
Get clients in any niche!
Delegate the launch of advertising to us — for free
Learn more
17.6

Advertising on the Telegram channel «አማራ ሚዲያ ማዕከል Amhara media center»
5.0
Share
Add to favorite
Channel temporarily not accepting requests
Choose another channel from recommendations or get a tailored list within your budget using AI
AI Channel Picker
Recent Channel Posts
imageImage preview is unavailable
#ዜናመሠረት የህክምና ባለሙያዎችን ድምፅ ያስተጋቡ አንድ ዶክተር ከድሬዳዋ ከተማ ተሰናብተው ገጠር ሄደው እንዲሰሩ ተወሰነባቸው
- የድሬዳዋ ጤና ባለሞያዎች ድርጊቱን ተቃውመው ፊርማ ማሰባሰብ ጀምረዋል
(መሠረት ሚድያ)- በድሬዳዋ ከተማ በሚገኘው ሳቢያን አጠቃላይ ሆስፒታል ሰራተኛ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት እና ከሰሞኑ የጤና ባለሙያዎች ያሰሙትን ድምፅ ያስተጋቡ አንድ ጠቅላላ ሐኪም የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸው ገጠር ሄደው እንዲሰሩ እንደተወሰነባቸው ታወቀ።
መሠረት ሚድያ የተመለከተው እና ሚያዝያ 9/2017 ዓ/ም በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ የተፃፈው ደብዳቤ ዶ/ር ሀብታሙ አለሙ የተባሉት እኚህ የጤና ባለሙያ 'የሙያ ስነምግባርን የተፃረረ ድርጊት' መፈፀማቸውን ጠቅሶ ጉዳዩ ባለመታረሙ አሁን ከሚሰሩበት የድሬዳዋው ሳቢያን ሆስፒታል ወደ ለገኦዳ ጉዱንፈታ ጤና ጣብያ እንዲዛወሩ መደረጋቸውን ይገልፃል።
"የዛሬ ወር ገደማ ቋሚ ቅጥር ከሳቢያን ሆስፒታል ጋር ፈፅሜያለሁ። ይህ ሆኖ እያለ ከሰሞኑ እኛ የኢትዮጵያ የጤና ተቋማት ሰራተኞች ድምፅ እያሰማን መሆኑን ተከትሎ እኔም አንዳንድ ፅሁፎችን ስላወጣሁ ኢላማ ተደርጌያለሁ" ያሉት ዶ/ር ሀብታሙ ውሳኔው ከመተላለፉ በፊት ባሉት ቀናት ስልክ እየተደወለ በጤና ባለሙያዎች እንቅስቃሴ ዙርያ አስተያየት እንዳይሰጡ ማስፈራርያ ሲደርሳቸው እንደነበር ጠቅሰዋል።
"እኔ በበኩሌ ጉዳዩ የመኖር እና አለመኖር መሆኑን ጠቅሼ እንደማላቆም ነገሬያቸዋለሁ። የከተማው ጤና ቢሮ ሀላፊ የሆኑትን ዶ/ር ፅጌረዳን ለማናገር ብሞክርም ያልተገባ ነገር ተናግረውኝ ስልክ ዘግተውብኛል" የሚሉት የጤና ባለሙያው ከዚያም እኚህ ሀላፊ ዶ/ር ሀብታሙ ወደሚሰሩበት ሆስፒታል በመደወል ከስራቸው እንዲታገዱ ማድረጋቸውን መስማታቸውን ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
ዶ/ር ሀብታሙ በቅርቡ 'Hakim' የተባለ የፌስቡክ ገፅ ላይ በርካቶች የተመለከቱት አንድ ፅሁፍ አጋርተው የነበረ ሲሆን እሱም "ስራዬ አድካሚ ቢሆንም፣ ደሞዜ ከ10,000ብር በታች ቢሆንም፣ የአእምሮ እርካታ ይሰጠኛል። ሆኖም... እርካታ ቤት ኪራይ አይከፍልም። እርካታ በቀን 3 ጊዜ መብላት አያስችልም። እርካታ ልጆቼን ለማስተማር አያስችልም። እርካታ ልብስ እና ጫማ ለመቀየር አያስችልም። እርካታ ትዳር መመስረት አያስችልም። እርካታ ለታክሲ ወረፋ ከመጠበቅ አያድንም። ጥያቄያችን ለሁሉም ግልፅ የሆነ ነው። የሚገባንን እንኳን ባይሆን የሚያስፈልገን ይደረግልን። ትኩረት ለጤና ባለሞያዎች!" የሚል ነበር።
ዶ/ር ሀብታሙ ለመሠረት ሚድያ በሰጡት ቃል ተወልደው ባደጉበት የድሬዳዋ ከተማ እስካሁን እየሰሩ እንዲቆዩ የፈለጉበት ምክንያት በፅኑ ህመም አጋጥሟቸው የእለት ተእለት ክትትል የሚያስፈገልጋቸው የቤተሰብ አባል ስላላቸው በመሆኑ እና እሳቸውም ብቸኛ አስታማሚ መሆናቸውን አስረድተው ይህን የሚያሳይ የድል ጮራ ሆስፒታል ዶክመንት ለሚድያችን አሳይተዋል።
በተላለፈው የቅጣት ውሳኔ ላይ ለድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ቅሬታ እያስገቡ የሚገኙት የድሬዳዋ ጤና ባለሞያዎች ፊርማ ማሰባሰብ ጀምረዋል።
"የሞያ አጋራችን የሆኑት ዶ/ር ሀብታሙ አለሙ በሞያቸው የተመሰገኑ፣ ትሁት፣ ስራቸውን የሚወዱ እና ሀላፊነታቸውን በአግባቡ የሚወጡ፣ በታካሚ እና በስራቸው ጉዳይ የማይደራደሩ ከዛም አልፎ ከስራቸው ውጪ በበርካታ የበጎ አድራጎት ስራዎቻቸው የሚታወቁ ከተማችን ወደፊት ከሳቸው ብዙ ምትጠብቅባቸው ወጣት ሀኪም ናቸው" ያሉት የድሬዳዋ ጤና ባለሞያዎች ስማቸውን ከማይገናኝ ነገር ጋር በማያያዝ፤ በማጠልሸት እና የሌላቸውን ስብዕና በመስጠት አግባብ ያልሆነ የውሸት ክስ በመደርደር በድሬዳዋ ከተማ ጤና ቢሮ የተሰጠውን ውሳኔ ኮንነዋል።
"የተሰነዘረባቸው ከእውነት የራቀ የሀሰት ክስ ትክክል እንዳልሆነ እኛ በቅርበት አብረናቸው የምንሰራ እና የምናውቃቸው የጤና ባለሞያዎች እና የሞያ አጋሮቻቸው በቂ ምስክሮች ነን" በማለት የቀረበበት ክስ እውነት እንኳ ቢሆን ቀድሞ ክስ ሊያቀርብበት እና የስነምግባር ግድፈት ተገኝቶበታል ብሎ ውሳኔ ማስተላለፍ የሚችለው እየሰራ የሚገኝበት ሆስፒታል እንጂ ባለሞያውን በቅርበት የማያውቀው አካል አይደለም ብለዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- የድሬዳዋ ጤና ባለሞያዎች ድርጊቱን ተቃውመው ፊርማ ማሰባሰብ ጀምረዋል
(መሠረት ሚድያ)- በድሬዳዋ ከተማ በሚገኘው ሳቢያን አጠቃላይ ሆስፒታል ሰራተኛ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት እና ከሰሞኑ የጤና ባለሙያዎች ያሰሙትን ድምፅ ያስተጋቡ አንድ ጠቅላላ ሐኪም የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸው ገጠር ሄደው እንዲሰሩ እንደተወሰነባቸው ታወቀ።
መሠረት ሚድያ የተመለከተው እና ሚያዝያ 9/2017 ዓ/ም በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ የተፃፈው ደብዳቤ ዶ/ር ሀብታሙ አለሙ የተባሉት እኚህ የጤና ባለሙያ 'የሙያ ስነምግባርን የተፃረረ ድርጊት' መፈፀማቸውን ጠቅሶ ጉዳዩ ባለመታረሙ አሁን ከሚሰሩበት የድሬዳዋው ሳቢያን ሆስፒታል ወደ ለገኦዳ ጉዱንፈታ ጤና ጣብያ እንዲዛወሩ መደረጋቸውን ይገልፃል።
"የዛሬ ወር ገደማ ቋሚ ቅጥር ከሳቢያን ሆስፒታል ጋር ፈፅሜያለሁ። ይህ ሆኖ እያለ ከሰሞኑ እኛ የኢትዮጵያ የጤና ተቋማት ሰራተኞች ድምፅ እያሰማን መሆኑን ተከትሎ እኔም አንዳንድ ፅሁፎችን ስላወጣሁ ኢላማ ተደርጌያለሁ" ያሉት ዶ/ር ሀብታሙ ውሳኔው ከመተላለፉ በፊት ባሉት ቀናት ስልክ እየተደወለ በጤና ባለሙያዎች እንቅስቃሴ ዙርያ አስተያየት እንዳይሰጡ ማስፈራርያ ሲደርሳቸው እንደነበር ጠቅሰዋል።
"እኔ በበኩሌ ጉዳዩ የመኖር እና አለመኖር መሆኑን ጠቅሼ እንደማላቆም ነገሬያቸዋለሁ። የከተማው ጤና ቢሮ ሀላፊ የሆኑትን ዶ/ር ፅጌረዳን ለማናገር ብሞክርም ያልተገባ ነገር ተናግረውኝ ስልክ ዘግተውብኛል" የሚሉት የጤና ባለሙያው ከዚያም እኚህ ሀላፊ ዶ/ር ሀብታሙ ወደሚሰሩበት ሆስፒታል በመደወል ከስራቸው እንዲታገዱ ማድረጋቸውን መስማታቸውን ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
ዶ/ር ሀብታሙ በቅርቡ 'Hakim' የተባለ የፌስቡክ ገፅ ላይ በርካቶች የተመለከቱት አንድ ፅሁፍ አጋርተው የነበረ ሲሆን እሱም "ስራዬ አድካሚ ቢሆንም፣ ደሞዜ ከ10,000ብር በታች ቢሆንም፣ የአእምሮ እርካታ ይሰጠኛል። ሆኖም... እርካታ ቤት ኪራይ አይከፍልም። እርካታ በቀን 3 ጊዜ መብላት አያስችልም። እርካታ ልጆቼን ለማስተማር አያስችልም። እርካታ ልብስ እና ጫማ ለመቀየር አያስችልም። እርካታ ትዳር መመስረት አያስችልም። እርካታ ለታክሲ ወረፋ ከመጠበቅ አያድንም። ጥያቄያችን ለሁሉም ግልፅ የሆነ ነው። የሚገባንን እንኳን ባይሆን የሚያስፈልገን ይደረግልን። ትኩረት ለጤና ባለሞያዎች!" የሚል ነበር።
ዶ/ር ሀብታሙ ለመሠረት ሚድያ በሰጡት ቃል ተወልደው ባደጉበት የድሬዳዋ ከተማ እስካሁን እየሰሩ እንዲቆዩ የፈለጉበት ምክንያት በፅኑ ህመም አጋጥሟቸው የእለት ተእለት ክትትል የሚያስፈገልጋቸው የቤተሰብ አባል ስላላቸው በመሆኑ እና እሳቸውም ብቸኛ አስታማሚ መሆናቸውን አስረድተው ይህን የሚያሳይ የድል ጮራ ሆስፒታል ዶክመንት ለሚድያችን አሳይተዋል።
በተላለፈው የቅጣት ውሳኔ ላይ ለድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ቅሬታ እያስገቡ የሚገኙት የድሬዳዋ ጤና ባለሞያዎች ፊርማ ማሰባሰብ ጀምረዋል።
"የሞያ አጋራችን የሆኑት ዶ/ር ሀብታሙ አለሙ በሞያቸው የተመሰገኑ፣ ትሁት፣ ስራቸውን የሚወዱ እና ሀላፊነታቸውን በአግባቡ የሚወጡ፣ በታካሚ እና በስራቸው ጉዳይ የማይደራደሩ ከዛም አልፎ ከስራቸው ውጪ በበርካታ የበጎ አድራጎት ስራዎቻቸው የሚታወቁ ከተማችን ወደፊት ከሳቸው ብዙ ምትጠብቅባቸው ወጣት ሀኪም ናቸው" ያሉት የድሬዳዋ ጤና ባለሞያዎች ስማቸውን ከማይገናኝ ነገር ጋር በማያያዝ፤ በማጠልሸት እና የሌላቸውን ስብዕና በመስጠት አግባብ ያልሆነ የውሸት ክስ በመደርደር በድሬዳዋ ከተማ ጤና ቢሮ የተሰጠውን ውሳኔ ኮንነዋል።
"የተሰነዘረባቸው ከእውነት የራቀ የሀሰት ክስ ትክክል እንዳልሆነ እኛ በቅርበት አብረናቸው የምንሰራ እና የምናውቃቸው የጤና ባለሞያዎች እና የሞያ አጋሮቻቸው በቂ ምስክሮች ነን" በማለት የቀረበበት ክስ እውነት እንኳ ቢሆን ቀድሞ ክስ ሊያቀርብበት እና የስነምግባር ግድፈት ተገኝቶበታል ብሎ ውሳኔ ማስተላለፍ የሚችለው እየሰራ የሚገኝበት ሆስፒታል እንጂ ባለሞያውን በቅርበት የማያውቀው አካል አይደለም ብለዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
476
15:41
24.04.2025
imageImage preview is unavailable
1300
13:27
20.04.2025
#ዜናመሠረት "እውነት ነው ለማኔጅመንት አባላት ቦነስ ከፍለናል። የተከፈለው የአንድ ወር ደመወዝ ብቻ ነው"- የኢትዮጵያ ፖስታ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ጋሻው መርሻ
- አቶ ጋሻው ለመሠረት ሚድያ ዘገባ ስድብ የተቀላቀለበት ምላሽ ሰጥተዋል
(መሠረት ሚድያ)- የኢትዮጵያ ፖስታ (Ethio Post) በነገው እለት ለሚከበረው የትንሳኤ በዓል ከማናጀር በላይ ላሉ ሀላፊዎቹ ብቻ የሁለት ወር ደሞዝ ቦነስ መስጠቱን መሠረት ሚድያ ማምሻውን መዘገቡ ይታወቃል።
በርካታ የተቋሙ ሰራተኞች በትናንትናው እለት የሰሙት እና "እጅግ አሳዛኝ" ብለው የገለፁት ድርጊት የኑሮ ውድነት ተባብሶ ታች ያለው ሰራተኛ ሲቸገር ከፍ ያለ ደሞዝ ያላቸው ቦነስ ብለው ብር መከፋፈላቸው እንዳስቆጣቸው ገልፀው ነበር።
ለዚህ ዜና በመሠረት ሚድያ የፌስቡክ ገፅ ላይ ስድብ የተቀላቀለበት ምላሽ ያስቀመጡት የኢትዮጵያ ፖስታ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ጋሻው መርሻ "እውነት ነው ለማኔጅመንት አባላት ቦነስ ከፍለናል። የተከፈለው የአንድ ወር ደመወዝ ብቻ ነው" ብለዋል።
መሠረት ሚድያ የተሰነዘረውን ስድብ ለማቅረብ ኤዲቶሪያ ፖሊሲው አይፈቅድም፣ ይሁንና አቶ ጋሻው ከስድብ ውጭ ያስቀመጡትን ፅሁፍ እንዲህ በቀጥታ ያቀርበዋል:
"እውነት ነው ለማኔጅመንት አባላት ቦነስ ከፍለናል። የተከፈለው የአንድ ወር ደመወዝ ብቻ ነው። ይኸው ቦነስ ለመላው ሰራተኛ በመስከረም ወር ተከፍሏል። ለማኔጅመንት አባላት እስካሁን ያልተከፈለው ከኦዲት ጋር በተያያዘ ብቻ ነበር። ኦዲቱ ሲጠናቀቅ አሁን ተከፈለ። ምንድን ነው ችግሩ?" ብለዋል።
"ከጥበቃ ጀምሮ እስከ ሱፐርቫይዘር ድረስ ያለው ሰራተኛ በኑሮ ውድነት እየተጠበሰ፣ ደሞዝ ይጨመርልኛል ብሎ ሲያስብ ከማናጀር በላይ ላሉት ብቻ የ2 ወር ደሞዝ ቦነስ ተብሎ የተቋሙን ገንዘብ መቀራመታቸው አሳዝኖናል፣ እነሱ በቦነሱ ብቻ ከ80,000 እስከ 212,000 ሲከፋፈሉ ተራው ሰራተኛ ለበዓል ዶሮ መግዣ አጥቶ ይውላል" ብለው ለመሠረት ሚድያ የተናገሩት አንድ የተቋሙ ሰራተኛ ናቸው።
አሁን ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከ2,200 በላይ ሰራተኞች ያሉት ሲሆን የሰራተኞቹ ደሞዝ ከ4,000 ብር ጀምሮ እስከ 106,000 ብር እንደሚደርስ ለሚድያችን የደረሰ አንድ መረጃ ያሳያል።
አብዛኛው ሰራተኛ ጠቅላላ ደሞዙ ከ16,800 ብር በታች ሲሆን የሀላፊዎቹ ደግሞ ጥቅማ ጥቅም ሳይጨምር ማናጀር 40,300፣ ዳይሬክተር 56,400 ብር፣ ቺፍ ኦፊሰር 76,300 ብር እንዲሁም ዋና ስራ አስፈፃሚ 106,100 ብር እንደሚያገኙ ይህ መረጃችን ያሳያል።
"ከስራ አስኪያጅ ጀምሮ ለፋሲካ በዓል የሁለት ወር ጉርሻ ለራሳቸው ወስደው ሰራተኛውን የበዪ ተመልካች አድርገውታል" ያሉን ሌላ የድርጅቱ ሰራተኛ ከኢኮኖሚ ማሻሻያው በኋላ ለሰራተኛው የተጨመረው ደመወዝ 10 ፐርሰንት እንደማይሞላ ጠቅሰዋል።
"ይህ በሆነበት ሁኔታ ነው እንግዲህ ለራሳቸው የሁለት ወር ደመወዝ ጉርሻ ተፈራርመው ለበዓላቸው የወሰዱት። እነሱ እየተዝናኑ ሰራተኛው ኑሮ አልገፋ ብሎት ሌት ተቀን እየታገለ ነው። ይህንን ጉድ የኢትዮጵያ ህዝብ ይስማው፣ ስሜ ሳይታይ አድርሱልን" ብለዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- አቶ ጋሻው ለመሠረት ሚድያ ዘገባ ስድብ የተቀላቀለበት ምላሽ ሰጥተዋል
(መሠረት ሚድያ)- የኢትዮጵያ ፖስታ (Ethio Post) በነገው እለት ለሚከበረው የትንሳኤ በዓል ከማናጀር በላይ ላሉ ሀላፊዎቹ ብቻ የሁለት ወር ደሞዝ ቦነስ መስጠቱን መሠረት ሚድያ ማምሻውን መዘገቡ ይታወቃል።
በርካታ የተቋሙ ሰራተኞች በትናንትናው እለት የሰሙት እና "እጅግ አሳዛኝ" ብለው የገለፁት ድርጊት የኑሮ ውድነት ተባብሶ ታች ያለው ሰራተኛ ሲቸገር ከፍ ያለ ደሞዝ ያላቸው ቦነስ ብለው ብር መከፋፈላቸው እንዳስቆጣቸው ገልፀው ነበር።
ለዚህ ዜና በመሠረት ሚድያ የፌስቡክ ገፅ ላይ ስድብ የተቀላቀለበት ምላሽ ያስቀመጡት የኢትዮጵያ ፖስታ ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ጋሻው መርሻ "እውነት ነው ለማኔጅመንት አባላት ቦነስ ከፍለናል። የተከፈለው የአንድ ወር ደመወዝ ብቻ ነው" ብለዋል።
መሠረት ሚድያ የተሰነዘረውን ስድብ ለማቅረብ ኤዲቶሪያ ፖሊሲው አይፈቅድም፣ ይሁንና አቶ ጋሻው ከስድብ ውጭ ያስቀመጡትን ፅሁፍ እንዲህ በቀጥታ ያቀርበዋል:
"እውነት ነው ለማኔጅመንት አባላት ቦነስ ከፍለናል። የተከፈለው የአንድ ወር ደመወዝ ብቻ ነው። ይኸው ቦነስ ለመላው ሰራተኛ በመስከረም ወር ተከፍሏል። ለማኔጅመንት አባላት እስካሁን ያልተከፈለው ከኦዲት ጋር በተያያዘ ብቻ ነበር። ኦዲቱ ሲጠናቀቅ አሁን ተከፈለ። ምንድን ነው ችግሩ?" ብለዋል።
"ከጥበቃ ጀምሮ እስከ ሱፐርቫይዘር ድረስ ያለው ሰራተኛ በኑሮ ውድነት እየተጠበሰ፣ ደሞዝ ይጨመርልኛል ብሎ ሲያስብ ከማናጀር በላይ ላሉት ብቻ የ2 ወር ደሞዝ ቦነስ ተብሎ የተቋሙን ገንዘብ መቀራመታቸው አሳዝኖናል፣ እነሱ በቦነሱ ብቻ ከ80,000 እስከ 212,000 ሲከፋፈሉ ተራው ሰራተኛ ለበዓል ዶሮ መግዣ አጥቶ ይውላል" ብለው ለመሠረት ሚድያ የተናገሩት አንድ የተቋሙ ሰራተኛ ናቸው።
አሁን ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከ2,200 በላይ ሰራተኞች ያሉት ሲሆን የሰራተኞቹ ደሞዝ ከ4,000 ብር ጀምሮ እስከ 106,000 ብር እንደሚደርስ ለሚድያችን የደረሰ አንድ መረጃ ያሳያል።
አብዛኛው ሰራተኛ ጠቅላላ ደሞዙ ከ16,800 ብር በታች ሲሆን የሀላፊዎቹ ደግሞ ጥቅማ ጥቅም ሳይጨምር ማናጀር 40,300፣ ዳይሬክተር 56,400 ብር፣ ቺፍ ኦፊሰር 76,300 ብር እንዲሁም ዋና ስራ አስፈፃሚ 106,100 ብር እንደሚያገኙ ይህ መረጃችን ያሳያል።
"ከስራ አስኪያጅ ጀምሮ ለፋሲካ በዓል የሁለት ወር ጉርሻ ለራሳቸው ወስደው ሰራተኛውን የበዪ ተመልካች አድርገውታል" ያሉን ሌላ የድርጅቱ ሰራተኛ ከኢኮኖሚ ማሻሻያው በኋላ ለሰራተኛው የተጨመረው ደመወዝ 10 ፐርሰንት እንደማይሞላ ጠቅሰዋል።
"ይህ በሆነበት ሁኔታ ነው እንግዲህ ለራሳቸው የሁለት ወር ደመወዝ ጉርሻ ተፈራርመው ለበዓላቸው የወሰዱት። እነሱ እየተዝናኑ ሰራተኛው ኑሮ አልገፋ ብሎት ሌት ተቀን እየታገለ ነው። ይህንን ጉድ የኢትዮጵያ ህዝብ ይስማው፣ ስሜ ሳይታይ አድርሱልን" ብለዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
1200
13:27
20.04.2025
imageImage preview is unavailable
#ዜናመሠረት የኢትዮጵያ ፖስታ ለትንሳኤ በዓል ከማናጀር በላይ ላሉ ሀላፊዎቹ ብቻ የሁለት ወር ደሞዝ ቦነስ መስጠቱ ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- የኢትዮጵያ ፖስታ (Ethio Post) በነገው እለት ለሚከበረው የትንሳኤ በዓል ከማናጀር በላይ ላሉ ሀላፊዎቹ ብቻ የሁለት ወር ደሞዝ ቦነስ መስጠቱን እየወጡ ያሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
በርካታ የተቋሙ ሰራተኞች በትናንትናው እለት የሰሙት እና "እጅግ አሳዛኝ" ብለው የገለፁት ድርጊት የኑሮ ውድነት ተባብሶ ታች ያለው ሰራተኛ ሲቸገር ከፍ ያለ ደሞዝ ያላቸው ቦነስ ብለው ብር መከፋፈላቸው እንዳስቆጣቸው ገልፀዋል።
"ከጥበቃ ጀምሮ እስከ ሱፐርቫይዘር ድረስ ያለው ሰራተኛ በኑሮ ውድነት እየተጠበሰ፣ ደሞዝ ይጨመርልኛል ብሎ ሲያስብ ከማናጀር በላይ ላሉት ብቻ የ2 ወር ደሞዝ ቦነስ ተብሎ የተቋሙን ገንዘብ መቀራመታቸው አሳዝኖናል፣ እነሱ በቦነሱ ብቻ ከ80,000 እስከ 212,000 ሲከፋፈሉ ተራው ሰራተኛ ለበዓል ዶሮ መግዣ አጥቶ ይውላል" ብለው ለመሠረት ሚድያ የተናገሩት አንድ የተቋሙ ሰራተኛ ናቸው።
አሁን ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከ2,200 በላይ ሰራተኞች ያሉት ሲሆን የሰራተኞቹ ደሞዝ ከ4,000 ብር ጀምሮ እስከ 106,000 ብር እንደሚደርስ ለሚድያችን የደረሰ አንድ መረጃ ያሳያል።
አብዛኛው ሰራተኛ ጠቅላላ ደሞዙ ከ16,800 ብር በታች ሲሆን የሀላፊዎቹ ደግሞ ጥቅማ ጥቅም ሳይጨምር ማናጀር 40,300፣ ዳይሬክተር 56,400 ብር፣ ቺፍ ኦፊሰር 76,300 ብር እንዲሁም ዋና ስራ አስፈፃሚ 106,100 ብር እንደሚያገኙ ይህ መረጃችን ያሳያል።
"ከስራ አስኪያጅ ጀምሮ ለፋሲካ በዓል የሁለት ወር ጉርሻ ለራሳቸው ወስደው ሰራተኛውን የበዪ ተመልካች አድርገውታል" ያሉን ሌላ የድርጅቱ ሰራተኛ ከኢኮኖሚ ማሻሻያው በኋላ ለሰራተኛው የተጨመረው ደመወዝ 10 ፐርሰንት እንደማይሞላ ጠቅሰዋል።
"ይህ በሆነበት ሁኔታ ነው እንግዲህ ለራሳቸው የሁለት ወር ደመወዝ ጉርሻ ተፈራርመው ለበዓላቸው የወሰዱት። እነሱ እየተዝናኑ ሰራተኛው ኑሮ አልገፋ ብሎት ሌት ተቀን እየታገለ ነው። ይህንን ጉድ የኢትዮጵያ ህዝብ ይስማው፣ ስሜ ሳይታይ አድርሱልን" ብለዋል።
በዚህ ዙርያ ከተቋሙ ምላሽ ከደረሰን ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- የኢትዮጵያ ፖስታ (Ethio Post) በነገው እለት ለሚከበረው የትንሳኤ በዓል ከማናጀር በላይ ላሉ ሀላፊዎቹ ብቻ የሁለት ወር ደሞዝ ቦነስ መስጠቱን እየወጡ ያሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
በርካታ የተቋሙ ሰራተኞች በትናንትናው እለት የሰሙት እና "እጅግ አሳዛኝ" ብለው የገለፁት ድርጊት የኑሮ ውድነት ተባብሶ ታች ያለው ሰራተኛ ሲቸገር ከፍ ያለ ደሞዝ ያላቸው ቦነስ ብለው ብር መከፋፈላቸው እንዳስቆጣቸው ገልፀዋል።
"ከጥበቃ ጀምሮ እስከ ሱፐርቫይዘር ድረስ ያለው ሰራተኛ በኑሮ ውድነት እየተጠበሰ፣ ደሞዝ ይጨመርልኛል ብሎ ሲያስብ ከማናጀር በላይ ላሉት ብቻ የ2 ወር ደሞዝ ቦነስ ተብሎ የተቋሙን ገንዘብ መቀራመታቸው አሳዝኖናል፣ እነሱ በቦነሱ ብቻ ከ80,000 እስከ 212,000 ሲከፋፈሉ ተራው ሰራተኛ ለበዓል ዶሮ መግዣ አጥቶ ይውላል" ብለው ለመሠረት ሚድያ የተናገሩት አንድ የተቋሙ ሰራተኛ ናቸው።
አሁን ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከ2,200 በላይ ሰራተኞች ያሉት ሲሆን የሰራተኞቹ ደሞዝ ከ4,000 ብር ጀምሮ እስከ 106,000 ብር እንደሚደርስ ለሚድያችን የደረሰ አንድ መረጃ ያሳያል።
አብዛኛው ሰራተኛ ጠቅላላ ደሞዙ ከ16,800 ብር በታች ሲሆን የሀላፊዎቹ ደግሞ ጥቅማ ጥቅም ሳይጨምር ማናጀር 40,300፣ ዳይሬክተር 56,400 ብር፣ ቺፍ ኦፊሰር 76,300 ብር እንዲሁም ዋና ስራ አስፈፃሚ 106,100 ብር እንደሚያገኙ ይህ መረጃችን ያሳያል።
"ከስራ አስኪያጅ ጀምሮ ለፋሲካ በዓል የሁለት ወር ጉርሻ ለራሳቸው ወስደው ሰራተኛውን የበዪ ተመልካች አድርገውታል" ያሉን ሌላ የድርጅቱ ሰራተኛ ከኢኮኖሚ ማሻሻያው በኋላ ለሰራተኛው የተጨመረው ደመወዝ 10 ፐርሰንት እንደማይሞላ ጠቅሰዋል።
"ይህ በሆነበት ሁኔታ ነው እንግዲህ ለራሳቸው የሁለት ወር ደመወዝ ጉርሻ ተፈራርመው ለበዓላቸው የወሰዱት። እነሱ እየተዝናኑ ሰራተኛው ኑሮ አልገፋ ብሎት ሌት ተቀን እየታገለ ነው። ይህንን ጉድ የኢትዮጵያ ህዝብ ይስማው፣ ስሜ ሳይታይ አድርሱልን" ብለዋል።
በዚህ ዙርያ ከተቋሙ ምላሽ ከደረሰን ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
915
13:27
20.04.2025
imageImage preview is unavailable
#ዜናመሠረት ካርፉር ሱፐርማርኬትን ጨምሮ በርካታ የውጭ የግብይት ማዕከላት በኢትዮጵያ ስራ ሊጀምሩ እንደሆነ ተሰማ
- ድርጅቱ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጣ ጠ/ሚር አብይ በቀጥታ ተቋሙን ሲያግባቡ ቆይተዋል
(መሠረት ሚድያ)- ግዙፉ የፈረንሳይ የሸቀጣ ሸቀጥ ግብይት ማእከል ካርፉር (Carrefour) ጨምሮ በርካታ ተመሳሳይ የውጭ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ስራ ለመጀመር እንደተስማሙ ታውቋል።
እንደ ኬንያ ባሉ ሀገራት ግዙፍ የሱፐርማርኬት ንግዶችን የሚያንቀሳቅሰው ካርፉር ወደ ኢትዮጵያ ገበያ እንዲገባ ጠ/ሚር አብይ አህመድ የድርጅቱን ዋና ስራ አስፈፃሚ በቀጥታ ሲያነጋግሩ እና ሲያግባቡ እንደነበር መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ይጠቁማል።
ካርፉር በሀገር ውስጥ ሊገኙ የማይችሉ እና በሀገር ውስጥ የሚገኙ ምርቶችን በስፋት እና በጥራት በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን በአለማችን ዙርያ በ40 ሀገራት ውስጥ 14,000 ሱፐርማርኬቶችን እንደሚያስተዳድር መረጃዎች ያሳያሉ።
"የካርፉር ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ለሌሎች ሱፐርማርኬቶችም ሆነ በሌላ ዝርፍ ላይ ላሉ ድርጅቶች መምጣት ምክንያት ይሆናል" ያሉን መረጃውን ለመሠረት ሚድያ ያጋሩ አንድ የመንግስት ሀላፊ በተለይ የመግዛት አቅማቸው ከፍ ያለ እና የውጭ ተቋማት ሰራተኞችን በከፍተኛ ደረጃ ይጠቅማል ብለዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- ድርጅቱ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጣ ጠ/ሚር አብይ በቀጥታ ተቋሙን ሲያግባቡ ቆይተዋል
(መሠረት ሚድያ)- ግዙፉ የፈረንሳይ የሸቀጣ ሸቀጥ ግብይት ማእከል ካርፉር (Carrefour) ጨምሮ በርካታ ተመሳሳይ የውጭ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ስራ ለመጀመር እንደተስማሙ ታውቋል።
እንደ ኬንያ ባሉ ሀገራት ግዙፍ የሱፐርማርኬት ንግዶችን የሚያንቀሳቅሰው ካርፉር ወደ ኢትዮጵያ ገበያ እንዲገባ ጠ/ሚር አብይ አህመድ የድርጅቱን ዋና ስራ አስፈፃሚ በቀጥታ ሲያነጋግሩ እና ሲያግባቡ እንደነበር መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ይጠቁማል።
ካርፉር በሀገር ውስጥ ሊገኙ የማይችሉ እና በሀገር ውስጥ የሚገኙ ምርቶችን በስፋት እና በጥራት በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን በአለማችን ዙርያ በ40 ሀገራት ውስጥ 14,000 ሱፐርማርኬቶችን እንደሚያስተዳድር መረጃዎች ያሳያሉ።
"የካርፉር ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ለሌሎች ሱፐርማርኬቶችም ሆነ በሌላ ዝርፍ ላይ ላሉ ድርጅቶች መምጣት ምክንያት ይሆናል" ያሉን መረጃውን ለመሠረት ሚድያ ያጋሩ አንድ የመንግስት ሀላፊ በተለይ የመግዛት አቅማቸው ከፍ ያለ እና የውጭ ተቋማት ሰራተኞችን በከፍተኛ ደረጃ ይጠቅማል ብለዋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
948
13:27
20.04.2025
imageImage preview is unavailable
#ዜናመሠረት "በሚቀጥለው ሳምንት በአክስዮን ሽያጩ ዙርያ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል"- ኢትዮ ቴሌኮም ለመሠረት ሚድያ
(መሠረት ሚድያ)- መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ኢትዮ ቴሌኮም በመጀመሪያ ዙር እያንዳንዳቸው 300 ብር ዋጋ ያላቸውን 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ከህዳር ወር ጀምሮ ማቅረቡ ይታወሳል።
ተቋሙ በሸጣቸው አክሲዮኖች ዙርያ ለህዝብ ተከታታይ መረጃ አለማድረሱ እና ቀጣይ መርሀ ግብሮች ተብለው በወቅቱ የተቀመጡት ቀናት በማለፋቸው በብዙዎች ዘንድ አግራሞትን እየፈጠረ ይገኛል፣ የመሠረት ሚድያ ተከታታዮችም በጉዳዩ ዙርያ ኢትዮ ቴሌኮምን እንድናናግር ተከታታይ ጥያቄ አቅርበዋል።
በዚህ ዙርያ በቅርቡ አስተያየታቸውን ያስነበቡት እውቁ የባንክ ባለሙያ አቶ ሙሼ ሰሙ ኢትዮ ቴሌኮም ከጃንዋሪ 31, 2025 ጀምሮ ተቀባይነት ያገኙ አክስዮን ገዢዎች እንደሚለይና ተቀባይነት ያላገኙ አክስዮን ገዢዎች ደግሞ እስከ ከኤፕሪል 14, 2025 ደረስ ገንዘባቸው መመለስ እንደሚጀምር መግለፁን አንስተዋል።
"እስከአሁን ድረስ ተቀባይነት ያገኙ አክስዮኖች አልተገለጹም... ቢያንስ ሕዝብን በማክበር ደረጃ የአክስዮን እውቅና መስጫ ጊዜው መራዘሙን አስመልክቶ አንድም ምክንያት አለመቅረቡ፣ መግለጫ አለመሰጠቱና ምንም እንዳልተፈጠረ በዝምታ ቀን መቆጠሩ የሚያስደምም ሆኖ አግኝቼዋለሁ" ያሉት አቶ ሙሼ "በጥቅሉ ገንዘባችሁን አግቼ፣ የአክስዮን እውቅና ሳልሰጥ፣ ወለድ ሳልከፍል፣ የጊዜ ሰሌዳውን ሳላሳውቃችሁ ገንዘባችሁ በግሽበት እየተመታ በፈለኩት ሁኔታና ጊዜ የገንዘባችሁን ቆይታ ማራዘም እችላለሁ ማለት ምን የሚሉት ውልና ከምን የመነጨ መብት እንደሆነ ግልጽ አይደለም" ብለዋል።
በዚህ ዙርያ መሠረት ሚድያ ኢትዮ ቴሌኮምን ያናገረ ሲሆን ተቋሙ ውጤቱን ለህዝብ የማሳወቁ ሂደት ግዜ መፍጀቱን አምኖ ይህም የተፈጠረው ሂደቱ ለተቋሙ የመጀመርያው ከመሆኑ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቅሷል።
"በቀጣይ ሂደት ዙርያ ከባለድርሻዎች ጋር ሰፋ ያለ ውይይት ማድረግ አስፈልጎ ነበር። በተጨማሪም አንዳንድ ዳታዎችን የማጥራት ስራ ላይ ትኩረት አርገን እየሰራን ነበር" በሚል ምላሹን ለሚድያችን የሰጠው ኢትዮ ቴሌኮም አሁንም ግልፅነት ያለው አሰራር ለመዘርጋት ፅኑ አቋም አለኝ ብሏል።
በሚቀጥለው ሳምንትም በዚህ ዙርያ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚኖር የገለፀው የቴሌኮም ኩባንያው በዚህ መግለጫ ላይ ስለ አክስዮን ሽያጩ እና ስለ ድልድል ውጤት ይፋ እንደሚደርግ አስታውቋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ኢትዮ ቴሌኮም በመጀመሪያ ዙር እያንዳንዳቸው 300 ብር ዋጋ ያላቸውን 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ከህዳር ወር ጀምሮ ማቅረቡ ይታወሳል።
ተቋሙ በሸጣቸው አክሲዮኖች ዙርያ ለህዝብ ተከታታይ መረጃ አለማድረሱ እና ቀጣይ መርሀ ግብሮች ተብለው በወቅቱ የተቀመጡት ቀናት በማለፋቸው በብዙዎች ዘንድ አግራሞትን እየፈጠረ ይገኛል፣ የመሠረት ሚድያ ተከታታዮችም በጉዳዩ ዙርያ ኢትዮ ቴሌኮምን እንድናናግር ተከታታይ ጥያቄ አቅርበዋል።
በዚህ ዙርያ በቅርቡ አስተያየታቸውን ያስነበቡት እውቁ የባንክ ባለሙያ አቶ ሙሼ ሰሙ ኢትዮ ቴሌኮም ከጃንዋሪ 31, 2025 ጀምሮ ተቀባይነት ያገኙ አክስዮን ገዢዎች እንደሚለይና ተቀባይነት ያላገኙ አክስዮን ገዢዎች ደግሞ እስከ ከኤፕሪል 14, 2025 ደረስ ገንዘባቸው መመለስ እንደሚጀምር መግለፁን አንስተዋል።
"እስከአሁን ድረስ ተቀባይነት ያገኙ አክስዮኖች አልተገለጹም... ቢያንስ ሕዝብን በማክበር ደረጃ የአክስዮን እውቅና መስጫ ጊዜው መራዘሙን አስመልክቶ አንድም ምክንያት አለመቅረቡ፣ መግለጫ አለመሰጠቱና ምንም እንዳልተፈጠረ በዝምታ ቀን መቆጠሩ የሚያስደምም ሆኖ አግኝቼዋለሁ" ያሉት አቶ ሙሼ "በጥቅሉ ገንዘባችሁን አግቼ፣ የአክስዮን እውቅና ሳልሰጥ፣ ወለድ ሳልከፍል፣ የጊዜ ሰሌዳውን ሳላሳውቃችሁ ገንዘባችሁ በግሽበት እየተመታ በፈለኩት ሁኔታና ጊዜ የገንዘባችሁን ቆይታ ማራዘም እችላለሁ ማለት ምን የሚሉት ውልና ከምን የመነጨ መብት እንደሆነ ግልጽ አይደለም" ብለዋል።
በዚህ ዙርያ መሠረት ሚድያ ኢትዮ ቴሌኮምን ያናገረ ሲሆን ተቋሙ ውጤቱን ለህዝብ የማሳወቁ ሂደት ግዜ መፍጀቱን አምኖ ይህም የተፈጠረው ሂደቱ ለተቋሙ የመጀመርያው ከመሆኑ ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቅሷል።
"በቀጣይ ሂደት ዙርያ ከባለድርሻዎች ጋር ሰፋ ያለ ውይይት ማድረግ አስፈልጎ ነበር። በተጨማሪም አንዳንድ ዳታዎችን የማጥራት ስራ ላይ ትኩረት አርገን እየሰራን ነበር" በሚል ምላሹን ለሚድያችን የሰጠው ኢትዮ ቴሌኮም አሁንም ግልፅነት ያለው አሰራር ለመዘርጋት ፅኑ አቋም አለኝ ብሏል።
በሚቀጥለው ሳምንትም በዚህ ዙርያ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚኖር የገለፀው የቴሌኮም ኩባንያው በዚህ መግለጫ ላይ ስለ አክስዮን ሽያጩ እና ስለ ድልድል ውጤት ይፋ እንደሚደርግ አስታውቋል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
1500
19:20
17.04.2025
imageImage preview is unavailable
#ዜናመሠረት "ስዩም ተሾመ ተሰውሮብኛል"- ፌደራል ፖሊስ
"ግለሰቡ በስም የሚታወቅ ስለሆነ ይሰወራል ብለን አናምንም፣ በቀጣይ ተገዶ እንዲቀርብ"- ከፍተኛ ፍርድ ቤት
(መሠረት ሚድያ)- በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ የሽብር ወንጀል ምድብ ችሎት ጉዳያቸው እየታየ የሚገኘው አቶ ዮሐንስ ቧያሌው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ "ስዩም ተሾመ የተባለው ግለሰብ በሕግ ቁጥጥር ስር ሆነን ሳለ በማኅበራዊ ሚዲያ ስማችንን እያጠፋ ነው" በሚል ለችሎቱ አቤቱታ አቅርበው እንደነበር ቀደም ሲል መዘገባችን ይታወቃል።
ፍርድ ቤቱም በስም የተጠቀሰው ግለሰብ ችሎት ቀርቦ ጉዳዩን እንዲያስረዳ በፌዴራል ፖሊስ በኩል መጥሪያ ቢላክለትም ለሁለተኛ ጊዜ ስዩም ተሾመ ተሰውሮብኛል ሲል ዛሬ ምላሽ መስጠቱን መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ያሳያል።
አቶ ዮሐንስ ቧያለው በበኩላቸው "ከጂቡቲ ጎበዜ ሲሳይን አመጣሁ ብሎ የሚመፃደቀው የፌዴራል ፖሊስ ላፍቶ ሞል ቢሮ ከፍቶ በየቀኑ የፍርድ ቤት ዳኞችን ሲሳደብ የሚውልን ግለሰብ ተሰውሮብኛል ማለቱ አሳፋሪ ነው" ሲሉ ለችሎቱ አስረድተዋል ።
አቶ ዮሐንስ አክለውም "ይህንን ግለሰብ ቀደም ሲል በሌላ ችሎት በስም ማጥፋት ወንጀል ከስሼው ቅጣት የተጣለበት ቢሆንም እስካሁን ቅጣቱን የሚያስፈፅም የመንግስት አካል ባለመኖሩ ያንኑ የጥፋት ድርጊት ቀጥሎበታል" ሲሉ ተናግረዋል።
"የእኔን ስም በተደጋጋሚ ማጥፋቱ የተለመደ ቢሆንም አሁን ደግሞ የዚህን ችሎት ዳኞች ስም እያጠፋ እና በችሎቱ ላይ ግልፅ የሆነ ተፅዕኖ እየፈጠረ በመሆኑ ትክክለኛ ፍትሕ እናገኛለን ለማለት እንቸገራለን" ሲሉ አክለዋል።
አቶ ክርስቲያን ታደለ በበኩላቸው "ስዩም ተሾመ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ሚዲያ አማካሪ ሲሆን ፖሊስ ይህንን ሰው ማቅረብ ያልቻለው ስዩም አንደኛ ደረጃ ዜጋ ስለሆነ ነው። አንደኛ ደረጃ ዜጎች ከሕግ በላይ ሥለሆኑ ፍርድ ቤት መቅረብ አይችሉም። ፍርድ ቤት ተገደው የሚቀርቡት ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዜጎች ብቻ ናቸው። ስዩም አማራ ቢሆን ኖሮ ተገዶ ይቀርብ ነበር ምክንያቱም በአሁኑ ወቅት አማራ ሶስተኛ ዜጋ ሆኗልና። ሁለት መቶ አማራዎችን ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር በተገናኘ በሚል ጓዳ ጎድጓዳ ውስጥ ገብቶ በእስር ቤት እያጎረ ያለ ፖሊስ እና አቃቢ ሕግ ስዩም ተሾመን አዲስ አበባ ውስጥ ተሰውሯል ሲባል ያሳፍራል" ሲሉ ነው ለችሎቱ ያስረዱት።
"ሞት በሚያስቀጣ አንቀፅ ተከሰን አቶ ስዩም የተባለው ግለሰብ ችሎቱን ከውጭ ሆኖ ተፅዕኖ የሚፈጥርበት ከሆነ ውጤቱ ከወዲሁ የሚታወቅ ነው" ብለዋል።
የሁለቱን አቤቱታ ያደመጠው ችሎቱ "ስዩም የተባለው ግለሰብ በስም የሚታወቅ ስለሆነ ይሰወራል ብለን አናምንም። በቀጣይ ግን ተገዶ እንዲቀርብ" ሲል ለሶስተኛ ጊዜ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
"ግለሰቡ በስም የሚታወቅ ስለሆነ ይሰወራል ብለን አናምንም፣ በቀጣይ ተገዶ እንዲቀርብ"- ከፍተኛ ፍርድ ቤት
(መሠረት ሚድያ)- በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ የሽብር ወንጀል ምድብ ችሎት ጉዳያቸው እየታየ የሚገኘው አቶ ዮሐንስ ቧያሌው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ "ስዩም ተሾመ የተባለው ግለሰብ በሕግ ቁጥጥር ስር ሆነን ሳለ በማኅበራዊ ሚዲያ ስማችንን እያጠፋ ነው" በሚል ለችሎቱ አቤቱታ አቅርበው እንደነበር ቀደም ሲል መዘገባችን ይታወቃል።
ፍርድ ቤቱም በስም የተጠቀሰው ግለሰብ ችሎት ቀርቦ ጉዳዩን እንዲያስረዳ በፌዴራል ፖሊስ በኩል መጥሪያ ቢላክለትም ለሁለተኛ ጊዜ ስዩም ተሾመ ተሰውሮብኛል ሲል ዛሬ ምላሽ መስጠቱን መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ያሳያል።
አቶ ዮሐንስ ቧያለው በበኩላቸው "ከጂቡቲ ጎበዜ ሲሳይን አመጣሁ ብሎ የሚመፃደቀው የፌዴራል ፖሊስ ላፍቶ ሞል ቢሮ ከፍቶ በየቀኑ የፍርድ ቤት ዳኞችን ሲሳደብ የሚውልን ግለሰብ ተሰውሮብኛል ማለቱ አሳፋሪ ነው" ሲሉ ለችሎቱ አስረድተዋል ።
አቶ ዮሐንስ አክለውም "ይህንን ግለሰብ ቀደም ሲል በሌላ ችሎት በስም ማጥፋት ወንጀል ከስሼው ቅጣት የተጣለበት ቢሆንም እስካሁን ቅጣቱን የሚያስፈፅም የመንግስት አካል ባለመኖሩ ያንኑ የጥፋት ድርጊት ቀጥሎበታል" ሲሉ ተናግረዋል።
"የእኔን ስም በተደጋጋሚ ማጥፋቱ የተለመደ ቢሆንም አሁን ደግሞ የዚህን ችሎት ዳኞች ስም እያጠፋ እና በችሎቱ ላይ ግልፅ የሆነ ተፅዕኖ እየፈጠረ በመሆኑ ትክክለኛ ፍትሕ እናገኛለን ለማለት እንቸገራለን" ሲሉ አክለዋል።
አቶ ክርስቲያን ታደለ በበኩላቸው "ስዩም ተሾመ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ሚዲያ አማካሪ ሲሆን ፖሊስ ይህንን ሰው ማቅረብ ያልቻለው ስዩም አንደኛ ደረጃ ዜጋ ስለሆነ ነው። አንደኛ ደረጃ ዜጎች ከሕግ በላይ ሥለሆኑ ፍርድ ቤት መቅረብ አይችሉም። ፍርድ ቤት ተገደው የሚቀርቡት ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዜጎች ብቻ ናቸው። ስዩም አማራ ቢሆን ኖሮ ተገዶ ይቀርብ ነበር ምክንያቱም በአሁኑ ወቅት አማራ ሶስተኛ ዜጋ ሆኗልና። ሁለት መቶ አማራዎችን ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር በተገናኘ በሚል ጓዳ ጎድጓዳ ውስጥ ገብቶ በእስር ቤት እያጎረ ያለ ፖሊስ እና አቃቢ ሕግ ስዩም ተሾመን አዲስ አበባ ውስጥ ተሰውሯል ሲባል ያሳፍራል" ሲሉ ነው ለችሎቱ ያስረዱት።
"ሞት በሚያስቀጣ አንቀፅ ተከሰን አቶ ስዩም የተባለው ግለሰብ ችሎቱን ከውጭ ሆኖ ተፅዕኖ የሚፈጥርበት ከሆነ ውጤቱ ከወዲሁ የሚታወቅ ነው" ብለዋል።
የሁለቱን አቤቱታ ያደመጠው ችሎቱ "ስዩም የተባለው ግለሰብ በስም የሚታወቅ ስለሆነ ይሰወራል ብለን አናምንም። በቀጣይ ግን ተገዶ እንዲቀርብ" ሲል ለሶስተኛ ጊዜ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
1500
19:20
17.04.2025
imageImage preview is unavailable
#ዜናመሠረት ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖም የታይም መፅሄት የአመቱ 100 ተፅእኖ ፈጣሪዎች ስብስብስ ውስጥ ተካተቱ
- በዘንድሮው ስብስብስ ውስጥ ዶናልድ ትረምፕ እና ኤሎን መስክ ተካተዋል
(መሠረት ሚድያ)- ዝነኛው እና ተፅእኖ ፈጣሪው ታይም መፅሄት በዘንድሮው የ '100 ተፅእኖ ፈጣሪዎች' ዝርዝር ውስጥ የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን ኢትዮጵያዊውን ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖምን አካተተ።
በዘንድሮው የታይም መፅሄት ዝርዝር ውስጥ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ፣ ባለሀብቱ ኤሎን መስክ እና የእንግሊዙ ጠ/ሚር ኬር ስታርመር መካተታቸው ታውቋል።
ዶ/ር ቴድሮስ በዚህ ዙርያ ማምሻውን የማህበራዊ ሚድያ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ሀሳብ "በዝርዝሩ ውስጥ መካተቴ በምሰራበት የአለም ጤና ድርጅት ውስጥ ለሚሰሩ ባልደረቦቼም እውቅና ነው" ያሉ ሲሆን በአለም ዙርያ በየቀኑ ግጭት ባሉባቸው ስፍራዎች ጭምር የጤና አገልግሎት ለማዳረስ የሚሰሩ ሰራተኞችን አስታውሰዋል።
በመፅሄቱ ላይ ስለ ዶ/ር ቴድሮስ ተጋባዥ ፀሀፊ በመሆን ያስነበቡት ዶ/ር ላሪ ብሪሊያንት የተባሉ የፈንጣጣ በሽታ ከአለማችን እንዲጠፋ ቁልፍ ሚና የተጫወቱ ሳይንቲስት መሆናቸውን መሠረት ሚድያ ተመልክቷል።
"ዶ/ር ቴድሮስ የአለም ጤና ድርጅት ሀላፊ ከሆኑ በኋላ የአለማችንን የጤና አገልግሎት ሽፋን ቀይረውታል፣ ይህ ደግሞ በበሳል አመራር እና ሳይንሳዊ በሆነ የውሳኔ አሰጣጥ የታገዘ ነበር። ዶ/ር ቴድሮስ ለአለም ጤና ስጦታ ናቸው" ያሉት ዶ/ር ላሪ በ194 ሀገራት የሚገኙ ሰዎችን ጤና የመጠበቅ ሀላፊነትን እየተወጡ የሚገኙ ብለዋቸዋል።
"አመራሩ መርህ ያለው ነው፣ ሀቀኛ ነው፣ ውጤት ተኮርም ነው። የአለማችን ህዝብ ከበፊት ግዜ በበለጠ ጤነኛ እንዲሆን አድርገዋል" በማለት ዶ/ር ላሪ ታይም መፅሄት ላይ አስነብበዋል።
በታይም መፅሄት መሪዎች (Leaders) ምድብ ከዚህ ቀደም ቀዳማዊ ሐይለ ሥላሴ እና ጠ/ሚር አብይ አህመድ ተካተው ነበር። ይሁንና 'የታይም የአመቱ ሰው (Time Person of the Year) የሚለውን ማዕረግ ግን ያገኙ ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ቀዳማዊ ሐይለ ሥላሴ ሲሆኑ ግዜውም እ.አ.አ በ1936 ጃንዋሪ ወር ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- በዘንድሮው ስብስብስ ውስጥ ዶናልድ ትረምፕ እና ኤሎን መስክ ተካተዋል
(መሠረት ሚድያ)- ዝነኛው እና ተፅእኖ ፈጣሪው ታይም መፅሄት በዘንድሮው የ '100 ተፅእኖ ፈጣሪዎች' ዝርዝር ውስጥ የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን ኢትዮጵያዊውን ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖምን አካተተ።
በዘንድሮው የታይም መፅሄት ዝርዝር ውስጥ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ፣ ባለሀብቱ ኤሎን መስክ እና የእንግሊዙ ጠ/ሚር ኬር ስታርመር መካተታቸው ታውቋል።
ዶ/ር ቴድሮስ በዚህ ዙርያ ማምሻውን የማህበራዊ ሚድያ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ሀሳብ "በዝርዝሩ ውስጥ መካተቴ በምሰራበት የአለም ጤና ድርጅት ውስጥ ለሚሰሩ ባልደረቦቼም እውቅና ነው" ያሉ ሲሆን በአለም ዙርያ በየቀኑ ግጭት ባሉባቸው ስፍራዎች ጭምር የጤና አገልግሎት ለማዳረስ የሚሰሩ ሰራተኞችን አስታውሰዋል።
በመፅሄቱ ላይ ስለ ዶ/ር ቴድሮስ ተጋባዥ ፀሀፊ በመሆን ያስነበቡት ዶ/ር ላሪ ብሪሊያንት የተባሉ የፈንጣጣ በሽታ ከአለማችን እንዲጠፋ ቁልፍ ሚና የተጫወቱ ሳይንቲስት መሆናቸውን መሠረት ሚድያ ተመልክቷል።
"ዶ/ር ቴድሮስ የአለም ጤና ድርጅት ሀላፊ ከሆኑ በኋላ የአለማችንን የጤና አገልግሎት ሽፋን ቀይረውታል፣ ይህ ደግሞ በበሳል አመራር እና ሳይንሳዊ በሆነ የውሳኔ አሰጣጥ የታገዘ ነበር። ዶ/ር ቴድሮስ ለአለም ጤና ስጦታ ናቸው" ያሉት ዶ/ር ላሪ በ194 ሀገራት የሚገኙ ሰዎችን ጤና የመጠበቅ ሀላፊነትን እየተወጡ የሚገኙ ብለዋቸዋል።
"አመራሩ መርህ ያለው ነው፣ ሀቀኛ ነው፣ ውጤት ተኮርም ነው። የአለማችን ህዝብ ከበፊት ግዜ በበለጠ ጤነኛ እንዲሆን አድርገዋል" በማለት ዶ/ር ላሪ ታይም መፅሄት ላይ አስነብበዋል።
በታይም መፅሄት መሪዎች (Leaders) ምድብ ከዚህ ቀደም ቀዳማዊ ሐይለ ሥላሴ እና ጠ/ሚር አብይ አህመድ ተካተው ነበር። ይሁንና 'የታይም የአመቱ ሰው (Time Person of the Year) የሚለውን ማዕረግ ግን ያገኙ ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ቀዳማዊ ሐይለ ሥላሴ ሲሆኑ ግዜውም እ.አ.አ በ1936 ጃንዋሪ ወር ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
968
19:20
17.04.2025
imageImage preview is unavailable
#ዜናመሠረት የሆለታ ከተማ ነዋሪዎች ለኮሪደር ልማት ከ40 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር በግዴታ እንዲሰጡ እየተጠየቁ መሆኑን ተናገሩ
(መሠረት ሚድያ)- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሆለታ ከተማ ነዋሪዎች ለኮሪደር ልማት በግዴታ እያንዳንዳቸው ከ40 ሺህ ብር እስከ 200 ሺህ ብር እንዲሰጡ እየተጠየቁ መሆኑን ተናገሩ።
ለመሠረት ሚድያ ቃላቸውን የሰጡ በርካታ ነዋሪዎች እንኳን ይህን ያህል ገንዘብ ኖሯቸው ሊሰጡ የተጠቀሰውን ያህል ገንዘብ በህይወታችን ዘመን ኖሮን አያውቅም ብለዋል።
"ለኮሪደር ልማቱ ማለትም ለእግረኛው መንገድ አፍርሱ አሉ፣ 30 አመትና ከዛ በላይ ግብር ሲከፈልበት ከኖረ ቦታ በርካታ ሜትሮችን አስጠጋን" የሚሉት ነዋሪዎቹ አሁን ደግሞ ከ40ሺህ ብር እስከ 200 ሺህ ብር ሲንቄ ባንክ አስገቡ እየተባሉ መሆኑን ተናግረዋል።
"ይህ ደሀ ህዝብ ከየት ያመጣል? የለንም! ሲባል በቃ እናተ ትለቁና መስራት ለሚችል ይሰጣል አሉን" የሚሉት ሌላኛው ነዋሪ የከተማው ነዋሪ ምን ማድረግ እንዳለበት እና ማንን ማናገር እንደሚችል ግራ ገብቶት ይገኛል ብለዋል።
"እኔ ሲመስለኝ አሰራራቸው ሆን ተብሎ ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲነሳ ይመስላል። ከላይ የመጣ ትዕዛዝ ነው ይላሉ፣ 50 ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክም ለ50ሰው ጌጡ ነው፣ ልማት የሚጠላ የለም ግን እኛ ካለን ላይ ሰተናል" ያሉት ነዋሪው "ኑሮ የከበደው እና ብቻውን የሚያወራ ህዝብ ይዘን ባንጨካከን፣ አንዳንዴም ቆም ብለን ብናስብ መልካም ነው" ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከ58 ከተሞች በላይ ላይ እያከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት በአፋጣኝ አቁሞ በሰብአዊ መብት ላይ የሚያደርሰውን ጫና መገምገም እንዳለበት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከሁለት ቀን በፊት ማሳሰቡ ይታወሳል።
ማንኛውም ዓይነት ሰዎችን ከቤታቸው የማስወጣት ሒደት ከዓለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ጥበቃ መርኅ ጋር የሚጣጣም መሆን አለበት ያለው አምነስቲ "በኮሪደር ልማት ምክንያት ሰዎች ያለ ሕግ ከለላ እና ሌሎች ጥበቃዎች በግዳጅ ከቤታቸው እየተፈናቀሉ ነው" ሲልም ጠቅሷል።
ለሆለታ ከተማ አስተዳደር በዚህ ዙርያ ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን ምላሽ ካገኘን እንመለስበታለን።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- በምዕራብ ሸዋ ዞን የሆለታ ከተማ ነዋሪዎች ለኮሪደር ልማት በግዴታ እያንዳንዳቸው ከ40 ሺህ ብር እስከ 200 ሺህ ብር እንዲሰጡ እየተጠየቁ መሆኑን ተናገሩ።
ለመሠረት ሚድያ ቃላቸውን የሰጡ በርካታ ነዋሪዎች እንኳን ይህን ያህል ገንዘብ ኖሯቸው ሊሰጡ የተጠቀሰውን ያህል ገንዘብ በህይወታችን ዘመን ኖሮን አያውቅም ብለዋል።
"ለኮሪደር ልማቱ ማለትም ለእግረኛው መንገድ አፍርሱ አሉ፣ 30 አመትና ከዛ በላይ ግብር ሲከፈልበት ከኖረ ቦታ በርካታ ሜትሮችን አስጠጋን" የሚሉት ነዋሪዎቹ አሁን ደግሞ ከ40ሺህ ብር እስከ 200 ሺህ ብር ሲንቄ ባንክ አስገቡ እየተባሉ መሆኑን ተናግረዋል።
"ይህ ደሀ ህዝብ ከየት ያመጣል? የለንም! ሲባል በቃ እናተ ትለቁና መስራት ለሚችል ይሰጣል አሉን" የሚሉት ሌላኛው ነዋሪ የከተማው ነዋሪ ምን ማድረግ እንዳለበት እና ማንን ማናገር እንደሚችል ግራ ገብቶት ይገኛል ብለዋል።
"እኔ ሲመስለኝ አሰራራቸው ሆን ተብሎ ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲነሳ ይመስላል። ከላይ የመጣ ትዕዛዝ ነው ይላሉ፣ 50 ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክም ለ50ሰው ጌጡ ነው፣ ልማት የሚጠላ የለም ግን እኛ ካለን ላይ ሰተናል" ያሉት ነዋሪው "ኑሮ የከበደው እና ብቻውን የሚያወራ ህዝብ ይዘን ባንጨካከን፣ አንዳንዴም ቆም ብለን ብናስብ መልካም ነው" ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከ58 ከተሞች በላይ ላይ እያከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት በአፋጣኝ አቁሞ በሰብአዊ መብት ላይ የሚያደርሰውን ጫና መገምገም እንዳለበት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከሁለት ቀን በፊት ማሳሰቡ ይታወሳል።
ማንኛውም ዓይነት ሰዎችን ከቤታቸው የማስወጣት ሒደት ከዓለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ጥበቃ መርኅ ጋር የሚጣጣም መሆን አለበት ያለው አምነስቲ "በኮሪደር ልማት ምክንያት ሰዎች ያለ ሕግ ከለላ እና ሌሎች ጥበቃዎች በግዳጅ ከቤታቸው እየተፈናቀሉ ነው" ሲልም ጠቅሷል።
ለሆለታ ከተማ አስተዳደር በዚህ ዙርያ ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን ምላሽ ካገኘን እንመለስበታለን።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
1200
19:20
17.04.2025
imageImage preview is unavailable
#ዜናመሠረት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ለነዋሪው የ100 ሚልዮን ብር አበድሩኝ ጥያቄ አቀረበ
- ብድሩ 'ለኮሪደር ልማት እና ለገበያ ማረጋጊያ' ይውላል ተብሏል
(መሠረት ሚድያ)- የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ነዋሪው ለቤት መስሪያ በሚል ለበርካታ አመታት በማህበር ከቆጠበው ገንዘብ ውስጥ የ100 ሚልዮን ብር አበድሩኝ ጥያቄ ማቅረቡ ተሰምቷል።
መሠረት ሚድያ የደረሰው እና መጋቢት 12/2017 ዓ/ም በከተማው የከንቲባ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ደርሴ የተፈረመ ደብዳቤ ለኮምቦልቻ ህብረት ስራ ማህበራት የተፃፈ ሲሆን የከተማ አስተዳደሩ 'ግዜያዊ የገንዘብ እጥረት' እንዳጋጠመው ይገልፃል።
"የከተማ አስተዳደሩ ጊዜያዊ የበጀት እጥረት ስላጋጠመው የጋራ መኖርያ ቤት ህብረት ስራ ማህበራት ካላቸው ቁጠባ ላይ ለኮሪደር ልማትና ለገበያ ማረጋጊያ አገልግሎት የሚውል ከሁሉም ማህበራት ብር 100 ሚልዮን እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ/ም የሚቆይ ብድር እንድትሰጡን" የሚለው የከንቲባው ፅህፈት ቤት ደብዳቤ ገንዘቡ በአስቸኳይ ስለሚፈለግ ገቢ እንዲደረግ ይጠይቃል።
የማህበራቱ አባላት ለመሠረት ሚድያ በሰጡት ቃል በድርጊቱ ክፉኛ እንደተበሳጩ እና እንደተገረሙ ገልፀዋል።
"ለማህበር ቤት ግንባታ ለረዥም አመታት ከመስሪያ ቤት በብድር እና ከልጆቻችን አፍ እየቀማን ስንቆጥብ ቆይተን ከነገ ዛሬ ቦታ ይሰጠናል ብለን ተስፋ ስናደርግ አሁን 100 ሚሊዮን ብር በብድር መልክ አምጡ መባላችን አስደንግጦናል" ያሉን አንድ የከተማው ነዋሪ ቆጣቢዎች አስተዳደሩ ብሩን ይመልሳል የሚል እምነት እንደሌላቸው ገልፀዋል።
"ለምን ይሆናል? ብለን ስንጠይቅም የሚሰጡን መልስ አንተ የልማት አደናቃፊ ነህ፣ የፅንፈኛ ደጋፊ ነህ፣ ሙሉ ስምህን ማነው? ከየት ማህበር ነህ? ወዘተ እያሉ ያሸማቅቃሉ" ያሉን ሌላኛው አስተያየት ሰጪ "ሰሚ እንደሌለ ብናውቅም የዚህን አስከፊ ድርጊት የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልን" ብለዋል።
በዚህ ዙርያ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደርን ለማነጋገር በተደጋጋሚ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- ብድሩ 'ለኮሪደር ልማት እና ለገበያ ማረጋጊያ' ይውላል ተብሏል
(መሠረት ሚድያ)- የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ነዋሪው ለቤት መስሪያ በሚል ለበርካታ አመታት በማህበር ከቆጠበው ገንዘብ ውስጥ የ100 ሚልዮን ብር አበድሩኝ ጥያቄ ማቅረቡ ተሰምቷል።
መሠረት ሚድያ የደረሰው እና መጋቢት 12/2017 ዓ/ም በከተማው የከንቲባ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉጌታ ደርሴ የተፈረመ ደብዳቤ ለኮምቦልቻ ህብረት ስራ ማህበራት የተፃፈ ሲሆን የከተማ አስተዳደሩ 'ግዜያዊ የገንዘብ እጥረት' እንዳጋጠመው ይገልፃል።
"የከተማ አስተዳደሩ ጊዜያዊ የበጀት እጥረት ስላጋጠመው የጋራ መኖርያ ቤት ህብረት ስራ ማህበራት ካላቸው ቁጠባ ላይ ለኮሪደር ልማትና ለገበያ ማረጋጊያ አገልግሎት የሚውል ከሁሉም ማህበራት ብር 100 ሚልዮን እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ/ም የሚቆይ ብድር እንድትሰጡን" የሚለው የከንቲባው ፅህፈት ቤት ደብዳቤ ገንዘቡ በአስቸኳይ ስለሚፈለግ ገቢ እንዲደረግ ይጠይቃል።
የማህበራቱ አባላት ለመሠረት ሚድያ በሰጡት ቃል በድርጊቱ ክፉኛ እንደተበሳጩ እና እንደተገረሙ ገልፀዋል።
"ለማህበር ቤት ግንባታ ለረዥም አመታት ከመስሪያ ቤት በብድር እና ከልጆቻችን አፍ እየቀማን ስንቆጥብ ቆይተን ከነገ ዛሬ ቦታ ይሰጠናል ብለን ተስፋ ስናደርግ አሁን 100 ሚሊዮን ብር በብድር መልክ አምጡ መባላችን አስደንግጦናል" ያሉን አንድ የከተማው ነዋሪ ቆጣቢዎች አስተዳደሩ ብሩን ይመልሳል የሚል እምነት እንደሌላቸው ገልፀዋል።
"ለምን ይሆናል? ብለን ስንጠይቅም የሚሰጡን መልስ አንተ የልማት አደናቃፊ ነህ፣ የፅንፈኛ ደጋፊ ነህ፣ ሙሉ ስምህን ማነው? ከየት ማህበር ነህ? ወዘተ እያሉ ያሸማቅቃሉ" ያሉን ሌላኛው አስተያየት ሰጪ "ሰሚ እንደሌለ ብናውቅም የዚህን አስከፊ ድርጊት የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልን" ብለዋል።
በዚህ ዙርያ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደርን ለማነጋገር በተደጋጋሚ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
2100
07:27
14.04.2025
close
New items
Selected
0
channels for:$0.00
Subscribers:
0
Views:
lock_outline
Add to CartBuy for:$0.00
Комментарий