

Channel statistics
Full statisticschevron_right........ ብቅ ብቅ ብለው አይተውኝ ክው ብለው ተመለከቱኝ ።
በእናቴ ጉዳይ በጣም ደካማ ነኝ !!!! በዛች በአንድ ቅፅበት በአስተያየታቸው ብቻ ብዙ ነገር አስቤ በአንድ ጊዜ አይምሮዬን አሳመንኩት ።
ሰለሞን ነገሩን እንደኔ በአንዴ መፍረድ አልፈለገም የኔን ዝምታ ለመስበር በሚመስል መልኩ
" ወ/ሮ .." ዞር ብሎ አየኝ ።
ሲያየኝ መልሼ ፍጥጥ ብዬ አየሁት ።
" ስማቸው ማን ነበር ?" አለኝ ።
እ የማ መስከረም ማለቴ መሰረት እያልኩ ስርበተበት እሱ ቀልጠፍ ብሎ
" ወ/ሮ መሠረት የሉም እንዴ " አላቸው ።
በጣም ትልቅ ሰው ነው ።!!!!! ትልቅ ሰው ሆኖ ባለ ስልጣን ሆኖ የጊቢው አስተዳደር ሆኖ እንኳን ያልሰጠሁትን አክብሮት ለእናቴ ሰጠልኝ !!!
ጎረቤቶቻችንም ከመመለስ ይልቅ በዝምታ ተመለከቱን ።
ነገሩ የበለጠ ረበሸኝ ። ስደነግጥ ራሴን መቆጣጠር ስለማልችል እጄ መንቀጥቀጥ ጀመረ ።
" ተረጋጊ እንጂ ልጄ ህይወትን መጥፎ ብቻ አርገሽ አትሳያት ከመፍረድሽ በፊት ጠይቂ " ብሎ በእጆቹ ትከሻዬን እያሻሸ አበረታታኝ ።
" ወዴት ሄዳ ነው የሚመልስልኝ የለም ?" አለ መልሶ በትህትና ።
የኛ ሰፈር ሰዎች አሁንም ዝም አሉ ።
በእርግጠኝነት ባለ ስልጣንና ባለ ሀብት እንደሆነ ቢያውቁ እሩቅ ቆመው ባላዩት እንድል አደረጉኝ !!🙌🙌( እኔ አላልኩም )!!
የዛኔ ዝምታቸው ከኔ ዝምታ ጋ እንደማይገጥም የተረዳሁት እኔ ወደ ውስጥ አየር ስቤ እናቴን የምትቀርባት ሴት ላይ አፍጥጬ
አምሳል እናቴ የት ናት ? አልኳት ። ስናደድ በደንብ ስለምታውቀኝ
" መጀመሪያ ተረጋጊ ቆይ ያምሻል የኔ ቆንጆ ተረጋጊ " አለችኝ ።
ከአቅሜ በላይ ከሆነ መንቀጥቀጥና ማልቀስ ነው የሚያረጋጋኝ ።
ለዛ ትክክለኛ ሰአት ስላልሆነ ራሴን ለመቅጣጠር ሞከርኩኝ ።
እሺ ንገሪኝ ደህና ነኝ !! አልኳት ለማወቅ እየተዘጋጀው ።
" ትላንት አባትሽ መቶ ነበር ..." ንግግሯን አላስጨረስኳትም ።
አባቴመ እናቴም እሷ እንደሆነች ታቂያለሽ እኔ አባት የለኝም !!!!ብዬ መለስኩላት ።
በአሳዛኝ እይታ ተመለከተችኝና ንግግሯን ቀጠለች።
" እና ትላንት በጣም ተጣልተው ሲጨቃጨቁና ሲመታትም ነበረ ከዛ ሲመሽ ሄደና ገና ወፎች ሳይንጫጩ መቶ እየጎተተ ይዟት ሄደ " አለችኝ እንደ ቀላል
ነገር ????????
ንግግሯ ግልፅ አደለም ለእረጅም ደቂቃዎች ያህል ስታወራ ተሳስታ ነው ብዬ ነገሮችን ለመረዳት ስሞክር ነበረ ።
ማለት አልኳት ግራ ገብቶኝ ። ጭራሽ ይባስ ብላ
" ይዟት ሄደ ይሄው እስካሁን ስንደውል አታነሳም ሰው እንዳይሰማ ብለን ዝም አልን "" ብላ ንዴቴን አባባሰችብኝ ።
የዛኔ ከልጅነት እስከ እውቀት በትህትና በእርጋታ በሰከነ ማንነት በሰው አክባሪነት ...... የምትታወቀው ጨዋዋ አብላካትን ደበኳትና
እንዴት ማንም መቶ ሲወርዳት ዝም ትላላችሁ ????......እንዴት እናቴ ስትመጣ ዝም ትላላችሁ ????...... እናቴ ለአንቺ ስትል እንባዋን እስከማፍሰስ አልደረሰችም የምር እንደዛ አይነት ሰው ነሽ !!!!!!?????ብዬ አበድኩባት ።
ሀገር አማን ብላ ባዶ እጅ የማታቀው አለምዬ በሁለቱም እጇ ፌስታል አንጠልጥላ ያ ድንቡሽቡሽ ጉንጯ ፈገግ እንዳለ ወደ ውስጥ ስትገባ አይን ለአይን ተገጣጠምን ።
ድርቅ ብላ ነው የቀረችው ።
ሴት መሆን እንዲህ ነው በእይታ ነገሮችን እናውቃለን ።
ከዛም በፍጥነት ወደኛ መታ ፌስታሎቹን መሬት በትናቸው
" አባ ...... አቡ " እዚህ ምን ታደርጋላችሁ ምን ተፈጠረ መስኪ ምን ሆነች ????....." ብላ የጥያቄ መአት አዘነበችብኝ ።
እሷ ውስጥ የእናቴን የዋህነትና እናትነት አየሁ የዛኔ የሆነ አካሌ ተቆርሶ ሊወሰድ መስሎ ተሰማኝና ድካሜን ከዛ በላይ መደበቅ አቅቶኝ እንባዬ አመለጠኝ ።
ካለቀስኩ እንደሚያመኝ ስለምታውቅ አምሳለ የምትባለው ሴት ወደኛ እየቀረበች
" ያምሻል እንዳታለቅሺ እባክሽ " ብላ ልታረጋጋኝ ሞከረች ።
በሰአቱ ለእናቴ የሚደርስ አንድ አካል ማጣቴ ለኔ አስከፍቶኛል !!!
በዛ ላይ እናቴ ብትሆን እስከ ሞት ተከትላቸው እንደምትሄድ ሁሉም ያውቃሉ !!!!
ሴትዮዋ እንዳትጠጋኝ ጮኩባት ።
እንደመደንገጥ ብላ ወጀ ዃላ ሸሸች ።
አለምዬ እቅፏ ውስጥ አስገብታ እንባዬን ተጋራችኝ ። !!!!!የኔ የዋህ !!!!!
የዛኔ ሰለሞን ቀና ብሎ ሹፌሩን ሲያየው ወዲያው ወደ አለምዬ መጣና መኪና ውስጥ እንድትገባ ምልክት ሰጣት ።
" አይ መስኪን ሳናገኝ የትም አንሄድም !!! የሆነ ነገር አድርግ እንጂ !!" ብላ ሰለሞን ላይ አፈጠጠችበት ።
ዝም ብሎ ትንሽ አሰላሰለና
" የሆነ የሰማችሁት ስም የለም ነቦታ ስም ።????
ሰውዬው የት እንደሚኖር አታውቁም ?" ብሎ ሁሉንም በየተራ አያቸው ።
ወሪያቸው ካላለቀ ከአቦል እስከ አራተኛ የሚያፈሉ ሰዎች በዛ በችግርና በጭንቀት ሰአት ሁሉም አፋቸውን ዘግተው ይመለከቱኛል ።
ከዛ በላይ መቆጣጠር አቅቶኝ ለመሳደብ ስነሳ አባቴ የሚባለው ሰውዬ ፊት ለፊት ግትር ብሎ በድንጋጤ ፍጥጥ እንዳለ ተገጣጠምን ???????.....
✍✍fidel........
1. ፈልገኝ እንጂ አታሳደኝ
2. ስራልኝ እንጂ አትመኘኝ
3. ጠብቀኝ እንጂ አታጣድፈኝ
4. ያዘኝ እንጂ አትበትነኝ
5. ስራብኝ እንጂ አታባክነኝ
6. ተጠቀምብኝ እንጂ እዩልኝ አትበለኝ
7. አሰራኝ እንጂ አፍነህ አታስቀምጠኝ
8. ከምንም በላይ እንደከብርህ አክብረኝ
የገንዘብ_አጠቃቀም_ጥበብ
🏆🏆🏆🥂 ገንዘብ ሳይኖረን ስለ አጠቃቀም ጥበብ ላነበብነው 👆👆😂😂
🙋♀🎬🎬አርባ ሰባት
.......... ከእንቅልፌ ቀሰቀሰኝ ። ከሆነ ጊዜ ጀምሮ ማንኛውም ድምፅ የረብሻና የችግር ድምፅ መስለው ነው የሚሰሙኝ !!!
ነርሷ የቤኪን ሁኔታ ለማየት በሩን ስትከፍት እኔ እንደ ጦርነት ድምፅ አይቼው በጣም ተረብሼ ነበረ ።
በድንጋጤ ብርግግ ብዬ ስነሳ እንቅልፍ አልወስድ ብሎት የሚቁለጨለጨው ቤኪ በሚያሳዝን ፊት እያየኝ ነበር የኔ አባት ።
በጣም እንደደከመው ፊቱ ላይ ይነበባል !!!
ቀስ ብላ ገብታ የሆነ የሆነ ነገር አየችና በፈገግታ ተሞልታ
" በጣም ደህና ነህ እንኳን ደስ አለክ " አለችው ።
አንድ ቦታ ለሰአት መቆየች የማይችለው ልጅ ተኝቶ መዋል ሰለቸው መሠለኝ
" ነገ ከዚ መሄድ እችላለሁ ነርስ በእናትሽ " አላት በሚያሳሳ ድምፅ ።
ብችልና ህመሙን ተጋርቼው ከዛ አልጋ ላይ ወርዶ ቢንጎማለልብኝ ደስ ባለኝ ነበር!!!!
ከዛ መልሼ ብተኛም እንቅልፍ እንደማይወስደኝ ስላወኩኝ ወርጄ ወደ ቤኪ ጋር ሄድኩና እጁን ይዤ ቁጭ አልኩኝ ።
ነርሷ ግሉኮሱን እየነካካች ቀና ብላ አየችንና
" እህት እኮ ሁሌም ከጎን ናት ማነው ታላቅ ?" አለችን ።
ሁለታችንም በፈገግታ እየተመለከትናት ማን ይመስላል አልኳት ቀስ ብዬ
" ወንዶች እየረዘሙ ስለሆነ በቁመት ብቻ እድሜ አይገመትም ብዬ ነው እኮ " አለችን ።
ደስ የምትሕ ሰው ናት በአንዴ ተቀራረብን ማለት ይቻላል ቀለል ብላ ነው የምታወራው ።
ቤኪም ቀጠል አድርጎ
" ከሁለታችን ማነው ቆንጆ " አላት ።
" የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ለእናንተ ቤት አይሰራም መሠለኝ ሁለታችሁም በጣም ነው የምታምሩት እኮ " አለችን በአድናቆት እየተመለከተችን ።
እናመሰግናለን ብዬ ዝም አልኩኝ እኔ ። ነርሷ
ጨራርሳ ልትወጣ ወደ በሩ ስትጠጋ
" ለማንኛውም እህቴ ሳትሆን ፍቅረኛዬ ናት በቅርብ የምንጋባ ይመስለኛል " ብሎ የኔንም የሷንም ቆሌ ገፈፈው !!!!!
ነርሷ ቀልድ መሠሏት መሠል ፈገግ ብላ ልትወጣ አለችና መለስ ብላ የምርህን ነው ??? አለችው ።
" አዎ ማርያምን " አላት ። ደስ የሚለው እሷም አልተመቀኘችም በፍቅር አይን እያየችን
" ያዝልቅላችሁ አረ ክፉ አይያችሁ !!!"። ብላን ከክፍሉ ወጣች ።
ወዲያው ቤኪ ወደ እቅፉ ስቦ ግንባሬን ሳመኝና ደረቱ ላይ አስተኛኝ ።
መልሶ እንቅልፍ ይወስደኛል ብዬ ባልገምትም ጠዋት በሰለሞን ጉትጎታ ነው ከቤኪ እቅፍ ውስጥ ከወሰደኝ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰደኝ ።
ዛሬ ቤኪም ነቃ ብሎ ነው የነቃው ።
በትንሹ የተሻለው ይመስል ነበረ !!!
የሚደራረጉ ነገሮች ተደርገውለት ዙሪያውን ክብብ አድርገን ቁጭ ብለን እያወራን ነበረ !!!
ቀኑ ረቡዕ ነው በድንገት የሰለሞን ስልክ ጠራ ።
ድክም ዛልልል ባለ ድምፅ አነሳ
" ሀሎ " አለ በጎረነነ ድምፁ
ከዛኛው ወገን ምን እንደተባለ አላውቅ
" ወይኔ ዛሬ ነው እንዴ ስንት ሰአት " አለ ከተቀመጠበት እየተነሳ ።
ትንሹ እሱን ዝም የሚያስብሉ የሰከነ ንግግሮች አካሄደና እሺ እሺ ብሎ ስልኩን ዘጋው ።
ወዲያውኑ ከኔ ቀድማ አለምዬ
" ምነው አባዬ " አለች።
" ዛሬ ረቡዕ መሆኑን ረስቼዋለሁ እኮ በእናታችሁ በሉ በሉ ልጆች ሶስታቹም ፍጠኑ ወደ ጊቢ ተመለሱ " ብሎ አዘዘ ።
አይ እኔ ከቤኪ ጋር ነው የምቆየው አልኩ ኮራ ብዬ ከነሱ በመቅደም ።
" እኛ እዚሁ እንሆናለን " አለ ያቤፅም ቀጠል አድርጎ ።
" ተነሱና ሂዱ አልኩ እኮ ዛሬ ፋይናል ፈተና እንደሚጀምር ረስታችሁታል አይደለ አሁን ግን አስታወስኳችቱ ስለዚ ምንም ጎበዝ ተማሪ ብትሆኑሞ የሆነ ነገር እዩና አስታውሱ ጥሩ ውጤት እንጠብቃለን!!!!!
እውነት ለመናገር ሙሉ በሙሉ ረስቻለሁኝ ። ከዛ አማራጭ ስለሌለኝ
እስክመለስ ጤነኛ ሆነክ ጠብቀኝ !!! ብዬው ወደ ጊቢ ሄድኩኝ ።
የሚያስጠላው ደግሞ ሀሳቤን መሠብሰብ ይከብደኛል እንዴት ብዬ እንደምሰራውም ሳላቅ ዶርም ሄጄ አየት አየት አረኩትና ተመልሼ ወጣሁ ።
ከዛም ፈተናዬን ተፈተንኩና ተሰብስበን ቢኪ ጋር ሄድን ።
ልክ ስገባ
" እናትዬ ናፍቀሽኝ ነበር እኮ "ብሎ እዛ ሁላ ሰው መሀል አሳፈረኝ ።
በትንሹ ፈገግ ብዬ በዝምታ አለፍኩት ።
ከዛም ስናወራ ስንቃለድ ቆይተን ሰአቱ ሲሄድ ጊዜ እናቴ ጋ መሄድ ነበረብኝ ።
ቃል ገብቼላታለሁኝ ።
ብቻዬን መሄድ አልፉኩኝም !!! ሰለሞንን አድርሰኝ አብረን እንሂድ ብሎ መጠየቁ ስለደበረኝ ፊት ለፊቱ ቆሜ ስለ እናቴ ሳወራ ነገሩን የተረዳው የቤኪ አባህ ተነስቶ አብሮኝ ወጣ ።
ሹፌሩ እየነዳ ከዃላ ተቀምጠን በፀጥታ መንገዳችንን ቀጠልን ።
ፈተና እንዴት ነበር ???አለኝ ።
እንደፈራሁት ስላልነበር
ቀላል ነው ብዬ ነው የመለስኩት ።
ከዛ ከጉዞ ቡሀላ እናቴ ጋ ደረስን ።
በጣም ናፍቃኝ ስለነበረ እየሮጥኩ ሄጄ በሩን አንኳኳው ።
አይከፈትም ???
ደጋግሜ ሳንኳኳ ከኛ ጎረቤት ያሉ ሰዎች ወጡና እንዳዩኝ ክው ብለው ተመለከቱኝ ?????
✍✍✍fidel......
🙋♀🎬🎬ክፍል አርባ ስድስት
.............ልቤ ቀጥ ድው ነው ያለችብኝ። ስልኩ እስከሚያልቅ መጠበቅ ስላልቻልኩኝ አንሄድም እንዴ ?? ብዬ አፈጠጥኩበት ።
ስልኩን እንደያዘው ሳይዘጋ
" መሽቷል በዚህ ሰአት እንዴት እንሄዳለን ብዬ ነው " አለ ለሁለታችንም እየመለሰ ነበር ።
አረ ብንሄድ ነው የሚሻለው ቅርብ አይደለ ምን ችግር አለው ብዬ ቀለል አድርጌ አወራሁት።
ደስ የሚለው ቤኪም ስልኩን ተቀብሎ ፈጠን ብሎ
" አባ ብትመጡ በጣም ደስ ብሎኛል ግን እ አቡ ናፍቃኛለች እኮ " አለው ።
ገና ድምፁን ስሰማ ፈገግ የምለው ነገር አለኝ ።
የቤኪ አባትም በትንሹ ፈገግ አለና
" እሺ መጣን በቃ " ብሎ ስልኩን ዘጋው ።
ከዛ ወሪያችንን ቀጠልን በጣም ብዙ ነገር ነገረኝ ።
መሸ ብለን ስናወራ የበለጠ እንዲመሽ አደረግነው ።
ገና መጣን ስላንን ጨራርሰን ወጣን ።
በመኪና እየሄድን ራሱ ስናወራ ነው የሄድነው።
ወደነ ቤኪ ጋር እየተቃረብን ስንመጣ ግን
" ስላዳመጥሽኝ በጣም አመሠግናለሁ ከማንም ጋ በዚህ ልክ ተቀራርቤ አላውቅም !!!
ሁል ጊዜ ስራና ስራ ላይ ብቻ ስለማተኩር ማንም ቀርቦ አውርቶኝ አያውቅም ስገምት ግን አብዛኞቹ ማውራት የምችልም አይመስላቸውም መሠለኝ " ብሎ ሳቀ ።
ለፈገግታው ምላሽ ቁጥብ ፈገግታዬን እያሳየሁት
ምን አልባትም ቀርበን ባናወራ እኔም እልክ ነበር እንቅስቃሴዎችክ እንዳለ የምልክት ናቸው እኮ !!!!!
ስገምት ግን ስልጣኑ ሀብትክና ዝናህ ወጣ ስለሚያረግህ ነው ።
ማለት ማንም ቢሆን እንደማንኛውም ሰው ቀርቦ ሊያወራክ አይችልም !!!
እኔም የኔነት ስሜት አዳፍሮኝ ነው አልኩትና ሁለታችንም ተያይተን ከትትት ብለን ሳቅን ።
ሁሉም ሰው ከላይ እንደሚታየው አይደለም ። አንዳንዱ ከላይ ስታዩት ንፁህ የዋህ ይመሰክራሉ ልና ስትቀርቡት ግን ምን ያህል ሰይጣን እንደሆነ ይታወቅበታል አንዳንዶቹ ደግሞ ከላይ ክፉ ኮስታራና መጥፎ ይመስሉና ልክ ስትቀርቧቸው ምን ያህል መሳቅ የሚያምርባቸው የዋህና ጥሩ መልካም ሰዎች መሆናቸውን ትረዱበታላችሁ !!!!
የቤኪ አባት ማለት ልክ ያ ሰው እንደማለት ነው ከላይ አይቼው ለልጁ የማያስብ ኮስታራ ገንዘብ የሚያሳድድ ሰው ጨካኝ ........ ብቻ በጣም ብዙ የማይመጥኑትን ማንነቶች ሰጥቼው ነበረ ስቀርበው ግን ፍፁም የተለየና ምርጥ ሰው ነው ።!!!!!!!
ከደቂቃዎች ቡሀላ ሆስፒታሉ ደረስን ። ለሊት ሆኖ ራሱ ውስጡ ቀን ነው የሚመስለው ነርሶች አሉ ፅዳቶች አሉ የደመቁ መብራቶች ብቻ ሁሉም ነገር አለ ።
ቀጥታ ወደ ቤኪ ክፍል ሄድን ።
ከፍተን ስንገባ አለምዬና ቤኪ እጅ ለእጅ ተያይዘው የሆዳቸውን እያወሩ ይመስላሉ ።
ክፍሉ ውስጥ ሁለት የተለያየ አልጋ ተጨምሯል አንዱ ላይ ጄሪ አንዱ ላይ ያቤፅ ልጥጥ ያለ እንቅልፍ ላይ ገብተዋል ።
ከፍተን እንደገባን ሁለቱም እየተመለከቱን በአንድ ድምፅ
" ቆያችሁ እኮ " አሉን ።
እኔና ሰለሞን ደግሞ ተያይተን ሳቃችንን ለቀቅነው ።
እነሱ በግርምትና በጥያቄ ፊት ትክ ብለው ሰከሩ እንዴ በሚመስል አስተያየት ያዩናል ።
እነሱ ምን አስበው እንደዛ እንደሚያዩን ስናስብ ደግሞ የበለጠ መሳቃችንን ቀጠልን ።
የኛ ከት ብሎ መሳቅ የተኙትን በአንዴ ቀሰቀሳቸው ።
ከተኙበት ቀና ብለው ፍጥጥ ብለው ተመለከቱኝ የዛኔ የምር ከአቅሜ በላይ ሆነብኝና መቆም እስኪያቅተኝ ድረስ ከትትትትት ብዬ ሳኩኝ ።
በሁለታችን ያልታወቀ የሳቅ ምንጭ አራቱም ግራ በመጋባት ቆመው እያዩን ነው ።
ከዛ በላይ እነሱን ግራ ላለማጋባት ብለን እንደምንም ወደራሳችን ተመልሰን በየተራ ደህና መሆናችንን ነገርናቸው ።
" አባ ምን ተፈጥሮ ነው ንገረኝ " አለ ቤኪ
ግንባሩን እየሳምኩኝ ምን ይፈጠራል ምን አስደነገጠክ ግን ደህና ሆንክልኝ አ አልኩት ።
" እኔ ሀያ ሰባት አመት ሳቀው እንደዚህ ሲስቅ አይቼው አላውቅም እኮ " ብላኝ በትንሹ ፈገግ ብላ ተመለከተችኝ።
ከኔ ጋር መዋል እንደዚህ ነው እንግዲህ ብዬ ራሴን ቆለል አደረኩኝ ።
ስንወጣ ከነበረበት ነገር አንፃር እንደዚህ ስላልጠበቁ ይመስለኛል ግን እንደዚህ የሚሉኝ እና ሁሉም ሰላም እንደሆነ አሳመናቸው ።
አለምዬ አቅፋ ግንባሬን እየሳመች
" ከድሮም እኮ መልአክ የሆንሽ ልጅ ነሽ የኔ ልዕልት " አለችኝ ።
ከዛም ትንሽ እያወራን ተሳሳቅንና ተከፋፍለን ተኛን ።
በጣም ደክሞኝ ስለነበረ ወዲያው ነው እንቅልፍ የወሰደኝ ።
ከተኛሁ ቡሀላ ግን ጓ የሚል ድምፅ ከእንቅልፌ ቀሰቀሰኝ ............
✍✍✍fidel .......
.............ጥያቄ ጠየቀኝ ። በሰአቱ ማለት ምናምን ብዬ ጥያቄውን ማራዘም አልፈለኩኝም ።
እኔም የዋዛ አይደለሁምና ደቂቃዎችን ሳላባክን
ተጣጥፌ ምርኩዝ እሆነዋለሁ ብዬ የሚገርም መልስ ሰጠሁኝ ።
በመልሴ የተደነቀ የሚመስለው ሰለሞንም ትክ ብሎ ተመለከተኝ ።
እኔም ትንሽ ግራ መጋቢትን ስለፈጠረብኝ ግን ለምን እንዲህ አይነት ጥያቄ ጠየከኝ ብዬ በመርማሪ ኤይታ አየሁት ።
በሰአቱ እሱም ሊነግረኝ የፈለገ አይመስልም ነበር ወዲያው አስተናጋጁ ቆንጆ ቆንጆ ሲታዩ በአይን የሚያጠግቡ ምግቦችን ከዚ በፊት አይቼ በማሚማቀው አቀራረብ ለየት ባለ ሁኔታ ማቀራረብ ጀመሩ ።
አንደኛ ንፅህናቸው ሁለተኛ የእቃቸው ጥራት መስተንግዷቸው .......... ብቻ የማገርም ነገር ነው ያየሁት ።
በህይት ውስጥ በተደጋጋሚ እያየ የመጣሁት ነገር ቢኖር ብር እያለሽና ሳይኘኖረሽ የሚፈጠሩ ልዩነቶችን በደንብ ማየትና ማስተዋል ችያለሁኝ ።
ሰው የዋለበትን ይመስላል ይባል የለ እኔም ከደህና ሰው ጋ በመዋሌ እነሱ የሚያገኙትን ፍቅርና እንክብካቤ ማየት ቻልኩኝ ።
ቤቱን ለየት ከሚያረገው ነገር አንዱ ደግሞ ሁሉም በተቀመጠበት ወንበር አቅራቢያ ፅድት ያሉ የእጅ መታጠቢያዎች አሉ ።
ተነስተን በየተራ ታጥበን ተመልሰን ቁጭ አልን ።
ደስ የሚለው የቤኪ አባት እንደ ሀብቱና እውቅናው አይደለም ቅድሚያ ለፈጣሪ ይሰጣል ።
ከመጀመራችን በፊት ፀሎት አድርጎ አማትቦ ቆርሶ ከእጁ ሰቶኝ ምናምን መብላት ጀመርን ።
በጣም የሚጥሙ ምግቦችን ከአድካሚና አሰልቺ የድካም ቀን ቡሀላ ጥግብ እስከምሕ ድረስ በላሁኝ !!!
በልተን ጨርሰን ምግቡ ተነሳስቶ እስኪያልቅ ድረስ አንድም ቃላት አልተመላለስንም በዝምታና በእርጋታ ተመግበን ጨረስን ።
እንደ ማወራረጃ ስፔሻል ጁስ መጣልንና የዛኔ ወሬያችንን ለመቀጠል ተመቻቸልኝ ።
ለማወቅና ለመስማት በጣም ጓጉቼ ነበረ !!!!!!
ፊቴንጰበደንብ ተመለከተና ፈገግ ብሎ
" ለማወቅ በጣም የቸኮልሽ ምመስለኛል " አለኝ ።
አዎ በጣም ሁሉንም ነገር ንገረኝ ። በመጀመሪያ ግን ለምንድነው እንደዛ አይነት ጥያቄ የጠየከኝ ????
ቤኪ ምኑን ታሞ ነበር እንዴት ዳነ?? ብዬ በጥያቄ አጣደፍኩት ።
" የዳነው በፈጣሪ እርዳታ ነው ።!!!!!! ሌላውን ራሱን መጠየቅ አለብሽ መንገር ከፈለገ ይነንገርሽ እኔ ልነግርሽ አልፈልግም "" አለችኝ ።
" ለማንኛውም ግን እኔ ክፉ ሆኜ ወይም የልጄን ስሜት መረዳት ከብዶኝ አይደለም !!!!
ማፍቀርን በጀንብ አውቀዋለሁ !!!!
ከፍቅር ለመለየት መሞከርም ጥፋት መሆኑን በደንብ አውቃለሁ !!!!!
እንደምታቂው ቤኪ በጣም ቆንጆ ተማሪ ነው !!! ( የማይካድ እውነታ ) በዛ ላይ የሀብታም ልጅ ነው ተብሎ ነው የሚወራበት ።
የሚገርምሽ በሱ ምክንያት የኔ ልጅ መሆኑ ሳያስጠላው ሁሉ አይቀርም !!!
ለማንኛውም ግን እሱ ደህና ሲሆን ሊነግርሽ ከፈለገ ሙሉውን ይነግርሻል " አለኝ ።
ከዛ በላይ ላስጨንቀው ስላልፈለኩኝ እሺ በቃ ብዬ ዝም አልኩኝ ። ድንገት ስልኩን አውጥቶ ያቤፅ ጋር ደወለለት ።
በአንድ ጥሪ አነሳው ።
" አቤት ጋሼ " አለ ፈጠን ብሎ።
" አለም ተኛች እንዴ ፍቅረኛህስ ምን አዲስ ነገር አለ " አለው ።
" አለምዬ እና ጄሪ ተኝቸዋል ። ቤኪ ደግሞ ፍጥጥ ብሎ ቁጭ እንዳለ ነው ተጨንቋል።
ማለት ከሄዳችሁ ጀምሮ ስላልደወላችሁ ... " ብሎ የተንጠለጠለ ሀሳቡን ተወው ።
" እሺ እሱ ደህና ነው አይደል " አለው ።
" አዎ ደህና ነው " አለ ።
ስልኩ ስፒከር ስላረገው ሁሉንም እየሰማሁ ነበረ ።
" አትመጡም እንዴ ?" አለ ያቤፅ ። የእኔም ጥያቄ ስለነበረ እሰይ ነው ያልኩት ።
" አይ አንመጣም ዛ "" ሲለው ልቤ ቀጥ ድው ነው ያለችብኝ ...........
✍✍✍fidel......
🙋♀🎬🎬 ክፍል አርባ አምስት
......... በድጋሜ በእናቴ ስልክ ተደወለ ። በሰአቱ ስልክ ማውራት ቀርቶ ወደ ጎን አርጎ ማንሳትም ከበደኝ ።
እጄ መንቀጥቀጡት ያስተዋለው የቤኪ አባት ዞሮ መጥቶ ስልኬን ተቀብሎኝ አንስቶ ላውድ ላይ አደረገው ።
" ሄሎ እናትዬ " አለች ። የእናቴን ድምፅ ስሰማው በአንዴ ተረጋጋሁኝና ስልኩን ተቀብዬው
እማ ደህና ነሽ ??? አልኳት ።
" አዎ አበባዬ ደህና ነኝ እሺ አታስቢ የኔ ቆንጆ " አለችኝ ።
እማ ምን ተፈጥሮ ነው ንገሪኝ እባክሽ ጎዳሽ እንዴ እ ምን አርጎሽ ነው ??? አልኳት መጥፎ ነገር ለመናገር ተዘጋጅቼ ።
" አታስቢ የኔ ወርቅ ምንም አላረገኝም ሰክሮ መቶ ትንሽ ተናገረኝ ታቂ የለ በሆነ ባልሆነ እንደሚከፋኝ " አለችኝ ፈገግ ያለ ድምፅ እያሰማችኝ ።
በሆዷ ብዙ ቁስልና ህመም የያዘች ይመስል በሆነ ባልሆነው ነው እንባዋ የሚፈሰው ከዛ ለምን ታለቅሻለሽ ስላት ከት ብላ ትስቃለች !!!????።
በዛች ቅፅበት በጣምምምም ብዙዙ ነገር አስቤ ስለነበር በረጅሙ ተንፍሼ እንዳስደነገጠችኝ ነገርኳት ።
እሷ ደግሞ ድርቅ ብላ ደህና መሆኗን እንዳምን አድርጋ አወራችኝ !!
እኔም በቀላሉ አመንኳትና ነገ እመጣለሁ ብዬ ቃል ገብቼላት ስልኩን ዘጋሁትና መኪናውን ተደግፌ በረጅሙ ተነፈስኩኝ ።
ከእኔ ባልተናነሰ ሁኔታ ተጨንቆ የነበረው ሰለሞንም በአንድ እጁ ወገቡን ይዞ በአንድ እጁ ደግሞ ከረቫቱን እያላላ ተነፈሰ ።
ምን ያህል ሊረዳኝ ዝግጁ እንደነበረ በአይኔ ያየሁት ነገር ስለሆነ ከተደገፍኩበት ቀና ብዬ
በጣም ነው የማመሰግነው እናም በጣም ይቅርታ አልኩት እጆቼን እያሻሸሁኝ ።
"ምንም አይደል ልጄ ነይ ከብርድ ላይ ጊቢ ወደ ውስጥ " ብሎኝ ሊገባ ሲል
የቤኪ አባት ብዬ ጠራሁት ።
ለምን እንደሆነ አላቅም ሰለሞን ማለትም አንቱ ማለትም ይከብደኛል ።
በጣም ወጣት ነዎ እኮ ቤኪን በስንት አመት እንደወለደውም አላውቅም ።
እሱም ወደኔ ዞር ብሎ ምነው በሚል ፊት አየኝ ።
ትንሽ ፈጣጣ ሆንኩኝ መሠለኝ ፈገግ ብዬ
አንዴ እንደ አባት ልቀፍህ ?? ብዬ በአሳዛኝ ፊት አየሁት ።
በነገራችን ላይ እንዲህ ያልኩት ያለ ምክንያት አይደለም !!!
ከደቂቃዎች በፊት ልጄ ብሎ ጠርቶኝ ነበረ ።
በምላሹ እሱም ፈገግ አለና እጁን ዘረጋልኝ እኔም ቶሎ ብዬ በዛ ግርማ ሞገስ ባጀበው እቅፍ ውስጥ ገባሁኝ !!!
የምር በጣም ደስ ብሎኝ ነበረ !!!! በትክክለኛ አባቴ እንደታቀፍኩኝ ነው የተሰማኝ ሁላ !!!!!
ምናለ እኔም እንደሱ አይነት አባት በኖረኝ ብዬ እንድመኝ አደረገኝ !!!!!!!
ከዛ እንባዬ መምጣት ሲጀምር አንዴ ከጀመረኝ ማቆሚያ የሌለኝ መሆኔን ስለማውቅ ቶሎ ከእቅፉ ወጥቼ በጣም አመሰግናለሁ ብዬ አሳጠርኩት ።
" ነይ ወደ ውስጥ ግቢ " ብሎኝ እኔን አስቀድሞ ተከትሎኝ መጣ ።
ከዛ ተመልሰን ቦታችን ጋር ተቀመጥን ።
ወዲያው አስተናጋጁ መጣና እሱን አየው ።
በአይኑ የአወንታ ምልክት እየሰጠ አንገቱን ሲነቀንቀው ወደኔ ዞር ብሎ " ምን ይምጣልሽ እመቤት " አለኝ በትህትና ጎንበስ ብሎ ።
ምን እንደሚባል የማላቀው እኔ ዞር ብዬ ሰለሞንን አየሁት ።
በአንድ እይታ ሰውን መረዳት የሚችል ሰው ነው !!!!
ጎንበስ ብሎ ወደ ሜኑ አየና የሆነ የሆነ ነገር ብሎት አስተናጋጁ ሄደ ።
ሰውዬው እስኪመለስ ልብ አንጠልጣይ ታሪኩን ለመስማት ጉጉት አደረብኝና አላስችል ቢለኝ ለወሬ ማስጀመሪያ
እና ቤኪ ምኑን አሞት ነው ? ብዬ ወደ ወሬው መለስኩት ።
ለትንሽ ደቂቃዎች በዝምታ ተውጦ አሰበ አሰበና ጥልቅ ሀዘን ውስጥ ገባ ።
እኔ አይን አይኑን እያየሁኝ ምላሽ እየጠበኩ እንደሆነ አሳየሁት ።
ያየኛል አየዋለሁ ያየኛል አየዋለሁ ።።!!!
ከደቂቃዎች መፋጠጥ ቡሀላ ግን ሰለሞን ጉሮሮውን እንደመጠራረግ አለና
" ልጄ በጣም ታሞብኝ ነበር በጣም " አለኝ ።
ምኑን ታሞ ነው ይሄን ያህል እ ምን ሆኖ ነበር ?? አልኩኝ ይበልጥ ለማወቅ እየጓጓሁ ።
" እስኪ ከዛ በፊት አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ እውነታውን ትነግሪኛለሽ ?" አለኝ ።
እሺ ደስ ይለኛል ምንድነው አልኩት መልሼ
" አያድርገውና ልጄ በረከት አይኖቹ ማየት ቢያቆሙ ምን ታደርጊያለሽ ??3" የሚል እጅግ ግራ የሚያጋባ ጥያቄ ጠየቀኝ ???.........
✍✍✍fidel....
.............. ቦታውን አሌቀውም የት እንዳለን እዚህ ምን እንደምናደርግ እንኳን አላውቅም የቤኪ አባት ስለሆነ ብቻ ተከትዬዋለሁ ።
የመኪናውን በር እንደከፈተ
" ውረጂ !" ብሎ ዝም ብሎ ተመለከተኝ ።
እዛ ድረስ ተከትዬው መጥቼ አልወርድም ብል ጥቅም አልባ ንግግር ነው ብዬ ስላመንኩ ቀጥ ብዬ ወርጄ ከመኪናው ጋር ተለጥፌ ቆምኩኝ ።
የት እንዳለን አላውቅም ??? ከፊት ለፊቴ ሆቴል እንዳለ ብቻ ይታየኛል !!!
ግን ጭር ያለ እና በዝምታ የተዋጠ ቤት ነው ።
የመኪናውን በር ዘጋውና መሄድ ጀመረ ።
እኔ እዛው ቆሜ ቀረሁኝ ።
" ነይ ጊቢ " አለኝ ዞሮ
ግን እዚህ ምን እናደርጋለን ? አልኩት እንደምንም ተዳፍሬ ።
" ምን እንዳላደርግሽ ፈርተሽ ነው እኔ ሰለሞን እኮ ነኝ አፈየበለጠ አታናጂኝ ክብር እየሰጠውሽ ነው የሌለኝን ትዕግስት አታስጨርሺኝ "አለኝ ጭምድድ ባለ ፊት ።
በፈጣሪ ስም ቀይ ስለሆነ ትንሽ በተናደደ ቁጥር ፊቱ እንደ ቲማቲም ይቀላና ግንባሩ ይጨማደዳል !!!!
ብቻ በጣም ነው የሚያስፈራው ምነው ባልተናገርኩ እንድል አደረገኝ !!!!
ተጨማሪ ቃላትን ሳላባክን ተከትዬው ወደ ውስጥ ገባሁ ።
የሚገርማችሁ ሌሎች ቦታ ካየሁት በላይ የሆነ ክብርን ገና ከበር ማየት ጀመርኩኝ ።
ገና ከበሩ ሞቅ ያለ ሰላምታ ጎንበስ ቀና የበዛበት መስተንግዶ ....... ብቻ ብዙ ነገር ። ...!!!!!!
የዛኔ የምር አልቻልኩም !!! ሀብታሞች እንዲህ ነው የሚኖሩት ?? እንድል አደረገኝ ።
በዛውም ደግሞ ከባለ ስልጣን ልጅ ጋ ማን ፍቅር ውስጥ ጊቢ አለሽ !!! እያልኩ ራሴን ወቀስኩኝ ።
ወዲያው ደግሞ መልሼ በዚህ ልክ የሀብታም ልጅ ሆኖ እኛ ትምህርት ቤት ማን ግባ አለው ??? እያልኩኝ ጥፋቱን ወደ ቤኪ አዞረዋለሁ ።
ጨዋታው ቀጠለ ለብቻችን ተቀመጥን ። አስተናጋጁን ቀና ብሎ አይቶት አንድ እጁን ከፍ አድርጎ መዳፎቹን ዘርግቶ አጠፋቸው ።
ወዲያው አስተናጋጁ ጎንበስ ብሎ ተመልሶ ሄደ ።
ሁሉም ነገር ለበጎ ነው ይባላል ምን አልባት ይሄን ህይወት ሊያሳየኝ ነው እንዴ ??!!ብዬ በሆዴ እያወራሁ ብቻዬን እስቃለሁ !!!!
" እሺ እንቀጥል "አለኝ
እ ምኑን ማለቴ እሺ አልኩኝ ከገባሁበት የልጅ ቀልድ ለመውጣት እየታገልኩኝ።
" አውቃለሁ አንተዋወቅም ቁጭ ብሎ ለማውራትም ገና ነን ግን ስለ ቤኪ በደንብ እንድታቂልኝ እፈልጋለሁ !!! እኔ ክፉ ሆኜ አይደለም ግን ልጄን ይነጥቁኛል ብዬ እፈራለሁኝ አንቺ ስለሱ ምን አታቂም አምሮ ተውቦ ልዑል ሆኖ የምታይውን በረከትን ነው የምታውቂው ተሳሳትኩ ??" አለኝ ከላይ የለበሰውን ኮት አውልቆ ወንበሩ ላይ እያስቀመጠ ።
ቃል ማውጣት አቃተኝ መሠለኝ በአወንታ ብቻ አንገቴን እየነቀነኩኝ ።
" እሺ ለማንኛውም እዚ ያመጣሁሽ እንድናወራ ስለፈለኩ ብቻ ነው ።
አሁን ላይ አንቺ ፍቅር ውስጥ የከተሽው በረከት ማለት እኔና ባለቤቴ ብዙ ያየንበት ብዙ ያጣንበት ብዙ ያገኘንበት ልጃችን ነው ።
ከእኔ ጋ ብዙ ባንገናኝም አለምዬ ብዙ ነገር እንደምታቂ ነግራኛለች ።
እና አሁን ያሉት ማንኛውም ነገር ድሮ ላይ አልነበረም ።
እኔና እናቴ ( አለምዬን ማለቱ ነው ) ከቤት ስንጠፋ አንድ ነገር አልነበረንም !!.
ገና ልጅ እያለን ነው በፍቅር የወደቅነው ።
ቤተሰቦቻችን በከባዱ ሲያስፈራሩን ሁሉንም ለመቻል ወስነን ከቤት ጠፋን ።
ሁለታችንም በየሆነ ቦታ ተበታትነን ስራ ለምስራት ሞከርን ።
እናቴ አሁን እንደምታያት አልነበረችም ተሞላቃ ያደገች የሀብታም ልጅ ትመስላለች እንጂ በብዙ የተፈተነች ሴት ናት ።
በሰአቱ እኔ ስራ ሳጣ እሷ እየሰራች በምታመጣው ብር ለመጀመሪያ ጊዜ በት ቸከራይተን ኬሻ አንጥፈን ለመተኛት እንድበቃ አደረገችኝ ።
በሰአቱ በትምህርቴ በጣም ጎበዞ ተማሪ ነበርኩኝ ።
የመማር እድሉን ሳላገኝ ቀርቼ ነበር ። ነገር ግን ሰው ቤት እየሰራች ትምህርቴን እንድጨርስ አደረገችኝ ።
በጣም በትልቅ ነጥብ አለፍኩኝ ።
ብታምኚም ባታምኚም ዩንቨርስቲ ገብቼ ትምህርት ጨርሼ እስክወጣ ድረስ በፅናት ብር እያጠራቀመች ጠበቀችኝ ።
ያ ነገር ለኔ ብርታት ሆነኝ ።
በተማርኩበት ስራ እስካገኝ ድረስ ጎን ለጎን መስራት ጀመርኩ ።
አንድ ላይ ሆነን እየኖርን ልጅ መውለድ ተስኖን ነበር ።
እኔ ደግሞ በጣም ወንድ ልጅ እመኝ ስለነበር ቅዱስ ሚካኤል ደጅ ሄጄ ወንድ ልጅ እንዲሰጠኝና ካሳካልኝ ብዬ መሳል የሌለብኝን ስለት ተሳልኩኝ ።
ፈጣሪ ይመስገን በዛው ወር አረገዘችና በመጀመሪያ ወንድ ልጅ ሰጠኝ ።
የሱ መወለድ ያቺ ጠባብ ቤታችንን ስለሞላልን በረከት ብዬ ስም አወጣሁለት ።
ከተወለድ አራት አመቱ አካባቢ ማታ በሰላም ተቃቅፈን ተኝተን ለሊት ላይ ድንገት ትንፋሹ ተቆራረጠች " ሁኔታው ትዝ ብሎት መሰለኝ እንባው መውረድ ጀመረ ።
ለምን እንደሆነ አላውቅም ወንድ ልጅ ሲያለቅስ ማየት በጣም ከባድ ነው !!!
አባት የለኝ ይሆናል ግን አባትነትን በደንብ አነውበት !!!!!
ልክ እንደ ከዚ ቀደሙ ምን አለ አባት ቢኖረኝና የአባትነት ፍቅርን ባየው ብዬ ተመኘው !!!!!( ለካ አባት አለኝ 🧐🧐)......
አንዱ አባት ልጁን ይክዳል አንዱ ለልጁ እንባውን ያፈሳል ....... ህየወት ተቃራኒ ናት !!!!
ምን ማለት እንዳለብኝም ሳላውቀው አፌ ላይ የመጣልኝን
ዋናው አሁን ላይ ከጎንክ ነው ለምን ታለቅሳለክ ብዬ ታሪኩን እንዲቀጥልልኝ ሰፍ ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ ።
ለመረጋጋት አየር እየሳበ እያለ እናቴ ደግማ ደወለች ።
አሁንም ከጎን ነክቼ ዝም ልለው ስል የእናቴ መሆኑን አየና
" አንሺው አንሺው እኔም ለመቀጠል ልዘጋጅ" አለኝ ፈገግ ብሎ ።
ውጩ እንደሆንኩ ካወቀች ጥያቄ ታበዛለች ብዬ ለመዋሸት ድምፄን ቀንሼ ሄሎ እማ ስላት ዝም አለችኝ ።
ሄሎ ሄሎ እማ ስል የሚያለቅስ ድምፅ ሰማሁኝ ።
ከደቂቃዎች በፊት ድምፄን መቀነሴን ረስቼው በድንጋጤ ከተቀመጥኩበት ብድግ ብዬ እማ ሄሎ ሄሎ አልኩኝ በጩኸች ።
ምንነቱንም ያላወቀው የቤኪ አባት ከኔ እኩል ከተቀመጠበት ተነስቶ ያየኛል ።
" ሀ ሀ ሀ ሀ ...." የሚስቅ የወንድ ድሞፅ ።
የአባቴ ድምፅ ነበር እናቴ እያለቀሰች እሱ እየሳቀ ??????
ነገሮችን አሰብኩና እየሮጥኩ ከሆቴሉ ወጣሁ ። እሱ ደግሞ
" ምንድነው ምን ተፈጠረ " እያለ ይከተለኛል ።
እናቴ እናቴ ችግር ውስጥ ናት አልኩ እየተርበተበትኩኝ ።
" እሺ መኪና ውስጥ ጊቤ እንሄዳለን ፍጠኚ " ብሎኝ ወደ መኪናው ስንገባ ድጋሜ በእናቴ ስልክ ተደወለ .........
✍✍✍fidel........
🙋♀🎬 ክፍል አርባ አራት
........ልጄን የወጋውና የስለት ልጄን ደም ያፈሰሰው ያንቺ አፍቃሪ ነው !!!
የዛ ቀን ምሽት በዛ በምሽት ምን እንዳወራችሁ አላውቅም ልጄን እንዲጎዳ አደረግሽብኝ ለዛ ነው አሁን ገባሽ " አለኝ ።
ኢዩኤል እንዲህ ያደርጋል ብዬ አልገምትም አላስብምም ነበረ !!!
ቀና ብዬ ጄሪን ተመለከትኳት ከኔ በላይ ደንግጣለች እጆቿን አፏ ላይ ደራርባ በጥፋተኝነት ስሜት ተውጣ ፈዛ እያየችኝ ነበረ ።
እውነት ለመናገር በሷ አልተናደድኩም ምክንያቱም እሷ ምንም አታቅም በዛ እርግጠኛ ነኝ ።
በሰአቱ ልመልስ የምችለው ነገር ስለሌለ በዝምታና በጥፋተኝነት ስሜት ሁሉንም አየዋቸው ።
የውስጤን የተረዳችኝ አለምዬም አንዴ እኔን አንዴ ባለቤቷን ለማረጋጋት እየሞከረች ነው !!
እኛ እዛ ቆመን ስንጨቃጨቅ ቤኪ በዝምታ ሲያዳምጥ ቆየና
" አባ ራሴ ነኝ ነገር የፈለኩት ምንም ነገር ቢፈጠር እሷ ጥፋተኛ አይደለችም እሷን አትናገርብኝ " እያለው ነበር ።
በሰአቱ ምን ያህል እንደሚወደኝና እንደሚያስብልኝ ለማወቅ ቀላል ነበር !!!!!
መጥፎ ሁኔታ ውስጥ ከትቼው ራሱ በዛ ሁኔታ ላይ ሆኖ ስለኔ እያሰበ ማየት ለኔ እንደ ጥንካሬ ነው !!!! እልና...
ነገር ግን የቤኪን አባት ሁኔታ ሳይ የጥፋተኝነት ስሜቴ ያገረሽብኝና ሽምቅቅ እላለሁ!!!!!
ቆመን እየተፋጠጥን እያለ ዶክተሩ ከነርሷ ጋር መጣ ።
" መድሀኒት ሊወስድ ነው እና ትንሽ ረፍት ማድረግ አለበት ብቻውን ተውት ትንሽ ደቂቃ " አለ ።
የሚገርማችሁ ዶክተሩ የቤኪን አባት ሲያወራ ያለው ክብርና እርጋታ በጣም የሚገርም ነው !!!!!!! ለነገሩ እንዴት አያከብረው ........
ለማንኛውም ግን ተያይዘን ከዛ ክፍል ወጣን በሩ እስኪዘጋ ድረስ ቤኪ የሆነ አስተያየት እያየኝ ነበር !!!!
እንደወጣን ጄሪ ፊቴን እስካዞር ጠብቃ
" አቡ በጣም ይቅርታ እሺ ለዚ ሁላ ጣጣ እኔ ነኝ ጥፋተኛ " አለችኝ ።
እሷን ቀለል እንዲላት ብዬ በሰአቱ የሌለኝን ፈገግታ እያሳየዋት
አንቺ ምን አደረግሽ ያምሻል እንዴ ቀውስ ደሞ ለበጎ ይሆናል ብዬ ፈገግ አስባልኳት ።
ወዲያው አለምዬ ወደኔ መታ አቀፈችኝና
" እንዳትከፊ እሺ ብዙ የተፈተንበት ልጃችን ስለሆነ የሱ ደካማ ጎን ስለተነካበት ፈርቶ ነው እሺ " አለችኝ ።
የዛኔ ከልቤ ስለ ቤኪ የማወቅ ጉጉቴ ጨመረ ።
እስከዛሬ ስላለፈ ህይወቱ ስለቤተሰቡ ስለ ሀብታቸው ...... ስለምንም ነገር አስቤም ሆነ ጠይቄው አላውቅም !!!!!
አባቱንም ከልቤ ተረዳሁት !!!!
አለምዬ ወደ ባለቤቷ ተመልሳ ከሱ ጋር ማውራት ጀመረች ።
የዛኔ ያቤፅና ጄሪ መተው በየተራ እንደ እህትና ወንድም አቅፈው አባበሉኝ ።
" ሰሌ በልጁ ቀልድ አያቅም !! በርግጠኝነት የምነግረሽ ነገር ቢኖር ቤኪ ምን ያህል እንደሚወድሽ ስለሚያውቅ ነው እንጂ ሌላ ሰው ቢሆን የነካው አንድ ደቂቃም አይገኝም !!!!!
ኢዩኤል ደግሞ ከጊቢም ለቆ ጠፍቷል የት እንዳለ ማወቅ ስላልቻለ ነው ዝም ያለው " አለኝ ያቤፅ ቀስ ብሎ ።
እስካሁን ካየዋቸውና በንግግሮች እንደተረዳሁት ከሆነ ቤኪ በሆነ ችግር ላይ ያለፈ ሰው እንደሆነ ግልፅ ነው !!!!
ለቤቱ ምን ያህል አስፈላጊና ውድ ልጅ እንደሆነ ገባኝ !!!
ብዙም ሳይቆይ ከአለምዬ ጋር ምን እንዳወሩ ባላቅም የቤኪ አባት ወደኔ መጣ ።
ገና አጠገቤ እንደደረሰ ሌላ ነገር ከማውራቱ በፊት ብዬ
ምንም ነገር አላወኩም ነበር በጣም ይቅርታ አልኩኝ አይኔን መሬት ላይ ተክዬ ።
ለትንሽ ደቂቃ በዝምታ ተመለከተኝና
" ነይ ተከተይኝ " አለኝ ። ቀጣይ ምን እንደሚፈጠር ያላወኩት እኔ በድንጋጤ ቀና ብዬ በየተራ ተመለከትኳቸው ።
የአለምዬን ፊት ሳየው ፍፁም የተረጋጋ ፊት ስለነበረ ትንሽ ተረጋጋሁ ።
በሰአቱ ሌላ አማራጭ የለኝምና እሺ ብዬ መንገድ ስጀምር ጄሪም አብራኝ ለመምጣት ስትሞክር
" አይ አይሆንም ሁለታችን የምንጨርሰው ነገር ነው " አላት
" ግን እኮ ...." ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ ያቤፅ ጎተት አድርጎ ወደ ራሱ ሳባትና ቀስ ብሎ አትጨነቂ አላት ።
ከዛ ትልቅ ሆስፒታል ስንወጣ በእርግጠኝነት ከአራት ሰአት በላይ ሆኗል ።
አለምዬ ለክፉ አትጥለኝም ብዬ እንጂ ማንን አምኜ በዛን ሰአት ከተናደደ ሰው ጋ እወጣለሁ !!
ገና በሩን ጨርሰን ዞር እንዳልን ሹፌሩ እየሮጠ መቶ በሩን ሲከፍት የቤኪ አባት እጁን ዘረጋ ።
የሚገርመው ሰውዬው ፈጥኖ በእጁ የያዘውን የመኪና ቁልፍ አውጥቶ ሰጠው ።
ምን አይነት መግባባት እንደሆነ አላቅም ????
እጁን ሲዘረጋ ምንድነው ብዬ በግርምት እያየሁ እያለ እነሱ ተግባብተዋል !!!
ከዛ እሱ መኪናውን ውስጥ እንድገባ አርጎኝ ወዴት እንደሆነ ባላቅም መሄድ ጀመረ።
እናቴ ጉዷን አልሰማች በዛ ሰአት ትደውላለች ። እኔ በዛ ማንሳት ችግር ነው ብዬ ዝም አልኩኝ
ከደቂቃዎች ጉዞ ቡሀላ ደረሰን ወረደና በሩን ከፍቶ ውረጂ አለኝ ። ቦታውን አላቀውም ......
✍✍fidel......
🙋♀🎬🎬🎬 ክፍል አርባ ሶስት
............ አሉኝ ። በፈጣሪ ስም እንዴት እንደደነገጥኩ እኔ ነኝ የማቀው !!!
ስልኩን ከአባቱ የበለጠ ወርውሬ የት እንደምሄድም ሳላውቅ በዛ ምሽት ዝም ብዬ ወጣሁኝ ።
" ቆይ ተረጋጊ ተረጋጊ " ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረኝ ።
የሀብታም ቅንጡ ስልኩን እየነካካ ከቢሮ ወተን እሱን እየተከተልኩ ስሄድ ጭራሽ ሹፌር ሳይቀር አለው ።
በሰአቱ እንደዚ አይነት ነገር አላስብም ነበር እንጂ ይሄ ቅብጠት ነው እል ነበር !!!!
ብቻ ግን ሰሎሞን ቤኪን ምን ያህል እንደሚወደው እንደሚያሶብለትና እንደሚጨነቅለት ያወኩት የዛን ቀን ነው !!!!!
ወንድ ልጅ በአደባባይ አያለቅስም የሚል ተራ ተረት ይዞት እንጂ እንባው አቅሮታል።
እኔ ሴት በሁሉም ቦታ ማልቀስ ህብረተሰቡ ፈቅዶላታልና እንባዬን መቆጣጠርም አልቻልኩኝም !!!!!
በሰአቱ የሰውዬው ንግግር
" አፍጥነው ንዳው ፍጠን "" እያለ በተደጋጋሚ ይጮክበታል ሹፌሩ በሚያስፈራ ፍጥነት እየበረረ ነው ማለት ይቻላል !!!
በሰአቱ ራሴን ላረጋጋ እሱን ላረጋጋ ግራ ገባኝ ።
ለሰው ቅድሚያ መስጠት የህይወት መርሄ ስለነበረ እንደምንም ራሴን አሳምኜና አረጋግቼ
ቤኪ ለሚወዳቸው ሰዎች ሲል ይጠነክራል ምንም አይሆንም ብዬ ለማረጋጋት ስሞክር አመድ የለበሰውን ፍም ነካክቼ ቀሰቀስኩት
" አንቺ እንደምታስቢውና በፊልም እንደምታይው ቀላል አይደለም የተወጉ ሰዎች ሁላ ይድናሉ ማለት አይደለም ገሀድ አለም ላይ እንዳለሽ አትርሺ !!!!
ልጄ የሆነ ነገር ከሆነ ግን እመኛኝ በከባዱ ነው የምጎዳሽ !!!!" አለኝ በሚያስፈራና በተናደደ ፊት !!!
የተናገረው ንግግር ልክ እንደሆነ ገብቶኛል !!!
ነገር ግን ቤኪ የተጎዳው በኔ ምክንያት አይደለም እኮ ለምን እኔ ላይ ይሄን ያህል ተናደደ የሚለው ጭንቀት ሆኖብኛል !!!!
ስንደርስ ግን ባለፉት ቀናቶች የነበረበት ቦታ ሳይሆን ትክክለኛ ሆስፒታል ነው የገባው ???
በቃ በጣም ታሞ ነው ብዬ በስንት ስቃይ የመለስኩትን እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩኝም !!!!
የቤኪ አባት ሲሄድ በዝምታ እሱን እየተከተልኩ ገባሁኝ ።
እንዴት እንዳወቀ ባላቅም ቀጥታ ቤኪ ያለበት ክፍል ውስጥ ሄድን ።
እጁ ላይ የተለያዩ ነገሮች ተሰካክተው አፉ ላይ መተንፈሻ ተደርጎ ምናምን ....በህይወቴ ላየው በማልፈልገው ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ተኝቶ አየሁት ።
እሱን እያየሁ እንዳላጣው እየፈራሁ አለቅሳለሁ በዛው ሰአት እናቴ ደጋግማ ትደውላለች ???? በመሀል ላብድ ምንም አልቀረኝም ማለት ይቻላል !!!!!!!
የቤኪ አባትም በጣም ፈርቶ ምን እንደሚያደርግ ራሱ ግራ ገብቶት ሲንቆራጠጥ ቆይቶ ዶክተሩ ሲመጣ
" ተናገር " አለ ቀጥታ ።
" አሁን ደህና ነው ደም በብዛት እየፈሰሰው ስለነበር ለእርሶ መደወል ነበረብን እና በፍጥነት ደም የሚሰጠው ሰው ያስፈልጋል " ብሎ ሀሳቡን ሳይጨርስ
እኔ እሰጣለሁ ከዚ በፊት አበረን ተመርምረናል የደም አይነታችን አንድ አይነት የደም አይነት ነው ያለን እና በሽታም የለብኝም ምንም እ ቶሎ ስጠውና አድነው !!! አልኩት በአንዴ እጄን ሰብስቤ ደም ለመስጠት እየተዘጋጀሁ ።
ዶክተሩ አንቱ እያለ እኔ አንተ ብዬ ጭራሽ በቁጣ ማውራቴ ትዝ ሲለኝ መቀራረባችን ይሆናል ብዬ ለራሴ ነግሬው ዝም አልኩኝ ።
ወደ ውስጥ ገብቼ ድጋሜ ቀለል ያለ ምርመራ አደረጉልኝና ደም ሰጥቼ እኔም እዛው ተኛሁ ።
መዳፎቼኖ እጥፍ ዝርግት እያደረኩ እንደነበር አስታውሳለሁ ከዛ ግን ስነቃ ከቤኪ አጠገብ የተመቻቸ አልጋ ላይ ተኝቼ ሰለሞን አለምዬ ጄሪ ያቤፅ ቤኪና ዶክተሩ ጭምር ፍጥጥ ብለው እያዩኝ ነበር !???
ሁኔታው የመሠለኝ ሞቼ የተነሳሁ ያህል ነው የሆነብኝ !!!!!
ተደናግጬ ሁሉንም በአይኔ እየማተርኩ ሳያቸው ቤኪ እዛው እንደተኛ በአሳዛኝ ፊት እያየኝ
" ለምን እንደዛ አደረግሽ ለኔ መድሀኒቴ ነሽ ዝም ብለሽ አጠገቤ ብትቀመጪ እድን ነበረ እኮ " አለኝ ።
" ብዙ ሰአት ስትቆይብን እኮ ፈራን አቡ " አለችኝ ጄሪ እጆቼን ደግፋ ይዛ ።
የቤኪ አባት ትኩር ብሎ ተመለከተኝና
" በአንቺ ምክንያት ያፈሰሰውን ደም መልሰሻል ጥሩ ነው ቢያንስ አሁን ንዴቴ አንቺ ላይ አይደለም " አለኝ ።
የኔ ተቆርቋሪ ጓደኛ ጄሪ ቀደም ብላ
" አብላካት ምን አደረገች እሷ እንዴት ለቤኪ መጎዳት መንስኤ ትሆናለች ?? " አለች ።
በጣም ንዴት ላይ ነበር
" ምክንያቱም በሷ ምክንያት ነው ልጄን የጎዱብኝ " አለ በቁጣ ።
" እኮ እንዴት እሷ ምን አደረገች ???" አለችው መለስ አርጋ
"" ምክንያቱም ልጄን የወጋው .........
✍✍fidel....
🎬🎬🙋♀ ክፍል አርባ ሁለት
....... እያየኝ ነበር ። ነገሮች የበለጠ እያናደዱኝ ነው !!!
እስከማቀው ወንድ የሴት ዶርም መግባት ሳይሆን መቅረብ አይችልም !!! አልኩኝ በፌዜ አፌን አጣምሜ ።
አንዳንዴ መቀራረብ ያናንቅ የለ !!! ለትንሽ ጊዜ ብንቀራረብ ይኸው አፍ ለአፍ መካፈት ጀመርኩ ።
እንደ አለቃ እንደ ጊቢው አስተዳደርነት ከማክበር ይልቅ ሰው ፊት በንቀት ስላናገርኩት ክብሩን እንደወሰድኩ አሰበ መሠለኝ ቀይ ፊቱና ጆሮው ለብቻ ቲማቲም መሠሉ ።
"" ወደ ቢሮ ሂጂ ነይ ውጪ ፍጠኚ !!" አለ በጣም በተቆጣ ድምፅ !!
ከዛ በላይ እልህ ውስጥ መግባት ጥሩ መስሎ አልታየኝም ለሱ ብዬ ሳይሆን ለእራሴ ብዬ ተነስቼ ጃኬት ደረብኩኝና አልፌው ወጥቼ ወደ ቢሮ ሄድኩኝ ።
ብዙም ሳይቆይ ተከትሎኝ መጣ እና በሩን ከውስጥ ቆለፈው ።
የዛኔ የምር ፈራሁኝ !!! ለምን አፈቀርክ ብሎ ልጁን ትምህርት አቋርጦ ውጪ እስከመላክ የሚያደርስ ጭካኔ ያለው ኮስታራ ሰውዬ እና እኔ የእናቷ ብቸኛ ልጅ አንድ ክፍል ውስጥ ተቆልፎብናል ማለት ለኔ ከባድ ነገር ነው ።
ላዬ ላይ ተከምሮ የነበረው ኮፍጣናነት ወኔና ደፋርነት በአንዴ ከኔ ራቁ !!!!
ስሜቶች እንደዚ ናቸው!!!!! ማንኛውም ስሜት ቅፅበታዊ ነው !!!!!
በስሜት መመራት በጣም መጥፎ ነገር ነው ለዛም ነው ስትናደድ አትናገር የሚባለው !!!
ውጪ ላይ እያለው ገንፍለው የወጡ ብዙ ቃላትን ያስባከኑኝ እነዛ ሁላ ስሜቶች አሁን ላይ የሉም ከኔ ርቀዋል !!!!!
" ተቀመጪ " ሲለኝ እንደ ከዚ ቀደሙ አላንገራገርኩኝም ቁጭ አልኩኝ !!!
እጄን እያፋተኩኝ ጠረንጴዛው ላይ አይኔን ተክዬ ቀረሁ ።
" የገዛ ልጄን ራሱ እንደዚ ታግሼ አላቅም !!!!! ማንም ሰው እንዲህ በንቀት ተናግሮኝም አያውቅም !!!
ነገር ግን ልጄ ላንቺ ያለውን ፍቅር ስላየሁ ነውዐየሌለኝን ማንነት እየታገስኩሽ ያለሁት ሰከን በይ!!" አለኝ ረጋና ቀስ ባለ ንግግር !!!!
መረጋጋቱ ረበሸኝ !!! ቀስ ብሎ ሲያወራኝ ይበልጥ አስፈራኝ !!!!
ምንም ማለት አልቻልኩኝም በዝምታ ቆየሁ ።
" ሀሳብ ካልሰጠሽበት ነገሮችን በእራሴ መንገድ መረዳት ይኖርብኛል ማለት ነው " አለ ።
የዛኔ በረጅሙ ተነፈስኩኝና ለማውራት ራሴን አነቃቃሁኝ !!
እናንተም እንደኛ ሰው ናችሁ ። !!!! አዎ ምን አልባት ብዙ ነገሮች አንገናኝ አንቀራረብም ጭምር ይሆናል ግን እንደተረዳሁት ከእናንተ ይልቅ እኛ ጋር ጥሩና እውነተኛ ፍቅር አለ !!!
በረከትንም በገንዘብ እየመረዝከው ነው !!!
በእርግጠኝነት ከዚ ቡሀላ ሰው ሲቀርበው የሀብታም ልጅ ስለሆነና ገንዘብ ስላለው እንደሆነ ማሰቡ አይቀርም በእርግጠኝነት !!!!
እኔ የተዋወኩት አንድ ትምህርት ቤት እየተማርን ነው ስለሱ የማቀው አንድም ነገር የለም ማለቴ አልነበረም እኔ የሀብታም ልጅ መሆኑን ሳላውቅ እሱ የደሀ ልጅ መሆኔን እያወቀ ነው ፍቅር ውስጥ የገባነው !!!
እኔ እሱን ሳስብ አንድም ቀን አብሮ ሀብት ትዝ ብሎኝ አያውቅም ተምሬ የመቀጠር እና ሰርቼ የማግኘት ፍላጎት እንጂ ቁጭ ብዬ በሰው ገንዘብ የመቀለብ ፍላጎትም የለኝም !!!!
አንተ እንደ አለምዬ አደለክም !!!እሷ ምርጥ ናት በገንዘብ አትመራም አትመካምም!!! አልኩት።
" እባክሽ መሥመር አትሳቺ እኔ እንደዛ ለማለት ፈልጌ አንደለም በማታቂው ነገር በርግጠኝነት አታውሪ !!!!.
በረከት ለኔ ብዙ ነገር ነው !!!! ለኔም ለአለምም ትልቅ ነገር ነው !
የልጅነት ልጃችን ነው በብዙ የተፈተንበት ነው !!!!
እኛም ም ከእናንተ በላይ በድህነትና በችግር ውስጥ ሆነን ነው የተዋደድነው !!!
ቢያንስ እናንተ ቤት አላችሁ እኛ እንኳን ቤት ይቅርና ከዝናብ የምንጠለልበት ሸራ እንኳን አልነበረንም !!!!!
እንደመሸ አውቃለሁ !! ልታዳምጪኝ ከፈለግሽ ሁሉንም ነገር ልነግርሽ ዝግጁ ነኝ እንደምታስቢው አይደለም እዚ የደረስነው ....." እያለ እያስረዳኝ እያለ ስልኩ ጠራ ።
አየውና ኮስተር ብሎ አነሳው !!
" ምን ለምን ???" ብሎ ስልኩን ጠረንጴዛ ላይ አስቀመጠው ።
ምንድነው ምን ተፈጠረ ምንድነው ....... እያልኩ ብጠይቅም የሚመልስለኝ አልነበረም !!!!!!
ቶሎ ስልኩን አንስቼ ምንድነው ?? አልኩኝ ።
" ቶሎ መምጣት ይኖርባችዃል በረከት እየደከመ ነው " አሉኝ ?????
✍✍✍fidel..........
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ፊደል✍✍» is a Telegram channel in the category «История», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 1.8K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 11.4, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 18.0 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий