

Channel statistics
Full statisticschevron_rightስሜታዊነት ዋጋ ያስከፍላል ሳናስብበት ድንገት ስለመጣልን ብቻ ወይ ደግሞ ድንገት ስለፈለግነው የምናደርገው ነገር ያስጠይቀናል ፤ አንዳንዴ ለማንኛውም ነገር በተለይ ለከባድ ውሳኔ ቆም ብለን ማንሰላሰል እና ፈጣሪን መጠየቅ ይኖርብናል ከሆነ በኋላ ለምን ሆነብኝ ማለት መፀፀት መፍትሄ አይሆንም ሳይሆንብን በፊት መጠንቀቅን መልመድ ያስፈልገናል ፤ ስለምንችል ብቻ ማድረግ በስሜታዊነት መመራት ይብቃን!
የእናንተው ምርጥ ጓደኛ 😊
........አለች እናቴ ???
ግን ለምን ማለቴ እናቴ በእይወቴ ዋሽታኝና ደብቃኝ እንደማታቅ የማቀው እኔ ነገሩን ተጠራጠርኩት ።
የተጠራጠርኩት ግን በፍፁም እናቴን አልነበረም እሱን እንጂ ።
አውቆ ወደኛ መመለሻ ዘዴ እየፈለገ ነው ብዬ አስቤ ነበር ።
" እናትሽን መጠየቅ ትችያለሽ ካለበለዚያ እኔ ነግርሻለሁ " አለ እጁን እያወራጨ ።
"" ስለምን ልትነግራት ነው ባክህ ??" አለች እናቴ ዝምታዋን ሰበረች።
" ዞር በል አንተ ካልነገርሻት እኔ እናገራለሁ !!" አለ ቤኪን እየገፈተረው ወደ ውስጥ ለመግባት እየሞከረ ።
ደስ የሚለው እሱን መጣል መግፋት ልክ እንደኔ በፍቅሩ አለመውደቅን ጨምሮ የማይቻል ነገር ነው ።
ቤኪ ማለት የፈጣሪ የእጅ ጥበብ ማመስገኛ መስሎ ነው የሚታየኝ በሁሉም ነገር !!
ከኔ ጋ ተጣልቶ ከሄደ ቡሀላ ሲመለስ የተቀየረው አንድ ነገር ቢኖር ትዕግስት ገዝቶ ነው የመጣው ።
በፊት ቢሆን እንኳን እንዲ እያመናጨቁት ዝም ሊሊ ይቅርና ስህተት የማያልፍ አፍላ ጎረምሳ ነው !!!
አሁን ግን በዝምታ ተረጋግቶ
" እባክህ ተረጋጋ ከፈለጉ ግባ ይሉክ ነበር እኮ ተሳሳትኩ " አለው ።
በጣም አንደተናደደ ፊቱና ንግግሩ በግልፅ ይናገራለ!!!!
ነገር ግን እዛ ላለነው ብሎ የታገሰ ይመስለኛለል !!
በዛብህ እኛ የማናቀው የሚያቀውን ሚስጥር ምንነት ማወቅ ፈለኩኝ !!!
እማ ምንድነው??? አልኳት
"ምንም ምንም ልጄ እሱን አትስሚዎ እሺ የኔ ቆንጆ "አለችኝ እየተንተባተበች !!
" መሠረት እባክሽ ከኔ ከሚሰሙት ከአንቺ ይሻላል ኤጭ ከተናገርሽ ተናገሪ አለቀ !!አላት ነገሩን እናቴ ላይ እየተናዘዘ???
" እውነት ??? ከልብህ ነው ። በላ ጀምርጨተናገር ከመጀመሪያ ጀምር እንጂ አይሻልም ???" አለች በሆነ መንገድ እያየችው !
" ምን ለማለት ፈልገሽ ነው ??" እያለ ለጠብ መጋበዝ ሲጀምር ቤኪ እንዳረጋጋ ብሎ ነው መሠለኝ አንድ ቡጢ
አለምዬ ደግሞ ደንግጣ ለቤኪ መከላከል ጀመረች ።
የከረረ ፀብ ውስጥ ሳይገቡ ሰውዪው ከዛ
አካባቢ ለቆ ወጣ ።
እሱ ስሄድልንና እናቴም ስትረጋጋ ጠብቄ
እማ ማነው ምንድነው ሚስጥሩ ?? አልኳት ።
ልጄ በጣም አደገኛ ሰው እንደሆነ እወቂ ከሱ ጋ ምንም ከማለትሽ በፊት ሳትነግሪኝ እንዳታገኝው !! ብዬ ላረጋጊት ሞከርኩኝ ።
የዛ ቀን ስለመሸ እነ ቤኪ ወደ ቤታቸው ሄዱ ። ልሸኘው ወጣሁና አብሪያቸው የኔ አራዳ አለምዬ አውቃን ወደ ፊት ጥላን ሄደች ።
እኔና ቤኪ ከተገናኘኘን በራሳችን አለም ውስጥ እንንሳፈፋለን !!!!
ማንንም ምንም ተናገረ ግድ አይሰጠንም ።
ትንሽ ሸኝቻቸው ተመለስኩኝ ።
ስገባ እናቴ በጣም እያለቀረች ነበር !!!
እማእናቴ ምን ሆነሽ ነው ምነው ???
አልኳት በዛ ልክ ማልቀሷ ግራ አጋብቶኝ ።
"ይሄን ሰውዬ ማየት አልችልም አልፈልግመመ!!!!!" አለችኝ እንባዋ እየወረደ ።
እሺ እማ ተረጋግተሽ ንገሪኝ ለምን ምንድነው የሁለታቹ ሚስጥር ምንድነው እኔ እንዳውቅ የሚፈልገው ነገር እንዳለ ሲያወራ የነበረው ምን ፈልጎ ነው ??
አልኳት ግራ አጋብቶኝ ተ
" ልጄ መስማት የሌለብሽ ነገር ነው " አለችኝ ቀስ ብላ ።
ማወቅ እፈልጋለሁ ንገሪኝ ማነው ሄሄ ሰው ??? አልኳት ።
" እ ........ እሱ ማለት ........
✍✍✍fhdel...
ክፍል ~~
ሀያ ስድስት
...........ቤኪ በሩን ከፈተ ። የእናቴ የድሮ ባል የኔ ደግሞ የእንጀራ አባቴ የነበረው ክፉ ሰውዬ ነው ። በልጅ አይምሮዬ የማስታውሰው ነገር እንዳለ እናቴን ምን ያህል ሲያሰቃያት እንደነበረ ምን ያህል ይደበድበን እንደነበረ ነው !!!!
ለኔ የማረሰው ጠባሳ ነው ።
በወጣ በገባ ቁጥር ሰክሮ በመጣ ቁጥር እየደበደበን እንዴት ያስለቅሰን እንደነበር አረሳም !!!!!
እናቴ ስታየው በጣም ተረብሻለች ወደ ዃላ ሸሽታ ፍጥጥ ብላ እያየችው ነው !
ቤኪ ከዚህ በፊት አይቶት ስለማያቅ ግራ ገብቶት እኔንም እናቴንም በደንብ ተመለከተንና እሱንም ተመለከተው ።
ስሙ በዛብህ ነው ። ስገምት እናቱ እንዲህ አይነት ስም ያወጡለት ሀጢያትህ በዛብህ ለማለት ይመስለኛለሸ !!!!!🙄🙄
" ምን ፈልገህ ነው ?" አለው ቤኪ ኮስተር ብሎ ። የሁለታችንም ዝምታና ድንጋጤ ችግር እንዳለ የሚያሳይ ነገር ነው !!!!
የሚገርማችሁ ትርጉሙን ባላውቅም የምር የሆነ ይመስል
" የአብላካት አባት ነኝ " አለ ኮራ ብሎ ።
አባትነት ራሱ ምን ማለት ነው ?????
እኔ እስከማቀው አባትነትን ከእናቴ ውጪ አላውቀውም እናትም አባትም ሆና ነው ያሳደገችኝ ለኔ ደስታ ስትል መከፋቷን ደብቃ !!! ቀን ከሌት እየለፋችና ራሷን ዝቅ አድርጋ እኔን ከማነኛውም ሰው እኩል አሳድጋኛለች !!!
የሚገርመው ሳስበወ ከበዛብህ ይልቅ ቤኪ እናቴ እያለም ቢሆን አባት የሚባል ነገር እንዳለ አስተምሮኛል!! !!!
በሰአቱ ቤኪ ግራ ተጋብቶ አንዴ እናቴን አንዴ እኔን በየተራ ተመለከተን ።
" የልጄ ቤት እኔዳልገባ ልትከለክለኝ ነው " አለው አፉን ሞልቶ ።
እኔ ግን የአንዳንድ ሰዎች ድፍረት ቢኖረኝ የት በደረስኩ ነበረ !!!!
ገና ለገና አያቁኝም ብሎ እናቴም ሲጀበድባት ሲሰድባት ዝም ስለምትል ብሎ የማይሆን ነገር ያደርጋል !!!
አዎ የዛኔ ልጅ ነበርኩ አሁን ግን ትልቅ ልጅ ነኝ ከዛ በላይ መታገሱን አልችልም !!!!!
ኤጭ በቃህ ስለማን ነው የምታወራው ??? እኔ እናት ብቻ ነው ያለኝ !!!
አባት የለኝም !!!! ወላጅም ቢሆን ሞቷል ወደ ማይቀርባት ሄዷል አለቀ !!!
ማን ነህ አንተ ????አልኩት ።
ከልቤ ነበር ያወራሁት ምክንያቱም በጣም ተናድጄ ነበር !!!!
አንዳንድ ሰዎች ፊት ለፊት ካልተነገራቸው አይገባቸውም !!!!
የዛኔ በረከት በሩ ፊት ቆመና
" ምንድነው የምታወራው አቡ ችግር አለ ?" አለኝ ወደኔ እየተመለከተ ።
አዎ አንዳንድ ሰዎች ለሰው ችግር ካልሆኑ ደስ አይላቸውም ዝም ሲባሉም አይገባቸውም !!!! አልኩት
በኔ ቤት ቅኔ መዝረፌ ነበር !!!!😂😂
" መሠረት ምነው ዝም አልሽ አትናገሪም " አላት ።
እሷን አታውራት ድምፅህንም እንድትሰማው አልፈልግም !!!
የዛኔ ልከላከልላት አልቻልኩም አቃለሁ አሁን ግን ህፃን አደለሁም እንደዛው ሆኜ የምቀር መስሎክ ብዙ በድለከናል አሁን ግን ልብሷንም እንድትነካ አልፈቅድልክም ገባህ!!!!
በንዴትና በማደግ ስሜት ውስጥ ሆኜ ነው የማወራው !!!
በነገራችን ላይ የምመኘው ነገር ነበር !!!! የሆነ ቀን አድጌ ለእናቴ ዘብ መቆም እፈልግ ነበረ!!
አለሁልሽ ደረስኩልሽ ሜለት እፈልጋለሁኝ ።
አውቃለሁ ገና አልጀመርኩም ሁላ ግን ደግሞ ቢያንስ ከእናቴ ፊት መቆም ለኔ አንድ ነገር ነው !!!!
በዛብህ ተብዬው ግን በጣም ደፋር ሰው ነው የኔን ንግግር ንቆ አሻግሮ እናቴን እየተመለከተ
" መሠረት " አላት ጮክ ብሎ ።
" ተረጋጋ ጮክ ብለክ እንዳታወራት እረፍ !!!"አለ ቤኪ ።
የኔ ኩራት ማንንም አይፈራም ሁሌም ለኔ ከፊት እንደቀደመልኝ ነው !!!!
እንደ ማንኛውም ሰው ደግሞ እኔም ለኔ የሚቆረቆር ሰው ስላለ ደስተኛ ሆኛለሁ ።
የቤኪ መኖር የልብ ልብ ሰጠኝ መሠለኝ
ከቤታችን ዞር በል ደግሜ ላይክ አልፈልግም ከአሁን ቡሀላ ከደረስክብን በጣም ትጎዳለክ ........ በጣም ብዙ ነገር እያልኩ መጮክ ጀመርኩኝ ።
አለምዬ እጆቼን ይዛ እንድረጋጋ እየነገረችኝ ነበር ።
እሱ ግን የኔን ንግግር ችላ ብሎ
" መሠረት ለምን እንደመጣሁ የምታቂ ይመስለኛል አደለም እንዴ ከዚ በላይ ደብቄ መያዝ አልችልሞ ወይ ተናገሪ ወይ ልናገር ነው ......!!!" አላት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ በሚመስል መልኩ !!!!
ቶሎ ወደ እናቴ ዞርኩኝ አንገቷን እየነቀነቀች ትመለከተኛለች ???
እሱም ለመናገር ሊጀምር ሲል
" አይ አይ ቆይ ቆይ ..."አለች እናቴ ????.......
✍✍✍fidel.......
ክፍል~~
ሀያ አምስት
........በንዴትም ስሜታዊ ሆኜ በጣም ተናድጄ ነበረ። የበለጠ ያናደደኝ ደግሞ መልሱ ዝምታ መሆኑ ነው ።
በእሱ ጉዳዬ እንባዬ አሽቃባጭ ናት መቆጣጠርም አልችልም ዝም ብሎ ነው የሚፈሰው !!!!
የዛኔም የድሮ ፍቅራችን ትዝ አለኝና አመለጠኝ ። ግን ድክመቴ መሆኑን ለሱ ማሳየት አልፈለኩኝም !!!
የመጨረሻዬ ነው ብዬ ወስኜ ፊቴን አዙሬ ልሄድ ፊቴን ሳዞር
" የኔ እናት ያላንቺ መኖር አልችልም እኮ " ብሎ እጄን ይዞ ወደራሱ ጎተተኝና እቅፉ ግንባሬን ጉንጬን እያገላበጠ ይስመኝ ጀመር ።
የመጨረሻ ነው ብዬ ወስኜ የነበርኩ ልጅ እሱ እቅፍ ውስጥ ስገባ ሁሉንም ነገር ረሳሁት ከእቅፉ ሳልወጣ በቀረሁ ብዬ ተሐኘሁ!!!!
ለምን እሺ ቆይ ለምን ??? አትወደኝም ??? ያሁላ ቃል ተግባር ውሸት ነበር ??? አልኩት እዛው እቅፉ ውስጥ እየሞኩኝ ።
" አቡ ከእራሴ በላይ እንደማፈቅርሽ ለኔ ህይወቴ እንደሆንሽ ታቂያለሽ እኮ " አለኝ ።
አውቅ ነበር እኮ ግን ደግሞ ጥለከኝ ሄድክ
በጣም ጎድተከኝ ነበረ ለምን ጥለከኝ ሄድክ ?? አልኩት እንባዬን እየጠራረኩና ከእቅፉ እየወጣሁኝ ።
" እባክሽ ተረጂኝ አዎ ጥፋት ነው ግን አንድም ላንቺ ብዬ ነው አንድም ደግሞ አባቴን መስማት ነበረብኝ !!" አለኝ ።
ለኛ ፍቅር ያ በቂ ምክንያት አይሆንም ሊሆንም አይችልም !!!!
ለአንቺ ብዬ ማለት ??? አልኩት በእልህ እንባዬን እያፈሰስኩኝ ።
" በቃ አባቴ የኔና አንቺን ግንኙነት አልፈቀደልኝም ነበር እሱ ደግሞ ማንንም አይሰማም ካስታወሺ የመጀመሪያ የፍቅር ጊዚያችን ቀን ቤት መተሽ ስሸኝሽ በመኪና ወደኛ የመጣው ሰው አባቴ ነበር !!!
እናም በአንቺ አስፈራራኝ እኔም አሁን ነው የተረዳሁት አዎ ስህተት መሆኑ ገብቶኛል እንደዛ ማረግ አልነበረብኝም !!!" አለኝ ።
በርግጥ ለኔ በቂ አልነበረም !!!
እኔ ማንም ባይደግፈኝ እንኳን እሱን አምነውም እደግፈውም ነበር !!!
" በቃ በስርአት እንዳስረዳሽ ፍቀጂልኝ ትንሽ ጊዜ ስጪኝ አንቺን ይቅርታ ለመጠየቅ ብዬ ምንም ነገር ባደርግም አይቆጨኝም አደርገዋለሁኝም !!" አለኝና ምላሼን ሳይጠብቅ ጎትቶ አቀፈኝ ።
" እመኚኝ እናቴ አንቺን ልጠላሽ አልችልሞ " ብሎ አይኔን ግንባሬን ጉንጬን እየሳመ ፀጉሬን ያሻሸኛል !!
ከዛ በላይ ውጪ ተቃቅፈን መቆም አልቻልንም እናቴና አለምዬ ተከታትለው ከቤት ወጡ ።
አለምዬ በአንዴ ፊቷ በደስታ በራ እናቴ ግን እኔን ጎድቶባታል ይቅርታ ለማድረግ ቀላል አይሆንም !!!
ይልቁንም የበለጠ ተናደደች ።
" ልጄ ሰዎች ሲመጡ መቀበል ከሆነ ትናቂያለሽ !!" አለችኝ ተኮሳትራ ።
በሰአቱ ምንም ልላት አልቻልኩኝም ። እማዬ ብቻ ብዬ በአሳዛኝ ፊት አየዋት ።
" መስኪ ይቅርታ በጣም " አላት እኔን ለቆ እሷን እየተመለከተ
" ተው ልጄ እኔ ጠልቼክ አደለም ግን አንዳንዴ ይቅርታ የማያስተካክላቸው ብዙ ነገሮች አሉ " አለችው በቁጭት ።
" አቃለሁ ግን ለሷ ብዬ ነው እኮ " አላት ።
" አይ ልጄ ነው ብለክ ነው .......ለማንኛውም ኑ ግቡና ቁጭ በሉ ደክሟችዋል "" አለችውና ወደ ቤት ገባች ።
ገብተን ተቀምጠን በደከመ መንፈስ ምግብ ለመብላት ተዘገጃጅተን ቁጭ ስንል በራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ማለት በሚቻል ሁኔታ በጣም በከባዱ በሩ ተንኳኳ ።???
እናቴ ክው ብላ ከተቀመጠችበት ተነስታ ብድግ ብላ አየችን ።
" ቆይ ቆይ እኔ ልክፈት " ብሎ ቤኪ ተነስቶ በሩን ከፈተ .........
✍✍✍✍fidel .........
ክፍል ~~
ሀያ አራት
........ከቤት ሲወጡ ተገጣጠምን ።
አለምዬ እናቴ ብቸኝነት እንዳይሰማት ስለምታስብላት ሁሌ እየመጣች አብራት እንደምትውል ሁሌ እናቴ ትነግረኛለች ይሄው ዛሬም አብረው ናቸው !!
ወደ ዋናው ወሬ ስገባ በረከትን ከስንት ጊዜያት ቡሀላ ማየት ለኔ በጣም ከባድ ነገር ነበር !!!!!!
ሳየው ድርቅ ብዬ ነው የቀረውት ።
ልክ እንደኔ ደግሞ እናቴና አለምዬም ድርቅ ብለው አንዴ እኔን አንዴ ቤኪን ማለቴ በረከትን እያፈራረቁ ያዩናል ።
አለምዬ ቀድማን ባነነችና ሮጣ ቤኪን አገላብጣ አቅፋ ሳመችውና ቀጥታ ወደኔ መታ እንደ እናት ያለ ስስት ሳመችኝ ።
ቀጥላ እናቴም መታ በየተራ ሳሙኝ ።
እኔ አይኔን ከበረከት ላይ መንቀል አልቻልኩም እሱ ደግሞ አይኔን ላለማየት መሬት ላይ እይታውን አድርጎ ጥፋቱን ማመኑን ለማሳየት እየሞከረ ይመስላል !!!
" መች ነው የመጣችሁት ሁለታችሁም ሳደውሉ መጣችሁ እኮ " አለች አለምዬ ወደ ሁለታችንም እየተመለከተች ።
እኛ ለመመለስ አቅሙ አልነበረንም ።
በዛን ሰአት ትንሽ ቃል ማውጣት ለኔ ከባድ ሆኖብኝ ነበር !!!!
እውነት ለመናገር በጣም ናፍቆኛል እጄን እያስቆምኩት እንጂ እህኔ የማገኘው የሱ አንገት ላይ ነበረ ።
አዎ በጣም ተናድጄበታለሁ ግን እኔ ከሱ ይቅርታ የምትል አራት ፊደል ብሰማ ለማቀፍ ዝግጁ ሆኜ እየጠበኩት ነው ።
እናቴ በቤኪ በጣም እንደተናደደች እናውቃለን ፊቷም ይናገራል !!!
ታዲያ ያ ጠልታው ሳይሆን እንደ ማንኛዋም እናት ለልጇ ስለምታስብ ነው !!!!,
አለምዬም ሁለታችንንም እኩል መጠየቅ ልክ እንዳልሆነ ቢገባት ወደ ቤኪ ቀርባ
" ልጄ መች መተክ ነው ሳትነግረኝ ለምን ?? ግን ደስብሎኛል ስላየሁክ " አለችው ።
" የሆነች .." ሲል ከንፈሮቼ መንቀጥቀጥ ጀመሩ ድምፁን ከሰማሁኝ በጣም ቆየሁ !!! ገና የሆነች ብሎ ሲል ስሰማው ከንፈሬ መንቀጥቀጥና ምላሴ መንቀጥቀጥ ጀመረ ።
ትርፍ ቃል እንዳላወጣ ፈርቼ በእጄ አፌን ሸፈንኩኝ ።
አለምዬ ነገሮች የመረዳት አቅም አላት!!!
እማዬ ቆማ ለመስማት ስትዘገጅ አለምዬ
"ፐየድሽው ነገስ " ብላ አሯሮይዛልኝ ገባች ።
እንድናዘራ ብላ እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ የኔና የሱ መፋጠጥ ሆኖ ነው እንጂ ለኛ ብላ ነው ።
እሱም ዝም ኤኔም ዝም ሆነ ነገሩ ።
አንዳንዴ እኔን ስለሰጠው ማመስገን ነበረበት እላለሁኝ !!!
ከድሮም ጀምሮ በራሱ ጥፋትም ብንደባበር እኔ ካላወራሁት አያወራኝም ነበር ።
ቤኪ የሚል ቃል ብቻም ብትሆን ከኔ ከሰማ ይቅርታ ጠይቆ አባብሎ ምናም ይታረቀኝ ነበረ ።
አሁንም እኔን እየጨበቀ መስሎ ስለተሰማኝ
ደህና ነህ ? አልኩት እንደምንም ሀይሌን አሰባስቤ ።
በአሁኑ ግን ያን ያህል ቀላል አልነበረም ቀና ብሎ አይኔን ተመለከተና መልሶ አቀረቀረ ።??!!
ያቺን ቃል ለማውጣት ለፍቼ ነው ። ክብሬን ትቼ ነው መጎዳቴን የደረሰብኝት በደል ያስለቀሰኝን እንባ መልሼ እካስበታለሁኝ ብዬ አስቤ ነበር !!!!
ዝም ስላለ ከዛ በላይ እሱን መጠበቅ ሰልችቶኛልም መንገድ ቀይሬ ቀጥ ወደ ቤት ልገባ ስል
" በማርያም ይቅርታ !!" አለኝ በአጭሩ ።
ስጠብቀው የነበረ ቃል ነው !!!! ኡፍ እንዴት ደስ እንዳለኝኝኝኝ !!!!!
ነገር ግን ይቅርታውን ፈለኩ እንጂ ለኔ በቂ አልነበረም ። ፊቴን አጨማድጄ እጅ በደረት እያደረኩ ወደሱ ቀረብኩኝ ።
ላልጨክንበት ነገር አጉል እን አክተር ሲያረገኝ እኮ ነው !!!!!🙄🙄
ልክ ወደሱ ስቀርብ ቆፍጠን ያልኩበት እየከዳኝ መጣ ።
እንደምንም ራሴን አሳምኜ ከሁሉም በፊት ነገሮችን ሊያስተካክልልንም ሊቋጨውም የሚችለው አንድ ነገር ብቻ ነው !! አልኩት
"እሺ ምን ምን ላድርግልሽ " አለኝ ።
ለምን አደረከው ??? ለምን ጥለከኝ ሄድክ ላንቺ ብዬ እንዳትለኝ እውነተኛ ምክንያትህን ንገረኝ ........ አልኩት በንዴትም ስሜታዊ ሆኜ ነበር ?????...
✍✍✍fidel ....
ክፍል~~
~~~ሀያ ሶስት
......... አይኗን ተክላ ቀረች ። ለምን እንደሆነ ባላቅም ልጅቷን ለማየት በጣም ጓጉቼ ነበር።
ቀጥታ ሄጄ ካሜራውን ከጄሪ እጅ ላይ ወሰድኩት ።
ያለመከራከር ካሜራውን ለቃልኝ ከቦታው ለቃ ሄደች ።
ጭራሽ ባላሰብኩትና ባልጠበኩት መንገድ ካሜራውን የሞላው የኔ ፎቶ ነበር ።
ራሴን እስከምጠራጠር ድረስ እየቀያየርኩ ማየት ጀመርኩኝ ።
ፎቶዎቹ ታስበውበት ተዘጋጅተውበት የተነሳዋቸው ይመስላሉ !!!!!
የገረመኝ ደግሞ ያን ያህል ቆንጆ ነኝ እንዴ ያስባሉኝ ፎቶዎች አሉ አብዛኞቹ ግን ላይብረሪ ካፌና ቤተ ክርስቲያን ናቸው ።
የመአት ፎቶዎች ናቸው ሁሉንም አይቼ ስጨርስ ቀና ብዬ ምንድነው በሚል አስተያየት አየውት ።
" ምነው ? ቆንጅዬዋ " ብሎ ፍጥጥ ብሎ አየኝ ።
በሰአቱ ካሜራውን ከስክሼ ብሰብረው ደስ ይለኝ ነበር ወዲያው ግን ቤኪ ምን ያህል ውድ እንደሆነ ነግሮኝ ስለነበር ተረጋግቼ አስቀመጥኩትና እየሮጥኩ ወደ ዶርም ሄድኩኝ ።
ዶርም ላይብረሪ መናፈሻ ወክ ማድረጊያችን ጋር ብቻ ሁሉም ቦታ ጋ ፈለኳት ጄሪን ማግኘት አልቻልኩም ።
ብዙ ነገሮችን እንደምታገናኛቸው እርግጠኛ ስለነበርኩኝ ነው!!
ምክንያቱም ደግሞ ከዚ በፊት ታይው ስላትም ስለነበር ተቀራርበንም ስላየች መጠርጠሯ አይቀርም !!
እኔም በሷ ቦታ ብሆን የማስበው ነገር ስለሆነ ፈርቻለሁ የት እንደማገኛት አላውቅምም !
ሙሉ ቀኑን ጠፍታብኝ ውላ ከስንት ፍለጋና ዙረት ቡሀላ ወንበሮቹ ጋር ተቀምጣ አገኘዋት ።
ሮጬ ሄጄ እግሯ ስር ቁጭ ብዬ
ጄሪ እኔ እንደዛ አስቤ አላቅም አንቺ እንዳሰብሽው አይደለም !!! አልኳት ።
ዝም ብላ ተመለከቸችኝና
" እውነት ነው አቡ ወንድሜ አንቺን ይወድሻል እኔ በረከትን እወደዋለሁ አንቺ ደሞ እሱን ትወጂዋለሽ እንደዛ ነው አይደለ !!!!! በጣም የተወሳሰበ ነገር ነው !!!!" አለችኝ እንባ እየተናነቃት ።
ከእራሴ በተማርኩት መሠረት በረከትትን እንደምትወደው ያስታውቅባታል ግልፅ ነገር ነው የሚሆነውም !!!!
ከጄሪ ጋር ጓደኛሞች ብንሆንም ጎበዝ ተማሪ ስለሆንኩኝ ፍቅር የማውቅ አይመስላትም ጠይቃኝ አታቅም እንጂ ቤኪን ምን ያህል እንደምወደው ብታውቅ እንዲ ባላለችኝ ነበር !!!!
በሰአቱ ምን ብዬ ለሷ እንደማስረዳም አላወኩኝም ግራ የተጋቡ ቃላቶች አንደበቴን ይዘውት ማውራት አቃተኝ ።
ዝምታዬ ደግሞ ሽንፈት መሠለት ። እሷ ልክ እንደሆነች ስላሰበች በረጅሙ ተንፍሳ ከተቀመጠበችበት ተነሳችና
" አታስቢ ጓደኝነታችን አይፋቅም ። የጎዳኝ ልብሽ እንጂ አንቺ አደለሽም ብድሬን ብመለስም ለልብሽ እንጂ ለአንቺ አይደለም እሺ "" ብላ በከባዱ አስፈራርታኝ ሄደች ።???
በሰአቱ ተከትዬ ላብራራላትም አልፈለኩኝም !! የተነሳችበት ቦታ ላይ ተክዤ ተቀምጬ እያለ በረከት ከፊት ለፊቴ ቆሞ መልእክቱና ትርጉሙ ያልገባኝ የሆነ ቅኔያዊ አስተያየት አይቶኝ ሄደ ።
ከዛ ቀን ቡሀላ ጄሪን ብለምናት እንኳን አብራኝ ልትሆን አልቻለችም
ኢዩኤል እኔን መከተል .....ጄሪ በረከትን መከተል .... በረከት እኔን መከታተል ተያያዝናት በመጣን ቁጥር ራሳችን አደከምን ።እንደምንም እየተማርን ግማሽ አመት ሆነን ።
የፋሲካ በአል ደረሰ ።
ወደ ቤት መሄድ ባልፈልግም እዛ ሆኜ የተበረዘ ጭንቅላቴን ፈታ ለማድረግ ብዬ ወደቤት ለመሄድ ፍቃድ አፃፍኩኝ።
ጄረ ይቅር ማይባል ቂም ይዛብኛለች ።
ከሁሉም እየሸሸሁ የቀሩትን ቀናት አሳለፍኩኝና ወደ ቤት ለመሄድ እቃዬን ቆላልፌ የምፈልገውን ይዤ ወጣሁኝ ።
ቤት እስክደርስ በጣም ቸኩዬ ነበር ከወራት ቡሀላ እናቴን ላያት ስለሆነ በጣም ደስ ብሎኛል ።
ብር ያን ያህል ስለማላጠፋ ከላከችልኝ ብር ላይ አውጥቼ የሆነ የሆነ ነገር ገዝቼ ይዤ ሄድኩኝ ።
ውስጥ እስከምገባ አላደርስ ብሎኝ እማ እማዬ እያልኩ ወደ በሩ ስጠጋ በረከት ከፊት ለፊቴ ድቅን ሲል እናቴና አለምዬ ከቤት ውጥት ሲሉ ተገጣጠምን .........
✍✍✍fidel......
ስጨርሱ ❤️ ማረግ አይረሳ አይከፈልበትም!!
ክፍል
~~~ሀያ ሁለት
............ስትለው ዞር አለ ። ክው ነው ያልኩት ምክንያቱም ከማይሆን ጢባራም ሰው ነው ፍቅር የያዛት ።
ለእራሴ እኔ ከሱ ራኩ ብዬ ስደሰት የበለጠ አቀረበችብኝ ።
ደግሞ ለሷ የማይሆን ሰው እንደሆነ ተሰማኝ ። እሱም ሲያየኝ ደንግጧል እኔም እያፈጠጥኩበት ስታየን ነገሮች ያልገቧት ጄሪ ሁለታችንንም በደንብ አቀባብላ አየችንና
" ትተዋወቃላችሁ ??" አለችን በእጇቿ ወደ ሁለታችንሞ እየጠቆመች።
እኩል እንደመባነን አልንና እሷ ላይ አፈጠጥን ። እኔ ከመናደዷ በፊት ምን ብዬ ላረጋጋት ብዬ እየተጨነኩ እያለ
" ጠራችሁኝ " አለን ከተቀመጠበት ተነስቶ ።
ደስ የሚለው ጄሪ ነገር አታረዝምም ቶሎ ነው የምትረሳው ወዲያው ወደ ፍቅሯ ተመለሰች ።
" አ አ አዎ ፈልገንህ ነበር " አለችው ከመፍራቷ ብዛት እጆቿን እያፋተገች።
እንደዛ ስትሆን አይቻት አላቅም ነበረ እና ምን ያህል እንደወደደችው ግልፅ ነው !!!
" እሺ አቤት " አለ ወደኛ እየቀረበ ።
በረከት ተብዬው ከሁለታችንም መልስ እየጠበቀ በየተራ ያየናል ጄሪ እኔን ታየኛለች ሁለቱም ሲያፈጡብኝ ግራ ገብቶኝ
እንዴ እኔ ምን ላድርግ አልኳቸው ።
ቀስ ብላ ወደኔ ተጠጋችና ...
" በእናትሽ እኔ ልሂድ አንቺ ምን ያህል እንደምወደው አጋነሽ ንገሪልኝ አደራ "" ብላኝ ምላሼንም ሳትጠብቅ እየሮጠች ሄደች ።
ምን ብዬ ልንገረው ካልነገርኩት ደግሞ ታኮርፈኛለች በዛ ላይ ይከፋታል እያልኩ ብቻዬን ሳወራ
" በጣሞ ቆንጆ ነሽ " ብሎ የመናገር ፍላጎቴንም በአንዴ ነጠቀኝ ።
እ ?? አልኩ ደንግጬ ወደዃላ እየሸሸሁ
" በጣም ነው የምታምሪው እንደምታቂ እርግጠኛ ነኝ " አለ ትንሽ ፈገግ ብሎ ።
ከሱ በፊት የለመድኩት ንግግር ነው የኔ ቤኪ እንደዛ ሲለኝ ብቻ ነው የሚያስደስቸኝ !!!
ግን አልዋሽም ደንግጫለሁኝ ።
ያምሀል እንዴ ለቁም ነገር ፈልገንህ ነው አትጃጃል አልኩት በጣም ተኮሳትሬ
" ምን አልኩ ታዲያ እኔ ልብ የሚያቀልጥ ውበት እንዳለሽ ነው የነገርኩሽ ተሳሳትኩ ቆንጆ " አለኝ ።
ሲታይ እንደዛ ጅል አይመስልም !!!
መጀመሪያ የፈራውላት ኮስታራ ስለነበረ እንቢ ይላታል ይኮራባታል ብዬ ነበር !!!!!
በሰአቱ ተናድጄ ስታስጠላ ጅል አትሁን እንደ ወንድ አክት አድርግ ብዬ በቆመበት ጥዬው ሄድኩኝ ።
ወደ ዶርም ሄይኩኝ ገና በሩን ከፍቼ ስገባ ከአልጋ ላይ ተወርውራ መጣችና
" እ ምን አለ ? እሺ አለ?? አወቀኝ ??? ስከተለው እንደነበር ያቃል አ??? ምን አለ ቶሎ ንገሪኝ ....." በደቂቃዎች ውስጥ በጣም ብዙ ቃላትን አወጣች !!!!!
በዛ ላይ ስፍስፍ ያለ የጓጓ ፊት እያሳየችኝ ነበር !!!!
የሷን ፊት አይቼ ላስከፋት አልችልም መዋሸት ሳልፈልግ ለሷ ብዬ
አላቅም ላስብበት አለኝ አልኳት ምን ለማለት እንጀፉኩም ግልፅ አልሆነልኝም !!!!!
" ያ ማለት እኮ 90% እሺ ሊሆን ይችላል በቃ እሱም አይቶኛል ብላ ፍንድቅድቅ አለች !!!
በደስታ የምትሆነውን አሳጣት ጉዷን አልሰማች !!!!
የዛ ቀን እሷን ላለማስከፋት ብዬ በዋሸዋት ውሸት እኔንም እሷንም ማይሆን ነገር ውስጥ አስገባሁኝ !!!
ከዛ ቀን ቡሀላ ጄሪ መቶ እስኪያወራት መጠበቅ ጀመረች ቀን በቀን እሱ ዙሪያ እየጎተተች ታዞረኛለች ።
ለተከታታይ ሁለት ሳምንት አካባቢ ያለመሠልቸት ፈለገችው !!!!
የሆነ ቀን ግን ተስፋ ቆረጠች መሠለች በጣም ከፍቷት ሙሉ ቀን ተኝታ ዋለች ።
አጠገቧ ቁጭ ብዬ እያባበልኳት እያለ ብድግ አለችና
" አቡ እህትሽ አይደለሁ ትወጂኝ የለ ሄደሽ አንዴ ብቻ ደግመሽ አውሪው እባክሽ በእናትሽ ...." ብላ ለመነችኝ ።
መጨከን አልቻልኩኝም ከእናቴ እና ከአለምዬ ጋ ካወራን ሁለት ቀን ስለሆነን መጀመሪያ እነሱ ጋ ደውዬ አወራዋቸውና ቀጥታ ወደሚቀመጥበት ቦታ ሄድኩኝ ።
ገና እንዳየኝ እኔን ማናደድ ያስደስተዋል መሠለኝ
" ስጠብቅሽ ነበር ቆንጅዬዋ ጠፋሽ እኮ ? " አለኝ መቀመጫ ወንበሩ ላይ በእጁ የያዘውን ካሜራ እየያስቀመጠ ።
ከቻልክ አታውራ አዳምጠኝ አልኩት ግንፍል ግንፍል እያልኩኝ
" እሺ አንቺ እንዳልሽ " አለኝ ።
አንድ ሀሳብ ብልጭ አለልኝ ቀጥታ ምን አስጠየቀኝ አልኩና ነገሩንም እንዳይቀይረው ፈርቼ
ቀጥተኛ መልስ ብቻ መልስልኝለማወቅ ነው ፍቅረኛ አለክ ??? አልኩት ።
" ይሄን ጥያቄ ካንቺ መሥማት አስደሳች ነገር ነው !!!! " አለ ማይገናኝ ነገር !!??
ኤጭ ቀጥታ መልስ ብዬ ጮኩበት
" ፍቅረኛ ሳይሆን ማፈቅራት ሴት አለች " አለኝ ካሜራውን በእጁ እያነሳ ።
ማናት ከይቅርታ ጋር ማወቅ እችላለሁ ?? አልኩት ። በዝምታ ቀርቀር ብሎ ፈለግ ፈለግ አደረገና ይቻት ብሎ ከርቀት ወደኔ አዞረው ።
ለማየት ጠጋ ስል እጁን ከፍ አደረገው ።
" በውበት የጊቢውን ሴቾች እንዳለ ትቦንሳለች ማንም አይደርስባትም ንግስት ናት !!" አለኝ ።
የበለጠ የማየት ፍላጎት አደረብኝና ስጠኝ ልያት ብዬ ከእጁ ልቀማ ስሞክር ቆሞ እጁን ወደ ላይ አደረገብኝ በጣም ረጅም ነው እንዲሁም እንኳን ከፍ አድርጎብኝ !!!!
ስጠኝ ስጠኝ እያየሁ ስንታገለ
" አብላካት "" አለች ጄሪ ጮክ ብላ ።
እኔ ያላስተዋልኩት ነገር እጁን ወገቤ ላይ አድርጎት ነበር ???
የሷ አይንም ያረፈው እጁ ላይ ነበር !!!
ቶሎ ብዬ ወደ ዃላ ሸሸሁኝና ያምሀል ብዬ ጮኩበት ።
ምንም ሳትሰማ ጥላኝ መንገዷን ስትጀምር ሮጬ ከፊቷ ቀደምኩኝና
ላንቺ ብዬ እኮ ነው ጄሪ ተረጋጊ እንደምታስቢው አደለም ?? አልኳት
" ምንድነው ያሰብኩት ??? እየተላፋችሁ እንደነበር ነው ??" አለችኝ በንዴት ተሞልታ ።
እንደዛ አይደለም አረ ወይኔ ማፈቅራት ሴት አለች ብሎኝ እሷን ላጣራልሽ እየሞከርኩ ነው ብዬ ላረጋጋት ሞከርኩኝ ።
ቀጥታ እሱን ቸመለከተችና ሄዳ ከእጁ ላይ ካሜራውን ወሰደችው እሷ ስትወስደው ዝም ነው ያለው??
ካሜራው ላይ አይኗን ተክላ በጣም ተመለከተችው......???
✍✍✍✍fidel.............
– ኣልበርት ኣንስታይን
አንተን ከምትፈልገው ነገር የሚያገናኝህ የአላማ ፅናት ነው፤ በህይወት የሚያሸንፈው ብርቱ የሆነ ወይ አስተዋይ (Smart) የሆነው አይደለም፤ ውስጡ ላመነበት ነገር እስከ መጨረሻው የሚጓዝ ነው።
ኑሮ ሊያደክምህ፣ ነገሮች ሊሰለቹህ፣ ህይወት ተደደጋሚ ልትሆን ትችላለች፤ የደስታን ጥግ ማየት ከፈለክ ግን ላመንክበት ጉዳይ መኖር ጀምር ከዛ በአላማህ ፅና!
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ፊደል✍✍» is a Telegram channel in the category «История», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 1.7K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 11.4, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 18.0 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий