

Channel statistics
Full statisticschevron_rightክፍል አርባ
........ደርቄ ቀረሁ ። በሰአቱ ራሴን የትም ሆነ እንዴትም ልደብቅም ሆነ ከአቶ ሰለሞን ልደብቀውም ሆነ እንዳያየኝ ላደርግ አልችልም!!!
በሰአቱ ያለኝ አማራጭ ቆሞ መጠበቅ ነበር !!
ልክ አባቷን በጉጉት እንደምጠብቅ ህፃን ልጅ በር በሩን እያየሁ ቆሞ መጠበቅ ነበር !!!
የልጁን ጤንነት ለማየት ተቻኩሎ የመጣው አባት ከዶክተሩ ጋር እያወራ በሩን ክፍት አድርጎ ገባ ።
ያቤፅ ደግሞ ከዃላ በድንጋጤ ቆሞ ምን ላርግ??? በሚል ፊት ይመለከተኛል !!!!
እኔ ከደነገጥኩት ባልተናነሰ ሁኔታ እሱም ደንግጧል ።
ለምን እንደዛ ሊለየን እንደፈለገ ባላውቅም የአመታት ጠላቱን እንዳየ ደመኛ ቀጥ ብሎ ቆሞ ፊቱን አጨማዶ ያየኛል !!????
ምን እንደማረግ ምን እንደምል የማላቀው እኔ አሁንም ግራ በመጋባት ስሜት ተሞልቼ ቆሜ እያየዃቸው ነው !!!!!
መፍትሄው እንደሆነ ሳናወቅ በመፋጠጥ ብቻ ደቂቃዎችን አባከንን !!!
ከዛም በቀስታና ግርማ ሞገስ በተላበሰ አረማመድ ወደኛ መምጣት ጀመረ።
ለዛ ቀን ሲባል የቤት ግድግዳ በአንድ በኩል ክፍት ቤሆን ኖሮ ብዬ ተመኘው !!!!!
እሱም አልበቃ ብሎ ምን አለ መሬት መደበቂያ ቦታ ቢኖራትም ብዬ ተመኝቻለሁ !!!!
ፊቱ ቀለል ያለ እና መልከ መልካም ቢሆንም ከዚ በፊት የተለያየንበት ሁኔታ ጥሩ ስላልነበረ እፈራዋለሁ !!!
አጠገቤ እንደደረሰ በጥፊ የሚያጋጨኝ መስሎ ተሰማኝ !!!!
ያቺ ትንሽ ቤት ራቀችብኝ ። !!!!!!
ከበሩ እኔ ጋር እስከሚደርስ ያለው ርምጃ ረዘመብኝ !!!!!!
ከስንት የልብ ምትና ፍራቻ ቡሀላ አጠገቤ ደረሰ ።
በቤኪ በግራ በኩል ቆመ ። እኔ በቤኪ በቀኝ በኩል ቆሜ እያጎረስኩት ነበረ !!!!
በስተመጨረሻም ፊት ለፊት ተፋጠጥን !!
" እዚህ ምን ታደርጊያለሽ ??"" ብሎ ዝምታውን ሰበረው ።
እ አይ እ ... እያልኩ የ አ ቤት ፊደላትን ጥሪ የተባልኩ ይመስል እ አይ እ እያልኩ እቀባጥራለሁ !!!!
" ባለፈው ቀን አላደመጥሽኝም መሠለኝ !!" አለኝ ። አሁንም የኔ መልስ ዝምታ ነው
በኩራት ከጁ ላይ ሰአት እየተመለከት
" ብዙ ሰአት የለኝም ግን እባክሽ ብቻሽን ላናግርሽ " አለኝ ?????
አሁን የበለጠ ፈራሁኝ ። !!!!!ግን አሁንም ቃል አላወጣሁም ዝም ብዬ አየዋለሁ ።
" እባክሽ " አለ እጁን ወደ በሩ እየዘረጋ ።
ምን ያርገኝ ምን ይበለኝም ሳላውቅ ቀጥጥጥ ብዬ ወጣሁ ።
ከዛ እጆቼን አጣምሬ አይኔን መሬቱ ላይ ተክዬ ቀረሁኝ ።
ከዃላይ ቀስ ብሎ መጣና ፊት ለፊቴ ግትር አለ ።
" የምትፈልጊውን ያሆል ገንዘብ እሰጥሻለሁ ስንትም ይሁን የአንቺንም የእናትሽንም ህይወት የምትቀይሪበት ገንዘብ ልስጥሽ ብቻ ከልጄ ራቂ "" አለኝ ???!!!!
ጭራሽ ያልጠበኩት ንግግር ነው ።
ሰው ሲያከብረኝ ነው የማከብረው ።
የነበረውን ሞገስ በአንዴ አጣ !!!!
ለሱ የነበረኝ ክብር ዝቅ ሲል ቀና ብዬ ተመለከትኩት !!!!!
ምን ማለት ነው ፍቅር በገንዘብ አይገዛም እሺ ?!!!!!!!
አለምዬን በገንዘብ ነው የገዛሀት እንዴ እ !!!!!
ሌላ ሰው እንዳይሰማ !!!
እኔ ማንነቱን እንጂ ያለበት ደረጃን ወይ ሌላ ነገሮች አደለም የወደድኩት !!!
ብዬ ተመልሼ ስገባ ...........
✍✍fidel........
ጠዋት ተገናኝተን ምሳ አብረን በልተን ሲመሽ ልለይሽ ነው ልቤ ፈራ የምትለው ልጅ.......አሁን ግን በሳምት አንዴ ተገናኝተን ተጣድፈህ መተህ ተጣድፈህ ስትሄድ ግራ ይገባኛል።
አይንሽን ባየው ባየው....እያልክ...እያሳከኝ እንዳልዘፈንክ....ምን አድርግ ነው የምትይኝ ሴትዮ ስትለኝ...ሌላ ሴት"ዮ ፍለጋ አይኔ ይንከራተታል። ብቻችንን እንደሆንን ሳይ ከራስህ ጋር ያወራህም ይመስለኛል....እኔንማ ሴትዮ አትለኝም..."
እወድሻለሁ ካጣሁሽ ሰው አልሆንም...ህይወቴ ያላንቺ ባዶ ናት ....የእናቴ ምትክ ነሽ ያለኝ አንደበትህ....አሁን አሁን ግን እወድሀለሁ ስልህ....እሺ ሲሆን መልስህ እደነግጣለሁ....!
ከእግር እስከራሴ ቀን በቀን የምታደንቀኝ ልጅ...ፎቶሽን አቅፌው ተኛሁ የምትለኝ ልጅ አሁን አሁን ግን....እንከን ፍለጋ አትኩረህ ስታየኝ...ከሌሎች ሴቶች ጋር ስታወዳድረኝ ከኔ ለመራቅ መንገድ የጀመርክ ይመስለኛል ...።
እርግጥ ነው...ኮኮቦች ሲፈጠሩ ፈዘው ያዩቸው መላዕክት ዛሬ ፈዘው አያዩአቸውም....።
እኔም ሁሌ ፈዘህ እየኝ እያልኩህ አይደለም። ግን ትኩረት ስትነፍገኝ ያለ ፍላጎት የተለጠፍኩብህ ይመስለኛል። የሰለቸሁህ ሲመስለኝ ልቤ ይሸበራል።....ሳልፈካ የከሰምኩ አበባ አይነት ስሜት ይሰማኛል።
ሴቶች ውብ ሆነው ለመታየት ይሄንን ያህል ለምን የሚለፉ ይመስልሀል...?
fashion industry እንዴት እንደዚስ ተስፋፋ...? በከተማው የውበት ሳሎኖች ለምን እንዲ በረከቱ...?
ሴቶች በውበታቸው ስለማይደራደሩ....ከአንተ ጋር ልንገናኝ ስንል መስታወት ፊት ስንት ሺ ጊዜ እንዲ ልሳቅ እንደዛ ብዬ እንደገለፈጥኩ ታውቃለህ...?
ሊፒስቲኬን ስንቴ አስለቅቄ ስንቴ እንደተቀባሁትስ...? ፀጉሬን ለማስያዝ ምን ያህል ጊዜ እንደፈጀብኝስ...?
ስንት ልብሶችን እንደቀያየርኩስ...?
ከአንተም ብሶ ቶሎ አትወጪም ብለህ ትነጫነጫለህ...በፊት ስንገናኝ በሊጥ ታጥቤ ብመጣም የኔ ቆንጆ ብለህ የአድናቆት ቃል እንደማታዘንብ...... አሁን አሁን ግን ከአጠገብህ ስደርስ ሽቶው አልበዛም ብለህ አፍንጫህን ለመያዝ ይዳዳሀል።
እንዲ ስትለኝ .." መንገድ ላይ ልሸኝሽ ካሉኝ ወንዶች ከአንዱ ጋር በመጣሁ ብዬ እብሰከሰካለሁ....አንዳንዴማ እንዳንተ በሎሚ ተፈግፍጌ ልምጣ ወይ ልልህ ምላሴ ላይ ይደርሳል .....
ምን አልባት እንዲ የልብ ልብ የተሰማህ ከእንግዲህ የእኔ ናት የትም አትሄድም ከልቧ ወዳኛለች ብለህ ይሆናል ...ግን አስተውል።
የወደድኩት ይሄንን ማንነትህ አይደለም።
ወድጄው የነበረው ማንነትህ ሌላ ነው። የሚያከብረኝ የሚወደኝ የሚሳሳልኝ ሌላ ሰው።
አሁን ባለህ ባህሪ ተዋውቀን ቢሆን ለሰላምታም ከአንተ ጋር የማጠፋው ጊዜ አይኖረኝም ነበር።
አንተ በዚ መንገድ መቀየር ከቻልክ....እኔንስ ትወደኛለች የትም አትሄድም ብለህ በእኔ በዚ ልክ እርግጠኛ ሆንክ እእእ...???
የወደዱትን መውደድ የቻለው ልቤ የተውትን መተው የጠሉትን መጥላት እንደሚችል ለምን አላሰብክም።
ግንኙነቶችን መቀጠል እንጂ መቁረጥ ጊዜ አይፈጅም።
ጓጆ መስራት ነው ከባዱ
ጊዜ አይፈጅም ለመናዱ...አብዱኪን አልሰማሀውም...?
ያንተ የሆንኩት በፍቃዴ እንጂ ማንም አስገድዶኝ እንዳልሆነው ሁሉ አብሬህ እንድቆይም ማንም አያስገድደኝም።
መራቅህን የማልወደው መቅረብ ስትፈልግ ነው። መሄድ ከፈለግ ግን መንገዱን ጨርቅ ያርግል...!
እሺ...!
❤️ like endayresa
2⃣📍ተፈጥሮ፣ ጊዜና ትዕግስት ሶስት ታላላቅ ሐኪሞች ናቸው።
3⃣📍ፍቅር፣ ገንዘብና ህመም ሚስጥር ሆነው መቆየት
አይችሉም፤ በፍጥነት ራሳቸው
4⃣📍እውነት ጫማውን እስከምታጠልቅ ድረስ ሃሰት በፍጥነት
ታዛመታለች።
5⃣📍ከፊትህ ስላለው መንገድ ለማወቅ በመንገዱ ያለፉትን ጠይቅ።
6⃣📍ጎረቤቶችህ እነማን እንደሆኑ ሳታውቅ ቤት አትግዛ።
7⃣📍ፀሓይ የምትወጣው ለሁሉ ነው።
8⃣📍ፀጥ ያለ ባህር አዞ የለውም ብለህ አታስብ።
9⃣📍ውድቀት ከባድ ቢሆንም ለመነሳት አለመሞከር ደሞ የከፋ ነው።
🔟📍 በጨለማ ሁሉም ቀለሞች አንድ ናቸው።
.......እጄን መጎተት ሲጀምር ከዛ በላይ ዝምታን ያልቻለው ቤኪ አባዬ !!! ብሎ ጭክ አለ።
የቤኪ አባት ኮስተር ሲል በጣም አስፈሪ ግዙፍ ነው !!!
ግንባሩን አጨማዶና ቅንድቡን ሰቅሎ ወደ ቤኪ ዞረ ።
እንዳይመታው ፈርቼ ነበር ግን በአባት እና በልጅ መሀል መግባት ስላልፈለኩኝ ግራ እየተጋባሁ እያለ ያቤፅ መቶ በአንድ እጁ እኔኔ በአንዱ እጅ ጄሪን ይዞ እየጎተተ አስወጣንና በር ላይ
"ገና ወደዚ ከመመለሱ ድጋሜ እንዲሄድ አታድርጊው በእናትሽ !!!!! " አለኝ ።
ምን አድርጌ ያቤፅ እ አልኩት መደበቅ የማይችለው አፉ ሁሉንም ነገር ነገረኝ ።
ቤኪ ወደ ውጪ የመሄዱና ትምህርት አቋረጥ የመቅረቱ ምክንያት እኔው መሆኔን ተናገረ!!!
ለካስ አባቱ ከእኔ ጋር አይቶት ነው ከአባቱ ጋር ተጣልቶ ጥሎኝ ለመሄድ የሞከረው ።!!!!
እናም ያቤፅ በቀስታ አረጋግቶ ነገረኝ !!
" ድጋሜ ችግር ውስጥ ከገባ ላይመለስ እንደሚልከው ተናግራል እሱ ደግሞ ካወራ አወራ ነው ።!!!" አለኝ
ከዛ በላይ ችግር መፍጠሩንም ሆነ ቤኪ እንደዛ ሆኖ ማየት አልችልም !!!!!!
ስለዛ ከጄሪ ጋር ተያይዘን ቀጥ ብይ ከዛ ቦታ ወጣሁኝ ።
ሁሉም ነገር አስከፍቶኛል በጣም ከባድና አሳዛኝ ቀን ነው ያሳለፍኩት !!
ከዛ ቀን ቡሀላ ቤኪን እንኳን በስርአት ማውራት አልቻልኩኝም !!!
ልክ አባትየውና ዶክተሩ ከዛ ክፍል ሲወጡ ያቤፅ ይደውልልኛል ገብቼ ስሜው ናፌቆቴን ተወጥቼ ቁስሉን ዳብሼ ነካክቼ አውርቼው ለማስታወሻ እያልኩ ፎቶ እያነሳሁት ......ብቻ በተመሣሣይ መንገድ እስስከ ሳምንት ድረስ በአንድ አይነት ሁኔታ ቀጠልን ።
ቀስ በቀስ ቤኪ እያገገመ መጣ ።
የኔ አካልም ልቤም ቀልቤም ሁሉ ነገሬ ቤኪ ጋር ሆኖ ትምህርቱን እየተውኩት መጣሁኝ ።
ተደብቄ ገብቼ ስንጫወች ሰንስቅ እየቆየን ስለነበር መማርን ረሳሁት !!!!
ፈተና እንደደረሰ ሰሰማ ብቻ የገረፍታ ንባብ እያነበብኩ ባለችኝ ጭንቅላት ፈተናውን ሰራሁት ።
በቀጣዩ ቀን ሌሌት የቀሰቀሰኝ የእናቴ ስልክ ነበር ።
ስለ ቤኪ ነግሪያት ስለነበረ ስለሱ አጥብቃ ጠየቀችኝ እኔም ደህና መሆንኑን ነገርኳት ።
እንደለመድኩት ሀገር አማን ብዬ ከጊቢ ወጥቼ የምገዛውን ገዛዝቼ ምግብ ቴክአዌ አድርጌ ወደ ቤኪ ጋር ደረስኩ ።
ሳየው የሚያሳዝን አስተያየት ተኝቷል ።
ትንሽ ቆይቼ እቀሰቅሰዋለሁ ብዬ ምግቦቹን መብያ ወንበሮቹ ላይ እየደረደርኩ እያለ ስልኬ ጠራ
ቀጥታ አነሳሁት ። ሄሎ ....
" አባትሽ ነኝ !!" አለ ።
እባክህ ዛሬ ደስ የሚል ጅማሮ ላይ ነኝ እና ማዘኔ አልፈልግም!!!!!! አልኩት ።
" ልጄ ተይ አረ ልቀርብሽ ስሞክር እንኳን ተረጂኝ !!!!!"አላኝ
እሺ ቡሀላ ደውላለሁ ዘጋሁት ።
በቀስታ ቤኪን ቀስቅሼ የተደተደረውን ምግብ አስተካክዬ ሰጠሁትና ሊበላ ተዘጋጅቶ ገና እጁን ሲሰበስበበሪ ክፍት አለ ????
በዛ ላይ ሰለሞን ነበር የበረከት አባት !!!
ክው ብዬ ደርቄ ቀረሁ ........
✍✍✍fidel.......
ክፍል ሰላሳ ዘጠኝ
........... ልታስገድይብኝ ነው ??" ብሎ አፈጠጠብኝ ።
ምንም የማላቀው እኔ ቤኪና ያቤፅን በየተራ እያየሁ ጉዳዩን እንዲያስረዱኝ ጠብቃለሁ !!!
ያቤፅ በሚያሳዝን ፊት አየኝና
" ሶል እሷ ምንም የምታቀው ነገር የለም ዛሬ ገና ነው እንደታመም የሰማችው " ብሎ ለመሸፋፈን ሞከረ ።
አሁንም ከኔ ጋ ምን እንደሚያገናኘው ግልፅ አልሆነልኝም ??????
ወደ ቤኪ ተጠግቶ እንደ ህፃን ልጅ ፀጉሩን አሻሸና ቀና ብሎ
" ትሰሚኛለሽ የስለት ልጄ ነው በልጅነት የተፈተንኩበት ልጄ ነው እዚጋ አምሮበት ደምቆ ተውቦ ስላገኘሽው ብቻ አይደለም ብዙ ዋጋና ፈተና ተከፍሎበታል!!!!
ትሰሚኛለሽ የብዙ ነገር ማስታወሻዬ ነው እንኳን እንደዚህ ሆኖ ላየው ይቅርና እንቅፋት ሲመታው ራሱ ያመኛል ገባሽ " አለኝ ።
ሳላስበው እንባዬ አመለጠኝ ። በተናገረው ንግግር ብቻ ሳይሆን የማላቀውን የአባትነት ፍቅር በሱ ላይ አየሁት !!!!
የማላቀውን አሳየኝ አባት ለልጁ ምን ያህል ዋጋ እንደሚከፍሉ ሳይ ......
ሁለት ልጄ ብለው ጠርተውኝ የማያቁ ድብደባ ጥላቻ ቁጣን አንዴም አባትነትን መካድን ቆይቶ መመለስን .....ብቻ የማይረቡ ነገሮችን እያሳዩኝ የነበሩት ሁለት አባት ከተባሉ!!! እሱን አሰብኩኝና የምር ከፋኝ !!!!!
ሳላስበው እንደ ህፃን ልጅ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩኝ !!!!!!!
አንዳንዴ የኔ ስጋ የምትለው ሲከዳህ በዙሪያክ መልካም ሰዎችን በመላክ ይክሳልና ጄሪና ያቤፅ ወደኔ መተው አባበሉኝ ።
ጄሪ እንባዬን ከፊቴ ላይ እየጠረገች
" እረፊ እነሱ ፊት አታልቅሺ " አለችኝ ወደ ጆሮዬ ተጠግታ በሹክሹክታ ።
ራሴን እንደምንም አሳምኜ እንባዬን ወደ ውስጥ መልሼ ተነፈስኩና
ለእርሶ ልጆ ነው እኔ ደግሞ ልጆን እወደዋለሁ ከእርሶ እኩል አስብለታለሁ እጨነቅለታለሁ ከችግሮች ልመልሰው እንጂ መቼም ችግር ውስጥ እንዲገባ አላረግም አልኩኝ አፌን ሞልቼ !!!
ሰው ቀና ብዬ ለማየት የምፈራ ልጅ ያንን ድፍረት ማን እንደሰጠኝም ላውቅም !!!???
ስገምት ግን አፌን ብዘጋ የተሻለ ነበር መሠለኝ የበለጠ ተናደደ ።
አንገቱ ላይ የተቋጠረውን ከረቫት እያላላ
" አንቺ የልጄን ጠባሳ የፈሰሰውን ደም ትመልሻለሽ " ብሎ በጩኸት ቤኪ የለበሰውን ብርድ ልብስ ገፈፈው።
በፈጣሪ ስም ከድንጋጤዬ ብዛት እዛው ቀጥ ልል ነበረ!!!!!
ቤኪ ለመሸፈን ቢሞክርም አየሁት ሆዱ ጋር በስለት እንደተወጋ ሰው አራት መአዘን ቅርፅ ታሽጋ በብዙ ነገር ተሸፋፍናለች !!!!
መጀመሪያ ላይ እኔ ዝም ብሎ ህመም ያመመው እንጂ እንደዚ አይነት ነገር አልጠበኩኝም !!!
ከድንጋጤዬ ብዛት እጄ እየተንቀጠቀጠ አፌ ተያያዘ ።
" እስካሁን ብዙ ነገር ስታወሪ አልነበር ምነው ድንገት ዝም አልሽ ጥፋትሽ ገባሽ "......እያለ ያወራል ???
እኔ እሱን ረስቼዋለሁ ንግግሩ አይሰማኝም ቤኪ ምን ሆነክ ነው ማነው እንዲህ ያደረገህ ማነው ምንድነው ........ምን እንደማወራም አላቅም ብቻ ድንገተኛ መርዶ እንደተነገራት እናት እጄን አንዴ ጭንቅላቴ ላይ አንዴ እሱ ላይ እያደረኩኝ እርበተበታለሁ ።
" ምን እንዳላወቀ ትሆኛለሽ ባንቺ ምክንያት እኮ ነው ከዚህ ቡሀላ ልጄ አጠገብ ባይሽ መጥፎ ችግሮች ይፈጠራሉ እወቂ!!!!!!
ልጄ አጠገብ እንዳላይሽ አሁን ቀጥ ብለሽ ከነ ጓደኛሽ ከዚህ ሂጂ ላትመለሽ .....ገባሽ !!!!" ብሎ እየጮከ እጄን መጎተት ሲጀምር .........
✍✍✍fidel......
ክፍል ሰላሳ ስምንት
........ክው ብሎ ። ዩንቨርሲቲ ውስጥ ከአንዴም አራቴ ያየሁት ሰው ነው ።
ወፈር ብሎ ረዘም ያለ ኩል የሆነ አለባበስ ያለው የሚያምር ቀይ ሰው ነው ግን ግንባሩ ጭምድድ ያለ ሰው ነው ።
የዚህ ሁሉ ልጅ አባትም አይመስልም !!!
በሁለት እጄ አጣምሬ የያስኩት እጁን ለቅቄ ወደ ዃላ እየደበኩኝ ፍጥጥ ብዬ አየሁት ያቤፅና ጄሪም በድንጋጤ አንዴ እኔን አንዴ የቤኪን አባት እየተመለከቱ ደርቀው ቀሩ ።
" ምንድነው እዚህ ምን ታደርጋላችሁ ያቤፅ " አለው ግርማ ሞገስ ያለው ወፍራም የተረጋጋ ድምፁን እያሰማ።
" አይ ቤኪ እኮ ....." ብሎ ዝም አለ ።
" ቀጥል በረከት ምን ??? " አለው ወደኛ እየቀረበ ።
" አረ ሶል ቤኪ ትንሽ አሞት እኮ አስደነገጠን እና ወደዚ ይዘነው መጣን አለ ወደ ቤኪ እየቀረበ ።
ዞር ብዬ ሳይ ቤኪ ብርድ ልብሱን ጭምቅ አድርጎ ይዞታል ???
የቤኪ አባት በዝግታ እየተራመደ ወደኛ ሲመጣ ያቤፅ ከፊት ቀድሞ ቆመና
" ሰሌ ደህና ነው አሁን ተረጋጋ እሺ እዚህ ጋ ቁጭ በል " አለው ወደ ወንበሩ እየጠቆመ ።
" ያቤፅ አትልፋ ታቀኛለህ እኮ " ሲለው በአንዴ ተግባቡ ።
መንገዱን ለቆ ጥጉን ይዞ ቆመ ።
ከያቤፅ ጥሪ እንደተረዳሁት ከሆነ ስሙ ሰለሞን ነው መሠለኝ። ሁላችንንም አልፎ ወደ ቤኪ ተጠጋና በእጁ ጨምቆ የያዘውን ብርድ ልብስ ገፈፈው ።
ክው ነው ያልኩት የቤኪ ሆድ ከጎን ላይ ታሽጓል ።
ምን ያህል ስሜቱን መደበቅ እንደቻለ አላውቅም እኔ ሙሉ ቀኑን አብሬው ስውል ሆዱ ላይ ስተኛ ስነካካው .........
እንዴህ እንደተቆጣጠረው አላውቅም እኔ !!!!!!
ምንድነው ምን ተፈጥሮ ነው ??? አልኩኝ አምልጦኝ ነው !!!!የቤኪ አባት ዞር ብሎ በሆነ በሚያስፈራ አስተያየት ተመለከተኝ ።
" በዚች ልጅ ምክንያት ነው አይደለ !!! " ብሎ በሚያስፈራ አስተያየት አየኝ ።
" አራ አባ እሷ ምንም የምታቀው ነገር የለም ስትሰማ ደንግጣ እየሮጠች መጣች አለቀ ብሎ ለኔ ለመሸፋፈን ሞከረ ።
" ዶክተርክ ሁሉንም ነገር ነግሮኛል ከማን ጋር ተጣልተህ ነው በል ተናገር ቶሎ ። "ፐብሎ ተናገረው ።
" እንደዛ አይደለም አባ እሷ ምንም አታቅም !!!!!!!!" አለው ።
" በሞትና ህይወት መሀል እያለህ ለሷ ትሟገታለህ ደደብ " አለው የአስተማሪ ነገር ።
ወዲያው ዶክተሩ መጣ ።
"እሺ አሁን ምን እናድርግ????" አለው የቤኪ አባት ወደ ዶክተሩ እየቀረበ !!!
እሱ ዞር ሲልልኝ ጠብቄ እጆቹን ይዤ ምን እየተፈጠረ እንደሆነ እየጠየኩት እያለ አባሁ ዞረ ።
ቶሎ ለመልቀቅ ሞከርኩኝ ። ነገር ግን ከእይታው ማምለት የማይታሰብ ነው ።
" ልጄን ልታስገድይብኝ ነዋ????.....አለኝ።
✍✍✍✍fidel.......
1★ ወፎች አይሸኑም
2★ጉንዳኖች ፈፅሞ አይተኙም፤ሳንባ የላቸውም፤ሰራተኛ ጉንዳን እስከ 7 ዓመት ሊኖር ይችላል ንግስቶ ግን እስከ 15 ዓመት ልትኖር ትችላለች::
3★ሻርክ ብቸኛው የማይታመም እንሰሳ ነው ምንም አይነት በሽታ አያጠቃውም ካንሰርን ጨምሮ::
4★ፈረሶች እና ላሞች ቁመው ነው እሚያንቀላፉት::
5★የማር ንብ ሁለት ሆድ ሲኖራቸው አንዱ ለማር ሲሆን ሁለተኛው ለሚመገቡት ምግብ ማስቀመጫ ያገለግላቸዋል::
6★ትልቁ ነጭ ሻርክ ከሶስት ወር በላይ ሳይበላ መጎዝ ይችላል::
7★አብዛኞቹ ዝሆኖች በክብደት ከስማያዊ አሳነባሪ(Blue whale) ምላስ ያንሳሉ::
8★በረሮ በርሀብ እስኪሞት ድረስ ለሳምንት ያህል ጭንቅላቱ ተቆርጦ በሂወት መቆየት ይችላል::
9★የአህያ አይን አቀማመጥ በአንድ ግዜ አራቱንም እግሮች ማይት ያስችሉታል::
10★ዶልፊን ውሀ ውስጥ ከ24ኪ.ሚ ርቀት ያለ ድምፅ በቀላሉ መስማት ይችላል::
11★የወባ ትንኝ(Mosquito) 47 ጥርስ አላት::
12★ማንኛውም ሁለት የሚዳ አህያ(zebra) እንድ አይነት መስመር አይኖራቸውም::
13★ቢራቢሮ የሚቀምሱት(taste) በሆላ እግራቸው ነው::
14★የወንድ ሸረሪት የወሲብ አካል በአንዱ የእግሩ ጫፍ ላይ ይገኛል::
15★ንቦች አምስት አይን አላቸው::
16★አሳማ በተፈጥሮ(physical) ወደ ሰማይ ማየት አያስችለውም::
17★አይጥ ከተራበች የራሶን ጅራት ትበላለች
18★ ለሚስቱ ታማኝ የሆነ እንስሳ ቀበሮ ብቻ ነው
18★ሰማያዊ አሳነባሪ (Blue whale) በመጠን እስካሁን በአለማችን ከነበሩ እና ካሉ እንሰሳዎች ትልቁ ነው::
20★ የለሌት ወፍ ብቸኛዋ ከአጥቢዎች መብረር የምትችል ሲሆን የእግር አጥንቶቾ ከመቅጠናቸው የተነሳ መብረር እንጂ መራመድ አትችልም::
21★የለሌት ወፍ ምንግዚም ከዋሻ ሲወጡ ወደ ግራ ይበራሉ::
22★እባብ አይኖቹ ቢከደኑም በአይኖቹ ቆብ ማየት ይችላል::
23★ወንድ የወባ ትንኝ አይናደፍም ሴቶ ብቻ ናት መናደፍ
የምትችለው:: /femal Anofiles mosqto/
24★ የዱር አይጥ (Rat) በፍጥነት መራባት የሚችሉ ሲሆን በ18 ወራት ብቻ 2 አይጦች 1 ሚሊዮን ዘመዶችን ማፍራት ይችላሉ::
25★አንድ ንብ አንድ የሾርባ ማንኪያ ማር ለማዘጋጀት ከ 4000 በላይ አበቦችን መጎብኝት አለባት ::
26★ቀንድ አውጣ ለ3 አመት መተኛት ይችላል::
27★ አንድ ላይ የተያያዘ የሸረሪት ድር ተመሳሳይ ወፍረት ካለው አንድ ላይ ከተያያዘ የብረት ሺቦ ይጠነክራል::
28★ዝሆኖች ከ3ማይል ላይ ያለ ውሀ ማሺተት ይችላሉ::
29★ኦይሰትር(Oyster) የተባለ የአሳ ዝርያ ከአንዱ ፆታ ወደ ሊላኛው እንዲሁም ወደ ነበረበት ለወሲብ በሚመቸው ፆታውን መቀየር ይችላል::
30★በየአመቱ 1/3 የሚሆነው የአለማችን ሰብል በተባይ/ነብሳት ይወድማል።
ስንት ቁጥር አግራሞትን ፈጠርባችሁ ?____
ክፍል ሰላሳ ሰባት
..........አይኑን ክድን አደረገው !!! በፈጣሪ ስም ለአራት ሰከንድ አይኑን ጨፍኖ ቢቆይ በዛች ሰከንድ አይኑን ጨፍኖ የሚቀር መስሎኝ ምን ላደርግ እንደነበረ ራሱ አላውቅም ???!!!!!
ብዙ ነገር ከማሰቤና ከመናገሬ ቀድሞ መሎሶ በዝግታ አይኑን ገለጠነ
" አቡ " አለኝ ።
ሞቼ ተነስቼ ቃላትን እየሰማሁ ነው የመሰለኝ ማለት እችላለሁ !!!!
ሁለት ፊደላት አረጋጉኝ !!! ከድንጋጤዬ ብዛት ግን መናገርም መንቀሳቀስም ከብዶኝ ነበር !!!
የሰማያዊት እናቴን ስም እየጠራሁ ደጋግሜ አማትቤ ራሴን አረጋጋሁኝ ።
ወደራሴ ስመለስ ቀረብ አልኩኝና እጆቹን አጥብቄ ይዤ
ቤኪ የኔ አባት እኔ አንተን አጥቼ መኖር አልችልም የኔ አባት እንዴትስ እችላለሁ " ፀጉሩን እየነካካሁ .እጆቹን እነሳምኩ ) አንተ ለኔ ፍቅርን ያስተማርከኝ ሰው ወዳድ ያደረከኝ ያበረታከኝ ፅኑ ሴት ያረከኝ ነገሮችን በተግባር ያሳየከኝ ሁሉ ነገሬ ነህ የድሮዬ የአሁኔ የወደፊቴም ...........በስሜታዊነት ሳላስበው በጣም ብዙ ከኔ ይወጣሉ የማልላቸውን ከየት እንዳመጣዋቸውም የማላቃቸው የፍቅር ቃላት ለፈለፍኩበት ።
እውነት ለመናገር ብዙ እንዳወራሁ የገባኝ ራሱ ንግግሬን ጨርሼ ሳያቸው ሶስቱም ከንፈራቸው ለጠጥ አድርገው በፈገግታ እየተመለከቱኝ እንደነበር ሳውቅ ነው !!!
" የኔ እናት እንደዚህ ያማሩ ንግግሮች ካንቺ መስማት ለኔ ፈውስ ነው እኮ " ብሎ አጥብቀው የያዙት እጆቼን ስሞ አንገቱን አስደገፈበት !!!
የቤኪ የግል ዶክተር የተባለው ሰውዬ
" ብዙ አታስወሩት ለቁስሉ ጥሩ አይደለም" ብሎን በነፃነት እንድናወራ ጥሎን ወጣ።
አራት እብድና የፍቅር ሰዎች አንድ የተዘጋ ከፍል ውስጥ ተገጣጠምን ።
ለወሬ እንዲመቸን አድርገን ወንበሩን አስቀምጠን መፋጠጥ ጀመርን ።
ለወሬ ማስጀመሪያ ብዬ
የቤኪ የዚህን ያህል ቅርብ ሰው ከሆንክ እንዴት አላቅህም ቆይ ????
አንድም ቀን አይቼክ አላቅም የት ነበር የምትማረው ?? አልኩት ያቤፅን አንን አይኑን በጥያቄ ፊት እያየሁኝ !!
" እኔ ግን በደንብ ነው የማውቅሽ ካንቺ ቀድሜ ነው መፈቀርሽንም ያወኩት ( ፈገግ እያለ )
እኔ የተማርኩት እዚህ አይደለም የምኖረውም እዚህ አካባቢ አልነበረም "" ብሎ በስሥም ብቻ የማቀውን የሀብታም ትምህርት ቤት ስም ጠራልኝ ።
ጄሪም እንደመንቃት ብላ ቆይ ግን ለምንድነው እነ አቡ ትምህርት ቤት የገባከው አለችው ።
ቤኪ ብዙ እንዳያወራ ነፈለገው ያቤፅ ከእራሱ በላይ እንደሚያቀው ሰው በኮንፊደንስ ተሞልቶ ነገረን
" ከአስተማራ ጋር እየተጣላ ትምህርት እያስደገሙት በጣም ሲቸገር ዘጠነኛ ክፍልን ብቻ እዛ ተምሮ ይመለስ ብለውየመንግስት ቢያስገቡት የበለጠ ረብሾ አንድ አመት ደገመ በሰከንድ ግን ቅይር አለ እድሜ ለአንቺ !!"
" ማለት " አለች ጄሪ ቀደም ብላ ።
" ትምህርት በገባ በሳምንቱ ጠብ አደረገችው ተቃራኒ ባህሪ ስላላቸው አብረው እሱ ግንፍል ሲል አቡ እያበረደች ።
እሱ ሊጣላ ሲል ፍቅር እየሰጠች ተንከባክባ በዛው እንዳቀጥል አደረገችዋ እንደዛ ተማሪ ያረገውን ጫማ አላደርግም የሚል በሽተኛ ልጅ ጠብ አደረገችው !!!!*" ብሎ ትንሽ ማጋነን የበዛባት ክሽን ያለች ቆንጆ ንግግር አደረገ !!!
አንዳችን አንዳችንን እየተጠያየቅን ስንስቅ ስንስቅ እዛው አመሸን ።
ሁላችንም ወደ ጊቢ የመመለስ እቅድ የለንም ደግነቱ ቁጭ ብለን ስናወራ ነበር ።
በመሀል እናቴ ደወለች ።
ብትሰማ ለአለምዬ እንደምትነግራትና እንደምትጨነቅ ስላወኩኝ ዝም እንዲሉ ተናግሬ ስልኩን አነሳሁት ።
" አብዬ ሳጀውይልኝ ዋልሽ እኮ እናቴ ጨነቀኝ እና ነው የደወልኩልሽ " አለችኝ ።
የኔ ኘዋህ እናት !!!!!!!❤❤❤
ድምፄን እያንሾካሸኩኝ ቀስ ብዬ
እናቴ ጠዋት እደውልልሻለሁ አሁን እያጠናሁ ነው እሺ ደህና ነኝ እወድሻለሁ አልኳት ።
እኔን ለማመን አታመነታም !!! እሺ እሺ እማ ብላ ስምኩን ዘጋችው ። ወዲያው ስልኩን ከመዝጋቴ
" አንድ ጥያቄ አለኝ እኔ " አለች ጄሪ
ምንድነዎ ተረጋጊ እንጂ ቀስ ብለሽ አውሪ አልኳት መልሼ
" በመጀመሪያ አራታችንም በአንድ ቀን ነው የምንጋባው !!!!
ጥያቄው ግን መች ነው የምንጋባው ሁላችሁም ተናገሩ ።
እኔ ከአራት አመት ቡሀላ ጥር ሀያ አንድ ላይ " አለች ፍልቅልቅ እያለች ።
ደስታዋ ፊቷ ላይ ይነበባል ።
እስካሁን በዝምላ ነቆየው ቤኪ
"" እኔ የምመኘው ግን ....." ሲል በሩ ብርግድ አለ ።
ያቤፅ የጄሪን እጅ ለቆ ብድግ አለ
" አባ " አለ ቤኪ ክው ብሎ .........
✍✍✍fidel........
ሼር አድርጉ ለአንድ አንድ ሰው ቢያንስ !!!
ክፍል ሰላሳ ስድስት
.......ስናይ ቤኪ በእጁ ላይ ብዙ ነገር ተደርድሮ ግሉኮስ ተደርጎለት ምናምን ...... የሚያስጠላ የሆስፒታል ድባብ ባለው መልኩ ተኝቷል ።
ሙሉ ቤቱን በአይኔ እያማተርኩ ከተመለከትኩ ቡሀላ ልወድቅ ስንገዳገድ ከቤኪ ጋር የነበረው አንድ ሰውዬና ጄሪ አተረፉኝ ።
ደጋግፈው ወንበሩ ላይ አስቀመጡኝ ።
ያቤፅ ምንም ማለት ፈርቶ መሠለኝ ጥጉን ይዞ ያየናል ።
እኔም ሆንኩ እናቴ ሆስፒታል የሚባል ደርሰን ስለማናውቅ እንደዛ አይነት ሁኔታዎችን የማውቃቸው ፊልም ላይ ብቻ ስለሆነ በጣም ደንግጫለሁ በድን ሆኜ ነበር ለደቂቃዎች
" አብላካት ማለት አንቺ ነሽ ?" ብሎ በትኩረት ተመለከተኝ ።
በሰአቱ ቃላት ለኔ በጣም ውድ ሆኑብኝና ማውራት ሲከብደኝ ጄሪ ቀደም ብላ
" አዎ እሷ ናት " አለችው ።
" ያንቺን ስም በተደጋጋሚ ሲጠራ ነበር ያቤፅ መታመሙን ለመደበቅ ሲሞክር ነበር ግን አንቺ በጣም ታስፈልጊዋለሽ ለዛ ነው ያስጠራሁሽ " አለኝ ።
ምን ሆኖ ነው ምንድነው የተፈጠረው ?? አልኳቸው ድምፄን ኩሽሽ አድርጌ ።
ለኔ ሳይመልሱልኝ ሶስቱም በየተራ እርስ በርስ ይተያያሉ ።
እኔ ደግሞ እንደዚ አይነት ነገር እፈራለሁ !!!!
ሰው ጥያቄ ጠይቄው ከኔ ይልቅ እይታውን ሌላ ሰው ላይ ካደረገ ወይ የሆነ ችግር ተፈጥሯል ወይም ደግሞ ለመዋሸት እያቀደ ነው ብዬ ነው የማምነው !!!!
ለመጠየቅ ደግሜም አላሰብኩም ወዲያውኑ
ለምንድነው የምትተያዩት ምንድነው የተፈጠረው ንገሩኝ !!!! ብዬ ጮኩኝ ።
"" ቀላል ነገር ነው የሚያስጨንቅ ነገር የለም " አለኝ ሰውዬው ቀደም ብሎ
ታዲያ ደህና ከሆነ ለምን አያወራኝም እ ለምን ዝም አለ አልኩት ከጭንቀቴ ብዛት
" እባክሽ ተረጋጊ የእንቅልፍ መድሀኒት ስለወሰደ ነው ትንሽ ሰአታት ቆይቶ ይነቃል " ብሎ ሊያረጋጋኝ ሲጠጋኝ ወደ ዃላ እየሸሸሁ
ያቤፅ ሲጀመር ይሄ ሰውዬ ማነው ከዚ በፊት አይተነው የማናቀው ሰው ቤኪ ጋር ምን ያደርጋል ??? ብዬ ተኮሳተርኩበት!!!
" አብላካት እረፊ እንጂ ( ወደ ሰውዬው እየዞረ ) ይቅርታ ዶክተር ስለተጨነቀች ነው " ብሎ ጥፋቴን ለመሸፈን ሞከረ ።
ዶክተር ነው እሱ ታዲያ ለምን አክሞ አያስነሳውም የዶክተር ማቴሪያል ለመን አልያዘም .........
እያልኩኝ የህፃን ጥያቄዎች እየጠኩኝ ነበር ።
" የግል ዶክተሩ ነው ተረጋጊ አብላካት " አለኝ ።
አይ ሀብታም !!!!😂😂😂 እኛ የግል ሽንት ቤት የለን !!.......
በሰአቱ ጭንቀት ላይ ስለነበርኩኝ ይሄን ነገር አላሰብኩትም ነበር ካለፈ ቡሀላ ነው ትዝ እያለኝ እስቅበት የነበረው ።!!!!
በሰአቱ እንደምንም አረጋግተውኝ ተቀመጬ እስኪነቃ መጠበቅ ጀመርኩኝ ።
ዶክተሩ እይዳለው በትንሽ ሰአት ውስጥ አልነቃም ።
በዛ ለሊት እየሮጥን የመጣን እስከ ቀትር ሰባት ሰአት የቤኪን ድምፅ መስማት አልቻልኩኝም !!!
አንዴ ሳለቅስ አንዴ ስነሳ አንዴ ስቀመጥ ....... ብቻ ሰከንድ ደቂቃን ደቂቃ ሰአትን ሰአት ሰአታትን እያፈራረቁ ዘጠኝ ሰአት አካባቢ ሆነ ።
አስር ጊዜ አፍንጫው ስር እየተለጠፍኩኜ የትንፋሹን ድምፅ ስሰማ ቆየሁኝ ።
ሲጨንቀኝ የምፀልያትን ፀሎት ደጋግሜ እየፀለይኩ ነበረ !!!
በስተመጨረሻም የአይኑ ሽፋሽፍት መርገብገብ ጀመሩ ።
ቤኪ ቤኪ ብዬ እላዩ ላይ ልጥፍ አልኩኝ ።
ሙሉ ሰውነቱን እየዳበስኩኝ በህይወት መኖሩን አረጋገጥኩኝ ።
ላለማመን እንጂ ያጣሁት ሁላ መስሎኝ ነበረ !!!!!
".....( ያቃስታል )...አቡ .....አ....አቡ....." የተቆራረጡ ጥሪዎች አሰምቶኝ መልሶ
".... ያ...ያማል ....." እያለኝ ፊደሉን በቅጡ ሳይጨርሱ አይኑ ክድን አደረገው ?????...........
✍✍fidel........
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ፊደል✍✍» is a Telegram channel in the category «История», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 1.8K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 11.4, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 18.0 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий