ የቅርብ የቅጥር አካሄድ ከዳይሬክተር በታች ያሉት ብቻ ለውድድር ክፍት ሆነው ሌላውን በሹመት መፈፀሙን ያመላክታሉ። በዋልታ ይሰሩ የነበሩ በርካታ አንጋፋ ባለሙያዎችም ከስራ እንደተገለሉ ወይም ዝቅ ብለው እንዲሰሩ እንደተደረጉ በተጨማሪ ታውቋል።
ሚድያውን በዚህ ዙርያ ለማነጋገር የሞከርን ቢሆንም ምላሽ አላገኘንም፣ ወደፊት ተጨማሪ ማብራርያ ካገኘን በዜናው ዙርያ እንመለስበታለን።
ከፋና በተጨማሪ በሌላኛው የመንግስት ሚድያ ኢቢሲ ውስጥ 400 ሰራተኞች በሀሰተኛ ወይም ፎርጅድ ዶክመንት ተቀጥረው መገኘታቸውን መሠረት ሚድያ በቅርቡ መዘገቡ ይታወሳል። ይህን የኢቢሲ ድርጊት ያጋለጠው የተቋሙ ሰራተኛ የሽብር ክስ ቀርቦበት ለእስር ተዳርጎ እንደነበር መረጃ አቅርበን ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
2700
09:51
27.02.2025
የዲጂታል ስክሪን ማስታወቂያ ባለቤቶች ከነገ ጀምሮ የብልፅግና ፓርቲ ማስታወቂያን በግዴታ እንዲያሳዩ ሊደረጉ መሆኑ ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የዲጂታል ስክሪን ማስታወቂያ ባለቤቶች እና ህንፃዎቻቸው ላይ የማስታወቂያ ስክሪን የገጠሙ ባለሀብቶች ከነገ ጀምሮ የብልጽግና ፓርቲ መልእክት የሆኑ ምስሎችን እና ጽሁፎችን በአስገዳጅነት እንዲያሰራጩ ጥብቅ ትዕዛዝ እንደተላለፈላቸው ታውቋል።
በራሳቸው ወጪ አውጥተው የሰሩትን የዲጂታል ስክሪን ለፖለቲካ ፓርቲ መልዕክት ማስተላለፊያ መደረጉ በህዝብ ዘንድ ለአንድ ወገን ያደሉ ወይም የፓርቲ አባል እንደሆኑ እንዳይወሰድባቸው የሰጉት ግለሰቦቹ አማራጭ እንዳጡ እና አጣብቂኝ ውስጥ እንደገቡ ተናግረዋል።
የብልጽግና ሹሞች ቁጣ በተቀላቀለበት መልዕክት በአስገዳጅነት ማስታወቂያውን ከነገ ጀምሮ ለማሰራጨት እንዳስገደዷቸው ጨምረው ተናግረዋል።
"ከሳምንት በፊት ለአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መሪዎች ሲመጡ 'እንኳን ደህና መጣችሁ' የሚልና ስለ አፍሪካ ህብረት ስብሰባ ተመሳሳይ ትዕዛዝ ተላልፎ ያስተላለፍነው የፖለቲካ ይዘት የሌለው በመሆኑ ነበር" የሚሉት የማስታወቂያ ድርጅቶቹ "አሁን የታዘዝነው የፖለቲካ ፓርቲ መልእክት ገበያው በተዳከመበት መሀል ከህዝቡ ጋር እንዳያቃቅረን ስጋት አለን" ብለዋል።
በሌላ በኩል በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ወቅት በርካታ የመኪና ኪራይ ስራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች ተሽከርካሪዎቻቸውን በነፃ ለስብሰባው አገልግሎት እንዲሰጡ ተገደው እንደነበር ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
"ቢዝነስ በተዳከመበት በዚህ ወቅትም ይሁን ድሮ በአመት አንዴ ጥሩ ስራ የምንሰራው እንደ አፍሪካ ህብረት ያሉ ስብሰባዎች ሲመጡ ነበር" የሚሉት የመኪና አከራዮቹ አሁን ግን እሱንም በግዴታ እንደተነጠቁ እና መኪናዎቻቸው የተመለሱላቸው ስብሰባው ካለቀ በኋላ መሆኑን አስረድተዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የዲጂታል ስክሪን ማስታወቂያ ባለቤቶች እና ህንፃዎቻቸው ላይ የማስታወቂያ ስክሪን የገጠሙ ባለሀብቶች ከነገ ጀምሮ የብልጽግና ፓርቲ መልእክት የሆኑ ምስሎችን እና ጽሁፎችን በአስገዳጅነት እንዲያሰራጩ ጥብቅ ትዕዛዝ እንደተላለፈላቸው ታውቋል።
በራሳቸው ወጪ አውጥተው የሰሩትን የዲጂታል ስክሪን ለፖለቲካ ፓርቲ መልዕክት ማስተላለፊያ መደረጉ በህዝብ ዘንድ ለአንድ ወገን ያደሉ ወይም የፓርቲ አባል እንደሆኑ እንዳይወሰድባቸው የሰጉት ግለሰቦቹ አማራጭ እንዳጡ እና አጣብቂኝ ውስጥ እንደገቡ ተናግረዋል።
የብልጽግና ሹሞች ቁጣ በተቀላቀለበት መልዕክት በአስገዳጅነት ማስታወቂያውን ከነገ ጀምሮ ለማሰራጨት እንዳስገደዷቸው ጨምረው ተናግረዋል።
"ከሳምንት በፊት ለአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መሪዎች ሲመጡ 'እንኳን ደህና መጣችሁ' የሚልና ስለ አፍሪካ ህብረት ስብሰባ ተመሳሳይ ትዕዛዝ ተላልፎ ያስተላለፍነው የፖለቲካ ይዘት የሌለው በመሆኑ ነበር" የሚሉት የማስታወቂያ ድርጅቶቹ "አሁን የታዘዝነው የፖለቲካ ፓርቲ መልእክት ገበያው በተዳከመበት መሀል ከህዝቡ ጋር እንዳያቃቅረን ስጋት አለን" ብለዋል።
በሌላ በኩል በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ወቅት በርካታ የመኪና ኪራይ ስራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች ተሽከርካሪዎቻቸውን በነፃ ለስብሰባው አገልግሎት እንዲሰጡ ተገደው እንደነበር ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
"ቢዝነስ በተዳከመበት በዚህ ወቅትም ይሁን ድሮ በአመት አንዴ ጥሩ ስራ የምንሰራው እንደ አፍሪካ ህብረት ያሉ ስብሰባዎች ሲመጡ ነበር" የሚሉት የመኪና አከራዮቹ አሁን ግን እሱንም በግዴታ እንደተነጠቁ እና መኪናዎቻቸው የተመለሱላቸው ስብሰባው ካለቀ በኋላ መሆኑን አስረድተዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
3400
12:33
23.02.2025
close
Reviews channel
keyboard_arrow_down
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
5.0
1 reviews over 6 months
Excellent (100%) In the last 6 months
c
**ffeennew@******.io
On the service since June 2022
15.01.202515:12
5
Everything is fine. Thank you!
New items
Channel statistics
Rating
17.6
Rating reviews
5.0
Сhannel Rating
1
Followers:
12.8K
APV
lock_outline
ER
7.5%
Posts per day:
0.0
CPM
lock_outlineSelected
0
channels for:$0.00
Followers:
0
Views:
lock_outline
Add to CartBuy for:$0.00
Комментарий