
Channel statistics
Full statisticschevron_right🙋♀🎬🎬አምሳ አንድ
............የሚገርማችሁ ይሄ ሁላ ነገር እንደተደረገች ቁጭ ብዬ እየሰማሁኝ ነበረ።
ለኔ ግን በጣም ከባድ ነገር ነው !!!!
ለደቂቃዎች
ምን አይነት መበደል እንደሆነ አላቅም ኤጭ ምን አረኩ ፈጣሪዬ ..... እያልኩ ያላደረኩት ነገር ያለ ይመስል !!!!????.......
በአንድ ሰአት በአንድ ሆስፒታል ውስጥ ሁለት የምወደቻው የኔ የምላቸው ሰዎች በሆስፒታል አልጋ ላይ ተኝተዋል!!!!
እናቴን የሚዬወራት ነገር መስማት ስለከበደኝ ለአለምዬ ትቻት ወደ ቤኪ ጋራ ሄድኩኝ!
በመስከኮቱ ሳይ ከተኛበት ተነስቶ ቁጭ ብሎ ነበረ ።
ምን ሆኖ ነው ብዬ ደንግጬ በሩን ክፍት አርጌ ገባሁኝ።
ገና አጠገቡ እንደደረስኩ ጥምጥም አለብኝ።
ምነው ምን ሆንክብኝ አልኩት የዛኔ ሀሳቤ ላይ የመጣው የሆነ መጥፎ ነገር ተፈጥሮ ነበር የመሰለኝ።
" ጥለሺኝ አትሂጂ !!!" አለኝ በአሳዛኝ ንግግር።
እኔም ጥዬው የመሄድ እቅድ የለኝም ፈጣሪ ይመስገን ።
አነጋገሩ አሳዝኖኝ ወሬው ስላሳቀኝ በህልምህ አየከኝ እንዴ አልኩት ፈገግ ብዬ ።
" እኔኮ ከልቤ ነው እናቴ ልክ አጠገቤ ስትሆኚ ሁሉም ሰላም ይሆናል ።
ነገ ከዚ ትወጣለህ ተብያለሁ አንቺ ካለሽ ሁሉም ሰላም ይሆናል ተመልሼ ወደዚ ቦታ መግባት ስለማልፈልግ አትለይኝ !!....." ብሎ ውስጤን ነካው ።
ነገ ልትወጣ ነው አልኩት ሰስላልሰማሁ ተገርሜ።
ይሄን ሁለት ቀን በእናቴ ጉዳይ ተወጥሬ ረስቼው ስለነበረ ይመስለኛል እንደዚህ የሚለውም!!! ከዛም ተነስቶ ጥምጥም ብሎ አቀፈኝ።
ልክ እቅፉ ውስጥ ስገባ ያሳለፍኩትን ነገር በተለይም ያለ ፍላጎት የተወለድኩ ልጅ እንደሆንኩ ሳስብ የሆነ ነገሮች ይገለባበጣሉ ከሱ እቅፍ ውስጥ መሆኔ ሲጨመር ቀጥታ ወደ እሜ ገጋ ሄደን።
ቤኪ ወደኳ መቅረበ ፈርተቀ ዳር ላይ ቀሞ እያየን ነበረ።
ገብቼ ሳይ በጥልቀት ገብተው እየመከሯት እሷና አለምዬ አጠገብ ለአጠገብ ሆነው ዐምን እንደተባሉ ሳላቅ ሁለቱም እያለቀሱ ነበረ ።
ገና እንዳየዋቸው አሳዘኑኝና ሁለቱንም ምንም ሳልላቸው ተመልሼ ወጣሂኝ።
ከዛም ከቤኪ ጋር ሆነን ጊቤውን ዞሮነው ቢያንስ እሱ በጣም ደህና ነው ያንን ማየት ራሱ ለእኔ ደስ የሚል ዜና ሆነ።
ከቤኪም ጋር ተለያየንና ወደ እናቴ ሄድኩኝ ።
በጣም ለእረጅም ሰአትና ደቂቃ ያህል ስታወራ ስለነበር ቀለል እንደሚላት ተስፋ አደርጋለሁ።
እግሮ ስር ቁጭ ብዬ ነገሮችን እሰክትነግረኝ መጠባበቅ ጀመርኩ ።
እናቴ በዝምታዋ ግራ መጋባት ስጀምር አለምዬ ወደኔ ቀርባ
" አታስቢ ደህና ናት እሺ ከሆስፒታሉ ነገ እንወጣለን እሺ !!!!" እያለችኝ እያለ እናቴ ሳላስበው መሬት ላይ ብርክክ ብላ ድፍት አለች??????🥶🥶🥶🥶🥶.........
✍✍fidel
......
አንዳንዴ በልጅነት ካለፍንባቸው ወይም አድገንም በድግግሞሽ ከቆየንባቸው የህይወት ሁኔታዎች ተነስተን ሃዘንተኝነት፣ ቁጡነት፣ ድብርት፣ ጭንቀት ለረጅም ጊዜ የምንቆይበት ስሜት ሊሆን ይችላል።
ታሪካችን ግን መድረሻችንን ሊወስን አይገባውም። በሃሳብ ትናንት ላይ ከተቀረቀርን ነጋችንም መልሶ እራሱ ሊሆን ይችላል።
ታዲያ ዛሬ ለምን ደስታን አትመርጥም?
ቃል ህይወት ነው
እስቲ እንዲህ እንበል
"ዛሬ ላይ ደስታን ወደ ህይወቴ ግባ እለዋለሁ"
ደጋግም
ደጋግም
ደጋግም
(በፍፁም እጅ እንዳትሰጥ)።😍😍🙌🙌
🙋♀🎬🎬ሀምሳ
...........በምላሿ የተደናገጥኩት እኔ ክው ብዬ አየዋት።
እናቴ አይን ውስጥ የሆነ የተደበቀ ስቃይ አለ።
እናቴን በደንብ አቃታለሁኝ በእኔ ወይ በሆነ ነገር ካላስፈራራት በቀር እንዲህ አትልም !!!!
አንኗ ውስጥ ያለውን ሀዘን ያነበበው ሰለሞንም በእጁ የሆነ ምልክት ተናገረ ።
ወዲያው ፖሊሶቹ መሣሪያቸውን አቀባበሉ። ከነሱ መሀል አንዱ
" በሰላም መለቀቅ ከፈለክ በግድያ ሙከራ እንዳትጠረጠር ጩቤውን ጣል " ብሎ አስጠነቀቀው ።
" እኔ እንደዛ የማድረግ ድፍረቱ የለኝም እኔ ንፁህ ሰው ነኝ " ብሎ እጁን ባነሳበት 🙌 ቅፅበት ከየት መጣ ሳልል አንዱ ፖሊስ ጭምድድ አድርጎ ያዘው።
ከዛም እጁን ወደ ዃላ ጠፍንጎ ይዞ በካቴና አሰረው ።
" ባለቤቴ እኮ ናት በግል ጉዳይ ላይ ጣልቃ አትግቡ " እያለ ለህግ አስተማሪውች ህግ ሲያስተምር አሳቀኝ !!!!!
ወዲያው ከዛ አካባቢ ይዘውት ሲሄዱ እናቴ ተነፈሰች ።
ግን በጣም ጎድቷታል ስቅቅ ብላ አለቀሰች።
የኔ እንስፍስፍ ሮጬ ሄጄ አቀፍኳት ።
የዛኔ የምር አለቀሰችብኝ እኔም አብሪያት መሬቱ ላይ ድፍት ብዬ ተቃቅፈን ስናለቅስ አለምዬም ተጨመረችልን ።
ደስ የሚለው ወዲያው አንፑላንስ መጣ።
እውነትም ያስፈልገናል እኔ ውስጤ እየተጎዳ ነው ያለው ።
እሷ ደግሞ ስነ ልቦናዋ ተነክቶብኛል የኔ እናቴ እኔ ልንገላታላት በጣም ከመሰቃየቷ የተነሳ አቅሟ ተሞጣል ።
በመሀል አለምዬ ሁለታችንንም አቅፋ እንደ እናት አባበለችን !!!!
ከዛም ተረባርበው እናቴን መኪና ውስጥ አስገቧት።
እኛም በሰለሞን መኪና ተከትለናቸው ወደ ሆስፒታል ሄድን።
ምርመራ ተደርጎላት ታይታ የተለመደ ማንነቷ ላይ እስክትመለስ ጠበኩኝና ተመርምራ ልብሷ ተቀይሮ ስትጨርስ አለምዬ ስላለች ብዬ ሁለቱንም ስሚያቸው ወደ ጊቢ ሄድኩኝ።
ሰለሞንም ወደ ስብሰባ ሄደ ።
ልክ ብቻዬን ስሆን ቋጥሬ የያዝኩት እንባዬ አመለጠኝ።
ከስንት ሰአት ጀምሮ ኮ እናቴ ደህና ትሁን መጀመሪያ ብዬ ነበር ።
ዶርም ስገባ ማንም የለም !!!!
ሁኔታውን ተጠቀምኩበት ።
ያለ ምንም ከልካይ እሪ ብዬ አለቀስኩ!!!!
እናቴ ተጀፍራ ነው የተወለድኩት ብሎ ማመኔ ቀርቶ ሳስበው እንባዬን ለቀኩት ።
ወዲያው ከየት መጣች ሳልላት ጄሪ በሩን ክፍት አርጋ ገባች ?!!!
እንዳየችኝ በድንጋጤ ፊቷን አጨመደደችና ተንበርክካ አቀፈችኝ ።
በሰአተ በጣም ከፍቶኛል !!!!
አይምሮዬ ተረብሿል ማረገውን ባላቅም ሳለቅስ ሳለቅስ ቆየሁኝ።
ወደዚች ምድር የመጣሁበት ቀን እየረገምኩ ቆየሁኘ።
ሁኔታዬ ያስጨነቃት ጄሪ አይኔ ሚያማትርበትን አብራ እየተከተለች ስትጨቀጭከቀኝ ሁሉንም ነገር አውጥቼ ነገርኳት ።
እሷም ከእኔ እኩል ደንግጣለች ያለጠበኩት ነገር ስለሆነ ከብዶኛል ።
ጄሪ ግ ካልሄድን ብላ ውጥር አድርጋ ስትይዘኝ ተያይዘን ወደ ጤና ጣቢያ ሄድን ።
አለሜዬ አጠገቧ ቁጭ ብላ የተኛችው እናቴን እያየች ትክዝ ብላለች ።
አጠገቧ ያሉት ፖሊሶች እናቴን እያወሯት መሠለኝ ።
እሷ ፊት ላለማልቀስ ራሴን ተቋቁሜ ስሄድ ፖሊሱ እያወራ ነበር
" ስለዚህ እየንደሰማሽው በብዙ ነገር መክሰስ ትችያለሽ !!
የሚገርማችሁ................
✍✍fidel.....
🙋♀🎬🎬 ክፍል አርባ ዘጠኝ
............... " ተደፍሬ ነው የወለድኩሽ ልላት አልችልም !!!" ስትል ጆሮዬ ውስጥ ጥልቅ አለ ።
በፈጣሪ ስም ጆሮዬ ነው ብዬ ነበር ልቤ ለመተንፈስ እየተናነቀኝ በእጆቼ እየደገፍኩኝ ማዳመጤን ስቀጥል
" ያለፈ ታሪክ ለምን ታነሻለሽ ???" አላት እሱ በቁጣ ።
የለቅሶ እና የሲቃ ድምፅ ይሰማል ....
" ላንተ ያለፈ ታሪክ ነው ለእኔ ግን የማይረሳ ቁስል ነው ።
እኔ ለልጄ አላንስም !!! እንኳንም ወለድኳት ለበጎ ነው የተሰቃየሁት የምታስብል ልጅ አለችኝ !!!!
ነገር ግን እኔ ያን ቁስል ያንን ህመምና ጭካኔ መርሳት አልችልም !!!!!!!!
አንተን የልጄ አባት ብዬ መሠየምን አልችልም !!!!!!
አንተን እንደ ባል መቀበል አልችልምምምም !!!!!!
አይገባህም እንዴ " ብላ ትጮካለች
በአሁኑ በድንጋጤና በንዴት ፈዝዤ አልቀረሁኝም ይልቁንም በአይኔ ዞር ዞር ብዬ እሱን የምገድልበት ነገር ስፈልግ ነበር !!!!
አለምዬና ሰለሞን ደግሞ በድንጋጤ ፈዘው እኔን እያዩኝ ነው !!!!!
መጀመሪያ ላይ እንዳያስቆሙኝ የተረጋጋሁ ሰው መስዬ ዝም አልኩኝ ። አይኔ ግን ማማተሩን አላቆመም።
በስተመጨረሻም አሮጌ ቤት ስለሆን ከስሩ የቆርቆሮ ግንጣይና ትልቅ እና ወፍራም የበር መቀርቀሪያ የሚመስል ዱላ ላይ አይኔ አረፈ ።
መጀመሪያ ላይ ምን እንደማደርግ መዘጋጀትና ማሰብ ጀመርኩኝ ።
ሙሉ እቅዴን ከጨረስኩ በሀላ ሁሉንም በየተራ አይኔን እያማተርኩ አየዋቸው ።
ሰለሞን በጥቂት ጊዚያት በደንብ አውቆኛል !!!!!
የሆነ ነገር እንደማደርግ ስለሚያውቅ እኔን ለመያዝ ዝግጁ ሆኖ እየጠበቀ ነበረ ።
ክፋቱ ደግሞ ሰይጣን እኔን ለማሳሳት በውስጤ እያቀረታታኝ ነበረ ።
የእናቴን ንግግሮች ደጋግሞ በጭንቅላቴ እያመላለሰ ጭካኔ ላይ እንዳተኩር ይነግረኛል !!!!
ከዛ በላይ ያልቻልኩት እኔ ቀስ ብዬ ወዳየውት መምቻ ሄጄ አነሳሁትና ሮጬ ወደ ቤቱ ልገባ ስል በተጠንቀቅ ሲጠብቁኝ የኘበሩት ሰለሞንና ፊቱን ማያሳየው ጠባቂው ጭምድድ አድርገው ያዙኝ።
ልቀቁኝ በማያገባችሁ አትግቡ .... እያልኩ እሪ ብዬ ጮኩባቸው !!!!! ሰለሞን ግን ቀስ ብሎ በተደጋጋሚ
" ተረጋጊ ትንሽ ደቁቃ አትታገሺም እንዴ ነገሮችን አታበላሺ " ሲለኝ ነበር ።
በሰአቱ የጋለ ንዴት ላይ ያለሁት እኔ መረጋጋት ተስኖኝ በባዶ ሜዳ ሳንባርቅ ከውስጥ በኩል በዛብህ ያንን ፊቱኝ ከስክሶ ወጣ ከዛ ያለምን እፍረት ፊት ለፊታችን ቆሞ መለፍለፍ ጀመረ።
" ምን ታረጋላችሁ እዚህ??" አለን የሚገርም ነገር ነው ።
እማዬ እስከዛ ሰአት ከውስጥ አሎወጣችም።
ነይ ውጪ ብዬ ስጮክ ፊቷን እየጠራረገች ከቤት ወጣች።
ምን ያህል ሰአት እንዳለቀሰች ማወቅ አልቻልኩኝም አይኗ ደም መስሏል አብጧል በድጋሜ እንባዋን እያፈሰሰች ነው ????
በማይገባ ሁኔታ ከላይ ልብሷ ተቀዶ ፀጉሯ ልክ ያልሆነ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ....... ብቻ በአስከፊ ሁኔታ ውስጥ ሆና ተመለከትኳት ?????😭😭😭
እናቴ ሆና ማየት የማልፈልገው ሁኔታ ስለሆነ መታገስም አልቻልኩኝም እንባዬ ዱብ ዱብ እያለ መወራጨት ጀመርኩኝ ።
ከነሱ አንፃር እኔ አልታይም ሁሉ ለመፈንከት ስንፈራገጥ ሳላስበው በያዝኩት ቆርቆሮ የራሴን እጅ ቀደድኩት !!!!!!
እውነት ለመናገር በሰአቱ የእጄ ቁስል ምንምአልተሰማኝም !!!!!!
ነዛገ ብረት ስለነበረ ግን እጄ ደም መድማት ጀመረ ።
እንኳን ራሴ ላይ በዛ ልክ ይቅርና የመርፌ ደም ራሱ ይረብሸኛል ።
እጄን ያነችው የኔ የዋህ እናት ልታግዘኝ ልትመጣ ስትል ጋም አድርጎ ያዛትና በእጁ የደበቀውን ቢላ አውጥቶ
" እረፊ ቁሚ " ብሎ አስፈራራት ።
የዛኔ ከአቅሜ በላይ ሆነ ።
እናቴን እንዲ ሲያሰቃያት ቆሜ ማየት ለእኔ ህመም ነው !!!!!
አለምዬም እንባዎቿን ከአይኗ እየጠራረገች በየዋህ አይን ታየኛለች ።
እባክህ ፍቀድልኝ እናቴን እንዲ ማየት አልችልም !!!! እያልኩት እያለ በሩ በእግር ተመቶ ተከፈተ ።
ክው ብዬ ስዞር የሚያስፈራ መሣሪያ የያዙ የመአት ሰዎይ ከውጪ ገቡ ።
እኔ የቤኪ አባትና ራሱን የሚደብቀው ጠባቂ ጉዳይ ምንም አይገባኝም በምን ሰአት ተነጋግረው ፖሊስ እንደጠሩ አላውቅም !!!!!!
ሰዎቹ ክብብ አደረጉን በሰአቱ በነገሮች የተደናገጠው በዛብህ ደግሞ እናቴ ላይ ስለቱን ደቅኖ እንዳትጠጉኝ ብሎ እንደማስፈራሪያ ሊጠቀምባት ሞከረ ።
" ስህተት አትስራ መሣሪያውን አውርድ " አሉት ።
ምን አይነት ድፍረት እንደሆነ አላውቅም
" ምንም አላደረኩም ካላመናችሁ ጠይቋት " አለ ኮራ ብሎ ።
እኔ ፍጥን ብዬ የሚፈስ ደሜን በአለምዬ ሻርፕ እየቋጠርኩ
እማዬ ቶሎ ተናገሪ እንጂ ያደረገሽን ፍጠኚ አልኳት በተስፋ ተሞልቼ
" የተነጋገርነው አትርሺ " አላት ፈገግ ብሎ
ምን እንዳደረጋት ሳላቀው እማዬ አጎንብሳ
" ምንም አላረገኝም " አለች ??????????????????😣😣😣
✍✍fidel..........
🙋♀🎬🎬አርባ ስምንት
............ፍጥጥ እንዳለ ተገጣጠምን !!! ቀና ብዬ እንዳየውት አጠገቤ ድንጋይ ቢኖር ምነኛ ደስ ባለኝ ነበረ መሠላችሁ።
እሱም ምን ሊያደርግ እንደመጣ አላውቅም እሱም ሲያየን ክው ነው ያለው ።
አምሳል እንዳየችው
" አብዬ ያውና አባትሽ " ብላ እጇን ጠቆመች።
ሁሉም ዞር ዞር አሉ ።
እናቴ የት ናት ???? ብዬ ወደሱ መሄድ ልጀምር ስር ተመልሶ እየሮጠ መሄድ ጀመረ ።
እኔ ልከተለው ልሮጥ ስል የቤኪ አባት እጄን ያዘኝ ።
እናቴን እሱኮ ነው የወሰዳት እንያዘው እንጂ ልቀቀኝ ብዬ ላመልጠው ስሞክር በጠንካራው ያዘኝ ።
ሹፌሩ እና ሰለሞን ተያዩና እንደተለመደው ተግባቡ።
ወዲያው ሹፌሩ ሩጫ በሚመስል ርምጃ ተከትሎት ወጣና መኪና ውስጥ ገባ።
ለምን እንደሆነ አላውቅም በሱ ተማመንኩበት ???ሁለቴም ሳላስብ በቃ አሁን አንጠልጥሎ ይዞት ይመጣል ብዬ ተኩራራሁኝ ።
የሚገርመው በአንድ ጊዜ ሁሉንም ረስቼው ባይሆንም በሰለሞን ላይ ከመተማመኔ ብዛት ከደቂቃዎች ቡሀላ እናቴ ትመጣለች ብዬ ተኩራራሁኝ ።
ከዛም ቀለል ብሎኝ ወደ ቤት ሳይ በሩ ተዘጋ እንጂ አለመቆለፉን አስተዋልኩኝ ።
ከዛም ደስ ብሎኝ በሩን ከፈትኩትና አማትቤ ወደ ውስጥ ስገባ
ቤቱ እንዳልሆነ ሆኖ ተዘበራርቋል እቃው መሬት ተዝረክርኳል የተቀደደ ልብስ አለ ??? አልጋው ምኑ ብቻ ሁሉም ዝብርቅርቅ ብሏል የዛኔ ደግም ልቤ በከባዱ ተረበሸ ግን እናቴ ላይ እንደሟሟረት ቆጠርኩትና ምንም ነገር ላለማሰብ ወሰንኩኝ ።
ደግሞ ለካ የመንግስተ ሰማይ የሚመስል ቤት ውስጥ የሚኖሩ ባለ ትዳሮች በር ላይ ቆመዋል ።
አለምዬን እንግዳ ማለት አልችልም ቤቱን ከእኔ እኩል ታቀዋለች ።
ለእናቴ እንደ አለምዬ አይነት ሰው የሰጠ አምላክ ምን ይሳነዋል !!!!
ግራ ገብቶኝ ዞር ብዬ አለምዬን አየዋት ።
ሙሉ ተፈጥሮዋ ገራሚ ነው በተለይ ደግሞ ሳትነገር የምታውቀው ነገር !!!!!!!!
ወዲያው ቶሎ ወደኔ መጣችና ቤቱን አየችው ። እን ግራ ተጋብቼ የቆምኩትን አልፋኝ ወደ ውስጥ ገባችና ራሷ የገዛቻትን ወንበር ይዛ መታ ከበሩ ራቅ አርጋ አስቀምጣው ሰለሞንን እንዲቀመጥ ነገረችው ።
ከዛ አብራኝ ወደ ውስጥ ገባች ። ቤቱን በደንብ አየችውና
" ችግር ተፈጥሮ ነበር አቡ መስኪዬን ይጠብቅልኝ የኔ አባት !!!!" አለች እጆቿን ዘርግታ ወደ ላይ እያንጋጠጠች ።
ከዛ እቃውን አነሳስተን በትንሽ ደቂቃዎች ውስጥ
ቤቱን ፏ አደረገነው ።
ከዛ ቡና አቀራረበችና ከሰል አያያዝኩላት ። ከዛ ወደ ውስጥ እንዲገባ አደረገችው ።
እንደ ጎደኛ ቁጭ አርጎ ያን ሁላ ነገር አውርቶኝ ቤቱ ጠባብ ነው ምናምን ብዬ አልለውም ያለፈበትን ነገር ስለማውቅ መሠለኝ !!
ከዛ ገብተን ቁጭ ብለን አለምዬ ቀስ ያለ ጭስ የበዛበት የሚገርም ቡና አፈላች ።
ሁለተኛ ላይ ደርሰን እያለ በቀስታ በር ተነኳኳ።
እናቴ መጣች ብዬ ሰፍ ብዬ ስጠብቅ የሰለሞን ሹፌር ነው ።
ማውራት መቻሉን እጠራጠራለሁ በዝምታ ተመለከተኝ ።
ግራ ገብቶኝ ሰለሞንን ሳየው ሁለቱ ተያይተው ተግባቡና ተነስቶ ወጣ ።😂😂
ከምኖረው ህይወት ጋ በዚህ ልክ ብግባባ የት በደረስኩ ነበረ !!!!!!
ከዛም ሁለቱ ተያይዘው ሲወጡ አላስችል ያለኝ እኔ ቸከትያቸው ወጣሁኝ ።
የእኔ አፍ ዝም እንደማይል ያወቀችው አለምዬ ደግሞ ከትላኝ መጣች ።
ከዛ ወተን አራታችንም ተፋጠጥን ።
ለካ በዝምታው ውስጥ ራሱ ከሰለሞን ጋ እያወሩ ነበረ መሠለኝ
..........
" ችግር የለውም ቀጥል " እስከሚለው ጠብቆ ዝምታውን ሰበረ ።
ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፁን ልሰማው ስለሆነ በጣም ቸኩያለሁ አልዋሽም ። !!!!
" ተከትዬዋለሁ አላወቀም " ብሎ በአጭሩ ወሬውን ቋጨው ።
ድምፁ ያምራል ግን የጠበኩት ንግግር ይሄ አልነበረም ።
ስለ እናቴ አንድም ቃል አልተናገረም ለምን ?????
እናቴስ አልኩት አይን አይኑን እየተመለከትኩኝ ።
እሱ በዝምታ ወደዃላ ሲሸሽ ሰለሞን ፈጠን ብሎ
" ይዘናት እንመጣለን እወቂ ግቡና ጠብቁን" ብሎ መንገድ ሲጀምር
አይ አኔም እመጣለሁ ብዬ እሪ አልኩ አማራጭ አልነበረውም ሁለታችንንም ይዘውን ሄድን ።
በመኪና ትንሽ ተጓዝንና የሆነ ቦታ ሲደርስ መኪናውን አቆመው ።
እዛ ምን ልናረግ እንደሄድን አልገባኝም???በዝምታ ወደ ውስጥ ልንገባ ስንል
" ተደፍሬ ነው የወለድኩሽ ።
✍✍✍fidel .....
........ ብቅ ብቅ ብለው አይተውኝ ክው ብለው ተመለከቱኝ ።
በእናቴ ጉዳይ በጣም ደካማ ነኝ !!!! በዛች በአንድ ቅፅበት በአስተያየታቸው ብቻ ብዙ ነገር አስቤ በአንድ ጊዜ አይምሮዬን አሳመንኩት ።
ሰለሞን ነገሩን እንደኔ በአንዴ መፍረድ አልፈለገም የኔን ዝምታ ለመስበር በሚመስል መልኩ
" ወ/ሮ .." ዞር ብሎ አየኝ ።
ሲያየኝ መልሼ ፍጥጥ ብዬ አየሁት ።
" ስማቸው ማን ነበር ?" አለኝ ።
እ የማ መስከረም ማለቴ መሰረት እያልኩ ስርበተበት እሱ ቀልጠፍ ብሎ
" ወ/ሮ መሠረት የሉም እንዴ " አላቸው ።
በጣም ትልቅ ሰው ነው ።!!!!! ትልቅ ሰው ሆኖ ባለ ስልጣን ሆኖ የጊቢው አስተዳደር ሆኖ እንኳን ያልሰጠሁትን አክብሮት ለእናቴ ሰጠልኝ !!!
ጎረቤቶቻችንም ከመመለስ ይልቅ በዝምታ ተመለከቱን ።
ነገሩ የበለጠ ረበሸኝ ። ስደነግጥ ራሴን መቆጣጠር ስለማልችል እጄ መንቀጥቀጥ ጀመረ ።
" ተረጋጊ እንጂ ልጄ ህይወትን መጥፎ ብቻ አርገሽ አትሳያት ከመፍረድሽ በፊት ጠይቂ " ብሎ በእጆቹ ትከሻዬን እያሻሸ አበረታታኝ ።
" ወዴት ሄዳ ነው የሚመልስልኝ የለም ?" አለ መልሶ በትህትና ።
የኛ ሰፈር ሰዎች አሁንም ዝም አሉ ።
በእርግጠኝነት ባለ ስልጣንና ባለ ሀብት እንደሆነ ቢያውቁ እሩቅ ቆመው ባላዩት እንድል አደረጉኝ !!🙌🙌( እኔ አላልኩም )!!
የዛኔ ዝምታቸው ከኔ ዝምታ ጋ እንደማይገጥም የተረዳሁት እኔ ወደ ውስጥ አየር ስቤ እናቴን የምትቀርባት ሴት ላይ አፍጥጬ
አምሳል እናቴ የት ናት ? አልኳት ። ስናደድ በደንብ ስለምታውቀኝ
" መጀመሪያ ተረጋጊ ቆይ ያምሻል የኔ ቆንጆ ተረጋጊ " አለችኝ ።
ከአቅሜ በላይ ከሆነ መንቀጥቀጥና ማልቀስ ነው የሚያረጋጋኝ ።
ለዛ ትክክለኛ ሰአት ስላልሆነ ራሴን ለመቅጣጠር ሞከርኩኝ ።
እሺ ንገሪኝ ደህና ነኝ !! አልኳት ለማወቅ እየተዘጋጀው ።
" ትላንት አባትሽ መቶ ነበር ..." ንግግሯን አላስጨረስኳትም ።
አባቴመ እናቴም እሷ እንደሆነች ታቂያለሽ እኔ አባት የለኝም !!!!ብዬ መለስኩላት ።
በአሳዛኝ እይታ ተመለከተችኝና ንግግሯን ቀጠለች።
" እና ትላንት በጣም ተጣልተው ሲጨቃጨቁና ሲመታትም ነበረ ከዛ ሲመሽ ሄደና ገና ወፎች ሳይንጫጩ መቶ እየጎተተ ይዟት ሄደ " አለችኝ እንደ ቀላል
ነገር ????????
ንግግሯ ግልፅ አደለም ለእረጅም ደቂቃዎች ያህል ስታወራ ተሳስታ ነው ብዬ ነገሮችን ለመረዳት ስሞክር ነበረ ።
ማለት አልኳት ግራ ገብቶኝ ። ጭራሽ ይባስ ብላ
" ይዟት ሄደ ይሄው እስካሁን ስንደውል አታነሳም ሰው እንዳይሰማ ብለን ዝም አልን "" ብላ ንዴቴን አባባሰችብኝ ።
የዛኔ ከልጅነት እስከ እውቀት በትህትና በእርጋታ በሰከነ ማንነት በሰው አክባሪነት ...... የምትታወቀው ጨዋዋ አብላካትን ደበኳትና
እንዴት ማንም መቶ ሲወርዳት ዝም ትላላችሁ ????......እንዴት እናቴ ስትመጣ ዝም ትላላችሁ ????...... እናቴ ለአንቺ ስትል እንባዋን እስከማፍሰስ አልደረሰችም የምር እንደዛ አይነት ሰው ነሽ !!!!!!?????ብዬ አበድኩባት ።
ሀገር አማን ብላ ባዶ እጅ የማታቀው አለምዬ በሁለቱም እጇ ፌስታል አንጠልጥላ ያ ድንቡሽቡሽ ጉንጯ ፈገግ እንዳለ ወደ ውስጥ ስትገባ አይን ለአይን ተገጣጠምን ።
ድርቅ ብላ ነው የቀረችው ።
ሴት መሆን እንዲህ ነው በእይታ ነገሮችን እናውቃለን ።
ከዛም በፍጥነት ወደኛ መታ ፌስታሎቹን መሬት በትናቸው
" አባ ...... አቡ " እዚህ ምን ታደርጋላችሁ ምን ተፈጠረ መስኪ ምን ሆነች ????....." ብላ የጥያቄ መአት አዘነበችብኝ ።
እሷ ውስጥ የእናቴን የዋህነትና እናትነት አየሁ የዛኔ የሆነ አካሌ ተቆርሶ ሊወሰድ መስሎ ተሰማኝና ድካሜን ከዛ በላይ መደበቅ አቅቶኝ እንባዬ አመለጠኝ ።
ካለቀስኩ እንደሚያመኝ ስለምታውቅ አምሳለ የምትባለው ሴት ወደኛ እየቀረበች
" ያምሻል እንዳታለቅሺ እባክሽ " ብላ ልታረጋጋኝ ሞከረች ።
በሰአቱ ለእናቴ የሚደርስ አንድ አካል ማጣቴ ለኔ አስከፍቶኛል !!!
በዛ ላይ እናቴ ብትሆን እስከ ሞት ተከትላቸው እንደምትሄድ ሁሉም ያውቃሉ !!!!
ሴትዮዋ እንዳትጠጋኝ ጮኩባት ።
እንደመደንገጥ ብላ ወጀ ዃላ ሸሸች ።
አለምዬ እቅፏ ውስጥ አስገብታ እንባዬን ተጋራችኝ ። !!!!!የኔ የዋህ !!!!!
የዛኔ ሰለሞን ቀና ብሎ ሹፌሩን ሲያየው ወዲያው ወደ አለምዬ መጣና መኪና ውስጥ እንድትገባ ምልክት ሰጣት ።
" አይ መስኪን ሳናገኝ የትም አንሄድም !!! የሆነ ነገር አድርግ እንጂ !!" ብላ ሰለሞን ላይ አፈጠጠችበት ።
ዝም ብሎ ትንሽ አሰላሰለና
" የሆነ የሰማችሁት ስም የለም ነቦታ ስም ።????
ሰውዬው የት እንደሚኖር አታውቁም ?" ብሎ ሁሉንም በየተራ አያቸው ።
ወሪያቸው ካላለቀ ከአቦል እስከ አራተኛ የሚያፈሉ ሰዎች በዛ በችግርና በጭንቀት ሰአት ሁሉም አፋቸውን ዘግተው ይመለከቱኛል ።
ከዛ በላይ መቆጣጠር አቅቶኝ ለመሳደብ ስነሳ አባቴ የሚባለው ሰውዬ ፊት ለፊት ግትር ብሎ በድንጋጤ ፍጥጥ እንዳለ ተገጣጠምን ???????.....
✍✍fidel........
1. ፈልገኝ እንጂ አታሳደኝ
2. ስራልኝ እንጂ አትመኘኝ
3. ጠብቀኝ እንጂ አታጣድፈኝ
4. ያዘኝ እንጂ አትበትነኝ
5. ስራብኝ እንጂ አታባክነኝ
6. ተጠቀምብኝ እንጂ እዩልኝ አትበለኝ
7. አሰራኝ እንጂ አፍነህ አታስቀምጠኝ
8. ከምንም በላይ እንደከብርህ አክብረኝ
የገንዘብ_አጠቃቀም_ጥበብ
🏆🏆🏆🥂 ገንዘብ ሳይኖረን ስለ አጠቃቀም ጥበብ ላነበብነው 👆👆😂😂
🙋♀🎬🎬አርባ ሰባት
.......... ከእንቅልፌ ቀሰቀሰኝ ። ከሆነ ጊዜ ጀምሮ ማንኛውም ድምፅ የረብሻና የችግር ድምፅ መስለው ነው የሚሰሙኝ !!!
ነርሷ የቤኪን ሁኔታ ለማየት በሩን ስትከፍት እኔ እንደ ጦርነት ድምፅ አይቼው በጣም ተረብሼ ነበረ ።
በድንጋጤ ብርግግ ብዬ ስነሳ እንቅልፍ አልወስድ ብሎት የሚቁለጨለጨው ቤኪ በሚያሳዝን ፊት እያየኝ ነበር የኔ አባት ።
በጣም እንደደከመው ፊቱ ላይ ይነበባል !!!
ቀስ ብላ ገብታ የሆነ የሆነ ነገር አየችና በፈገግታ ተሞልታ
" በጣም ደህና ነህ እንኳን ደስ አለክ " አለችው ።
አንድ ቦታ ለሰአት መቆየች የማይችለው ልጅ ተኝቶ መዋል ሰለቸው መሠለኝ
" ነገ ከዚ መሄድ እችላለሁ ነርስ በእናትሽ " አላት በሚያሳሳ ድምፅ ።
ብችልና ህመሙን ተጋርቼው ከዛ አልጋ ላይ ወርዶ ቢንጎማለልብኝ ደስ ባለኝ ነበር!!!!
ከዛ መልሼ ብተኛም እንቅልፍ እንደማይወስደኝ ስላወኩኝ ወርጄ ወደ ቤኪ ጋር ሄድኩና እጁን ይዤ ቁጭ አልኩኝ ።
ነርሷ ግሉኮሱን እየነካካች ቀና ብላ አየችንና
" እህት እኮ ሁሌም ከጎን ናት ማነው ታላቅ ?" አለችን ።
ሁለታችንም በፈገግታ እየተመለከትናት ማን ይመስላል አልኳት ቀስ ብዬ
" ወንዶች እየረዘሙ ስለሆነ በቁመት ብቻ እድሜ አይገመትም ብዬ ነው እኮ " አለችን ።
ደስ የምትሕ ሰው ናት በአንዴ ተቀራረብን ማለት ይቻላል ቀለል ብላ ነው የምታወራው ።
ቤኪም ቀጠል አድርጎ
" ከሁለታችን ማነው ቆንጆ " አላት ።
" የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ለእናንተ ቤት አይሰራም መሠለኝ ሁለታችሁም በጣም ነው የምታምሩት እኮ " አለችን በአድናቆት እየተመለከተችን ።
እናመሰግናለን ብዬ ዝም አልኩኝ እኔ ። ነርሷ
ጨራርሳ ልትወጣ ወደ በሩ ስትጠጋ
" ለማንኛውም እህቴ ሳትሆን ፍቅረኛዬ ናት በቅርብ የምንጋባ ይመስለኛል " ብሎ የኔንም የሷንም ቆሌ ገፈፈው !!!!!
ነርሷ ቀልድ መሠሏት መሠል ፈገግ ብላ ልትወጣ አለችና መለስ ብላ የምርህን ነው ??? አለችው ።
" አዎ ማርያምን " አላት ። ደስ የሚለው እሷም አልተመቀኘችም በፍቅር አይን እያየችን
" ያዝልቅላችሁ አረ ክፉ አይያችሁ !!!"። ብላን ከክፍሉ ወጣች ።
ወዲያው ቤኪ ወደ እቅፉ ስቦ ግንባሬን ሳመኝና ደረቱ ላይ አስተኛኝ ።
መልሶ እንቅልፍ ይወስደኛል ብዬ ባልገምትም ጠዋት በሰለሞን ጉትጎታ ነው ከቤኪ እቅፍ ውስጥ ከወሰደኝ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰደኝ ።
ዛሬ ቤኪም ነቃ ብሎ ነው የነቃው ።
በትንሹ የተሻለው ይመስል ነበረ !!!
የሚደራረጉ ነገሮች ተደርገውለት ዙሪያውን ክብብ አድርገን ቁጭ ብለን እያወራን ነበረ !!!
ቀኑ ረቡዕ ነው በድንገት የሰለሞን ስልክ ጠራ ።
ድክም ዛልልል ባለ ድምፅ አነሳ
" ሀሎ " አለ በጎረነነ ድምፁ
ከዛኛው ወገን ምን እንደተባለ አላውቅ
" ወይኔ ዛሬ ነው እንዴ ስንት ሰአት " አለ ከተቀመጠበት እየተነሳ ።
ትንሹ እሱን ዝም የሚያስብሉ የሰከነ ንግግሮች አካሄደና እሺ እሺ ብሎ ስልኩን ዘጋው ።
ወዲያውኑ ከኔ ቀድማ አለምዬ
" ምነው አባዬ " አለች።
" ዛሬ ረቡዕ መሆኑን ረስቼዋለሁ እኮ በእናታችሁ በሉ በሉ ልጆች ሶስታቹም ፍጠኑ ወደ ጊቢ ተመለሱ " ብሎ አዘዘ ።
አይ እኔ ከቤኪ ጋር ነው የምቆየው አልኩ ኮራ ብዬ ከነሱ በመቅደም ።
" እኛ እዚሁ እንሆናለን " አለ ያቤፅም ቀጠል አድርጎ ።
" ተነሱና ሂዱ አልኩ እኮ ዛሬ ፋይናል ፈተና እንደሚጀምር ረስታችሁታል አይደለ አሁን ግን አስታወስኳችቱ ስለዚ ምንም ጎበዝ ተማሪ ብትሆኑሞ የሆነ ነገር እዩና አስታውሱ ጥሩ ውጤት እንጠብቃለን!!!!!
እውነት ለመናገር ሙሉ በሙሉ ረስቻለሁኝ ። ከዛ አማራጭ ስለሌለኝ
እስክመለስ ጤነኛ ሆነክ ጠብቀኝ !!! ብዬው ወደ ጊቢ ሄድኩኝ ።
የሚያስጠላው ደግሞ ሀሳቤን መሠብሰብ ይከብደኛል እንዴት ብዬ እንደምሰራውም ሳላቅ ዶርም ሄጄ አየት አየት አረኩትና ተመልሼ ወጣሁ ።
ከዛም ፈተናዬን ተፈተንኩና ተሰብስበን ቢኪ ጋር ሄድን ።
ልክ ስገባ
" እናትዬ ናፍቀሽኝ ነበር እኮ "ብሎ እዛ ሁላ ሰው መሀል አሳፈረኝ ።
በትንሹ ፈገግ ብዬ በዝምታ አለፍኩት ።
ከዛም ስናወራ ስንቃለድ ቆይተን ሰአቱ ሲሄድ ጊዜ እናቴ ጋ መሄድ ነበረብኝ ።
ቃል ገብቼላታለሁኝ ።
ብቻዬን መሄድ አልፉኩኝም !!! ሰለሞንን አድርሰኝ አብረን እንሂድ ብሎ መጠየቁ ስለደበረኝ ፊት ለፊቱ ቆሜ ስለ እናቴ ሳወራ ነገሩን የተረዳው የቤኪ አባህ ተነስቶ አብሮኝ ወጣ ።
ሹፌሩ እየነዳ ከዃላ ተቀምጠን በፀጥታ መንገዳችንን ቀጠልን ።
ፈተና እንዴት ነበር ???አለኝ ።
እንደፈራሁት ስላልነበር
ቀላል ነው ብዬ ነው የመለስኩት ።
ከዛ ከጉዞ ቡሀላ እናቴ ጋ ደረስን ።
በጣም ናፍቃኝ ስለነበረ እየሮጥኩ ሄጄ በሩን አንኳኳው ።
አይከፈትም ???
ደጋግሜ ሳንኳኳ ከኛ ጎረቤት ያሉ ሰዎች ወጡና እንዳዩኝ ክው ብለው ተመለከቱኝ ?????
✍✍✍fidel......
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ፊደል✍✍» is a Telegram channel in the category «История», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 1.8K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 11.4, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 18.0 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий