

Advertising on the Telegram channel «©Legal details center© :የህግ ማብራሪያ ማዕከል©»
ለማንኛውም የማስታወቂያ አገልግሎትእና የህግ ምክር አገልግሎት በዚህ ሊንክ ያናግሩን 🛑⚖️በዚህ channel ስለ ሕግ ጉዳይ ምክር ይሰጥበታል እንዲሁም በሀገሪቱ የወጡ ህጎች በSoft Copy ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ረገድ የድርሻውን ለመወጣት:- 🛑⚖️ነባር እና አዳዲስ አዋጆች 🛑⚖️መማሪያ መጽሀፎች በPdf እና በppt,ይለጠፍበታል ignorance of law is no excuse 💪
Channel statistics
Full statisticschevron_rightባህርዳር፣ ህዳር 15/2018 (አብክመ ጠ/ፍ/ቤት)
የአማራ ክልል የፍትሕና የህግ ኢኒስቲትዩት ላለፉት 20 ዓመታት በርካታ ቁጥር ያላቸውን ዳኞችና አቃቢያነ ህጎች በማሰልጠን ፣ ለክልሉ እና ለሀገሪቱ የዳኝነት እና የፍትሕ ስርዓት መሻሻል ጉልህ አስተዋጽኦ ሲያደርግ ቆይቷል።
ኢኒስቲትዩቱን ጠንካራ የስልጠና ፣ የምርምር እና የፍትሕ መረጃ ማዕከል ለማድረግ የለውጥ እና ተቋማዊ የማሻሻያ ስራዎች እየተደረጉ ሲሆን ፣ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በ2017 በጀት ዓመት ካከናወናቸው ስራዎች አንዱ ኢኒስቲትዩቱን እንደገና በማደራጀት እና ተጠሪነቱን ለጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን የተጀመረው እንቅስቃሴ ተጠቃሽ ነው።
ኢኒስቲትዩቱ ፣ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ስር እንደገና በተደራጀ ማግስት ለመጀመሪያ ጊዜ ለ8 ወራት በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር ያሰለጠናቸውን የ 17ኛ ዙር የቅድመ ስራ ሰልጣኞች አስመርቋል።
የምረቃ መረሀግብሩን የከፈቱት የኢኒስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ደሴ ጥላሁን (ዶ/ር) ተመራቂዎቹን ፣ በበርካታ ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ አልፋችሁ እዚህ በመድረሳችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና አመራሮች፣ የክልሉ መንግስት እንደ ክልል የዳኝነት እና የፍትሕ ስርዓቱን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት ውስጥ የወሰዱትን ቁርጠኛ አቋም ያደነቁት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ወደ ዳኝነት እና አቃቢያነ ህግነት ሙያ ለሚቀላቀሉ የቅድመ ስራ ሰልጣኞች የተሰጠው ተግባር ተኮር ስልጠና፣ እጩ ዳኞች እና አቃቢያነ ህጎቹ በእውቀት ፣ በክህሎት እና በላቀ ሙያዊ ስነምግባር ማህበረሰባቸውን በቅንነት እና በታማኝነት እንዲያገለግሉ በቂ አቅም የፈጠረ ነው ብለዋል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ እጩ ዳኞች እና አቃቢያነ ህጎች ማህበረሰባቸውን በፍጹም ሙያዊ ስነ-ምግባር ፣ በላቀ የአገልጋይነት መንፈስ እና ቁርጠኝነት ለማገልገል ያላቸውን ዝግጅት በተመለከተ በተወካያቸው አማካኝነት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ ከዳኝነት እና ከፍትሕ ስርዓቱ ጋር የተያያዙ ፣ ከሙያዊ ስነ-ምግባር እና ህዝብን በታማኝነት ማገልገል የዳኝነት እና የፍትሕ ባለሙያዎቹ ተቀዳሚ ሀላፊነት መሆኑን የሚያስገነዝቡ የስነ-ጽሁፍ ስራዎች ቀርበዋል።
የቅድመ ስራ ሰልጣኞችን መመረቅ ያበሰሩት እና ለተመራቂዎቹ የስራ መመሪያ ያስተላለፉት ፣ የእለቱ የክብር እንግዳ፣ የኢኒስቲትዩቱ የቦርድ ሰብሳቢ እና የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አለምአንተ አግደው፣ በክልሉ የዳኝነት እና የፍትሕ ማሻሻያ ላይ እየተደረጉ ያሉ የለውጥ ስራ ማሻሻያዎች ቀጣይነት ያለው ተቋማዊ ግንባታን ታሳቢ አድርገው መከናወናቸውን ተናግረዋል።
የክልሉን የዳኝነት እና የፍትሕ ስርዓት አገልግሎት አሰጣጥ በዘላቀነት ለማሻሻል ኢኒስቲትዩቱ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ስር ሆኖ እንደገና እንዲደራጅና በርካታ የአሰራር ማሻሻያዎች ተቋሙ ላይ በተካሄዱበት ማግስት ፣ እንዲሁም የክልሉ መንግስት የዳበረ የዳኝነት እና የፍትሕ ስርዓት ለዘላቂ ልማት እና ጤናማ የህብረተሰብ መስተጋብር ያለውን ድርሻ በመረዳት እየወሰድናቸው ያሉ የማሻሻያ ስራዎችን በላቀ ቁርጠኝነት እያገዘ ባለበት ሰዓት መመረቃቸውን የገለጹት ክቡር ፕሬዝዳንቱ፣ ተመራቂዎች ሙያችሁን እና የተሰጣችሁን ሀላፊነት ለግል ፍላጎታችሁ ሳይሆን በህበርተሰባችን መካከል የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት እና ህዝባችሁን በታማኝነት ለማገልገል እንድትጠቀሙበት አደራ እላለሁ ብለዋል።
በያዝነው ዓመት የባሕል ፍርድ ቤቶችን በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች እውቅና የመስጠት እና የማቋቋም ስራ ይሰራል ያሉት ክቡር አቶ አለምአንተ አግደው ፣ የባህል ፍርድ ቤቶቹን በማጠናከሩ ሂደት የቅድመ ስራ ሰልጣኝ ተመራቂዎቹ በሙሉ አቅም ማገዝ ይኖርባችኋል ብለዋል።
ምረቃችሁ የመጨረሻ ሳይሆን ህዝባችሁን ለማገልገል የምትነሱበት ምእራፍ ነው ያሉት ክቡር ፕሬዝዳንቱ፣ በሕግ የበላይነት የሚያምነውን እና ያስተማራችሁን ማህበረሰብ አርአያነት ባለው ሙያዊ ስነምግባር እንድታገለግሉ አደራ እላለሁ ብለዋል።
በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የተለያዩ መረሀግብሮች የተካሄዱ ሲሆን፣ በቆይታቸው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የቅድመ ስራ ሰልጣኞች እውቅና እና ሽልማት ተሰጧቸዋል።
1. 🔍 የምስክርነት ቃልን እና የሰነድ ማስረጃን ስለመመዘን
➡️ ሁሉንም ዓይነት ማስረጃ የመመርመር ግዴታ: ፍርድ ቤቶች ለክርክሩ ፍትሐዊነትና ትክክለኛ ውሳኔ መስጠት ተገቢ ነው ብለው ያመኑትን ማናቸውንም ዓይነት ማስረጃ አስቀርበው የመመርመር ግዴታ አለባቸው (ሰ/መ/ቁ. 207967)።
➡️ የማስረጃ ምዘና መርህን ስለመጣስ: ፍርድ ቤቶች የቀረቡላቸውን ማስረጃዎች በሙሉ (የሰው ምስክርም ሆነ የሰነድ) መርምረውና መዝነው ፍሬ ነገርን የማጣራት ኃላፊነት አለባቸው (ሰ/መ/ቁ. 208495)። በተለይም፣ የቀረበን የሰነድ ማስረጃ ከግምት ውስጥ ሳያስገቡ ወይም ሳይመረምሩ በሰው ምስክሮች ቃል ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚሰጥ ውሳኔ የማስረጃ ምዘና መርህን የሚጥስና መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ነው (ሰ/መ/ቁ. 208495)።
➡️ የጽሑፍ ውል ይዘት ቅድሚያ: በሕግ አግባብ የተከናወነ የጽሑፍ ውል ይዘት ሙሉ እምነት የሚጣልበት በቂ ማስረጃ ስለሆነ፣ ውሉን በምስክር ቃል ማስተባበል አይቻልም (ሰ/መ/ቁ. 235005)። በመሆኑም ፍርድ ቤት የጽሑፍ ውልን ሳይመዘን በሰው ምስክሮች ቃል ላይ ብቻ ተመርኩዞ መወሰን መሰረታዊ የማስረጃ ምዘና ስህተት ነው (ሰ/መ/ቁ. 235005)።
➡️ የተረጋገጠ ሰነድ አስገዳጅነት: በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ (DOAR) ስልጣን ባለው አካል የተረጋገጠ እና የተመዘገበ ሰነድ ሙሉ እምነት የሚጣልበት በቂ ማስረጃ ነው፤ ስለዚህ የውክልና ሰነድ በሰው ምስክር ሊስተባበል እንደማይችል መገንዘብ ይገባል (ሰ/መ/ቁ. 201608)።
➡️ የቀድሞ ውሳኔን እንደ ብቸኛ ማስረጃ መውሰድ: ቀደም ሲል በቀረበ ክስ ላይ የተሰጠ ውሳኔን እንደ ብቸኛ በቂ ማስረጃ በመቁጠር የሌላኛውን ወገን ማስረጃ ሳይመዝኑ ፍርድ መስጠት የማስረጃ ምዘና መርህን የሚጥስ መሰረታዊ የሙግት አመራር ስህተት ነው (ሰ/መ/ቁ. 206676)።
➡️ ማስረጃን አለመቀበልና ምክንያት: የፍርድ ቤት ውሳኔ በግራ ቀኙ ከቀረቡት ማስረጃዎች አጠቃላይ ይዘት ጋር በማገናዘብ መሆን ሲገባው፣ ፍርድ ቤቱ ለውሳኔ የሚያስፈልጉትን ማስረጃዎች ብቻ በመውሰድ ሌላውን ያልተቀበለበትን ምክንያት ሳይገልጽ ውሳኔ መስጠቱ የማስረጃ ምዘና መርህን ያልተከተለ ነው (ሰ/መ/ቁ. 207967)።
2. 🗣 የምስክር ቃል አሰማም እና የክርክር ሥርዓት (Procedural Requirements)
➡️ የአንዱን ወገን ምስክር ቃል ሳይሰሙ ማለፍ: አንድ የፍሬ ነገር ጭብጥ በሰው ምስክሮች እንዲጣራ ትዕዛዝ ከተሰጠ በኋላ፣ የአንድ ወገን ምስክሮች ሳይሰሙ ውሳኔ መስጠት የፍርድ አመራር ሥርዓት መርህን የሚጥስና መሰረታዊ የህግ ስህተት ነው (ሰ/መ/ቁ. 205709, 223270)።
➡️ በዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ላይ ያለመወሰን: በወንጀል ክስ፣ ወንጀሉ መፈጸሙን የማስረዳት ኃላፊነት የዐቃቤ ሕግ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግን ማስረጃ ሳይሰማ፣ በተከሳሽ በቀረበው ማስረጃ ላይ ብቻ ተመስርቶ ዐቃቤ ሕግ ክሱን አላስረዳም በሚል በነፃ መልቀቅ መሰረታዊ የክርክር አመራር መርህን የተከተለ አይደለም (ሰ/መ/ቁ. 235007)።
➡️ የተጨማሪ ማስረጃ አግባብነት: ፍርድ ቤት ለትክክለኛ ፍርድ አሰጣጥ ተጨማሪ ማስረጃ እንዲቀርብ ካዘዘ፣ በቀረበው ማስረጃ (ለምሳሌ የባለሙያ ማብራሪያ) ላይ የግራ ቀኙን አስተያየት በመቀበልና በመስማት ተገቢውን ውሳኔ መስጠት ይገባዋል፤ ሳይሰማ መወሰን የመሰማት መብትን ይጋፋል (ሰ/መ/ቁ. 206044)።
➡️ የክሱ ዝርዝር እና የመከላከል መብት: ወንጀሉ በበርካታ ግለሰቦች ሲፈጸም፣ የእያንዳንዱ ተከሳሽ ተሳትፎ (ሚና) በክሱ ላይ በግልጽ መገለጽ አለበት፤ ይህ ሳይገለጽ መቅረቱ ተከሳሾችን የመከላከል ሕገ መንግሥታዊ መብትን ያጣብባል (ሰ/መ/ቁ. 228597)።
➡️ የወንጀል ማስረጃ መስፈርት: በወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት ቁጥር 134(1) መሰረት፣ ተከሳሽ በሰጠው የእምነት ቃል ብቻ የጥፋተኝነት ውሳኔ ለመስጠት፣ ዝርዝር የተሰጠው ቃል ከተከሰሰበት ወንጀል ዝርዝር ጋር አንድ መሆን አለበት (ሰ/መ/ቁ. 209051)።
3. ✨ ልዩ የምስክርነት ሁኔታዎች
➡️ የሐሰተኛ የምስክርነት ቃል: በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 6 መሠረት፣ ቀደም ሲል የተሰጠው ፍርድ በሐሰተኛ የምስክርነት ቃል ላይ ተመስርቶ መሆኑ ከተረጋገጠ፣ ዳግም ዳኝነት (Re-examination) ሊጠየቅ ይችላል (ሰ/መ/ቁ. 206332)።
➡️ የሕፃናት ምስክርነት: ወንጀል የተፈጸመበት ቦታ ላይ የነበሩ ሕፃናት ምስክርነታቸውን ሲሰጡ፣ ፍርድ ቤቱ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያ ድጋፍ በማድረግና ለህፃናት ምቹ በሆነ የችሎት አኳኋን (Child Friendly Court) የምስክርነት ቃላቸውን መቀበል አለበት (ሰ/መ/ቁ. 238882)።
➡️ ያልተካደ የፍሬ ነገር ማረጋገጫ: ጋብቻ መኖሩ ካልተካደ ነገር ግን የተፈጸመበት ቀን ላይ ብቻ ክርክር ከተነሳ፣ ይህ የፍሬ ነገር ክርክር ሲሆን፣ በሕግ ተለይቶ የተቀመጠ የማስረጃ አይነት ስለሌለ በማንኛውም ማስረጃ ማረጋገጥ ይቻላል (ሰ/መ/ቁ. 229489)።
1. 🛡 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ እንደ መከላከያ ማስረጃ እንጂ እንደ ፍርድ ቤት ግዴታ ያለመወሰዱ
➡️ በአባትነት ማረጋገጫ ክስ ላይ ዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ አባትነትን ለማረጋገጥ የሚቀርብ የመከላከያ ማስረጃ እንጂ፣ ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ሊያዝ የሚገባው አይደለም። የአባትነት ክስ ሲቀርብ ተከሳሹ መጥሪያ ደርሶት ለመቀበል ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቶ የመከራከር መብቱን ራሱ የተወ ከሆነ፣ ቀርቦ የመከላከያ መብቱን ስላልተጠቀመ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ የመጠየቅ መብቱን ከክሱን ከመከላከል ጋር እንደተወ ይቆጠራል [ሰ/መ/ቁ 154767]። በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በሌለበት ውሳኔ መስጠቱ ስነ ስርዓታዊ አግባብን የጣሰ አይደለም [ሰ/መ/ቁ 154767]።
2. 📜 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ትዕዛዝ በሦስተኛ ወገን (ኑዛዜ ተጠቃሚ) ሲጠየቅ
❌ የቤተሰብ ሕግ የአባትነት መካድ ክስ ሊያቀርቡ የሚችሉ ወገኖችን ማንነት ይገድባል። የኑዛዜ ተጠቃሚ የሆነ ሦስተኛ ወገን፣ የመካድ ክስ ለማቅረብ ከተፈቀደላቸው ሰዎች ውስጥ የማይካተት በመሆኑ፣ እንዲሁም የመካድ ክስ ለማቅረብ የሚያስፈልገውን የፍርድ ቤት ፈቃድ አስቀድሞ ባለማግኘቱ፣ ያለምንም ሕጋዊ መሠረት የዘረመል (D.N.A) ምርመራ እንዲደረግ ማዘዙ ከመነሻው በሕጉ የተመለከተውን ሥርዓት ያልተከተለ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው [ሰ/መ/ቁ 152719]።
3. 🔨 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ትዕዛዝ ባለመፈጸሙ ምክንያት በፍሬ ነገር ላይ መወሰን
⏳ ለቀጠሮ ምክንያት የሆነው ጉዳይ (እንደ ዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ውጤት) ሳይፈጸም የቀረው ከተከራካሪ ወገኖች በአንዱ ጉድለት ከሆነ፣ ፍርድ ቤቱ የጉዳዩን መፈጸም ሳይጠብቅ የመሰለውን ውሳኔ ለመስጠት ይችላል [ሰ/መ/ቁ 152100]። በመሆኑም፣ ፍርድ ቤቱ ዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ፣ ትዕዛዙን አልፎ በሌሎች ማስረጃዎች (ለምሳሌ በሰው ምስክር ቃል) ላይ ተመስርቶ የሟች ልጅነትን ማጽናቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት አይደለም [ሰ/መ/ቁ 152100]።
4. ⚖️ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ እንደ ገዥ (Conclusive) ማስረጃ አለመቆጠሩ እና ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር መመዘን
🔬 የዘረመል (DNA) ምርመራ ውጤት ብቻውን ፍፁማዊ ገዥ (conclusive) ማስረጃ አይደለም ። አባትነትን የማረጋገጥ ዓላማ ሲኖር፣ የምርመራ ውጤቱ በሌሎች የማስረጃ ዓይነቶች (ለምሳሌ ልጁን እንደ አባት በመንከባከብ፣ የሰው ምስክር ቃል ወይም የልጅነት ሁኔታ) ሊረጋገጥ ከሚችለው ፍሬ ነገር ጋር ተመዝኖ መታየት አለበት ።
5. 👂 የሳይንሳዊ ማስረጃን የመስማት ግዴታ (ለማስተባበል)
🚨 ፍርድ ቤቶች በተከራካሪ ወገኖች የልጅነት ግምትን ለማስተባበል ሲባል የዘረመል ምርመራ እንዲደረግ የቀረበውን አቤቱታ በአግባቡ ማስተናገድ አለባቸው ።
🛑 አንድ ወገን የልጅነት ግምትን ለመቃወም የዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቆ እያለ ፣ የስር ፍርድ ቤት ጥያቄውን ሳይመረምር ወይም ውድቅ ያደረገበትን ምክንያት ሳይገልጽ ውሳኔ መስጠቱ ፣ እንዲሁም በሰው ምስክሮች ቃል ላይ ብቻ ተመርኩዞ አባትነትን ማረጋገጡ የሰበር ሰሚ ችሎት ገዥ ትርጉም የሚፃረር መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው ።
📝 በልደት ምስክር ወረቀት ወይም በልጅነት ሁኔታ (circumstantial evidence) የተረጋገጠ የሕግ ግምት በሳይንሳዊ ማስረጃዎች እንደ ዲ.ኤን.ኤ ምርመራ ሊስተባበል ይችላል ።
6. 💵 የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ወጪ እና የፍትሕ አሰጣጥ
💰 ምንም እንኳን ምርመራውን የጠየቀው ወገን ወጪ የመሸፈን ኃላፊነት ቢኖርበትም ፣ የገንዘብ አቅም አለመኖር ፍትሕን ሊያጓድል አይገባም። ፍርድ ቤቱ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ወጪው በማን ይሸፈን የሚለውን ከሕግ አኳያ አይቶ መወሰን ሲገባው፣ ይህን አለማድረጉ ስህተት ነው ።
7. ⭐️ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራ ጥራት እና ተጨማሪ የባለሙያ አስተያየት
⚰️ ከሟች አስክሬን የተወሰደ የዘረመል (DNA) ናሙና በብክለት ምክንያት አስተማማኝ ውጤት መስጠት ባልቻለበት ሁኔታ፣ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን የበለጠ ግልጽ ለማድረግ ተጨማሪ የልዩ አዋቂ ባለሙያ አስተያየት መስማቱ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 136ን የተከተለ በመሆኑ የሚነቀፍ አይደለም ።
8. 👰♀️ በጋብቻ ውስጥ ለተወለደ ልጅ የአባትነት ግምት እና የመካድ ክስ
💍 በጋብቻ ውስጥ የተወለደ ወይም የተጸነሰ ልጅ የአባትየው ነው ተብሎ በሕግ ይገመታል ። አባትነት በሕግ በተሰጠው ግምት መሠረት የተረጋገጠ እንደሆነ፣ አመልካች የምርመራውን ውጤት ከመጠየቅ በፊት በቤተሰብ ሕጉ በሚፈቅደው አግባብ የመካድ ክስ ማቅረብ ይኖርባታል ። በፍሬ ነገር ደረጃ በጋብቻ ውስጥ መወለድ መረጋገጡ፣ የዘረመል (DNA) ምርመራ ይደረግ የሚለውን ክርክር ተቀባይነት ያሳጣዋል ።
9. 🗑 በሌላ ማስረጃ አባትነት ሲረጋገጥ የዲ.ኤን.ኤ. ምርመራን ውድቅ ማድረግ
📄 በልደት ምስክር ወረቀት ወይም በቂ የሰነድና የሰው ማስረጃዎች በመመርመር እናትነት ወይም ልጅነት የተረጋገጠ እንደሆነ ፣ ፍርድ ቤቶች ተጨማሪ የዲ.ኤን.ኤ ምርመራ እንዲደረግ የቀረበው ክርክር ተቀባይነት የለውም በማለት ውድቅ ሊያደርጉ ይችላሉ ።
በዩናይትድ ስቴትስ ቨርጂኒያ ግዛት የሚገኙ ዳኞች በስድስት አመት ተማሪ በጥይት ለተመታችው የቀድሞ መምህር 10 ሚሊየን ዶላር እንዲሰጥ ወስናዋል። ዳኞች ሐሙስ እለት ከቀድሞው መምህር አቢ ዘወርነር ጋር በሲቪል ክስ የቀረበውን የይገባኛል ጥያቄ በመደገፍ የትምህርት ቤቱ የቀድሞ አስተዳዳሪ የስድስት አመት ህፃን በክፍሉ ውስጥ ሽጉጥ አለው የሚለውን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ችላ ብለዋል ሲል ይህንኑ ውሳኔ አሳልፈዋል።
የ28 ዓመቷ ዝወርነር በጃንዋሪ 2023 በጥይት የተመታችው አንደኛ ክፍል ውስጥ ባለው የንባብ ጠረጴዛ ላይ ተቀምጣ ሳለች ነበር። ለሁለት ሳምንታት የሚጠጋ ሆስፒታል ውስጥ ያሳለፈች ሲሆን ስድስት ቀዶ ህክምና አድርጋለች። ከጥቃቱ በኃላ አሁንም የግራ እጇን ሙሉ በሙሉ መጠቀም አልቻለችም። በስድስት ዓመት ህጻን የተተኮሰው ጥይት ለጥቂት መምህሯን ልቧን ከመምታት ስቷል።
ውሳኔው ከተገለጸ በኋላ ቨርጂኒያ ኒውፖርት እንደዘገበው የሪችክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ረዳት ርእሰ መምህር በሆነው በኤቦኒ ፓርከር ላይ 40 ሚሊዮን ዶላር ካሳ እንዲከፍል ተጠይቋል። ከመምህሯ ጠበቆች አንዱ ዳያን ቶስካኖ ብይኑ በት/ቤቱ ውስጥ የተከሰተው ነገር "ስህተት ነው ተብሎ ሊታለፍ የማይቻለው፣ደህንነት በትምህርት ቤት ውስጥ የመጀመሪያው ጉዳይ መሆን አለበት" የሚል መልእክት እንዳለው ተናግረዋል።
የተማሪው እናት በቸልተኝነት የጦር መሳሪያ አያያዝ ክስ የ4 ዓመት እስር ተፈርዶባታል። በልጁ ላይ ምንም አይነት ክስ አልቀረበም፤ የእናቱን ሽጉጥ ያገኘው በልብስ ማስቀመጫ መሳቢያ ላይ ሲሆን መሳሪያውን ከእናቱ ቦርሳ ውስጥ በማውጣት ወደ ትህምርት ቤት ይዞት ሄዷል።
📂 የጉዳይ ዝርዝሮች
* የሰበር መዝገብ ቁጥር፡ 41379
* 🗓️ የውሳኔ ቀን፡ ጥቅምት 05 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም.
* 👥 ተከራካሪ ወገኖች፡
* አመልካች፡ ወ/ሮ ተክአ ወ/ጊዮርጊስ
* ተጠሪ፡ አቶ ገብረእግዚአብሔር አማረ
💡 የሕግ ትርጉም (የህግ አተረጓጎም)
* 🗣️ የምስክር ማስረጃ በጠቅላላ ውሎች፡ በተወሠነ ጥሬ ገንዘብ የቡቲክ አልባሳትን እንዲገዛለት ለአንድ ሰው የራሱን ጥሬ ገንዘብ የሠጠ ሰው ገንዘቡ ካልተመለሰለት ወይም አልባሳቱ ካልተገዙለት ይህንን በሰው ምስክር ለማስረዳት በሕጉ ክልከላ ያልተደረገበት ስለመሆኑ ከፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2ዐዐ1 እስከ 2ዐ26 ድረስ ያሉት ድንጋጌዎች መንፈስ ያስገነዝባል።
* 💰 የገንዘብ ባለቤትነት ግምት፡ የንግድ ሕግ ቁጥር 743 በሐዋላ ወረቀት አውጪ ስላለበት ኃላፊነት የሚደነግግ እንጂ በሐዋላ የተላከ ገንዘብ ባለቤት ማን እንደሆነ የሚወስን አይደለም፡፡... በመሆኑም ጥሬ ገንዘብ በእጁ ያደረገ ሰው ባለቤት ሆኖ ይገመታል (ፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1193(1))።
* 🚫 የአደራ ውል እና የገንዘብ ማስረጃ፡ የአደራ ውል ማለት አንድን ዕቃ ተቀብሎ የመጠበቅ ግዴታ ነው (ፍ/ብ/ሕ/ቁ. 2779)፡፡ አንድ ሰው ለሌላ ሰው ገንዘብ የሰጠው ዕቃ ገዝቶ እንዲልክለት ከሆነ፣ ይህ ግንኙነት የአደራ ውል ትርጓሜን አያሟላም፡፡ ስለዚህ፣ ከብር 500 በላይ የሆነ የአደራ ውል በጽሑፍ መረጋገጥ አለበት (ፍ/ብ/ሕ/ቁ. 2782/1/) የሚለው ደንብ፣ ግንኙነቱ የአደራ ካልሆነ ተፈጻሚነት የለውም፡፡
🧐 የችሎቱ የውሳኔ ምክንያት
* (ብር 20,000.00): ተጠሪ ብር 20,000.00 በባንክ መቀበላቸውን አምነው፣ ገንዘቡ የተሰጣቸው ለአሜሪካ ጉዞ እንደሆነ ቢከራከሩም ይህንኑ አዎንታዊ መከራከሪያቸውን አላስረዱም፡፡ አመልካች ግን ገንዘቡን መላካቸውን በሐዋላ ወረቀት አረጋግጠዋል፡፡ በዚሁ መሠረት ገንዘቡን የተቀበለው ተጠሪ ባለቤት እንዳልሆነ የማስረዳት ሸክም ነበረበት (ፍ/ብ/ሕ/ቁ. 1193(1))።
* (ብር 10,000.00): አመልካች ገንዘቡን የሰጡት በአደራ እንዲቀመጥ ሳይሆን የቡቲክ አልባሳት ገዝተው እንዲልኩላቸው መሆኑን በሁለት ምስክሮች አስረድተዋል፡፡ የክልሉ ሰበር ችሎት ይህንን ግንኙነት እንደ አደራ ውል በመቁጠር ከብር 500 በላይ ስለሆነ በምስክር አይረጋገጥም ማለቱ የሕግ ስህተት ነው፡፡
* ማጠቃለያ፡ ግንኙነቱ በአደራ ውል ሥር የማይወድቅና በጠቅላላ የውል ድንጋጌዎች (ፍ/ብ/ሕ/ቁ. 2001-2026) የሚገዛ ሲሆን፣ በዚህ ክፍል ደግሞ በምስክር ማስረዳትን የሚከለክል ድንጋጌ የለም፡፡ አመልካች በምስክር ስላስረዱ ተጠሪ ገንዘቡን የመክፈል ኃላፊነት አለባቸው፡፡
⚖️ ውሳኔ
* ❌ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት በመዝገብ ቁጥር 25ዐ75 የሰጠው ውሳኔ ተሽሯል፡፡
* ✅ የክልሉ ማዕከላዊ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት (በመ/ቁ. 1ዐ314) እና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት (በመ/ቁ. 24ዐዐ9) የሰጡት ውሳኔ ፀንቷል፡፡
* 💸 ተጠሪ (አቶ ገብረእግዚአብሔር አማረ) ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ብር 30,000.00 (ሠላሳ ሺህ ብር) ክስ ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ከሚታሰብ ህጋዊ ወለድ ጋር ለአመልካች (ወ/ሮ ተክአ ወ/ጊዮርጊስ) እንዲከፍሉ ተወስኗል፡፡
* 📄 ተጠሪ ለዚህ ችሎት የክርክር ወጪና ኪሣራ ብር 1,500.00 (አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር) ለአመልካች እንዲከፍሉ ተወስኗል፡፡
⚡️ Launch your Telegram ads in minutes with access to verified channels, groups, mini apps, and bots.
Reach real, bot-free audiences — from crypto to lifestyle — with automated placements, live analytics, and measurable results.
How it works:
1️⃣ Sign up via this link: Telega.io
2️⃣ Add funds
3️⃣ Choose channels and add your ad post
➡️ We’ll take care of the rest
Stay ahead — 6 000+ channels to test, track, and scale!
⚡️ Launch your Telegram ads in minutes with access to verified channels, groups, mini apps, and bots.
Reach real, bot-free audiences — from crypto to lifestyle — with automated placements, live analytics, and measurable results.
How it works:
1️⃣ Sign up via this link: Telega.io
2️⃣ Add funds
3️⃣ Choose channels and add your ad post
➡️ We’ll take care of the rest
Stay ahead — 6 000+ channels to test, track, and scale!
⚡️ Launch your Telegram ads in minutes with access to verified channels, groups, mini apps, and bots.
Reach real, bot-free audiences — from crypto to lifestyle — with automated placements, live analytics, and measurable results.
How it works:
1️⃣ Sign up via this link: Telega.io
2️⃣ Add funds
3️⃣ Choose channels and add your ad post
➡️ We’ll take care of the rest
Stay ahead — 6 000+ channels to test, track, and scale!
*
❖#በመርህ_ደረጃ_ወንጀል የመንግስትን እና የህዝብን ጥቅም የሚጎዳ ተግባር ተደርጎ የሚቆጠር በመሆኑ ክስ የሚመሰረተው በመንግስት ዐቃቤ ህግ ነው። ሆኖም አንዳንድ የወንጀል አይነቶች በግል ተበዳይ እና በከሳሽ መካከል በሚደረግ እርቅ እንዲያልቁ ሕጉ ይፈቅዳል። በእርቅ ማለቁ ለሁለቱም ወገኖች ጊዜን፣ ወጪንና ጉልበትን ከመቆጠብ ባሻገር በህብረተሰቡ ውስጥ ሰላማዊ የሆነ ማህበራዊ መስተጋብር ትስስርን ያጎለብታል ።
❖#በወንጀል_ጉዳዮች_ላይ_እርቅ_የሚፈቀደው በአንጻራዊነት ክብደታቸው ዝቅተኛ በሆኑ እና በግለሰቦች መካከል በሚፈጠሩ ጉዳዮች ላይ ነው። እነዚህ ወንጀሎች በመንግስት ወይም በህዝብ ላይ ከባድ ጉዳት የማያስከትሉ በመሆኑ ጉዳዩ በግል ስምምነት እንዲያልቅ ይፈቀዳል።
❖#የግል_አቤቱታን_መሰረት_ሲያደርግ: አንዳንድ የወንጀል አይነቶች የሚመሰረቱት በተበዳዩ አካል የግል አቤቱታ ላይ ብቻ ነው። አቤቱታው ከተነሳ በኋላም ቢሆን ተበዳዩ እርቅ ለማድረግ ፈቃደኛ ከሆነ ክሱ ሊቋረጥ ይችላል።
@በእርቅ ማለቅ የሚችሉበት የወንጀል አይነቶች የሚከተሉት ናቸው ።እነሱም
1. የእጅ እልፊት (አንቀጽ-560(1) ፣
2. የዛቻ ወንጀል (አንቀጽ-580) ፣
3. ታስቦ የሚፈጸም ቀላል የአካል ጉዳት (አንቀጽ 556(1)፣
4. በቸልተኝነት የሚፈጸም ቀላል የአካል ጉዳት (አንቀጽ-559(3))፣
5. አመንዝራነት (አንቀጽ-652) ፣
6. ስድብና እና ማዋረድ (አንቀጽ-615) ፣
7. የስም ማጥፋት ወንጀል (አንቀጽ-618) ፣
8. በቤተዘመድ ንብረት ላይ የተፈጸመ ንብረት ነክ ወንጀል (አንቀጽ-664)
9. ጋብቻን በተንኮል ወይም በማታለል መፈፀም(አንቀጽ-646)፣
10. ቀለብ የመስጠት ግዴታን ያለመወጣት(አንቀጽ-558)፣
11. በሌላ ሰው ሀብት ያለአግባብ መጠቀም(አንቀጽ-678)፣
12. አግኝቶ መደበቅ(አንቀጽ-679)፣
13. በሰው ንብረት ላይ ሁከት ማድረግ(አንቀጽ-686)፣
14. በሌላ ሰው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ
(አንቀጽ-689)…ወዘተ ናቸው ።
በወንጀል ጉዳዮች ላይ እርቅ የሚፈፀምበት ሂደት#በጠቅላይ_ዐቃቤ_ህግ_መመሪያ_ቁጥር 22/2010 ጉዳዩ እንዴትእንደሚመራ፣ ተበዳዩ ምን መብቶች እንዳሉት እና እርቅ ሲደረግ ምን አይነት ጥንቃቄዎች መወሰድ እንዳለባት በዝርዝር ተቀምጧል::
Source :Tesgaye Demeke.Lawyer
ይሄን የምታነበው 🫵🫵🫵
https://www.youtube.com/@legaledetailscenter
ቤተሰብ መልካምነት ለራስ ነው!!
200 ሰዎች እስኪ አሁን ሰብስክራይብ አድርጉልኝ።ለ እኔ የእናንተ እርዳታ ትልቅ ነገር ነው
እኔ በ መድኃኒአለም ፣በ ድንግል ማርያም ክርስቲያኖች ፡ሙስሊሞች በአላህ ስም አልላችሁም
ፈቃደኛ ከሆናችሁ አግዙኝ
👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@legaledetailscenter
https://www.youtube.com/@legaledetailscenter
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «©Legal details center© :የህግ ማብራሪያ ማዕከል©» is a Telegram channel in the category «Образование», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 5.6K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 17.4, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.92 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий