
©Legal details center© :የህግ ማብራሪያ ማዕከል©
ለማንኛውም የማስታወቂያ አገልግሎትእና የህግ ምክር አገልግሎት በዚህ ሊንክ ያናግሩን 🛑⚖️በዚህ channel ስለ ሕግ ጉዳይ ምክር ይሰጥበታል እንዲሁም በሀገሪቱ የወጡ ህጎች በSoft Copy ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ረገድ የድርሻውን ለመወጣት:- 🛑⚖️ነባር እና አዳዲስ አዋጆች 🛑⚖️መማሪያ መጽሀፎች በPdf እና በppt,ይለጠፍበታል ignorance of law is no excuse 💪
Channel statistics
===================
ትእዛዝ (order ) ,,,ብይን ( Ruling ) ,, ፍርድ (Judgement ),,ዉሳኔ ( Decision /Decree )
እነዚህ አራት ቃላት በሕግና በፍርድ ቤት የሥራ ሂደት ዉስጥ ተመሳሳይ ቢመስሉም የራሳቸው የሆነ የተለየ የሕግ ትርጉምና ደረጃ አላቸው ,,,,,,,,
1, ትእዛዝ ( Order )
" ትእዛዝ " ማለት አንድ የፍርድ ቤት ክርክር ከመጀመሩ በፊት ወይም በሂደት ላይ እያለ ፍርድ ቤቱ አንድን ነገር እንዲደረግ ወይም እንዳይደረግ የሚሰጠው መመሪያ ነው ።
ባህሪው
ጉዳዩ መዝጋት ወይም መጨረስ ሳይሆን ለሂደቱ መቀላጠፍ የሚሰጥ ነው ።
ለምሳሌ :
"ይህ ንብረት ለጊዜው እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ ታግዶል " ወይም " ተከሳሽ ለቀጣይ ቀጠሮ ምስክሮች ይዞ ይቅረብ " የሚሉ መመሪያዎች ትእዛዝ ይባላል ።
2, ብይን ( Ruling )
" ብይን" የሚሰጠው በክርክሩ ሂደት ዉስጥ ለሚነሱ መከራከሪያ ነጥቦች ( Interlocutory matters ) ምላሽ ለመስጠት ነው ።
ባህሪው
ዋናው የክርክር ዉጤት ( ማን አሸነፈ ? ማን ተሸነፈ ?) ሳይሆን በመሀል የሚነሱ የህግ ክርክሮችን ለመወሰን ነው ።
ለምሳሌ ;
" ፍርድ ቤቱ ይህንን ክስ ለማየት ስልጣን አለው / የለዉም " ወይም " ክሱ በይርጋ ይታገዳል / አይታገድም " የሚለው ዉሳኔ ብይን ይባላል ።
ብይን ብዙ ጊዜ ክርክሩን አያበቃዉም ይልቁንም ሂደቱን ይቀጥላል ።
3, ፍርድ ( Judgement )
" ፍርድ " ማለት ፍርድ ቤቱ የቀረበለትን ማስረጃዎች መርምሮ ; የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶና መዝኖ የሚሰጥ የመጨረሻ ድምዳሜ ነው ።
ባህሪው
ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ የደረሰበትን የሐቅና የህግ ድምዳሜ በዝርዝር የሚያስቀምጥበት ሰነድ ነው ።
ለምሳሌ ;
" ከሳሽ የንብረቱ ባለቤት መሆናቸውን ፍርድ ቤቱ አረጋግጧል "
የሚለው ሰነድ ፍርድ ነው
4,ዉሳኔ ( Decision /Decree )
" ዉሳኔ " በፍርድ ላይ ተመስርቶ የሚሰጥ ተግባራዊ ትዕዛዝ ነው ።
በፍርድ መደምደሚያ ላይ " በዚህ መሠረት ",,,,,,,,,ተብሎ የሚቀመጠው ነጥብ ነው ።
ባህሪው
በፍርድ የተረጋገጠውን መብት ወይም ግዴታ ለይቶ የሚያስቀምጥና ተፈፃሚ የሚሆን ነው ።
ለምሳሌ ;
ፍርዱ " ከሳሽ ባለቤት ናቸው " ካለ,,,,,
ዉሳኔዉ " ተከሳሽ ቤቱን ለከሳሽ በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ ያስረክቡ" የሚለው የመጨረሻ ትዕዛዝ ነው ።
ማጠቃለያ / ልዩነት
/ቃል/ ትኩረት / መቼ ይሰጣል ?
# ትእዛዝ
ለስራ ሂደት መመሪያ መስጠት
በማንኛውም ጊዜ
# ብይን
በመሀል ለሚነሱ መከራከሪያዎች መልስ መስጠት
በሂደት ላይ
# ፍርድ
ማስረጃ መዝኖ ድምዳሜ ላይ መድረስ
በክርክሩ ማብቂያ
# ዉሳኔ
መብትና ግዴታን ለይቶ መወሰን
በፍርድ መጨረሻ
https://t.me/Laww21C
***
በዳንኤል ፍቃዱ / ጠበቃና የህግ አማካሪ/
1. የአስፈጻሚው ፍርድ ቤት ሥልጣን እና ተግባር
የውሳኔው ተገዢነት፦ የአስፈጻሚው ፍርድ ቤት የተሰጠውን የፍርድ ውሳኔ የማስፈጸም ጠባብ ሚና ብቻ ነው ያለው። በፍርዱ ላይ አዳዲስ መብቶችን የመጨመር ወይም ግዴታዎችን የመቀነስ ሥልጣን የለውም (As is principle)።
ትርጓሜ፦ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን በድጋሚ የመስማት ሥልጣን ባይኖረውም፣ በፍርዱ አጻጻፍ ላይ ግልጽ ያልሆኑ ነጥቦች ካሉ ውሳኔው ሊፈጸም በሚችልበት ሁኔታ ላይ ጠባብ የትርጓሜ ሥራ ሊሠራ ይችላል።
2. ሐራጅ እንደ የመጨረሻ አማራጭ
ቅድሚያ የሚሰጣቸው አማራጮች፦ የንብረት ሽያጭ የመጨረሻው አማራጭ ነው። ሕጉ ከሐራጅ በፊት በስምምነት፣ በግል ሽያጭ ወይም ንብረቱን በዓይነት በማካፈል ዕዳው የሚከፈልበትን መንገድ ያበረታታል።
ሐራጅን የማስቆም መብት (አንቀጽ 427)፦ አንድ የፍርድ ባለዕዳ ሐራጁ ከመጠናቀቁ በፊት ሙሉ ዕዳውን፣ ወለዱን እና የአፈጻጸም ወጪውን ከከፈለ ሐራጁን የማስቆም መብት አለው። ከፊል ክፍያ ግን ሽያጩን አያስቆምም።
3. የሥነ-ሥርዓት መስፈርቶች (የሐራጅ ማስታወቂያ)
የሐራጅ ማስታወቂያ፦ ሕጋዊ ሐራጅ ለማካሄድ ስለ ንብረቱ ትክክለኛ መግለጫ እና ወቅታዊ የገበያ ዋጋ የያዘ ማስታወቂያ (በአንቀጽ 423 መሠረት) መውጣት አለበት።
ጥብቅ ተገዢነት፦ ተጫራቾች በማስታወቂያው ላይ በተጠቀሰው መግለጫ ይገደዳሉ። ለምሳሌ ማስታወቂያው ላይ የተጠቀሰው የቦታ ስፋት ካለው ትክክለኛ ስፋት ያነሰ ቢሆንም፣ ገዢው የሚያገኘው በማስታወቂያው ላይ የተጠቀሰውን ስፋት ብቻ ነው።
4. የሁለተኛ ሐራጅ ሥርዓት (አንቀጽ 428)
የመጀመሪያ ሐራጅ፦ የቀረበው ከፍተኛ ዋጋ ፍርድ ቤቱ ካስቀመጠው ግምት ጋር እኩል ካልሆነ ወይም ካልበለጠ ንብረቱ አይሸጥም።
ሁለተኛ ሐራጅ፦ የመጀመሪያው ሐራጅ ካልተሳካ፣ በሁለተኛው ሐራጅ ወቅት ንብረቱ ለቀረበው ከፍተኛ ዋጋ ይሸጣል። በዚህ ደረጃ ዕዳው እንዲከፈል ለማድረግ ሲባል መጀመሪያ የተቀመጠው ግምት ዋጋ አይኖረውም።
5. የሦስተኛ ወገኖች ጥበቃ (አንቀጽ 418)
ተቃውሞ የማቅረብ መብት፦ በፍርዱ ሂደት ውስጥ ተከራካሪ ያልነበሩ ሦስተኛ ወገኖች፣ ንብረቱ ከመታገዱ በፊት በንብረቱ ላይ ሕጋዊ መብት ወይም ይዞታ ካላቸው አፈጻጸሙን የመቃወም መብት አላቸው።
የውል ቅድሚያ፦ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ እንደሚያሳየው፣ ንብረቱ ከመታገዱ በፊት የተደረገ ሕጋዊና የተመዘገበ የሽያጭ ውል፣ ምንም እንኳ የባለቤትነት ካርታው ዝውውር ባያልቅም፣ ከእገዳው በላይ ቅድሚያ ይሰጠዋል።
6. የሕገ-መንግሥት ገደቦች (የገጠር መሬት ሽያጭ ክልከላ)
የመሬት ባለቤትነት፦ በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 40(3) መሠረት መሬት የመንግሥትና የሕዝብ ነው።
የገጠር መሬት ሽያጭ፦ የገጠር መሬትን ለዕዳ መክፈያነት በሐራጅ መሸጥ በፍጹም የተከለከለ ነው። በገጠር መሬት ላይ ያሉ እንደ መጋዘን ያሉ ግንባታዎችንም ለመሸጥ የሚደረግ ጥረት በሕግ ፊት ዋጋ የለውም።
7. የክፍያ ክፍፍል (አንቀጽ 403)
በተመጣጣኝ የማካፈል መርህ፦ አንድ አበዳሪ ንብረቱን ቀድሞ ስላሳገደ ብቻ ቅድሚያ አያገኝም። ከሽያጩ የሚገኘው ገንዘብ፣ ንብረቱ ሳይሸጥ በፊት የአፈጻጸም ጥያቄ ላቀረቡ ሁሉም የፍርድ ባለመብቶች እንደ ዕዳቸው መጠን በተመጣጣኝ (Pro-rata) ይከፋፈላል።
ለበለጠ መረጃ ቻናላቺንን ይወዳጁ
t.me/judgeoffed
ወላጅ እናቱንና እህቱን በዘግናኝ ሁኔታ የገደለው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ።
አሰቃቂ የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ገርቦ ቀበሌ ነው።
በዚሁ ቀበሌ ወላጅ እናቱንና እህቱን በዘግናኝ ሁኔታ በገደለ ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ ውሳኔ መተላለፉን የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግና የምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
የምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ፖሊስ የወንጀልና ታክቲክ ጉዳዮች ምርመራ ዘርፍ አስተባባሪ ኢንስፔክተር ደሣለኝ ዳመና ምን አሉ ?
" ተከሳሹ ወጣት ሰንበቶ መንገሻ ይባላል።
ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም ለግድያ የሚያበቃ ምንም ዓይነት ጥል ሳይኖር የመኖሪያ ቤቱን በር ከውስጥ በመቆለፍ ወላጅ እናቱንና እህቱን በሳንጃ በጭካኔ ገድሏል።
ፖሊስ ባደረገው ማጣራት፣ ወንጀል ፈጻሚው ወላጅ እናቱን በሳንጃ አንገታቸውን፣ ሆዳቸውንና ጀርባቸውን በመውጋት፣ እንዲሁም ጡታቸውን በመቁረጥ ሕይወታቸው እንዲያልፍ አድርጓል።
ይህን ድርጊት አይታ የጮኸችውን ታናሽ እህቱንም በአንገቷ አካባቢ ደጋግሞ በመውጋት ለሞት ዳርጓክ።
ተከሳሹ ቀደም ሲል የመከላከያ አባል ነበር በሕገ-ወጥ መንገድ ከድቶ (ኮብልሎ) የወጣ ነው። " ብለዋል።
የሀዲያ ዞን ሾኔ ምድብ ችሎት ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ አቶ ግዛቸው ታደሴ በበኩላቸው፤ ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመበትን አኳኋን ከፖሊስ ጋር በመሆን በምርመራ ማጣራታቸውን ገልጸዋል።
ለፍርድ ቤቱም የአስከሬን ምርመራ ማስረጃ፣ ተከሳሹ ለወረዳው ፍርድ ቤት የሰጠው የእምነት ክህደት ቃል እና የሰው ምስክሮችን በማቅረብ ክስ ተመስርቷል።
የክስ መዝገቡን የተመለከተው የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሾኔ ምድብ ችሎት የድርጊቱን አሰቃቂነትና የተከሳሹን የጭካኔ ደረጃ ከግምት ውስጥ በማስገባት ግለሰቡ በሞት እንዲቀጣ በሙሉ ድምፅ ወስኖበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ወላጅ እናቱንና እህቱን በዘግናኝ ሁኔታ የገደለው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ።
አሰቃቂ የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ገርቦ ቀበሌ ነው።
በዚሁ ቀበሌ ወላጅ እናቱንና እህቱን በዘግናኝ ሁኔታ በገደለ ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ ውሳኔ መተላለፉን የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግና የምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
የምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ፖሊስ የወንጀልና ታክቲክ ጉዳዮች ምርመራ ዘርፍ አስተባባሪ ኢንስፔክተር ደሣለኝ ዳመና ምን አሉ ?
" ተከሳሹ ወጣት ሰንበቶ መንገሻ ይባላል።
ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም ለግድያ የሚያበቃ ምንም ዓይነት ጥል ሳይኖር የመኖሪያ ቤቱን በር ከውስጥ በመቆለፍ ወላጅ እናቱንና እህቱን በሳንጃ በጭካኔ ገድሏል።
ፖሊስ ባደረገው ማጣራት፣ ወንጀል ፈጻሚው ወላጅ እናቱን በሳንጃ አንገታቸውን፣ ሆዳቸውንና ጀርባቸውን በመውጋት፣ እንዲሁም ጡታቸውን በመቁረጥ ሕይወታቸው እንዲያልፍ አድርጓል።
ይህን ድርጊት አይታ የጮኸችውን ታናሽ እህቱንም በአንገቷ አካባቢ ደጋግሞ በመውጋት ለሞት ዳርጓክ።
ተከሳሹ ቀደም ሲል የመከላከያ አባል ነበር በሕገ-ወጥ መንገድ ከድቶ (ኮብልሎ) የወጣ ነው። " ብለዋል።
የሀዲያ ዞን ሾኔ ምድብ ችሎት ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ አቶ ግዛቸው ታደሴ በበኩላቸው፤ ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመበትን አኳኋን ከፖሊስ ጋር በመሆን በምርመራ ማጣራታቸውን ገልጸዋል።
ለፍርድ ቤቱም የአስከሬን ምርመራ ማስረጃ፣ ተከሳሹ ለወረዳው ፍርድ ቤት የሰጠው የእምነት ክህደት ቃል እና የሰው ምስክሮችን በማቅረብ ክስ ተመስርቷል።
የክስ መዝገቡን የተመለከተው የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሾኔ ምድብ ችሎት የድርጊቱን አሰቃቂነትና የተከሳሹን የጭካኔ ደረጃ ከግምት ውስጥ በማስገባት ግለሰቡ በሞት እንዲቀጣ በሙሉ ድምፅ ወስኖበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
1)እናት የምታቀርበዉ የመካድ ክስ ሰመቁ 167286 መጋቢት 27 ቀን 2011 ዓ.ም
2)የድምፅ ብክለት (nuisance civil code 1225) ቅፅ 11, 42824
3)መመሪያወች ከህግ ዉጭ መዉጣት አዋጅ ቁጥር 1183/2020 አንቀፅ 53 እና ተከታዮቹ
4)የመፋለም መብት(petitory action) ቅፅ 10,43600 & HOF 67/2011
5) በህጉ በተቀመጠዉ ጊዜ ዉርሱን ያጣራ ወራሽ የዉርስ ሀብት ክፍፍል ክስ ቅፅ 10,38533
6)በአደራ የተሠጠን ዕቃ በዉሉ ላይ ገደብ ከሌለዉ ከአደራ ተቀባዩ ለማስመለስ(Contract of bailment) ቅፅ 10,48048
7)ቀጣይነት ያለዉ የዉል መጣስ(continous breach of contract) ቅፅ 6,28686
8) ህገወጥ ዉል(unlawful contract) ቅፅ 12,43226
9)የዉርስ ሀብቱን ስመሀብት በጋራ ያስመዘገበ ወራሽ ሠመቁ 151868 ያልታተመ
10)የወራሽነት የምስክር ወረቀት ይሰጠኝ አቤቱታ ሠመቁ 236246 ያልታተመ
11)የዉርስ ሀብትን በጋራ ይዞ እየተጠቀመ ባለ ሠዉ ላይ የሚቀርብ ክስ 216383 ያልታተመ
12)ሟች በህይወት እያለ ንብረቱን በያዘዉ ሰዉ ላይ ማች ከሞተ በኋላ በወራሾች የሚቀርብ ክስ 213601 ያልታተመ
13)በወለድ አግድ (antichresis) የማይንቀሳቀሰዉን ንብረት በመያዣ የሠጠ ሰዉ እዳዉን በማንኛዉም ጊዜ ከፍሎ ንብረቱን ማስመለስ ይችላል ቅፅ 13 72463
14)የመያዣ ዉል(mortgage) ቀሪ የሚሆን(character of lapse)እንጅ የይርጋ ጉዳይ(period of limitation) አያስነሣም ቅፅ 10 44800
15)የመንግስትን መሬት በህገወጥ መንገድ መያዝ ሰመቁ 93013,96203 ያልታተመ
16)ባልና ሚስት በሁኔታ ፍች ባለመኖሩ ለረጅም ጊዜ በየግላቸዉ ተለያይተዉ ከኖሩ በኋላ የጋራ ሀብት ንብረት ክፍፍል በተመለከተ ቅፅ 4 20938,HOF 49/10,50/10 &71/12
17)ዳግም ዳኝነት (Review of judgment) ዉሳኔ ከተሰጠ በኋላ በማንኛዉም ጊዜ ምክንያቱም ማስረጃዉ ወንጀል ጠቀስ,በሀሠት የተዘጋጀ መሆን ስላለበት
t.me/judgeoffed
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ስነ-ምግባር ሰዎች፦ በተለያዩ ቦታዎች ማድረግ ወይም ያለማድረግ የሚጠበቅባቸውን ባህሪያት ወይም ተግባራት መገለጫ ሲሆን ይህም በሥነ ምግባር ደንቦች ውስጥ ተካቶና ተዘርዝሮ ሊገኝ ይችላል።የስነ-ምግባር ደንቦች ተግባራዊነታቸው፦
~ #በስራ_ቦታዎች
~ #በትምህርት_ቤቶች
~ #በማኅበረሰብ_ውስጥ
~ #በሀይማት_ተቋማት
~ #ሰው_በተሰበሰበባቸው_ቦታዎች_እና_በመሳሰሉት_ቦታዎች_ይገኛሉ። የሞያ ስነ-ምግባር ደንቦች ሰራተኞች ወይም ባለሞያዎች በስራ ቦታቸው ማክበር የሚጠበቅባቸውን መርሆች፣ህጎች እና መመሪያዎች ስብስብ ነው። ባለሞያዎች በተለይም ዐቃቤያን ሕግ፣ ዳኞች ሊኖራቸው ስለሚገባ የሞያ ስነ-ምግባር የተለመዱ ብሔራዊ ልማዶችን እና ዓለም ዓቀፍ ህጎችን እንዲሁም የተለያዩ የሀገር ወስጥ ህጎችን መሠረት በማደረግ እንዳስሳለን።
፨፨፨፨
>> በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የተለመዱ የሕግ ባለሞያዎች የሞያ ስነ-ምግባር ደንቦች <<
፨፨፨
የሞያ ስነ-ምግባር ደንቦች ከሀገር ሀገር ሊለያዩ ቢችሉም በበርካታ ሀገራት ተቀባይነት ያገኙ እና በስራ ላይ የሚውሉ፦
፩ኛ #የዳኞች
፪ኛ #የዐቃቤያን_ሕግ_ሥነ_ምግባሮች_አሉ። በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የሕግ ባለሞያዎችን ሊገዙ የሚችሉ የተለያዩ የሥነ-ምግባር ደንቦች ወይም ስምምነቶች ያሉ ሲሆን ሀገራትም እነዚህን ደንቦች እንደ ሀገራቸው ነባራዊ ሁኔታ ተግባራዊ ሲያደርጉ ይስተዋላል። በመቀጠል እነዚህን የሞያ ሥነ-ምግባር ደንቦች እንመለከታለን።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
>> #የዳኞች_ስነ_ምግባር <<
እ.ኤ.አ በ2002 የወጣው የባንጋሎር የዳኝነት ሥነ-ምግባር መርሆዎች በሰፊው የታወቀ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው ሲሆን ዳኞች በሥነ ምግባር፣ በታማኝነት እና በገለልተኝነት ማገልገል እንዳለባቸው ያስቀምጣል።ቁልፍ መርሆቹ የሚከተሉትን ያካትታሉ፡-
፩ኛ #ነጻነት_Independence
፪ኛ #አለማዳላት_Impartiality
፫ኛ #ታማኝነት_ሀቀኝነት_Integrit
፫ኛ #ጨዋነት_Propriety
፬ኛ #እኩልነት_Equality
፭ኛ #ብቃት_እና_ትጋት_Competence_and_Diligence የሚሉትን ቁልፍ መርሆች ሲሆኑ በዝርዝር ስንመለከታቸው ደግሞ፦
>> ነጻነት Independence <<
ዳኞች ከፖለቲካ ተጽእኖ፣ ከፓርቲዎች እና ከውጭ ጫናዎች ነጻ መሆን አለባቸው። በግላዊ ፍላጎቶች ወይም ግንኙነቶች ላይ ተጽዕኖ ማሳደር የለባቸውም።
~~~
>> አለማዳላት Impartiality <<
ጉዳዮችን በሕግ እና በማስረጃዎች ላይ ብቻ በመመስረት መወሰን አለባቸው።
~~~
>> ታማኝነት Integrity <<
ዳኞች በታማኝነት መሥራት እና የዳኝነትን ክብር ማስጠበቅ ያለባቸው ሲሆን በሁሉም እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ያለአግባብ የሆኑ ተግባራትን ማስወገድ አለባቸው።
~~~
>> ጨዋነት Propriety <<
ዳኞች የዳኞች የአኗኗር ዘይቤን መጠበቅ ያለባቸው ሲሆን ከማኅበራዊ ጉዳዮች እራሳቸውን መገደብ ይኖርባቸዋል። እንዲሁም የፍትሕ አካላትን መልካም ስም ሊያበላሹ ከሚችሉ ተግባራት እራሳቸውን ማራቅ አለባቸው።
~~~~
>> እኩልነት Equality <<
ሁሉንም ግለሰቦች እና ባለጉዳዮች ያለ አድልዎ እና በአክብሮት መያዝ አለባቸው።
~~~
>> ብቃት እና ትጋት Competence and Diligence <<
ዳኞች ስራቸውን ብቃት ባለው የሕግ እውቀት እና በሕግ አግባብ ማከናወን አለባቸው።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
>> #የዐቃቤያን_ህግ_ስነ_ምግባር <<
ዐቃብያነ ህጎች መንግሥትን በመወከል ክስ ማቅረብ እና የጥፋተኝነት ውሳኔዎችን ማሰጠት ብቻ ሳይሆን ፍትሕን የማስከበር ኃላፊነት አለባቸው። በ1990 በወጣው የተባበሩት መንግስታት የዐቃብያነ-ሕግ ሚና መመሪያዎች እና የብሔራዊ የክስ ኮዶች ላይ እንደ ሰፈረው ይህን ሀላፊነታቸው በሚወጡበት ወቅት ሊከተሏቸው ከሚገቡ ስነ-ምግባሮች መካከል፡-
፩ኛ #ፍትሃዊነት_Fairness
፪ኛ #አለማዳላት_Impartiality
፫ኛ #ታማኝነት_ሀቀኝነት_Integrity
፬ኛ #ሙያዊነት_Professionalism
፭ኛ #ተጠያቂነት_Accountability
፮ኛ #ትብብር_Cooperation የሚሉት ሲሆኑ ዝርዝር ምልከታውን በተመለከተ፦
>> ፍትሃዊነት Fairness <<
ለተከሳሾች ትክክለኛ አያያዝ ማድረግ እና የተጎጂዎችን መብት መጠበቅ እንዲሁም ማንኛውንም ዓይነት ጭፍን ጥላቻ ወይም አድልዎ ማስወገድ ይጠበቅባቸዋል።
~~~
>> አለማዳላት Impartiality <<
ጉዳዮችን መመርመር እና መወሰን ያለባቸው ከግል እምነት ወይም ውጫዊ ጫና ውጪ በመሆን ሕግን መሠረት በማድረግ መሆን አለበት።
~~~
>> ታማኝነት ሀቀኝነትIntegrity <<
ማንኛውንም የጥቅም ግጭት ማስወደግ ያለባቸው ሲሆን አስገዳጅ ማስረጃዎችን ጨምሮ ማስረጃን በመግለጽ ረገድ ሐቀኝነትን መጠበቅ አለባቸው።
~~~
>> ሙያዊነት Professionalism <<
በህጋዊ አካሄዶች እና በሥነ-ምግባር ሀላፊነቶች ውስጥ ብቁ በመሆን ምስጢራዊነትን መጠበቅ እንዲሁም በማስተዋል እርምጃዎችን መውሰድ ይጠበቅባቸዋል።
~~~
>> ተጠያቂነት Accountability <<
ለህጋዊ መስፈርቶች እና ለሥነ-ምግባር ቁጥጥር አካላት ተጠያቂ ናቸው።
~~~
>> ትብብር Cooperation <<
ከሕግ አስከባሪዎች፣ ተከላካይ ጠበቆች እና ከፍርድ ቤቶች ጋር በትብብር እና በአክብሮት መሥራት አለባቸው።
በአጠቃላ፦#ስነ_ምግባር_ለሰው_ልጆች_የእለት_ተዕለት_እንቅስቃሴ_እጅግ_አስፈላጊ_ተግባር_ሲሆን_ከሞያቸው_ባህርይ_አንፃር_ደግሞ_ልዩ_ጥንቃቄ_እና_ትኩረት_የሚፈልጉ_የስራ #መስኮች_አሉ። ከእነዚህም ውስጥ የሕግ ሞያ አንዱ ሲሆን የሕግ ባለሞያ ሆነው በተለያየ ስራ ላይ የተሰማሩ የሕግ ባለሞያዎች የፍትሕ ስርዓቱን ውጤታማ ለማድረግ የሥነ-ምግባር ደንቦችን ማክበር ይኖርባቸዋል።
ለበለጠ መረጃ ቻናላቺንን ይወዳጁ
t.me/judgeoffed
Baga Ayyaana Iid al-Fixrii waggaa1447ffaan nagaan geessan.
Ethio Law Family Hordoftoota amantaa Islaamaa hundaan baga nagaan isin gahe jechaa ayyaanni kun kan Nagaafi,kan Jaalalaa akka isiniif tahu hawwa.
IID MUBAARAK!
ፊልም የሚመስል እውነተኛ የድሬዳዋ ፖሊስ ገድል!
ፍቅረኛውን ገድሎና አልጋ ዉስጥ ቀብሮ ለዓመታት ተሰውሮ የነበረውን አረመኔ ነፍሰ ገዳይ፤ በዘመናዊ የቴክኖሎጂ እና የስነ-ልቦና ጥበብ ተጠቅማ በቁጥጥር ስር ያዋለችው ጀግናዋ ዋና ሳጅን ስንዱ ካሳሁን የመነጋገሪያ ርዕስ ሆናለች።
ይህች የድሬዳዋ ፖሊስ መርማሪ፤ ገዳዩን በሶሻል ሚዲያ ካገኘችው በኋላ ራሷን እንደ "ፍቅረኛ ፈላጊ ነጋዴ" በማስተዋወቅ ለወራት የፍቅር ቃላትን እየወረወረችና ፎቶዎችን እየላከች ልቡን አሸነፈችው።
ወንጀለኛው የፍቅር ጓደኛ አገኘሁ ብሎ ሲመጣ በህግ ካቴና አጠለቀችለት።
ይህ ታሪክ በቅርቡ በአባይ ቲቪ "ካቴና" ፕሮግራም ላይ የቀረበ ሲሆን፤ ፀሐፊው ዋና ሳጅን ማሙሽ አዳፍሬ፤ "ይህች ጀግና ልትሾምና ልትሸለም ይገባል" ሲሉ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን እና ከንቲባ ይህንን የሴቶችን ብቃት ያሳየ ድንቅ ስራ እውቅና እንዲሰጡ ጥሪ ቀርቧል።
ጌጡ ተመስገን
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
1. የዐቃቤ ሕግ ተግባርና ሥልጣን ከወንጀል ጥቆማ ተቀባይ-መርማሪ-ከሳሽነት በላይ ነው:: ዐቃቤ ሕግ (public prosecutor) የወንጀል ምርመራን በራሱ ያደርጋል፣ ወይም ከመርማሪ ፖሊስ ጋር ተባብሮ ይመረምራል፣ ወይም ዐቃቤ ሕግ እየመራው መርማሪ ፖሊስ እንዲመረምር ያደርጋል። ስለሆነም ያለ ዐቃቤ ሕግ ዕውቅና ወይም ተሳትፎ የሚደረግ የወንጀል ምርምራ የለም::
2. ዐቃቤ ሕግ አንድ ተጠርጣሪ ሕግን ተከሎ ከተያዘ በኋላ እንደ ሁኔታው ከፖሊስ ጋር ተወያይቶ በዋስ ይለቃል ወይም የወንጀል ምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ብቻውን ወይም ከመርማሪ ፖሊስ ጋር ቀርቦ ስለ ምርመራው ሂደት እና ስለ ተጠርጣሪው የዋስትና ጉዳይ ክርክር ያደርጋል::
መርማሪ ፖሊስ ብቻውን በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርቦ ክርክር የሚያደርግ ከሆነም የዐቃቤ ሕግ ስለሚደረገው ክርክር መሪ ትእዛዝ ይሰጣል::
ስለሆነም መርማሪ ፖሊስ ያላግባብ ተጠርጣሪ በዋስ እንዳይወጣ ቢያደርግ፣ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጥ በችሎት ቢከራከር ወይም ፍ/ቤት በዋስ የፈታውን ተጠርጣሪ ወዲያውኑ ባይፈታ ዐቃቤ ሕግ በሥልጣን ያላግባብ መገልገል ርእስ ሥር በመርማሪው ላይ ምርመራ እንዲጣራ ያደርጋል::
3. ዐቃቤ ሕግ በፍርድ ቤት የተሰጠው ፍርድ ወይም የቅጣት ውሳኔ የተከሳሽን መሠረታዊ መብቶች ወይም የወንጀል ፍትሕ ዓላማን የማያሳካ ሆኖ ባገኘው ጊዜ ስለ ተከሳሽ ይግባኝ ይጠይቃል::
4. በተከሳሹ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ እና የቅጣት ውሳኔ ከተላለፈ በኋላ ተከሳሹ ወንጀሉን አለመፈጸሙን የሚያረጋግጥ በቂ ማስረጃ ካገኘ ጉዳዩ ፍርዱን በሰጠው ፍርድ ቤት በድጋሚ እንዲታይ (review of the criminal judgement) ዐቃቤ ሕግ ለፍ/ቤት "የወንጀል ፍርድ ድጋሚ ይታይልኝ" አቤቱታ የማቅረብ ግዴታ አለበት::
እና ሌሎችም ተግባሮች አሉት
ሰ/መ/ቁ.208350 (ቅፅ 26)
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
©Legal details center© :የህግ ማብራሪያ ማዕከል© is a Telegram channel in the category «Образование», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 5.2K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 27.4, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.92 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий