
- Main
- Catalog
- Religion & Spirituality
- Advertising on the Telegram channel «ዝክረ ቅዱሳን zikre kidusan»

Advertising on the Telegram channel «ዝክረ ቅዱሳን zikre kidusan»
contet creation
Channel statistics
Full statisticschevron_rightIt's easy with Telega.io. As the leading platform for native ads and integrations on Telegram, it provides user-friendly and efficient tools for quick and automated ad launches.
⚡️ Place your ad here in three simple steps:
1 Sign up
2 Top up the balance in a convenient way
3 Create your advertising post
If your ad aligns with our content, we’ll gladly publish it.
Start your promotion journey now!
4.ቅድስት ሐና ነቢይት (የሳሙኤል እናት - 1ሳሙ. ከ1 - 2ን ያንብቡ)
5.ቅዱሳን ኡሲፎርና ኡርያኖስ (ሰማዕታት)
6.አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ኢትዮዽያዊ (ፍልሠቱ)
7.ቅዱስ ሄኖስ ነቢይ
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን 3.አባታችን ኖኅና
እናታችን ሐይከል
4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
7.ቅድስት ሰሎሜ
8.አባ አርከ ሥሉስ
9.አባ ጽጌ ድንግል
10.ቅድስት አርሴማ ድንግል
=>+"+ ምንም እንኩዋ በለስም ባታፈራ:
በወይን ሐረግም ፍሬ ባይገኝ:
የወይራ ሥራ ቢጐድል:
እርሾችም መብልን ባይሰጡ:
በጐች ከበረቱ ቢጠፉ:
ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ:
እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል:: በመድኃኒቴ
አምላክ ሐሴት አደርጋለሁ:: +"+ (ዕን. 3:17)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
በቴሌግራም ለመከታተል👉https://t.me/mahberememenan
🛑በዩቲብለመከታተል👉 https://youtube.com/@zetewahedo27?
❖ ጥቅምት ፮ (6) ❖
✞✞✞ እንኩዋን ለቅዱስ "ዲዮናስዮስ ሐዋርያዊ" ወአባ "ዸንጠሌዎን" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
+"+ ቅዱስ ዲዮናስዮስ ሐዋርያዊ ሊቅ +"+
=>በዘመነ ሐዋርያት ከነበሩና አስደናቂ ታሪክ ከነበራቸው
ቅዱሳን አንዱ ይህ አባት ነው:: ቅዱስ ዲዮናስዮስ
በትውልዱ አረሚ (ግሪካዊ) የሆነ ፈላስፋ: ከነ አሪስቶትል
ሲያያዝ የመጣውን ፍልስፍና ጨርሶ በማጥናቱ ርዕሰ
ሊቃውንት (የፈላስፎች አለቃ) የሚል ስም ተሰጥቶት
ነበር::
+በግሪክ አቴና (ATHENS) ለነበሩ ፈላስፎችም ሁሉ
የበላይ ሲሆን በአርዮስፋጐስ (ሐዋ. 17) ታላቁ ሰው
እርሱ ነበር:: ይህ ሁሉ ሲሆን ግን እድሜው ገና ወጣት
ነበር:: ቅዱስ ዲዮናስዮስ ፈላስፋ ስለ ሆነ ቅሉ
ይመራመር ነበር::
+ይልቁኑ ስለ እውነተኛው አምላክ ያስብ ነበር:: በግሪክ
ምድር ከሚመለኩ 250 አማልክት መካከል ቁም ነገር
አልተገኘምና:: ነገር ግን አንድ ቀን ዓለም በተፈጠረች
በ5,534 ዓመት: መጋቢት 27 ቀን: በዕለተ ዓርብ: 6
ሰዓት ላይ ምድር ተናወጠች:: ፀሐይ ጨለመች: ጨረቃ
ደም ሆነች: ከዋክብትም ረገፉ::
+በዚህ የተደናገጡ የአቴና (ATHENS) ነዋሪዎችና
ፈላስፎች ወደ ዲዮናስዮስ ተሰብስበው "መምሕራችን
የተፈጠረውን ነገር መርምረህ አስረዳን" አሉት::
+ዲዮናስዮስም ባለው ጥበብ ባሕሩን: የብሱን: ፀሐይ:
ጨረቃን: ከዋክብትን መረመራቸው:: "ወረከቦሙ
ኅዱዓነ" እንዲል በቀደመ ቦታቸው አገኛቸው:: ግራ
ቢገባው እንቅልፍ ከዐይኑ ተከለከለ::
+ከዚያም ወደ ቤተ መዛግብቱ ገብቶ መጻሕፍትን
ሲያገላብጥ "አርስጣላባ" የሚባል ግዙፍ መጽሐፍ
አግኝቶ ቢገልጠው "እልመክኑን" የሚል ጽሑፍ አገኘ::
ወደ ውጪ ወጥቶ በሕዝቡና ጠቢባኑ ፊት ልብሱን ቀድዶ
አለቀሰ::
+እነርሱም ደንግጠው "ምነው መምሕራችን? ምን
ሆንህ?" ቢሉት "የማይታየው አምላክ ቢወርድ
በምቀኝነት ገደሉት የሚል ጽሑፍ አገኘሁ" አላቸው::
"እልመክኑን" ማለት "የማይታይ አምላክ" ማለት ነውና::
"ዘኢያስተርኢ ኅቡዕ እስመ አስተርአየ ለነ:
እሳት በላኢ አምላክነ" እንዲል::
+ከዚህ በሁዋላ ደቀ መዛሙርቱን (ተማሮቹን) ጠርቶ
(ኡሲፎስና ኡርያኖስ ይባላሉ) "እልመክኑን" የሚለውን
ስም "ከቤተ ጣዖቱ በር ላይ ለጥፉት" ብሏቸው
ለጠፉት:: በእንዲህ ያለ መንገድ 14 ዓመታት አልፈው
ቅዱስ ዻውሎስ ወንጌልን እየሰበከ አቴና ደረሰ:: ዘመኑም
በ48 ዓ/ም ነበር::
+ወደ ከተማዋ ሲገባ በጣዖት ቤቱ በር ላይ
የተለጠፈውን ጽሑፍ ተመለከተና ያስተምራቸው ያዘ::
ትምሕርቱን የሰሙ ጠቢባኑና ሕዝቡ ሐዋርያውን ይዘው
ወደ ዲዮናስዮስ ፊት አቀረቡት:: "ምንድን ነው በደሉ?"
ቢላቸው "አዲስ አምላክን ሲያስተምር አግኝተነዋል"
አሉት::
+ቅዱስ ዻውሎስም "እኔ አዲስ አምላክን
የምሰብክላችሁ አይደለሁም:: ይልቁኑ ከቀድሞም
የፈጠራችሁ: ቀጥሎም የሞተላችሁ: እናንተም
"እልመክኑን" ብላችሁ ሳታውቁት ታመልኩት የነበረውን
ጌታ እንጂ:: እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው አላቸው::
+ዲዮናስዮስም ቅዱስ ዻውሎስን "ለዚህ ምን ምልክት
አለህ?" ቢለው "የዛሬ 14 ዓመት: መጋቢት 27 ቀን:
በዕለተ ዓርብ 6 ሰዓት ላይ ታላላቅ ተአምራት የተደረጉ
አይደለምን! እነዚህ ሁሉ የተደረጉት በስቅለቱ ጊዜ ነው"
ሲል መለሰለት::
+ዲዮናስዮስም ፈጥኖ በክርስቶስ አመነ:: የአካባቢው
ጠቢባንና ሕዝቡም አምነው ከመሪያቸው ጋር ተጠመቁ::
ቅዱስ ዻውሎስም ቅዱስ ዲዮናስዮስን አስተምሮ የአቴና
የመጀመሪያው ዻዻስ አደረገው:: ቅዱሱም ክርስቲያኖችን
ያበዛ: መንጋውንም ያጸና ዘንድ ብዙ ተጋ::
+በተለይ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ታዋቂ
ደራስያን አንዱ ሆነ:: በርካታ ድርሰቶችንም በመንፈስ
ቅዱስ ደረሰ:: ዛሬ ድረስ እንኩዋ ሃይማኖተ አበው
ውስጥ የሚገኘው ድርሰቱ (ዘዲዮናስዮስ) ጣዕሙ ልዩ
ነው:: ቅዱሱ ለብዙ ዘመናት ለወንጌል አገልግሎት
ተግቶ: በዚህች ቀን የአካባቢው አገረ ገዥ አንገቱን
አስቆርጦት ሰማዕት ሆኗል::
+የሚገርመው ግን ሲገድሉት በቦታው ሰው ስላልነበረ
ቅዱሱ ተነስቶ: ተቆርጣ የወደቀች ራሱን አነሳት:: በጐኑ
አቅፎም ደቀ መዛሙርቱ እስካሉበት ሒዶ በፊታቸው
ዘንበል አለ:: ምዕመናንም እያለቀሱና እየዘመሩ
ከአርድእቱ ኡሲፎስና ኡርያኖስ ጋር ቀብረውታል::
እነርሱም አብረውት ተሰይፈዋልና::
+"+ አባ ዸንጠሌዎን ዘጾማዕት +"+
=>ታላቁ ጻድቅ: ሰባኬ ወንጌልና ገዳማዊ አባ
ዸንጠሌዎን የተስዓቱ (ዘጠኙ) ቅዱሳን መሪ (አባት)
ናቸው:: ጻድቁ ሃገረ ሙላዳቸው ሮም ቢሆንም
ገድላቸውን የፈጸሙት በኢትዮዽያ ነው::
+ወላጆቻቸው በሮም ቤተ መንግስት የቀኝ መንበር
ያላቸው ክቡራን ቢሆኑም ልጃቸውን ይማር ብለው ወደ
ገዳም ከተቷቸው:: በገዳም ትምሕርቱን ከጠነቀቁ
በሁዋላ በዚያው ጠፍተው ወደ ግብጽ ወረዱ:: በዚያም
መነኮሱ::
+እድሜአቸው እየገፋ ሲሔድ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት
8ቱን ቅዱሳን ሰብስበው: በአቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል)
መሪነት ወደ ሃገራችን መጡ:: በ470ዎቹ አካባቢ
የነበረው ንጉሥ አልዓሜዳም በክብር ተቀብሎ አክሱም
ውስጥ "ቤተ - ቀጢን" የሚባል ቦታን ሰጣቸው::
+ዘጠኙ ቅዱሳን በአንድነት: ቀን ቀን ወንጌልን
ሲያስተምሩ ውለው ሌሊት ሲጸልዩና መጻሕፍትን
ሲተረጉሙ ያድሩ ነበር:: ነገር ግን ለየብቻቸው
መኖራቸውን መንፈስ ቅዱስ ስለ ወደደ ሁሉም
በየራሳቸው ገዳማትን መሠረቱ::
+አባ ዸንጠሌዎንም ከአክሱም ከተማ በላይ ከደብረ
ቆናጽል ጐን ወደ ሚገኝና 'ጾማዕት' ወደ ሚባል ረዥም
ተራራ ወጡ:: ቦታው ዛሬ "እንዳባ ዸንጠሌዎን" ይባላል::
በዚያም አስቀድመው ለወንጌል አገልግሎት እየተጉ
ድውያንን ፈወሱ::
+ሙታንን አስነሱ: አጋንንትን አሳደዱ:: ብዙ ተአምራትንም
አደረጉ:: እንዲያውም አንድ ቀን ወይራውን በጧት
ተክለው: በሠርክ ትልቅ ዛፍ ሆነላቸው:: ከዚያ ዘንጥፈው
እሳቱን በቀሚሳቸው ላይ አፍመው ማዕጠንት
አሳርገዋል::
+የሚገርመው ያ ዛፍ ዛሬም ድረስ ለምስክርነት ቁሟል::
እኛም ሳይገባን ሔደን በዓይናችን አይተነዋል:: አምላከ
ቅዱሳን ግሩም ነው !!! በመጨረሻ ዘመናቸው ግን ጻድቁ
5 ክንድ ርዝመት ባላት ጾማዕት (በዓት) ውስጥ ገብተው
ቆሙ:: ለ45 ዓመታት ሳይቀመጡና ሳይተኙ በእንባ
ቢጸልዩ ቅንድባቸው ተላጠ:: አካላቸውም በአጥንቱ ብቻ
ቀረ::
+በ6ኛው ክ/ዘመንም በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት
መድኃኔ ዓለም መጥቶ "ወዳጄ! ስምህን የጠራ:
መታሰቢያህን በእምነት ያደረገውንም ሁሉ እምርልሃለሁ"
አላቸው:: ያን ጊዜ አጥንቶቻቸው ተወዛወዙና ነፍሳቸው
በክብር ዐረገች:: ከዚህ አስቀድሞም ንጉሡን አፄ
ካሌብን አባት ሆነው ያመነኮሱት እርሳቸው ናቸው::
=>አምላከ አበው የወጡ ወገኖቻችንን ሁሉ በሰላም
ይመልስልን:: ከክብረ ቅዱሳንም አይለየን::
=>ጥቅምት 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዲዮናስዮስ ሐዋርያዊ
2.አባ ዸንጠሌዎን ዘጾማዕት
+"+ ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ +"+
=>እነዚህ ነገሥታት ሞገሶቻችን: ብርሃኖቻችን ናቸውና ደስ እያለን እንወዳቸዋለን: እናከብራቸዋለን:: ሥላሴ ቢመርጧቸው ዛሬ ላለንበት ሕይወት መሠረቱን ጥለው አልፈዋልና::
+2ቱ ቅዱሳን ነግሥታት መንትያዎች ሲሆኑ ወላጆቻቸው ንጉሥ ታዜር / አይዛና / ሠይፈ አርዕድ እና ንግሥት አሕየዋ / ሶፍያ ይባላል:: ንጉሡና ባለቤቱ ልጅ ቢያጡ ወደ እግዚአብሔር ለመኑ:: ፈጣሪም በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት 2 ዕንቁዎችን አስረከባቸው::
+ንግስት አሕየዋ (ሶፍያም) መጋቢት 29 ቀን በ311 ዓ/ም ጸንሳ: ታሕሳስ 29 ቀን በ312 ዓ/ም 2ቱን ቅዱሳን ወልዳቸዋለች:: "አምላክ ሽሙጥን አራቀልኝ" ስትልም "አዝጉዋጉ" ብላቸዋለች:: እነዚህ 2 ፍሬዎች በልጅነታቸው ከወቅቱ ሊቀ ካህናት እንበረም ኦሪቱን ጠንቅቀው ተምረዋል::
+ከእግዚአብሔር የተሰጡ ናቸውና በ12 ዓመታቸው ወደ ቤተ መቅደስ ገብተዋል:: ትንሽ ቆይቶ ግን አባታቸው ታዜር በማረፉ ሕዝቡ 2ቱን ቅዱሳን "ንገሡልን" አሏቸው:: እነርሱም "እኛ የፈጣሪ አገልጋዮች ነንና አንችልም" በማለታቸው ለተወሰነ ጊዜ እናታቸው አስተዳደረች::
+ቆይቶ ግን ቅዱስ ሚካኤል ለሊቀ ካህናቱ እንበረም "የፈጣሪ ፈቃዱ ስለ ሆነ አትዘኑ:: 2ታችሁም በአንድ ዙፋን ላይ ንገሡ: ታላቅ ጸጋ ለሃገሪቱ ይሆናል በላቸው" አለው::
+ሊቀ ካህናቱም የታዘዘውን ተናግሮ: በ19 ዓመታቸው: 2ቱንም በአንድ ዙፋን ላይ "ነገሥተ ኢትዮዽያ" ሲል አስቀምጦ ቀባቸው:: ስማቸውን "ኢዛና" እና "ሳይዛና" አላቸው:: ቅዱሳኑ እንደ ነገሡ ቀዳሚ ሥራቸው የቀናችውን ሃይማኖት መፈለግ ሆነ::
+በወቅቱ ፍሬምናጦስ (የሁዋላው አቡነ ሰላማ) በቤተ መንግስቱ ውስጥ የቅርብ አማካሪ ነበርና ጠርተው ተጨዋወቱት:: "አንተ ወንድማችን! ክርስቶስ ይወርዳል: ይወለዳል ተብሎ የተቆጠረው ሱባኤ እኮ አልፏል:: ምነው ቀረሳ? በርግጥ ምሥጢሩ ንገረን" አሉት::
+እርሱም አትቶ: አመሥጥሮ: ከ300 ዓመታት በፊት አምላክ ሰው መሆኑንና ዓለምን ማዳኑን አስተማራቸው:: "አጥምቀን?" ቢሉት "አልችልም" አላቸው:: እነርሱም ከብዙ ስጦታ ጋር ወደ ግብጽ ላኩት::
+ቅዱስ አትናቴዎስም ፍሬምናጦስን "አቡነ ሰላማ" ብሎ ከብዙ መጻሕፍት ጋር ላከው:: በመጀመሪያ ኢዛናና ሳይዛና ተጠመቁ:: ስማቸውም "አብርሃ ወአጽብሃ" ተባለ:: ቀጥሎም ሠራዊቱና ሕዝቡ ተጠመቀ::
+ሃገራችንም በእነዚህ ቅዱሳን አማካኝነት ከጨለማ ወደ ብርሃን መጣች:: የክርስትና ደሴት ሆነች:: ሃገረ እግዚአብሔርነቷንም አጸናች:: ቅዱሳኑ ከዚህ በሁዋላ በሞገስ ክርስትናን ያስፋፉ ዘንድ ደከሙ:: ከ154 በላይ አብያተ ክርስቲያናትን ሲያንጹ አብዛኞቹ ፍልፍል ነበሩ::
+በተለይ ግን በአክሱም ከተማ ላይ ያነጿትና 12 ቤተ መቅደሶች የነበሯት የጽዮን ቤተ ክርስቲያን ልናያት ትናፍቀናለች:: ጌጧ: ብርሃኗ ውል ውል ይልብናል:: ይህቺው ቤተ ክርስቲያን በ10 ኛው ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት በእሳት አውድማታለችና:: መሠረቱ ግን ዛሬም አለ::
+ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ ግን ክርስትናን ለማስፋፋትና መንግስትን ለማጽናት ሲሉ ከአክሱም በተጨማሪ በሽዋም ዙፋንን ዘረጉ:: ለብዙ ዓመታትም አምላክ በፈቀደው መንገድ እስከ የመን ድረስ ገዙ:: ክርስትናንም አስፋፉ::
+ቅዱስ አብርሃ በተወለደ በ52 ዓመቱ: በ364 ዓ/ም ጥቅምት 4 ቀን ሲያርፍ ወንድሙ ለ15 ዓመታት ብቻውን አስተዳድሯል:: በ379 ዓ/ም ደግሞ በዚሁ በጥቅምት 4 ቀን ቅዱስ አጽብሃም በተወለደ በ67 ዓመቱ በክብር ዐርፏል::
+ከሁለቱም መቃብር ላይ ለ30 ቀናት የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ ታይቷል:: ጌታችንም በማይታበል ቃሉ "ስማችሁን የጠራውን: መታሰቢያችሁን ያደረገውንም እምርላቹሃለሁ" ሲል ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል::
+"+ ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ +"+
=>ሐናንያ ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ስማቸው ተመዝግቦ ከተቀመጠልን ከጥቂቶቹ ዋነኛው ነው:: ከነገደ እሥራኤል ተወልዶ: በሕገ ኦሪት አድጐ: ከወጣትነት ዕድሜው ትንሽ እልፍ ሲል ጌታችን ወንጌልን ማስተማር ጀምሯልና ጠራው:: እርሱም በበጐ ፈቃድ ተከትሎታልና ከ72ቱ አርድእት ደመረው::
+ለ3 ዓመታት ከጌታ እግር ተምሮ: ከዕለተ ስቅለት በፊት ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት ነበር:: ምክንያቱም ቅዱስ ሉቃስ እንደ ጻፈልን ሰብዐው አርድእት "ጌታ ሆይ! አጋንንት በስምህ ተገዙልን" ማለታቸውን አስቀምጦልናል:: (ሉቃ. 10:17) ቅዱስ ሐናንያ በበዓለ ዕርገት ተባርኮ በ50ኛው ቀንም መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::
+በሚያስተምር ጊዜ የሶርያዋን ደማስቆን ማዕከል አድርጐ ነበር:: በሁዋላም አበው ሐዋርያት የዚህች ከተማ የመጀመሪያው ዻዻስ አድርገው ሹመውታል:: ጌታ ባረገ በ8ኛው ዓመት ክርስቲያኖችን ያሰቃይ የነበረው ሳውል (የሁዋላው ቅዱስ ዻውሎስ) ወደ ደማስቆ የተጉዋዘው ክርስቲያኖችን በተለይም ቅዱስ ሐናንያን ለማሠር ነበር::
+ለእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ ይሆን ዘንድ መብረቅ ዐይኑን አጠፋው:: ወዲያውም ጌታችን ሳውልን ወደ ሐናንያ እንዲሔድ ነው የነገረው:: ከ3 ቀናት በሁዋላ ጌታችን ለሐናንያ ተገልጦ አነጋግሮታል:: ሳውል (ዻውሎስ) ወደ ሐናንያ የደረሰው በመሪ ነበር::
+2ቱ እንደተገናኙ ቅዱስ ሐናንያ ሳውልን አስተማረው: ፈወሰው: አጠመቀው: በጐ መንገድንም መራው:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ሐዋርያ የቅዱስ ዻውሎስ የንስሃ አባቱ ይሰኛል:: (ሐዋ. 9:1-19)
+ከዚህ በሁዋላ ቅዱስ ሐናንያ ለብዙ ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወንጌልን አስተማረ መከራንም ተቀበለ:: በመጨረሻም በዚህ ቀን ክፉዎች ከብዙ ስቃይ በሁዋላ በድንጋይ ወግረው ገድለውታል::
=>አምላከ አብርሃ ወአጽብሃ "ድሃ ተበደለ: ፍርድ ተጉዋደለ" የሚል ዳኛ: ሃይማኖቱ የቀና መሪንም ያምጣልን:: የቅዱሳኑን ክብር በእኛ ላይ ያድርግልን::
=>ጥቅምት 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱሳን ነገሥት አብርሃ ወአጽብሃ
2.ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
4.ቅዱስ ባኮስ ሰማዕት
5.ቅዱሳን ባባ እና ማማ
6.ቅዱስ ዮሐንስ ሕጽው
=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ
2.ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
3.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
4.ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ (ሰማዕት)
=>+"+ እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ: ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር: ልመናና ጸሎት: ምልጃም: ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ: ስለ ነገሥታትና መኩዋንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ:: ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው:: +"+ (1ጢሞ. 2:1-4)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
በቴሌግራም ለመከታተል👉https://t.me/mahberememenan
🛑በዩቲብለመከታተል👉 https://youtube.com/@zetewahedo27?
††† ጥቅምት 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት †††
+" ቅዱስ ጊዮርጊስ ሐዲስ "+
††† ሰማዕቱ የተወለደው በምድረ ግብጽ አሕዛብ (ተንባላት) በሰለጠኑበት የመጀመሪያው ዘመን ነበር:: በተለይ ተንባላቱ ግብፅና ሶርያን ከያዙ በኋላ ባልተጠበቀ ፍጥነት በኃይልም በሰውም ተደራጅተው ነበር:: ቅዱስ ጊዮርጊስ (ልብ በሉልኝ ሊቀ ሰማዕታት አይደለም) የተወለደው በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ነበር::
+እናቱ የተመሠከረላት ክርስቲያን ብትሆንም እንዳለመታደል አባቱ ተንባላታዊ (አሕዛብ) ነበር:: ስሙንም መዛሕዝም ይሉታል:: ሕጻኑ እንደተወለደ ያወጡለት ስም አሕዛባዊ ከመሆኑ ባለፈ በሰዓቱ መጠመቅ አልቻለም:: የወቅቱ ሕግ ከወላጆቹ አንዱ አሕዛባዊ ከሆነና አጠምቃለሁ ቢባል የሚከተለው ሰይፍ ነበር:: በዚሕ ምክንያት ሳይጠመቅ 7 ዓመት ሞላው::
+እናቱ ግን ሕጻን ቢሆንም ፍቅረ ክርስትናን ታስተምረው ነበር:: ባይጠመቅም ጸበሉን: እመነቱን ትቀባው ነበር:: ደብቃ ቅዳሴ ታሰማውም ነበር:: አንድ ቀን ግን ሕጻናት ሲቆርቡ አይቶ ካልቆረብኩ ብሎ አለቀሰ:: ምን ታድርገው? ወደ ውጪ አውጥታ ከአውሎግያ (የሰንበት በረከት) አበላችው:: "ጌታየ! ልጄን እርዳው" አለች::
+ልክ በአፉ ሲቀምሳት መዓዛ መንፈስ ቅዱስ አደረበትና ፍጹም ተደሰተ:: ትንሽ ከፍ ሲል ለምን እንደማይጠመቅና እንደማይቆርብ እናቱን ጠየቃት:: "ልጄ ሆይ! ይገድሉሃል" አለችው::
ከዚህች ቀን ጀምሮ የሚጠመቅበትን ዘዴ ይፈልግ ጀመር::
+አስቀድሞ ትምሕርተ ክርስትናን ተማረ:: ለአካለ መጠን ሲደርስ አፈላልጐ ጠንካራ ክርስቲያን የሆነች ሴት አገባ:: ጥቂት ጊዜ ከቆየ በኋላ ሚስቱን ስለ መጠመቅ አማከራት:: "ሌላ ሃገር ሒደህ ተጠመቅ" አለችው:: ከግብፅ ተነስቶ ሶርያ ገባ::
አባቶችን አፈላልጎ ተጠመቀ:: ቀጥሎም መንገዱን ወደ ልዳ አደረገ::
+ወደ ደብሩ ተጠግቶ አባቶችን "ስም አውጡልኝ" ቢላቸው መንፈስ ቅዱስ አናግሯቸው "ጊዮርጊስ" አሉት:: እሱም ደስ እያለው: ባጭር ታጥቆ የልዳውን ቅዱስ ጊዮርጊስ ያገለግለው ገባ:: ትንሽ ቆይቶ ሁከት መንፈሳዊ ተሰማው:: ማለትም ስለ ሃይማኖቱ ደሙን ማፍሰስ ፈለገና ወደ ግብፅ ተመለሰ::
+በዚያ ያሉ አሕዛብ በክርስትና ስም: ልብስና ሞገስ ሲመለከቱት ተበሳጩ:: ዕለቱኑ አሠሩት:: ሌሊት እናቱና ሚስቱ መጥተው አሉት:- "አደራ! ፍቅረ ዓለም እንዳያታልልህ:: ሰማዕት ብትሆን ላንተም ክብር: ለእኛም ሞገስ ነው" ብለውም አጽናኑት:: እንዲህ ያሉ እናትና ሚስት ማግኘትም ታላቅ እድል ነው::
+ሐዲስ ጊዮርጊስም ጸና:: ከዚያች ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት ደበደቡት: አካሉን ቆራረጡት: ደሙንም መሬት ላይ አንጠፈጠፉት:: በየመንገዱ እየጎተቱ ተሳለቁበት:: እርሱ ግን ክርስቶስን ወዷልና ሁሉን ታገሰ:: ሌሊት በሆነ ጊዜም ጌታችን ተገልጦ "ከሰማዕታት ተቆጠርህ" አለው::
+በማግስቱ በአደባባይ አንገቱን በሰይፍ ቆረጡት:: ክፋታቸው የጸና ነውና ሥጋውን በእሳት አቃጠሉት:: ወደ ባሕርም ጣሉት:: እናቱ ከባሕር ስታወጣው ግን ምንም አላገኘውም ነበር:: በዚሕች ቀን እናቱና ሚስቱ በክብር ቀብረውታል::
+" አባ ስምዖን ሊቀ ዻዻሳት "+
+በምድረ ግብጽ ተነስተው: በማርቆስ ወንጌላዊ መንበር ላይ ይቀመጡ ዘንድ ከተገባቸው ሊቃነ ዻዻሳት አንዱ እኒህ አባት ናቸው:: ከልጅነታቸው መንነው ብዙ ዘመናትን በተጋድሎ በማሳለፋቸው ሥጋዊ አካላቸው ደካማ ሆኖ ነበር::
+ከገዳማዊ አገልግሎታቸው ቀጥሎም ከእርሳቸው በፊት ለነበሩ ሁለት ፓትሪያርኮች ረዳት ሆነው አገልግለዋል:: በዚህ ጊዜም ለመንጋው የሚሆኑ ተግባራትን ከመፈጸማቸው ባሻገር በጾምና በጸሎት መጋደልን አልተዉም ነበር::
+ጊዜው ደርሶ በእግዚአብሔር ፈቃድ: በሕዝቡና ዻዻሳቱ ምርጫ: የእስክንድርያ 51ኛ ፓትርያርክ ሲሆኑ እርሳቸው እንደ ሌሎቹ አበው 'አልፈልግም' ብለው ነበር::
+ቀደም ሲል እንዳልነው አካላቸው በተጋድሎ የተቀጠቀጠ ነበርና በመንበራቸው ላይ ለብዙ ጊዜ መቆየት አልቻሉም::እግራቸውን በጠና በመታመማቸው ፈጣሪ ነፍሳቸውን እንዲቀበል ለመኑት: እርሱም ሰማቸው:: ሊቀ ዻዻሳት ሆነው በተሾሙ በ165ኛው ቀን (ማለትም በ5 ወር ከ15 ቀናቸው) በክብር ዐርፈው ተቀብረዋል::
††† ቸሩ አምላክ ከሰማዕቱ ጽናትን: ትእግስትን: ጸጋ በረከትን ይክፈለን::
††† ጥቅምት 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሐዲስ (ሰማዕት)
2.አባ ስምዖን ሊቀ ዻዻሳት
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘአርማንያ
4.ቅድስት ታኦድራ ልዕልት
5.ቅድስት ታኦፊላ
6.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
=>ወርኀዊ በዓላት
1.በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱሳን ሊቃነ ካህናት አበው (ዘካርያስና ስምዖን)
4.አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
5.አቡነ ዜና ማርቆስ
6.አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል
7.ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ (ዓምደ ሃይማኖት)
††† " ስለዚሕ ወንድሞቼ ሆይ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ:: ልባሞች እንደመሆናችሁ እላለሁ:: በምለው ነገር እናንተ ፍረዱ:: የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን?... እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ ነን:: ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና:: "††† (1ቆሮ. 10:14-18)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
በቴሌግራም ለመከታተል👉https://t.me/mahberememenan
🛑በዩቲብለመከታተል👉 https://youtube.com/@zetewahedo27?
Reviews channel
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ዝክረ ቅዱሳን zikre kidusan» is a Telegram channel in the category «Религия и духовность», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 13.3K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 12.3, with 0 reviews and an average score of 0.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 30.0 ₽, and with 0 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий