
Channel statistics
Full statisticschevron_right.......... መሳሪያ የያዘ ሰው ተመለከትኩ ። ደንግጬ ወዲያው ለበላይ ነገርኩት ።
ብርግግ ነው ያለው ከኔ በላይ ደንግጧል ይባስ ብሎ ደግሞ አሜኑን አቅፎት መፍትሄ እንደመፈለግ እዛው አስቀመጠውና መርበትበት ጀመረ ።
ከዛ በድጋሜ ያ ሰውዬ ወደኛ ሲመጣ ተመለከትኩት ።
ያው ያው ብዬ ጮኩኝ ወዳየውበት አቅጣጫ እጄን እየጠቆምኩኝ ።
በላይም በድንጋጤ ዞረና ሰውዬውን ሲያየው በአንዴ ተረጋጋ ።
ምክንያቱ ደግሞ አባይ እንደጠብቀን የላከው ሰው ስለነበረ ነው ።!!!!
ፈጣሪ ይመስገን ያንን ጫካ በሰላም አቋረጥን ። መኪና መጠበቂያ ጋር ቆመን ከረጅም ሰአት ቡሀላ አንድ መኪና መጣልን ። ከዛም ሰፈሩን ለቀን ሄድን .......
ከተማ ስንድረስ ምን እንደሚጠብቀን....የት እንደምንሆን ....ምን እንደምንበላ...አንድም የማቀው ነገር አልነበረም !!!!
ብቻ ተከትላው ትሂድ ..... ተብዬ እንደተሸኘውት በላይን እየተከተልኩ ነበር ።
ከረጅምምም ጉዞ ቡሀላም በስተመጨረሻ ከተማ ገባን ።
እውነት ለመናገር ከሆነ አዲስ አበባ ስንመጣ የተሰማኝ ደስታ በጣም ልዩ ነው !!!.አየሩ ራሱ እጅግ የሚስብ ነው !!!!...... ነገር ግን አዲስ አበባ ስመጣ የበፊቱ ህይወቴ ትዝ ይለኛል አባቴ እናቴ የእንጀራ አባቴ የመድፈር ሙከራ ታናሽ እህቴ ያለችበት ሁኔታ ብቻ ሁሉም ነገር ትዝ አለኝና ቆሜ ከልቤ አለቀስኩ ።
ደግነቱ በላይ ግድም የለውም የሚያባብለኝ የለምና ራሴን በእራሴ አፅናንቼ ዝም አልኩኝ !!!!!🤐🤐🤐🤐
ከዛም እሱን እየተከተልኩ ወደ አንድ ቤት ሄድን ስንደርስ የገባንበት ጊቢ ትልቅ ነው ብዙ ሰዎች አሉ ።
የጊቢው ገፅታና ለኛ የተከራየው ቤት ግን በጭራሽ አይገናኝም ነበር ።
ውስጥ ለውስጥ ይዞኝ ተጓዘ ። በዛ ላይ መክሊቴን በጀርባዬ አዝዬ አሜኑን በፊት ለፊት አቅፌ ነው የመጣውት እና ደክሞኝ ነበር ።
በሩን ከፍቶት ወደ ውስጥ ስንገባ ከዛኛው ቤት የባሰ ነው ። በጣም ጠባብ እና በቅጡ እንኳ ቀለም የሌለው ወደ አንድ በኩል ያጋደለ ቤት ውስጥ ነው ይዞኝ የሄደው ። ???? እኔኮ ያሰብኩት ከተማ ይዞኝ ሲመጣ የተሻለ ነገር እንዳለ ነበር 😥😥
ቦታውን ቀድሞ የሚያውቀው ይመስላል ። ተመልሶ ወቶ ዳቦና ሙዝ ገዝቶ መጣ ።
እሷን ቀምሰን አደርን ።
በቀጣዩ ቀን ከቤት እንዳልወጣ ነግሮኝ ከቤት ወጣ ።
ከዛም አመሻሽ ላይ አንዳንድ ነገር ገዝቶ መጣ ከሰል ማያያዣ ምናምን ። እኔ ግን ከዛ ይልቅ ስጠብቅና ስፈልግ የነበረው የሚበላ ነገር ነው !!!!
በባዶ ሆዴ ሁለት ልጅ በግራና በቀኝ ሳጠባ ነው የዋልኩት ።
ምግብ ከማጣቴ ብዛት ወተትም በስርአት አይወርድልኝም ነበር ።
የሚያሳዝነው ግን ስቅቅ ብዬ ምግብ ምን ገዛህ ስለው ወደገዛት አንድ አሮጌ ድስትና ወደ ከሰል ማንደጃው እየጠቆመ
" መስሪያው ተገዛልሽ እኮ ሰርተሽ ብያ ...!!???🤔🤔 " ነበር ያለኝ !!!!
ምኑን ልስራው አልኩት በተከፋ ድምፅ በዛን ሰአት ደግነቱ አሜኑ ተኝቶ ነበር መክሊቴም ቀስ ብላ ተኛችልኝ ።
ረሀብን በእንቅልፍ ብቻ አይደል መሸወድ የሚቻለው እኔም እራሴንና ሆዴን ለመሸወድ ብዬ ልጆቼን አቅፌ ክፉ ሳልናገር የተነጠፈችው ኬሻ ላይ ለጥ አልኩኝ !!!!።
እሱ በርግጠኝነት የሆነ ነገር በልቶ ነው የመጣው እንጂ እኔን ሊበላኝ ነበር የሚደርሰው!!!!!
ቀኑን ሙሉ በሩን እንኳን አልከፈትኩም ሌሎች ተከራዮች ስላሉ ከማንም ጋር መነካካት አልፈለኩኝም ነበረ ።
እና ቁጭ ብሎ መዋል ደግሞ ረሀብን ከሚያመጡና ከሚያባብሱ ነገሮች አንዱ ነው !!
ቤት ውስጥ ልስራ ልንቀሳቀስ እንዳልል ባዶውን የተቀመጠ ቤት ምን ላደርገው ነው ???
ማለቴ ቢያንስ የሆነ ነገር ቢኖር ወይ ሳጣጥብ ወይ ሳስተካክል እውል ነበር ።
ብቻ ግን ከልጆቼ ቀጥሎ ረሀቤን ታቅፌ ተኝቼ ነገሮችን ማሰብ ጀመርኩኝ ።
ትዝ ይለኛል ህፃን እያለሁ አስታውሳለሁ አባቴ ረሀብን በጣም ይጠላውና ይፈራውም ጭምር ነበረ !!!
ተሳስቼ ራበኝ ካልኩ ከእናቴ ጋ በጣም ነበር የሚጣሉት እና አሁን ላይ አባቴ ቢኖርና ቢያየኝ በርግጠኝነት ያዝን ነበር ።
ለነገሩ እሱ ቢኖርማ እንዲ አልሆንም ነበር .......!!!!!!
ብቻ ግን አይምሮዬን በብዙ ሀሳቦች ወጥሬ እንደምንም እንቅልፍ ወሰደኝ ።
ለሊት ላይ እንዳይቀሰቅሰኝ ፈርቼ ነበር ፈጣሪ ይመስገን አልነቃሁም !!
ጠዋት ላይ ስነቃ ሳይ በሩ ክፍት ነበር ። በጣም ደንግጬ አይኔን ሳማትር በላይ ቤት አልነበረም ።
ቶሎ ብዬ በሩን ዘግቼ ወደ ልጆቼ ስመለስ የልጅነት ልጄ የመጀመሪያዬ አሜኑ ምን እንደነካብኝም ሳላቀው እንዳጣውት ተሰማኝ ።
ቀና አድርጌ ሳየው ከአይኑ ደም እየፈሰሰ ነበር ደም ስላችሂ በጣም ቀይ የሚያስፈራ ወፍራም ደም ............?????😭😭😭😥😥😥😥
✍✍✍✍fidel.......
https://t.me/fidel_z28
በእንድ ወቅት አንድ ገበሬ አህያው ጉድጎድ ውስጥ ትገባበታለች፡፡ ጉድጓዱ ሩቅ ከመሆኑ
የተነሳ አህያዋ በራሷ ለመውጣት በእጅጉ ተቸገረች፡፡ በጣምም መጮህ ጀመረች፡፡
ባለቤቱም አህያዋን ለማውጣት ብርቱ ሙከራ ቢያደርግም ሊሳካለተ አልቻለም፡፡ አህያዋም
ብዙ ያገለገለችና ያረጀች ስለሆነች እንዲሁም ሌሎች እንስሳትም ወደ ጉድጓዱ
እንዳይገብበት በማሰብ ጉድጓዱ ውስጥ ሊቀብራት ወሰነ፡፡
ጎረቤቶቹንም አስተባብሮ ጉድጓዱን በአፈር መሙላት ጀመረ፡፡ አህያዋ ይህን ስትመለከት
እየቀበራት መሆኑነ ተረዳችና በሰቀቀን አለቀሰች፡፡ይሁን እንጂ አህያዋ አፈር ሲደፋባት አንድ
ነገር ታደርግ ጀመር፡፡ አፈሩ በተደፋባት ቁጥር አፈሩን እያራገፈች ከአፈሩ ውስጥ ብቅ ትል
ጀመር፡፡በተደጋጋሚ ከሚደፋባት አፈር ላይ መቆምም ትጀምራለች፡፡በሂደት ውስጥ በአፈሩ
ላይ በቆመች ቁጥር ከነበረችበት ጉድጓድ ከፍ እያለች ከፍ እያለች በመጨረሻም ጉድጓዱ
ውስጥ ሙሉ ለሙሉ መውጣት ቻለች፡፡በሚገርም ሁኔታ አህያዋን ሊቀብሯት ሞከሩት ሰዎች
በአህያዋ አወጣጥ በእጅጉ ተደነቁ፡፡
︵ በህይወታችን ውስጥ ያለው አማራጭ ወደ ላይ መውጣት አልያም ደግሞ ወደታች ወርዶ
ከጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ተቀብሮ መቅረት ብቻ ነው!
ምርጫው የኛ ነው🫡🫡🫡🫡
............. የሚያስፈራ ደም ከአይኑ መፍሰስ ጀመረ ።
የኔ ትንሽ ልጅ በሰአቱ ምን እንደተሰማው አላውቅም !!!!
" እማ አይኔን አመመኝ " እያለ በነዛ ትንንሽ እጆቹ አይኑን ለማሸት ሲሞክሮ ፊቱን ደም በደም አደረገው !!
እንደዛ ሆኖ ሳየው በጣም ነው የደነገጥኩት እጄ እና እግሬ ተሳስረው ለትንሽ ደቂቃ በዝምታ የተቀመጥኩኝም ይመስለኛል !!!
ብዙም ሳልቆይ ግን ከኔ ሌላ ማንምእንደሌለው ስላወኩኝ ቶሎ ተነስቼ እኔም ታጥቤ ፊቱን ለማጠብ ሞከርኩኝ ።
ከዛ ከነበርንበት ሀገር ስመጣ ያረሳሁት ዋነኛ ነገር የአማኑኤል ፀበል መያዝን ስለነበር የክርስትና ደጁ ትማረው ቅዱስ አማኑኤል አድንልኝ እያልኩ በሀይላንዱ ክዳን አይኑ ላይ አፈሰስኩለት ።
ክብር ለፈጣሪ ይሁን ወዲያው ደሙ አቆመ ።
ከዛ ግን ለረጅም ደቂቃዎች አሜን አይኑን አልገለጠም ነበር ።
የበለጠ እየጨነቀኝ ሲመጣ በእጄ ይዤ ልገልጥለት ስሞክርም በሀይል ይገፋኛል ማለቴ ብቻ አላውቅም በጣም የሚያስደነግጥ ስሜት ውስጥ ገባሁ !!!!............
" እማ ጧዬ እማ " አለኝ እየተኮላተፈዐበዛ ጣፋጭ አፉ ።
በባዶ ሆዴ ስለነበርኩኝ ወተት አይወጣልኝም ብዬ ተነስቼ ብዙ ውሀ ጠጣሁ ።
ከዛም ቶሎ ወደልጄ ተመልሼ እየጨመኩኝ ለማጥባት ሞከርኩኝ ።
በዛ ሰአት አሜን ከእንቅልፏ እንዳትነሳ ከልቤ ስፀልይ ነበር !!!!!
ምክንያቱም ርቧት እንደምትነሳ ስለማውቅ ነበር !!!!.......
አሜኑ ብዙም ሳይቆይ በዛው አሸለበው ።
ተመስገን ነው ያልኩት ከዛ እሱን አስተኛሁና ። ተነስቼ ፀለይኩለት ። አይምሮዬ ብዙ ነገሮችን እያሰበ ነበር ግን አያድርግብኝ እያልኩ ራሴን አረጋጋሁ ።
ከዛም ተነስቼ አባይነህ አንድ ላይ የቋጠራቸውን ነገሮች ሁሉንም ፈታታዋቸው ።
ከዛን ስመለከት ብዙ ነገሮች አድርጎልን ነበረ ።
ትላንት ሙሉ ቀኑን አለማስተዋሌ በጣም አናደደኝ !!!!
ምክንያቱም በጣም ርቦኝ ነበር!!!!!!!!!
" ያለፈው አይቆጭክ የወደፊቱ አያምልጥህ " ነውና ነገሩ ........
ላማረርኩበት ይቅር በለኝ ብዬ እንኳን አገኘው ብዬ ተመስገን አልኩ !!🙏🙏
ከዛም በር ላይ ወጣ ብዬ የወዳደቁ እንጨቶችን ለቅሜ ተመልሼ ገባሁና አያይዤ የተላከልኝን ቀይ ሽንብራ ቆላሁኝ ከዛም የጤፍ ዱቄቱን አቦካሁትና ቆንጆ ቂጣ ጋግሬ ውሀዬን አቅርቤ ለመብላት ስሞክር አንድ ጉርሻ እንኳን አልዋጥ አለኝ !!!!
ከዛም መፍትሄ ብዬ ያሰብኩት አሜንን መቀስቀስ ነበር ።
ከዛም አማትቤ አይኑን ለማየት እየፈራሁ በቀስታ ቀሰቀስኩት ...።
ፈጣሪ ይክበር ይመስገን ልጄ አይኑን ገለጦ አየኝ !!!!!!🙏🙏🙏
ነገር ግን ከዚ በፊት እንደነበረው ትልልቅና የሚያሳሱ አይኖች አልነበረም የተመለከትኩት ።
በአንድ ጊዜ አይኑ ሙጭ ሙጭ ብሏል ??!!!!
በጣም ትንሽ ሆኖ ነበር ???
ወዲያው ግን አይኔ ላይ ውልብ ያለው ልክ ከነ አባይ ቤት ስንወጣ እናቱ መክሊትን ትታ አሜንዬን ያየችበት አይንና አስተያየት ነበረ!!!!
በጣም ተናደድኩ !!!!
ሙሉ ቀኑን ስለሷ ሳስብና ስብከነከን ዋልኩኝ ።
ከልጄ ጋ ሲሆን ተበላልኝና ለሱም እያጎረስኩ ቂጣችንን በልተን መክሊቴ ስትነሳ ጡት አጠባዋትና ተመልሰው ተኙልኝ ።
እኔ ሙሉ ቀኑን ስብከነከን ነበር !!. አንዴ በላይ መቶ ነግሬው እያልኩ ነው የዋልኩት !!
ለነገሩ እሱ ምን ጥቅም አለውና ነው ????
ሁሌም እኔን በችግር ጊዜ ጥሎ መሄድ ነው እሱ የሚያቀው ።
ዛሬም ረሀብ ሊገለኝ ሲደርስ ጥሎኝ ወቶ ቤቱ ጭልምምም እስከሚል ድረስ አመሸ ።
ከስንት ጥበቃ ቡሀላ በመከራ መጣ ።
ልክ ሲገባ ግን በሌለን ብር እና መተዳደሪያ ጠጥቶ ነው የመጣው !!!?????
ምን አይነት ነገር እንደሆነ አላውቅም !!!!
ከሱ ጋ ለመጨቃጨቅ አቅም ስላልነበረኝ
ተመልሼ ከልጄ አጠገብ ጋደም ልል ስል በዛ በለሊት ጊቢ ውስጥ ጩኸቱን አቀለጡት ????
" ሌባ ሁላ ኑ ውጡ " የሚል ድምፅም አለ ........?????
✍✍fidel.....
ይህንን ጥያቄ ያለማቋረጥ ራስህን ጠይቅና ገዢ መመሪያ ተብሎ ከሚጠራው ከዚያ ክፍል ጋር እንዴት እንደምትዛመድ በማየት ራስህን በሚገባ መርምር፡፡ አሁን ያለችኝ ነፍስ የማነች? የልጅ፣ የወጣት … የአምባገነን፣ የቤት እንስሳ ወይስ የዱር እንስሳ?”
#ማርከስ_አውሬሊየስ
የተሰጠኸው ለምንድነው? ለምን ምክንያት፣ ለምን ተልዕኮ፣ ለምን አላማ ነው? እና በጣም አስፈላጊው ደግሞ፣ የምትሰራው ? የሚለው ነው፡፡
በየቀኑ የምትከውናቸው ክንዋኔዎች በምን መንገድ እሴቶችህን ያንጸባርቋቸዋል? ዋጋ ከምትሰጠው የሆነ ነገር ጋር ወጥነት ባለው መንገድ ነው ወይስ ከራስህ አላማ ውጪ ለሆነ ለየትኛውም ነገር ታወላውላለህ?
እነዚህን ጥያቄዎች ስትመረምር፣ በመልሶቹ ምቾት ላይሰማህ ይችል ይሆናል፡፡ ጥሩ ነው፡፡ ያ ማለት ባህሪይህን ለማረም፣ ማለትም ማርከስ ከጠቀሳቸው አራዊት ፍጥረታት የተሻልክ ለመሆን የመጀመሪያውን እርምጃ ወስደሃል ማለት ነው፡፡ በተጨማሪም ግዴታህ በሕይወትህ እንድትሰራው የጠራህን ነገር ለማግኘት ተቃርበሃል ማለት ነው፡፡
አንድ ጊዜ ጥሪህን ካገኘኸው፣ ለመፈጸም በትንሹ እየተጠጋህ ነው።
.......... የሚል ድምፅ ሰማሁ ። በጣም ደንግጬ ቀና ስል አጉል እንደ ወንድ ሲያደርገው በሞቅታ ስሜት ሆኖ በሩን በርግዶ ወጣ ።
ይባስ የሚያስደነግጠው ግን ልክ በላይ ሲወጣ እኔም ከዃላ ብቅ ብዬ ሳይ ሴትዮዋ
" ይኸው እነዚ ናቸው ድምፃቸውን አጥፍተው የሰረቁኝ ለዛውም ከውጪ ነው ያስመጣሁላት ሌባ ከቸገራችሁ አጠይቁም" አለች 😥
በጣም ነበር የከፋኝ !!!!!
አንዳንድ ጊዜ ድምፃችንን አጥፍተን የራሳችንን ህይወት መኖር ስንጀምር ሁሉም የሆነ ሴራ እያሴርን ወይም ለሆነ ጥፋት እየተዘጋጀን ይመስላቸዋል !!!!
እንደውም በጣም የምትገርመኝ አንድ አባባል አለች
"" ደሀ ስትሆን ሰላምታህ እንደ ልመና ይታያቸዋል " !!!!!!
የምትል ቆንጆ ንግግር አለች ። 100 በ 100 እውነት ነው ብዬ አስባለሁ ።
የዛኔም እነሱም እንደ እኛ ተከራይ ቢሆኑም ዝቅ እና ወጣ ያለች የወደቀች ቤት ውስጥ ስላለን እና ቃል አውጥተንም ስለማናቅ መፀዳጃ ቤት ለመግባት ካላሰብኩ በቀር ከቤትም ስለማልወጣ አዲስ ሰለሆንኩ ብቻ ሌባ ናት ብላ እጇን ቀሰረችብኝ ????
ከዛ ቀስ በቀስ የጊቢው ሰው ወጣ ።
ከዛም አከራዮቹም ወጡና " ምንድነው ምንድነው ?" አለ አባትየው ግርማ ሞገስ ባለው ድምፅ ።
ሴትዮዋ ቅልብልብ ብላ
" አዲስ የመጡት ተከራዮች ሌባ ናቸው አንድም ቀን እቃ ጠፍቶና ተሰርቆ የማያቀውን በገቡ በሶስተኛ ቀን የልጄን ወድ ጃኬት ሰረቁኝ " አለች አፏን ሞልታ ።
አከራዩ በቀስታ ወደኛ ዞሩ ።
" በላይ ማለት አንተ ነህ ?" አለ አተኩሮ እየተመለከተ
" አዎ " አለ በላይ ።
የፈራ ይመስላል ሁኔታው !!! ኮራ ኮፍጠን ያለ ወንድ ከውንድሙ ጀምሮ ይፈራል !!??
ጣልቃ መግባት እንዳለብኝ ስለተሰማኝም
ይቅርታ ጋሼ እኛ ምንም ነገር አልሰማንም አላየንም ጭምር ። አልኩኝ ኮስተር ብዬ
" አንቺ እህቱ ነሽ ?" አለ መለስ አድርጎ ።
ለነገሩ ላየ ለተመለከተ ወንድምና እህት እንደምንመስል እርግጠኛ ነኝ ።
ታናሽ እህቱ ነው የምመስለው !!!
በዛን ሰአት እዛ ሁላ ሰው ፊት ሚስቱ ነኝ ለማለት አንደበቴ አልፈቅድ አለኝ !!!!!
እኔ በዝምታ ስዋጥ ግን በላይ ቀደም ብሎ
" የሁለት ልጆቼ እናት ናት ባለቤቴ ናት " አለ ።
የዛኔ አንገቴን ድፍት አረኩ ። ምክንያቱም በጨለማ ብርሀን ሳያቸው ገና የልጆቼ እናት ሲል አፋቸውን እያጣመሙ ነበር !!!
የአንድ ሁለት ሳምንት የቡና መጣጫ ርዕስ እንደሆንኩ ስለማውቅ ነበር የምር የከፋኝ !!!
ሰውዬውም የደነገጠ ፊት እያሳየኝ
" የምር ነው ?" አለ ።
አዎ ባለቤቴ ነው አልኩኝ ነገሩን ለማሳጠር እየተናነቀኝ .....
አከራዩና የአከራዩ ባለቤት ወደኔ ሲመጡ እንደሁሌው በላይ ጥሎኝ ወደ ቤት ገባ ።
እኔም እን ከዚ ቀደሙ ራሴን በርታ አድርጌ ለብቻዬ ቆምኩኝ ።
" እሺ ማነው ስምሽ " አለኝ
" ለአለም " አልኩኝ ኮራ ብዬ ።
ምክንያቱም ኩሩ አባቴ ያወጣልኝ ስም ነው ።
ሲመስለኝ ለአለም ያለኝ አለምን የሚያስደንቅ ታሪክ እንደሚኖረኝ ታውቆት ነው መሠል 🙌🥹
" ደስ የሚል ስም ነው !!
እሺ መሠረት የምትለው የምሯን ነው ማለቴ በስተትም ቢሆን አስገብተሻል ከሆነ ......" ብሎ ረጅም ንግግር እንዳለ እያሳበቀ በአጭሩ ቋጨው ።
በፍፁም አላደረኩም እኔ የአባቴ ልጅ ነኝ ሲቀጥል የሞገሴ ልጅ ነኝ ።
በስርአት ተገድቤ ነው ያደኩት ግማሽ እድሜዬንም ቢሆን ......
ብዬ እኔም ያልተቋጨ ንግግሬን ገደብኩት
የሚገርም ሰው ነው !!!! ወዲያው ወደተሰበሰቡት ሰዎች ዞሮ
" በቃ አልወሰደችም አልረኩም አለች አይደል " አላት ።
ስላመነኝ በጣም ደስ ብሎኝ ነበር በጣም !!!!!
ሴትዮዋ ግን አንባረቀች
" እንዴ ግርምሽ እኔ ለምይ ብዬ እዋሻለሁ እሷ እንደወሰደችው እርግጠኛ ነኝ ።
ዛሬ የመጣችን ሴት ከኔ አስበልጠህ ልታምን ነው ???......
✍✍✍fidel....
........ ከኔ አስበልጠህ ልታምን ነው ብላ ጮኸች ።
" ውሸት የሚናገር ፊት የላትም ንግግሯም እውነት ይመስላል ለምን ብዬ አላምናትም ?" አላት ።
በጣም የተረጋጋ ሰው ነው !!!! እሷ ደግሞ በተቃራኒ
" እኔ በአይኔ አይቻታለሁ እንደውም ሙሉ ቀኑን ስትወጣ ስትገባ ነበረ ። አጮልቃ ስታየንም አይቻታለሁ ።
እኔ የዋህ ሆኜ በመልካምነት ዝም አልኳት የገጠር ልጅ እንዲ አያደርግም ብዬ ነበር ዝም ብላትእኔ ሱቅ ስወጣ ጠብቃ ወሰደችው " አለች ።
በፈጣሪ ስም በዚልክ መዋሸትና ማስመሰል አልጠበኩኝም
ነበረ ። በስነ ስርአት ልክ እንደ እውነት አድርጋ ነው ያወራችሁ ።
እኔን ሁላ ልታሣምነኝ ነበር ማለት ይቻላል !!
ወዲያው ግን ብዙም ሳይቆይ ከትልቁ ቤት አንዲት ቀይ ቀጭን ልጅ በእጇ የሆነ ጃኬት አንጠልጥላ ወጣች ።
እዛ ለተሰበሰበው ሰው አንዳች ትኩረት አልሰጠችም ።
ማስቲካዋን እያላመጠች በአንድ እጇ ደግሞ ስልኳን ይዛ ወታ የተዘረጋው ገመድ ላይ ልብሱን ወርወር አድርጋ ስትመለስ
" የልጄ ልብስ " ብላ ጮከች ሴትዮዋ ።
" ጠፋ ብለሽ ያቀድሽው ልብስ ይሄ ነው " አላት አከራዩ አሁንም በእርጋታ ሆኖ ።
" አዎ የልጄ ውዱ ልብስ ነው " ብላ ከተሰቀለበት አወረደችው ።
በነገሮች የተሸማቀቀች ትመስላለች ።
ግን በጣም ደረቅ ከመሆኗ የተነሳ ይቅርታ ብሎ ከመግባት ይልቅ እዛ ግትር አለች ።
እሱም በእርጋታ ሆኖ
" ሄልዱ ይሄ ልብስ አንቺ ጋር ምን ያደርጋል ልጄ ?"አላት
" እኔንጃ አባቢ ከልብሴ ጋር ተቀላቅሎ ገብቶ ነበር የኔ ስላልሆነ መልሼ አወጣውት " አለች ትንሽ በቀበጠ ንግግር ነገሩን ቀለል አድርጋ ........
ለእሷ እኔ አፈርኩ !!! እሷ ግን አሁንም ድርቅ እንዳለች ቆማለች ????🤔🤔
ነበረ ። በስነ ስርአት ልክ እንደ እውነት አድርጋ ነው ያወራችሁ ።
እኔን ሁላ ልታሣምነኝ ነበር ማለት ይቻላል !!
ወዲያው ግን ብዙም ሳይቆይ ከትልቁ ቤት አንዲት ቀይ ቀጭን ልጅ በእጇ የሆነ ጃኬት አንጠልጥላ ወጣች ።
እዛ ለተሰበሰበው ሰው አንዳች ትኩረት አልሰጠችም ።
ማስቲካዋን እያላመጠች በአንድ እጇ ደግሞ ስልኳን ይዛ ወታ የተዘረጋው ገመድ ላይ ልብሱን ወርወር አድርጋ ስትመለስ
" የልጄ ልብስ " ብላ ጮከች ሴትዮዋ ።
" ጠፋ ብለሽ ያቀድሽው ልብስ ይሄ ነው " አላት አከራዩ አሁንም በእርጋታ ሆኖ ።
" አዎ የልጄ ውዱ ልብስ ነው " ብላ ከተሰቀለበት አወረደችው ።
በነገሮች የተሸማቀቀች ትመስላለች ።
ግን በጣም ደረቅ ከመሆኗ የተነሳ ይቅርታ ብሎ ከመግባት ይልቅ እዛ ግትር አለች ።
እሱም በእርጋታ ሆኖ
" ሄልዱ ይሄ ልብስ አንቺ ጋር ምን ያደርጋል ልጄ ?"አላት
" እኔንጃ አባቢ ከልብሴ ጋር ተቀላቅሎ ገብቶ ነበር የኔ ስላልሆነ መልሼ አወጣውት " አለች ትንሽ በቀበጠ ንግግር ነገሩን ቀለል አድርጋ ........
ለእሷ እኔ አፈርኩ !!! እሷ ግን አሁንም ድርቅ እንዳለች ስት ቆማለች ????🤔🤔
አከራዩ ወደኔ ዞረና
" ይቅርታ በጣም ለአለም ያለ ስምሽ ስም ወጣልሽ ።
ትዕግስት ፈጥነሽ ይቅርታ ጠይቂ " ብሏት ጥሎ ወደ ቤቱ ገባ ።
እሷ እንኳን ልጠይቅ አሁንም በምን ልስደባት እያለች እያሰበች ይመስል ትንሽ ደርቃ ቆመችና ወደ ቤቷ ገብታ በሯን ቆለፈች ከዛ ሁላችንም ወደ ቤት ገባን ።
እን ልክ ስገባ
በላይ ለአሜን ብዬ ያስቀመጥኳትን ቂጣ እየበላት ነበር ።
ረሀብን በደንብ ስላየውት ልጄ ሲራብ የሚሰማውን አሰብኩኝና ከእጁ ላይ መነተፍኩት ።
ከእራሱ ጋ አለመሆኑ የጠቀመኝ ይመስላል ምንም ሳይለኝ ተኛ ........
እንደምንም እያልን ህይወታችንን ቀጠልን ። .... ......
በላይ የኮብል ስራ ጀመረ ። እኔ አራስ ይዤ ነገሮች አልመቻች ስላሉኝ መስራት አልቻልኩኝም ።
ቀስ በቀስ አንዳንድ ነገሮችን ገዛን ።
እንደ ሰው እንጀራ ጋግሮ ሽሮ መብላት ጀመርን 🙏🙏
ሳስበው የሚያስከፋኝ ነገር ግን አለ ። እርሱም የበላይ ንግግር ነበረ ። .....
እኔ ሁለት ልጅ ይዤ ሙሉ ቀኑን ከጠዋት እስከ ማታ ደፋ ቀና ስል ነው የምውለው ።
ነገር ግን ቤት ውስጥ ስለምውል ብቻ በላይ ከስራ ሲመጣ
" እዚ ተዘፍዝፈሽ እየዋልሽ " ሳይለኝ አንድ ቀን አልፎ አያውቅ !!!?????😥😥
ሁሉም ይሁን ብዬ አለፍኩት🙏!!
አንድ እለተ ሰንበት ቀን አቅራቢያ የቤተክርስቲያን ድምፅ ስለሰማሁ ደጁም ስለናፈቀኝ ብዬ መክሊቴን አዝዬ አሜንዬን ደግሞ አቅፌ ከቤት ወጣሁኝ ።
መንገዱአያስቸግርም አስፖልት ዳሩን ይዞ ቀጥ ብሎ መሄድ ነበር ከዛ ፊት ለፊት ቤተክርስቲያኑን አየውት ።
ነጠላ የለበሱትን እየተከተልኩ ነው የሄድኩት ።
ከዛም ለረጅም ሰአታት ህይወቴን ሙሉ ዘክዝኬ የልቤት መሻት ሙሉ ነገርኩት ።
በዋናነት የፀለይኳት ነገር ግን " ስራ ስጠኝ " ብዬ ነበር ።
ምክንያቱም በጣም ያስፈልገኝ ነበር ።
ቀኑ 19 ነው ። የምወዳት ቀን!!!!
ህዝብ በጣም ነበረ ። እሁድ እሁድ እኛ ጋ ሰው ሁሉ ቤተስኪያን ስለሚሳለም እንዲያ ነው ብዬ አለፍኩት ።
ከዛም ተሳልሜ ልጄንም አሻሽቼ ከዛ ወጣሁ ። በአስፖልቱ ዳር እየሄድን ነበር ። አቅፌው የነበረው አሜኑ ካልወረድኩ ብሎ አልቅሶ አውርጄ በእጄ ይዤው መሄድ ስንጀምር ከዃሃዬ ያሉት ሰዎች እየሮጡ አልፈውኝ ሄዱ ???
ምን ተፈጠረ ብዬ ደንግጬ ስዞር ቀዩ ትልቁ የጭነት መኪና ሲኖትራክ መኪና ወደኛ እየመጣ ነበር ..............!!!?????🤐🤐🤐🤐🤐😞
✍✍✍✍fidel......
..........ወደኛ እየመጣ ነበር ። ለመሮጥ እግሬ ተሳሰሩ ግን ልጆቼን አስቤ አንጠልጥዬ መኪናውን እያየው ለመሮጥ ስሞክር ባለውለታዬ እኛን ለማዳን ብሎ ወደ አስፖልቱ ገብቶ መስመር ስቶ ከሌላ መኪና ጋር ተላተመ ።
ከደቂቃዎች በፊት የፀለይኩት ፀሎት ሙሉ ተሰማልኝ ፈጣሪ ይመስገንልኝ ። ..........🙏🙏🙏🙏
ያንን ቀን ተመስገን ብቻ ብዬ አለፍኩት ።
መኖር ከተባለ መቃብርም ይሞቆ የለ ህይወትን ቀጠልናት ።
እኔም ቀስ በቀስ ነገሮችን እየለመድኩ መጣሁኝ ።
በእድሜም በአስተሳሰብም እየበሰልኩ ነው ።
ቦታውን በደንብ ስለለመድኩት ቤተ ክርስቲያን መሄድን አዘወተርኩኝ ።
አንድ የቀን ሙሉ ቀን ከቤተክርስቲያን ስመለስ ወደ አንድ ዳር ላይ የተቀመጠች አንዲት ሴት ፍራፍሬ ስትሸጥ አየዋት ።
አሜንዬ እጁን እየጠቆመ እማ እማ እያለ ይመለከተኛል ?
ፍላጎቱን ማሳካት አለመቻሌ ግልፅ ነው ምክንያቱም በላይ በላሽ ጠጣሽ ጨረሺው ተዘፍዝፈሽ እየለፋሁ ..... ከሚሉት ተራ ቃላቶች የተሻለ አንድም አያውቅም !!!
እንደ ሚስት ብቻ ሳይሆን እንደ ልጆች እናት ለሆነ ነገር ብሎ አምሳ ሳንቲ ሰቶኝ አያቅም ??
ለማንኛውም ግን እጆቹን ያየችው ነጋዴዋ ሴትዮ ከፊት ለፊት አንዱን አንስታ
" ና እንካ " አለችው በፈገግታ ተሞልታ ።
የኔ ልዑልም ድክ ድክ ብሎ ሄዶ ተቀበላት ።
ከዛ አመሰግናለሁ ስላት ውስጤ ፊቴ ላይ የተፃፈ ይመስል
" ስራ የለሽም ?" አለችኝ
አዎ በቅርብ ነው ከክፍለ ሀገር የመጣውት አልኳት መልሳ ግን
" የገጠር ሰው ግን አትመስይም ቆንጆ ፀጉር ቆንጆ ግን የተጎዳ ፊት ነው የሚታየኝ " አለች ።
ሰውን የሚወስነው አኗኗሩ ስለሆነ ነው ።
ንግግሯ ነክቶኝ ትዝታን ቀስቅሶብኝ በዝምታ ስዋጥ
" ለምን ይሄንን ስራ አጀምሪም ?" አለችኝ ።
ማንጎና ሎሚ እና አቮካዶ ይዛ አየዋትና ስለ ስራው አንድም አላቅም እኔ በቃ ፍጥጥ ብዬ ሳያት ምንም እንደማላቅ ገባት መሰለኝ
" ለሊት ተነስተሽ 02 ትገቢና በርካሽ ታመጫለሽ እዚ ጨምረሽ ትሸጫለሽ " አለችኝ።
እሺ ግን መጀመሪያ በምን ልገዛ ደሞ ልጆቼስ አልኳት ጨንቆኝ
" ባለቤትሽ ይጠብቃ ጠዋት ደሞ ስራ ከሄደ አንቺ ትጠብቂለታለሽ " አለችኝ ቀለል አድርጋ ።
በጣም ነበር ደስ ያለኝ ብር አገኛለው ብዬ ሳይሆን ስራ ይኖረኛል ብዬ አስቤ ነው ።ቤት መዋል ሰሎችቶኝም ነበር ።
እንደሚጠበቀው ያለመጠራጠር እሺ አልኳት ።
ነገር ግን እኔ 02 የሚባለውንም ታክሲ መያዧውንም አላውቀውም እንዴትእሄዳለሁ አልኳት ።
ቤቱን አሳይቻት ለሊት መታ መታ ልትቀሰቅሰኝ ተስማምተን ወደቤት ሄድን ።
ለበላይ ብነግረው እዛም እንደማልሄድ ስላወኩኝ በዝምታ እንቅልፍም ሳይወስደኝ ቁልጭ ብዬ አደርኩኝ ።
ከዛ የውጪ በር ላይ ስደርስ 02 ብዬ እጮካለሁ ስላለችኝ ድምጿን እንደሰማሁ ቶሎ ወጣሁ ።
አምጥተን ጨርሰን ልጆቼን ይዤ እዛ መሸጥ ጀመርን ።
በአስራ ዘጠኝ ብር አምጥታልኝ ሰላሳ ብር ሸጥኩት !!!!
በቀጣዩ ቀን በሰላሳ ብር አመጣን አርባ ብር ሸጥኩት ።
ልጅ ይዤም ስለምቀመጥ ይመስለኛል ደጉ የሀገሬ ሰው ሳይፈልግም ቢሆን ይገዛኛል ።
አመት ጄ ላይ ብር ገብቶ የማያውቅ ሴት አሁን ላይ ብር ማስቀመጥ ጀመርኩኝ ።
የሰጠችኝን መለስኩ ።
ማታ ከበላ በፊት ስለምገባ እሱ በጣም ስለሚያመሽ ለሊት ቤተ ክርስቲያን መሄዴን እንጂ ምንም ነገር አያቅም ።
ግዴለሽ ስለሆነ ትኩረት ስለማይሰጠኝ እንጂ በእርገጠኝነት ለማወቅ ቀላል ነበር !!!!
በነዛ ሁሉ ሁኔታዎች ግን ፈጣሪ በጣም ጠብቆኛል ሁለቱም ልጆቼ እያደጉልኝ ነው ።
እርስ በርስ ይደጋገፋሉ ይጫወታሊጨ።
አንዳንዴ እንቅልፍ ማጣቱ አስእ ሰአት መንቃቱ ብርዱ የውሾቹ ጩኸት ብቻ ሁሉም ነገር ያስጠላኝና እነሱን ሳይ ዳግም እበረታለሁ !!!!!
በብዙ ሁኔታውች ውስጥ ሆነን የከተማ ህይወትኔ እንደ ሁሌው በብቸኝነትም በድካምም ስሜት እያስተናገድን ቀጠልን ።
በዛ ሁኔታ ውስጥ ያላስተዋልኩት ነገር ነበር ። እሱም ደግሞ የወርቅነሽን ጉዳይ ነው ።
ማለቴ በጣም ጥሩ ሰው የማትሳሳት ደግ ሴት አድርጌ ካብኳተ!!!!!
ከአምላክ የተላከይ መልአክ አድርጌ ሳልኳት ሙሉ በሙሉ ጥሩ አድርጌ አስቢያትም ነበር ........??????
✍✍fidel......
.......የሚገርመው ግን አሰርታኝ ስጨርስ ቀስ በቀሶ ብሩን እንድሰጣት እና እሷ ጋ እንዳጠራቅም ትነግረኝ ጀመር ።
ሀሳቧ ግልፅ ስለሆንልኝ ከዛን ቀን ቡሀላ ስራ እንደማልሰራ ነግሪያት ከሷ ራኩ ።
አንድ አንድ ቀን እያረፍኩኝ ግን መስራቴን ቀጥዬ ነበር ።
ብሩ በርከት ሲልልኝ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሁለቱም ልጆቼ ብር አውጥቼ ልብስ ገዛው ።
ለኔ በጣም ትልቅ ድል ነበር !!!!!
እንደ ቀልድ አዲስ አበባ ውስጥ ወራቶችን ተቀመጥን ።
በወራቶች መሀል ስህተት ይሁን አይሁን ባላውቅም ድጋሜ ልጅ ልወልድ ነው ። ከብዙ አመት ቡሀላ ደገምኩት ።
ከእስከዛሬው ቀለል ያለ የእርግዝና ወራትን አሳለፍኩኝ ።
በስተመጨረሻም በድጋሜ ሴት ልጅ ሰጠኝ !!
ምንም ቢሆን ጋቢ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ተከራዮችና የአከራያችን ባለቤት መተው ጠይቀውኛል ።
በእናት ያላየሁትን በትንሹም ቢሆን በነሱ አየውት ።
የአከራያችን ሚስት ናት ስም ያወጣችልኝ ።
" እኔ የአንቺ ነገር በዚ እድሜሽ የሶስት ልጅ እናት መሆንሽ ስለሚያስገነርመኝ የአብስራ ብያታለሁ " አለች ። በዛው ፀና ።
ለልጄ ልብስ አልቸገረኝም ወንድሟና እህቷ ያደጉበት በቂ ልብስ አለኝ ።
ክረስትናዋንም ፏ አድርጌ ባለችኝ ነገር ደገስኩላት ። ........
ከሞገሴም ሆነ ከውንድሜ ጋር ከተገናኘን አራት አመታት ተቆጠሩ ።!!!!..
ለኔ አዲስ አይደለም ለምጄዋለሁ ። ነገር ግን ሞገሴ እድሜው በሄደ ቁጥር የሆነ ነገር እንዳይሆን እፈራለሁ !!!!
በዛ ላይ የሆነ ቀን እኔም ሁሉም ተሳክቶልኝ እንደምኖር ነው የማስበው !!!!!
በላይ ከዛኛው ስራ ቀይሮ ብረታ ብረት ማቅለት ስራ አግኝቶ እየሰራ ነው ።
እኔ የጎዳና ንግዴን አጧጧፍኩት!
አንዳንዴ በላይ በሳምንት የሚያገኘውን እኔ በቀን ላገኘውም እችላለሁ ።
እኔ ባንክ ስላልነበረኝ ለወደፊታችን እያልኩኝ ብር እደብቅ ነበር ።
የተሻለ ነገር ላይ ስንደርስ ቤት ቀየርን ።
በነገራችን ላይ በጣም ብዙ ነገሮች እየተስተካከሉና እየተቀየሩ መተው ነበር ከበላይ ውጪ .......
እሱ እንዲስተካከል ለማድረግ ብዙ ለፍቻለሁኝ ግን ያው ነው ። የኔን ምክር ንቆ ራሱን የአረቄና የጠጅ ምርኮኛ አድርጎ ቀረ ።
ከውጪ ለሚያየው በቀን አንድ ጉርሻ እየቀመሠ የሚሄድ ነው የሚመስለው በጣም ክስት ብሏል ። !!!!
በነገራችን ላይ አንዳንዴ መጥፎ ገጠመኞች ለበጎ የመሆን እድላቸው ሰፊ ነው !!! በጣም ሰፊ ሆኖልኛል!!!
አሜኑ በጣም ጎበዝ ተማሪ ሆኖልኛል መክሊቴ ከትምህርት ይልቅ ሌላ ነገር ላይ ትኩረቷን ጥላለች ።
እንደዛ አያድጉም የት ሊደርሱ የተባሉት ልጆቼ አሁን ላይ በጣም ቆንጆ መንታ የሚመስሉ ልጆች ሆነዋል !!!
የአብስራ ደግም ኬጂ እየተማረች ነው ።
አኖዳንዴ ስንሰባሰብ ነገሮችን አይና በጣም እገረማለሁ ማለቴ ምክንያተቱም ለኔ እንደ ጓደኛ ፍቅረኛ ባል እናት አባት ዘመዴ ሆነዋል ።
የምር እኔ ነኝ የወለድኳቸው ?? እላለሁኝ ሁላ !!!???😊😊
ህይወትን እየኖርን ነው ። ደንቦች ቢያስቸግሩንም ስራ እየሰራሁ ነው ። ቀስ ብዬ ንግዴን አሰፋውት የቤተ እቃ መሸጥ ጀመርኩ።
እኔ እያደኩ ስመጣ በላይ እየወረደ መጣ ። !!!
በባልና ሚስት መሀል እንደዚ ባይባልም በጊዜው እሱ ከኔ ጠባቂ ሆነ !!
ጊዜ እንዲሆ ነው ይቀያየራል !!!!!
ዛሬ ለአንዱ ያደላ ነገ ለሌላው ይሰግዳል ..!!!!!
ከበላይ ፍቃድ ሳልጠብቅ ራሴን ማንቀሳቀስ ስጀምር ብዙ ነገሮች ያጓጉኝ ጀመረ ብዙ ፍላጎቶች መጡልኝ ።
አዲስ የገባንበት ጊቢ እንደ እህት እንደ ጓደኛ የተግባባዋት አንዲት ልጅ አለች በላይን ስለማላምነው ልጆቼን ለሷ አደራ ሰጥቼ ወደ እናትና አባቴ መንደር ሄድኩኝ።
የእንጀራ አባቴ ቅድሚያ እንዲያየኝ ስላልፈለኩ ጎረቤታችንን ስንት ጨቅጭቄ አሳምኜ ወደሷ ቤት ገባሁ ።
በነገራችን ላይ ወደዛ የሄድኩት ለትልቅ ነገር ነው ።
ምክንያቱም ከዛ በላይ በጥያቄ መብሰልሰል አልፈለኩኝም ነበረ ።
ስለ አባቴ ሞት ማወቅ ነበረብኝ ።ቢያንስ የእናቴን ስም አልጥላው ።!!!
ከብዙ አመታት ቡሀላ እኔን ለማወቅ ቢቸገሩም በልጅነቴ ቤት ሲመጡ የነበሩ ነገርችን እያስታወሶኸፈኩ እንዲያምኑኝ አደረኩ ።
ቡና ካጠጡኝ ቡሀላ ለመስማት እየፈራሁም ቢሆን ቀጥታ ወደ ዋና ነጥቡ ገባሁ ።
አባቴ እንዴት ነው የሞተው ???? ማነው የገደለውስ አልኳቸው .......
✍✍✍fidel......
ኦሮማይ ...
/በአሉ ግርማ/
.............ማነው የገደለው አልኳቸው ። ሁሉም ዝም ዝም አሉ ።ድርቅ ካለ ከቤቱ ወለል ጋ መፋጠጥ ቡሀላ እናትየው በአሳዛኝ ፊት ሆና
" ልጄ አባትሽ ማለት የብዙ ሰዎች አባት ነበር !!! መልአክ ነው ደግ እና ሩሩህ ነበረ ።
እንኳን ሰው ሳር ቅጠሉ ነው የሚወደው ......
ምን ዋጋ አለው ደህና ሰው አይበረክትም አደለ ገና በልጅ እድምው አፈር በላው " አለች ።
የተቀሰቀሰብሶቷን በእንባ አጅባ እየነገችኝ ።
እሱን አውቃለሁ ስለ አባቴ ጥሩነስ ስሰማ ነበር የቆየውት እዚ እስከነበርኩኝ ቀን ድረስ እንዴት ሞተ?
ማለቴ ብዙሀኑ በእናቴ ምክንያት እንደሞተ ነው የሚያወሩት አልኳት ምላሽ እንደምጠብቅ እያሳነሁ ።
ሁሉም ላይ ትንሽ የድንጋጤ ፊት ስለተመለከትኩ ይበልጥ ጉዳዩን የማወቅ ጉጉቴ እየጨመረ ነበር ።
" ይቅር ይበለን ሙት ወቃሽ አያድርገን ልጄ !!
እርግጥ እኛም የምናቀው ነገር የለም ማለት በአሉ አሉ ነው ነገሩን የሰማነው ያልቸረጋገጠ ነገር ነው " አለችኝ ።
እሺ ቢያንስ ትንሽ ንገሩኝ ህሊናዬ እንዲያርፍ ያህል እባካችሁ አልኳቸው ።
" አባትሽ በጣም ታሞ ነበር ( የበሽታውን ስም ማስታወስ አልቻልኩም እንጂ ወጣ ያለ ስም ጠርታለች ) እና ግን ጠበል ወስዶ ደህና ሆኖ ነበር ታክሞም ነበር ።
ቸሻለዎ ብለን እኔና ጓደኞቹ ሆነን ገብተን ጠይቀነው ፀሀይ ላይ እንዳይወጣ እና እርጥበት እንዳይነካው ጭንቅላቱንም በኮፍያ እንዲሸፍን አድርገነው ቀትር ላይ ወደ ቤት ተመለስን ።
አመሻሹ ላይ ነው በጩኸቱ መርዶውን የሰማን !
ነፍሱን ይማርልን 🙏🙏
ነገር ግን እኛ በቦታው ስንደርስ አባትሽ ፀጉሩ በምላጭና በውሀ ተደርጎ ሙልጥ ተደርጎ ተላጭቶ እና ውሀ ተደፍቶበት መሰል ከአልጋው ጋ ተጣብቆ ተጣብቆ......."
ወሬውን ባጨርሰው ይሻላል እነሱም ማልቀስ ጀመሩ እኔም ስቅቅ እስኪያረገኝ እንደ አዲስ አለቀስኩኝ ።
በርግጥ በልጅነቴ ስለሞተ ነገሩ አልተገለጠልኝም አልቅሼም አልቀበርኩትም አሁን በደንብ ተወጣሁት !!!!.... እስኪበቃኝ አለቀስኩ !!!.
በቀጥታ ባይነገረኝም እናቴ ብሩን የግሏ ማረግ ስለምትፈልግ እሷ እንዳደረገችው ግልፅ ነገር ነው ።
የዛኔ ይበልጥ ጠላዋት ።???
አንዳንድ ጊዜ በደንብ አስብና የእናቴን ሀዘን አለመቀበሌ ያስቆጨኝ ነበር !!
ነገር ግን ዘለላ እንባዬም ለሷ አይገባትም !!
ከደቂቃዎች መላቀስና ራስን ለማረጋጋት መሞከር ቡሀላ በረጅሙ ተነፈሰችና
" አንድ ነገር ልንገርሽ ልጄ ይሄ ቤት ቦታዎቹ ሱቆቹ ሁሉም በእርግጠኝነት በአንቺ ስም ናቸው እርግጠኛ ነኝ ። !!.ለገንዘብ ብላ አባትሽን የገደለችው ሴት አሁን ላይ የለችም ፈጣሪ ቀደመ።
ነገር ግን የእንጀራ አባትሽ እጅም ያለበት ይመስለኛል በአባትሽ ላብ እሱ ሚስቱ በሞተች በአርባዋ ሌላ አግብቶ እየተንቀቤረረ ሰፈሩን እያወከ ነው የቄሳርን ለቄሳር አደል የሚለው የአንቺን ለአንቺ አስመልሺ " አለችኝ ።
በጣም የተለየና ልብን የሚያደነድን ንግግር ነበር !
በጣም ወኔ ሰጠችኝ አበረታታችኝ ንግግሯ በሙሉ ልክ እንደሆነ እንዳስተውል አደረገችኝ ።
እንደማስበው ከሆነ ሁሉንም ጊዜ ሲከነክናቸው የኖሩ ይመስላል አነጋገራቸው ።
ፈጣሪ ይመስገን ጥሩ የማሰብ ችሎታን ሰቶኛል!!! በደቂቃዎች ውስጥ ብዙ ነገሮችን አሰብኩኝና ቀጥታ ወደ እርምጃ ገባሁ ።
መጀመሪያ የሄድኩት ከኛ በቅርብ ያለ ፖሊስ ጣቢያ ነበር ።
እድሜዬ ትንሽ ቢሆንም ሰውነቴና የሶስት ልጅ እናት መሆኔ ትልቅ እናት አደረገኝ መሠለኝ እንደ ትልቅ ሰው አስተናገዱኝ እኔም ሳየው ቀለል ያለኝን መርጬ አወራሁት ።
በጣም በጥሞና አዳመጠኝ !!
ጉዳዩን በአንድ ጊዜ ስለተረዳውና ግልፅም ስለሆነ የዛኔው አብረን ሄደን ማየት እንደምንችል ነገረኝ ።
ተመስገን🙏🙏🙏🙏 ነው ያልኩት ።
ከዛም ሁለት ፖሊስ እና እኔ ሆነን ወደ አባቴ ቤት ገሰገስን ።
በጣም የሚገርመው ግን በሩን ስናንኳኳ የከፈተችልንን ሴት ሳይ ማመን አልቻልኩም
.......
✍✍✍fidel...
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ፊደል✍✍» is a Telegram channel in the category «История», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 1.5K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 11.4, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 18.0 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий