
Channel statistics
ክፍል አስራ ዘጠኝ
.......ከፊቷ ሄጄ ቆምኩኝ ። ልጅቷዐበድንጋጤ ወደዃላ ልትወድቅ ምንም አልቀራትም !!!
" እ አቤት ምነው ምን አረኩ " አለችኝ በፍራቻ ከንፈሯ እየተንቀጠቀጠ ።
የፈራችበት ምክንያት አልገባኝም ነበር ማለት ሰፈር ውስጥ ፀበኛ ተደባዳቢ ነው ስለሚባል ነው ወይስ ለምን ቀና ብላ ለማየት ትፈራኛለች ???
ምክንያቷን ባላውቅ ብቻ ዝም ብዬ ሳያት ነበር ።
ከእኔ አንፃር አጭር የምትባል ልጅ ናት እና እኔን ለማየት የግድ ቀና ማለት አለባት ።
በእጇ የፀሀዩን ግለት ከአይኗ እየጠበቀች
" አቤት ችግር አለ ምን ሆነክ ነው " አለችኝ ።
ምን አስቤ እንደሆነ አላውቅም ስታወራኝ ማውራት አቃተኝ !!!
ከእራሴ ጋር የገባውበት ግራ የገባ ስሜት ልረዳው ስላልቻልኩ ከራሴ ጋ መታገል ከብዶኝ ከፊቷ በቆምኩበት ቦታ ቁጢጥ ነገር ብዬ ጭንቅላቴን ይዤ ራሴን ለመረዳት ስሞክር
" ምንድነው ምን ሆነክ ነው አሞክ ነው እንዴ በአማኑኤል ና ተነስ ....." ብቻ በድንጋጤ ዝምታዋና ፍርሀቷ ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ እግሬ ስር ያለሀሳብ ተንበርክክ በስስት አይን እያየችኝ ነበር ስታወራ የነበረው ??
በዝምታ እየተመለከቷት ነበረ እና ፊቷን ሳየው ለረጅሞ አመት ተዋውቀን ተግባብተን ተዋደን የቆየን ያህል እየተሰማኝ ነው ???
የሆነ አለ አይደል ብዙ አመት አብሮኝ የቆየ አይነት ሰው በቃ ለእኔ እንደዛ ነው የሚሰማኝ ።
ለረጅም ሰአት በሰስት ሳያት ግራ የተጋባችው ልጅ ፊቴን እንደ ጥፊ ነገር ነካ ነካ እያደረገችኝ
" ግን ደህና ነህ ?" አለችኝ ።
አዎ ደህና ነኝ ብዬ ቆምኩኝና አንድ እርምጃ ከሷ ሸሸሁኝ ።
እሷም ከተንበረከከችበት ጉልበቷን እየጠረገች ተነሳችና ፊቷን ጨምደድ አድርጋ ለትንሽ ደቂቃዎች ተመለከተችኝና ያንን ወደፊት የመጣ ፀጉሯን ወደዃላ እየወረወረች ጥላኝ ሄደች ።
ስትሄድ ቅሪ አትሂጂ ብላትና አቅፊያት ብቆይ ደስ እንደሚለኝ አይነት ስሜት እየተሰማኝ ነው !!!
ግን እንደምንም ራሴን ተቆጣጥሬ ፊቴንም ሳላዞር ቀጥ ብዬ ወደ እናቴ ቤት ሄድኩኝ ።
የኔ እናት ፊቷ ላይ የሆነ የደበራት ትመስል ነበር
ደህና ነሽ እናቴ ? አልኳት አልጋ ላይ እየተጋደምኩ
" ልጄ እኔ ማንም እንደሌለኝ እያወክ እንዴት እንዲህ ትተወኛለህ ቆይ እ ከሆነ ጊዜ ጀምሮ እኮ ከኔ ርቀሀል ጠዋት ወተህ ማታ ነው የምትመጣው ምን ነካብኝ ልጄ?? "አለችኝ
ሳላስበው ድንጋጤ ውስጤን ወረረው ምን ያህል እንደተቀየርኩ ብዙ ማሳያዎች አሉ ግን ይሄን ያህል ያስታወቀብኝ አልመሠለኝም ።
ወዲያው ከባድ ንዴት ጭንቀት ፍራቻ የተደበላለቀበት ስሜት ተሰማኝ ።
ከነ ሳሚ ቤተሰብ ጋ በመተዋወቄም ሆነ ሰላምን ጥሩ ሙድ ላይ ማየቴ ለነሱ ደስታ መፍጠሬ ቢያስደስተኝም ግን በእራሴ እንድናደድ የሚያረግ ሀሳብ በአይምሮዬ እየተመላለሰ አስቸገረኝ !!!
በህይወቴ አንድም ቀን ለእናቴ እንደዛ አይነት ነገር አርጌ አላውቅም ማለቴ ስጦታ ገዝቼላትም አላውቅም !!
ምን አልባትም ያንን ነገር የገዛሁት ለእናቴ ቢሆን ኖሮ ሰፈሩን በእልልታ አድምቃ እየዞረች ልጄ ደረሰልኝ ልጄ የገዛልኝ እያለች እንደምታሳይ እርጥጠኛ ነኝ ማንም ቢሆን ምስክሬ ነው !!!
ለሰላም በማረጌ ባልፀፀትም ለእናቴ ባለማረጌ አበሳጨኝ !!!
ቀኑ እየመሸ ስለነበር ምንም ሌላ እርምጃ ሳልወስድ በዝምታ አዳመጥኳትና ዝም ብዬ ተኛሁ ።
ልክ የቀጣዩ እሁድ ቀን በጠዋት ተነስቼ ቤተክርስቲያን ተሳልሜ ስፖርት ሰርቼ እንጀጨረስኩ ቀጥታ ወደቤት መጣሁኔ እናቴን ጠራዋት ።
ገላዬን ታጥቤ ወጥቼ እስክመጣ ጠጅ ነው የምትይው ቡና ናፍቆኛል እያፈላሽ ጠብቂኝ ብያት ኪሴ ውስጥ ያለችቅንና የደበኳትንም ይዤ ወጣሁኝ ።
ወጥቼ ብሩን ሳይ ሳላስበው ለካ አንድ አንድ እያልኩኝ ጨርሻታለሁ አምስት መቶ ሰባ ብር ናት የቀረች ።
የስፖርት ክፍያ ጌጡን የምገዛበት ሲነሳ አርባ ብር ብቻ እንደሚቀር አሰላሰልኩኝ ።
ገበያ ን አደርገዋለሁ እያልኩ ራሴን እያሳመንኩ ቀጥ ብዬ ስሄድ አሁንም በድጋሜ አየዋት ።
ነፍስ ካወቅን ቡሀላ ምን ተፈጥሮ ሳንተያይ ይሄንን ያህል አመት አስቆጥረን አሁን ቀን በቀን ምክንያቱ ባይገባኝም እንኳን የዛኔ ራሴን ገታ አንርጌ ምንም እንዳልተፈጠረ ቀጥ ብዬ አልፊያት ሄድኩኝ ።
ቀጥታ እዛው ቦታ ላይ ነበረ የሄድኩት ። የሚያማምሩ ጌጣጌጦቼ አሉ ።
ከሰላም በሰጠዋት አይነት ሌላ የሚያምር የአንገጠፈት ጌጥና የእጅ አንባር አየሁኝ ።
እዛ ቆሜ ሳስበው መልስ እንዳለኝ የገመትኩትን ብር አንድ ብርም ሳይመለስ ያኛውም ሳልከፍል ያለችኝን ሙሉ አጠፋው ።
ግን ለእናቴ ስለሆነ ምንም ይሁን ብዬ ሄድኩኝ ።
ቤት ስደርስ እንደምፈልጠው የምላ ቀጤማዋን ተጠቅማ ቤቱን የሌለ አሳምራ ጠበቀችኝ ።
እኔም ቸኩዬ እናቴ ነይማ ብዬ ከውጪ ወደ ውስጥ እንድትገባ አረኳትና
ከልጅሽ የሚሰጥሽ ስጦታ አለ ትቀበይኛለሻ አልኳት ፈገግ ብዬ
" ለእኔ ልጅ ?? ምን አስቸገረክ ብር እንዳገኘክ ለራስክ ወይ ልብስም ብትሆን አገዛም ነበር " አለችኝ ።
ከእሳሷ በላይ ለኔ ሟች ናት !!!
ከዛም አሳምራ አስቀምጣ የሰጠችኝና የእጅና የአንገት ጌጥ አውጥቼ ፊት ለፊቷ ያስኩት
በጣም ደንግጣለች ገና እንዳየችው ለእኔ ነው ግን ?? ብላ አነሳችውና ማየት ስትጀምር በደስታ ተሞልተን እያለ ሰካራሙ አባቴ ከአራት ቀን ቡሀላ በእለተ እሁድ ለዛውም በሰንበት ረፋዱ ገድ ገድ እያለ ወደ ውስጥ ገባ ........😭😭😭
✍✍✍fidel.....
ክፍል አስራ ስምንት
......... ማነው አልኳት ።
ምክንያቱን ባላቅም በትንሹ ፈገግ አለች ። ለምን እንደሳቀች ባላቅም በእራሴ ፍቅረኛዋን ስላስታወስኳት በደስታ ነው የምትስቀው ብዬ ደምድሜ ተበሳጭቼ ዝም አልኩኝ ።
" እ እንግዲህ የኔ ፍቅረኛ .......( ረዘም ያለ ዝምታ ) ... ፍቅረኛ ማለቴ ስተት ከሆነ ባላቅም የኔ አማካሪም የምወደውም ወንድሜ ሚስጢረኛዬ ጓደኛዬ ፍቅረኛዬ ሁሉ ነገሬ አባቴ ነው እኔ ያንተን ፍቅረኛ ለማየት ፈልጌ እንጂ ፍቅረኛ የሚባል የለኝም " ብላኝ አረፈች ።
ሌላጨፍቅረኛ ስለሌላት እና ሁሉ ነገሯ አባቷዐመሆኑ ደስ ቢለኝም መዋሸቷ አያደደኝ ።
ምክንያቱም እኔ በሷ እልህ ማያን ባላስባት እዚህ ግራ የገባው ስሜት ውስጥ ባልገባሁ ነበረ !!!!
ለነገሩ ማን ያቃል ምን አልባት በምክንያት ሊያግባባን ፈልጎ ይሆናል ፈጣሪ ??? ወይስ የቆየ ነገር አሁን ተገልጦልኝ ነው !?? እና ማያን ሳያት ለምንድነው የምደነግጠው ???
.......
በጣም ብዙ ነገሮችን እያሰብኩኝ ከእራሴ ጋር ሀይለኛ የራስ መጋባት ጦርነት ውስጥ ገብቼ አረፍኩት ።
ደስ የሚለው ከሀሳቤ ያነቃኝ ከረጅም ሰአታት ቡሀላም ቢሆን ውብ ሆና የመጣችውን ሰላምን ተመለከትኳት ።
በጣም ታሳዝናለች የሆነ የማታውቀው ፍራቻ ሰላም ነስቷታል !!!
በዛ ላይ ቤቱን ልክ እንደ እንግዳ ነው እየዞረች የምትመለከተው !!
ምን ያህል የብቸኝነት ህይወትና የተዘጋ ክፍል እንደከበዳት ፊቷ ማሳያ ይመስለኛል !!!
ሳሚም ከዃላዋ መቶ እጇን ይዞ ወንበር ላይ አስቀመጣት ።
የቤት አጋዧ እንዳየቻት በደስታ አቀፈቻት ስገምት ከድሮ ጀምሮ የቆየች ሰው ናት መሠለኝ !!!
ከዛም ቶሎ ምግብ አቀራረበችና መብላት ልንጀምር ስንል በስመአብ ብዬ ቀና ስል ሶስቱም እያለቀሱ ነው ።
ደነገጥኩ ሳሚ ልዕልና ምንድነው ምን ተፈጠረ አልኳየው ግራ እየተጋባው ።
ልዕልና ከተቀመጠችበት ጠረንጴዛ ብድግ ብላ መጣችና ጥምጥም ብላ አቀፈችኝ ።
በፈጣሪ ስም ሙሉ ሰውነቴ የሆነ ነገር ሲነዝረኝ ተሰማኝ !!!
ወዲያው ለቀቀችኝና እየተቀመጠች
" ማርያምን አንተ ለኛ ባለውለታ ነክ ከላይ የተላክ መልእክተኛ ነክ ብታምንም ባታምንም እንዲ ተቀምጠን ከበላን ከሶስት አመት በላይ ሆኖናል እኮ !!!!!" ብላ መልሳ ማልቀስ ጀመረች ።
ሳሚም ቀበል አድርጎ
" ላንተ ቃል የለኝም ልጅ ፈጣሪ ይስጥክ " ብሎ ንግግሩን በአጭሩ ገታው ።
ይባስ ብሎ ሰላምም ቀበል አድርጋ
" ከላይ የተላክ መልአክ ነክ ይሄ ጅማሮ ነው ለእኔ ታስፈልገኛለክ " ብላኝ አረፈች ።
ሲጀመር ወደዚህ ቤተሰብ የተቀላቀልኩበት መንገድም ግራ የሚያጋባኝ እኔ በዚህ ልክ ሲሄድ በቃ ፈጣሪ በእኔ ላይ አድሮ ስራውን እየሰራ ነው ብዬ አሰብኩ !!!
ግን በምን ስራዬ እንደሆነም አላውቅም !!!!
ብቻ ግን በሁኔታዎቹ በጣም ደስተኛ ነኝ!!!በእራሴ እየኮራሁ ነው ሁላ !
ከዛ እንባቸውን ጠራርገው ወደ ምግቡ ተመለስን ።
እዛ ቤት ስሄድ የምበላየው ምግቦች በስመአብ እስከ ሁለት ቀን ያቆዩኛል ማለት እችላለሁ !!!
ሀገር አማን ብዬ ምግቡን እያጣጣምኩ እየበላሁ ልጨርስ ስል ያላሰብኩትን ዱብዳ የሆነ ጥያቄ ጠየቁኝ ።
የሳሚ ሚስት ትንሽ እንደበላች ነበር የተነሳችው እናም ቁጭ ብላ ስታፈጥብን ነበር ።
ልዕልናም ስትጨርስ
" እኔ አንድ ሀሳብ አለኝ " አለች ፍልቅልቅ እያለች ።
መጀመሪያ ላይ ጉዴን ሳላውቅ የሚያምረው ፈገግታዋን በመመልከት ብቻ አብሪያት ስስቅ ነበር
" ምንድነው ልጄ እሺ ተናገሪ " አላት ።
" እማዬ ከቤት ወታ ስለማታቅ አንድ ቀን ሰብሰብ ብለን የነ ሚኪ ቤት ሄደን ቤተሰቦቹን እንተዋወቃቸው ደስ አይልም " አለች ምን ደስ የሚል ነገር እንዳወራች ባላውቅም ።
መጀመሪያ ሚኪ ስትል እኔን አልመሠለኝም መሠለኝ ዝም ብዬ ነበር
" ደስ አይልም ሚኪ " ስትል ነበር ክው ብዬ አፌ ውስጥ ያለው ምግብ ትን ብሎኝ ልሞት እስክደርስ አስደንብሮን ሁላችንም እስክንጨነቅ ድረስ አሰቃይቶኝ በስንት መከራ ለቀቀኝ !!
በሂወቴ ትልቅ መርዶ ብሰማ ራሱ እንደዛ የምደነግጥ አይመስለኝም በስመአብ !!!
በስንት ስቃይ ከተረጋጋሁ ቡሀላ ሰላምና እሷ ምነው ምንድነው ምን ተፈጠረ ... እያሉ በጥያቄ ቢያስጨንቁኝም ምርጡ ሳሚ ግን ስሜቴን ተረድቶት በዝምታ ተቀምጦ ቆየና በስተመጨረሻም
" ምን ችግር አለ እሁድ ይጋብዘናል ግን እኔ ከቤት ይልቅ መጀመሪያ ካፌ ነገር ብትጋብዘን ባይ ነኝ " አለና በአይኑ ምልክት ሰጠኝ ።
እ እሺ አረ ችግር የለውም ብቻ ሰላም ይሻላት እንጂ አልኩኝ እየተንተባተብኩኝ ።
ከዛም በቻልኩት ፍጥነትና ምክንያት ደራርቤ ቶሎ ከዛ ቤት ወጣሁ ።
ለእኔ በጣም አስደንጋጭ ጥያቄ ነው ።
ራሴን ካወኩ ጀምሮ በስተት እንኳን የሰው ቤት ገብቼ አላውቅም አድጌ የክላስ ጓደኞቼንም ቢሆን ቤት ላለመውሰድ ነው የነሱ ቤት የማልሄደው !!!
የልዕልናን ዘግናኝ ጥያቄ እያሰላሰልኩ ወደቤት ስሄድ ከፊቴ ማያ ስትመጣ ተመለከትኳት ።
በአጋጣሚ ብዙ ጊዜ እያገኘዋት እንደሆነ ይታወቀኛል !!!
ልክ እሷን ሳያት ልዕልናንም ችግሬንም ድንጋጤዬንም ሁሉንም እንድረሳ አድርጋ ትኩረቴን ተቆጣጠረችው!!!
በልቤ ላይ እየተካሄደ ያለው የስሜት ጨዋታና ከሆነ ጊዜ ጀምሮ እሷን ማግኘቴ ሲገጣጠምብኝ ላናግራት ወሰንኩ ።
ልክ በአጠገቤ ስታልፍ ምን እንደምላት ሳላስብ እንኳን
ማያ ቁሚ ብዬ ከፊቷ ሄጄ ግትር አልኩ????
✍✍✍fidel.........
..
ክፍል አስራ ሰባት
.........ወደ መታጠቢያ ቤት ሮጥን ።
በር ላይ ስንደርስ እኔ እዛው ቆምኩ ልዕልና በሩን ከፍታ ልትገባ ስትል ከትት ብለው ሲስቁ ሰማን ።
ነገሮች ግራ አጋብተውኝ ልዕልናን ስመለከታት በሩን ኳ ኳ እያደረገች
" ማ ማ ደህና ነሽ ምንድነው ሰላም ናችሁ " አለቻት።
በጭንቀት ልባችን ልትወጣ ደርሳ ነበር ሳሚ ግን ፈገግ ብሎ በሩን ከፍቶ ብቅ አለና
" ደህና ነን አታስቡ አረ የድሮውን አስታውሰን ነው እኮ " አለ ።
እሱ ላይ ያንን ፈገግታ ማየት ደስ የሚል ነገር ነው ።
በባለቤቱ ጉዳይ በጣም እንደተጎዳ ግልፅ ነገር ነው!!
በምላሹ ተደስተን ሁለታችንም ተመልሰን ወደ ሳሎን ሄደን ፊት ለፊት ለፊት ለፊት ተቀመጥን
እውነት ለመናገር ረብሾኛል እኔ ከእራሴ ጋ እየተጋጨሁ ነው ደ
እኔ ስለ ፍቅር ምንም የማላውቅ ልጅ አሁን ከራሴም ጋ አልተግባባሁም ።
ሰሞኑን እየተፈጠሩ ባሉት የእንግዳ ስሜቶች ጥርቅም በጣም እየተጎዳሁ ያለሁ ይመስለኛል !!!!
ምክንያቱም ተሰምተውኝ የማላቃቸው ስሜቶች ሁለት በተለያየ አለም በሚኖሩ ሴቶች ላይ እየተሰማኝ ነው ???
የትኛው ስሜት ምን እንደሆነ ራሱ አላውቅም እኔ ስሜቶቹ ምን እንደሆኑ ራሱ አላውቅም !!!
ብቻ ማያን ሳያት የሚከሰቱት እነዛ የማላቃቸው ስሜቶች አሉ ራሴን አለመቆጣጠር መደንገጥ መወዛገቦች አሉ ???
አሁን ላይ ደግሞ ልዕልናን ሳያት የሆነ ስሜት አለ ደስ ይለኛል እንድትነካኝ አልፈልግም ምክንያቱም የሚፈጠረውን የልብ ንዝረት አልችለውም !!!
ስትቀርበኝ እፈራለሁ !! ሳያት የሆነ የሚያሳሳት ነገር አለ .......እና ብቻ ግን እኔ ግራ ገብቶኛል እነዚ ቀይ ቆንጆና ጠይም ቆንጆ ሴቶች ግራ አጋቢ ስሜቶችን እያበዙብኝ ነው ያ ደግሞ ለእኔ ጥሩ አይደለም !!!
እኔ ታች ቁጭ ብዬ ልዕልናን ላለማየት አይኔን ሳማትርና ስታገል ነበር ።
ለደቂቃዎች በዝምታ የቆየች ቢሆንም ጭንቀቱ ለቀቅ ሲያደርጋት ነው መሠለኝ
" ደህና ነክ ግን አንተ ?" አለችኝ ጠረንጴዛ ላይ ያስቀመጠውን ኩትን እጅ ነካ እያደረገች ።
እኔ ከአይኗ ለመራቅ ስሞክር እሷ ጭራሽ ያንን ቀይይይይ እና ለስላሳ የሚያንፀባርቅ እጇን ትልክብኛለች ወይ ጉዴ !!!
ደግነቱ ቶሎ እጇን አነሳችለኝ እንጂ ውሀ ሆኜ ነበር !!!
ራሴን አረጋግቼ
ደህና ነኝ አረ ምነው ? አልኳት
" እኔንጃ ፊትክ የተረበሽክ ይመስላል " አለችኝ እጆቿን ከአገጯ ጋር እያወዳጀች ።
ስትነካኝ ብደንግጥም እንድትነካኝ ባልፈልገም ሳያት ምናለ እጆቿን አቅፌ በተቀመጥኩ ከጉንጮቼ ጋር አጣምሬ በቆየሁ ብዬ እመኛለሁኝ !!!
በነገራችን ላይ ስለሁሉም ቁንጅና ተናግሬ ራሴን ዘነጋሁት መሠለኝ ☺️☺️
እና እናቴና ሌሎች በርካታ ሰዎች እንደሚሉት ከሆነ
የሚያምር የቆዳ ቀለም ከሚያምር አይን ጋር ሰልካካ አፍንጫ ከተደረደሩና ነጭ ከሆኑ ውብ ጥርሶች ጋር ለስላሳና በመጠኑ ያደገ ፀጉር ስፖርት የጀመርኩት ከብቸኝነት ለመሸሽ እና ጊዜዬን ለማሳለፍ ቢሆንም የሚያምርና የተስተካከለ አቋም ዘመኑን ከዋጀ አለባበስ ጋር ብዙ ነገር ሰቶኛል !!!
ብቻ ምን አደከማቹ ልቅም ያልኩ ቆንጆ ነኝ !!!😂
አልፎ አልፎ እነሱን ብጠራጠራቸውም የእናቴ ክብ መስታወት ፊት ስቆም ራሴን እንደ ቆንጆ መቁጠር እጀምራለሁ !!!
ከገባሁበት ራስን የመቆለል ሰመመን ውስጥ ያነቃችኝ
" ደግሞ ፍቅረኛክን ሳታስተዋውቀኝ አ " ስትል ነበረ ።
እንደዛ ስትል ማያ ትዝ አለችኝ ግን ከውሸቶቼ መሀል አንድ ልቀንስ ብዬ አስቤ
ያንቺን ባል አስተዋውቂኝ እንጂ እኔ ፍቅረኛ የለኝም አልኳት ።
የሆነ ፈገግታ አየሁባት የምን እንደሆነ አላውቅም ግን ደስ ብሏታል ።
ፍቅረኛ እያላት ምንድነው እንዲ የሚያስደስታት ሆይ ።
ውይ የሀብታም ልጆች ግን ከመቼው ነው ይቺ ልጅ ፍቅረኛ የያዘችው ምናለ ቢያስ ትንሽ ብትቆይ ወይ ቢያንስ ደግሞ ከኔ ጋ ባትተዋወቅ ለነገሩ ከመሠሎቿ ጋ መሆን አለባት ያመኛል እንዴ ........
በጣም ቦዙ ነገሮች እየቀባጠርኩ ብቻዬን ሳወራ ነበረ ።
" የኔን ፍቅረኛ እኮ ታቀዋለህ " አለችኝ ።
ክው ነው ያልኩት ።
ማ እኔ አልኳት ግራ ገብቶኝ ።
" አዎ ታቀዋለህ እኮ " አለችኝ
ምላሹን የመስማት ፍላጎት ባይኖረኝም
ማነው ?? አልኳት
✍✍✍fidel.....
ሼር አድርጉ ቤተሰብ
https://t.me/fidel_z28
ክፍል አስራ ስድስት
.........ቆምኩኝ ። ከዛ ልዕልናን ዞሬ ሳያት እንዴት እንደተረዳችኝ ባላውቅም ከተቀመጠችበት እየተነሳች
" እማ እሱኮ ሚኪ ነው አስተዋውቅሻለሁ ያልኩሽ ልጅ እሱ ነው ጥሩ ልጅ ነው በዛ ላይ የአባዬ ጓደኛ ነው እኮ " አለቻት ልክ እኔ በያት ልላት አመት እዳሰብኩት ለዛውም የተሻለ አርጋ አሳመነችልኝ ።
ቀስ ብላ ተረጋጋች አየር እየሳበችና እየተነፈሰች ራሷን አረጋጋች ።
ይቺ ሴት እብድ አይደለችም !!!! ምን ማረግ እንዳለባትም ሆነ ምን እያረገች እንደሆነ ጠንቅቃ ታውቃለች ራሷን እንዴት እንደምታረጋጋ ሳየቀር ታውቃለች ።
ሰው ስለበደላት የሰው ጥላቻ ብቻ ነው እሷን የጎዳት !!!!
እና እሷን ለማረጋጋት በጣም ቀላል ነገር ነው !!!
እኔም እድሌን ተጠቀምኩኝ እግሯ ስር በርከክ ብዬ እያረጋጋዋት
ላንቺ ባይመጥንሽም ስለ አንቺ ስለነገሩኝ ትንሽዬ ስጦታ አምጥቼልሻለሁ ማየት አፈልጊም ?? አልኳት ።
ተመቻችታ እየተቀመጠች ቁጥብ ፈገግታ አሳየችኝ ።
ከዛም ብልጭልጭ ቢሆንም በምርጫ ጎበዝ ነኝ መሠለኝ ስጦታውን ሳወጣሁ ሁሉም ተገርመው አዩኝ ሳስበው አልጠበቁም መሠለኝ !!
እሷም በጣም እንደወደደችው እንድገምት የሚያደርግ ፊት አሳየችኝ ።
ከዛም ከማስቀመጫው ላይ አውጥታ እየወሰደች
" በጣም ያምራል " አለችኝ በለሆሳስ ።
ድምጿ በጣም ደስ ይላል !!! በዛ ላይ በጣም ቆንጅዬ ናት !!! በርግጠኝነት ሳሚ ራሱን ጥፋተኛ አደረገ እንጂ በቁንጅናዋና በእድለኝነቷ የተነሳ በቅናት ተገፋፍታ እንዲ ያደረገቻት ይመስለኛል !!!
ግን ምን አይነት ጭካኔ ነው በፈጣሪ የፈለገ ቢሆን እንዴት አብሮ አደግ ጓደኛዋን እንዲ ታደርጋታለች ሴትዮዋን ባቃትና የኔ እናት ብትሆን የምገላት ሁላ መስሎ ተሰማኝ !!!
ብቻ ግን ቃሉ አትፍረድ !! ነውና ፈርጄ ከጨረስኩም ቢሆን አስታውሼ ዝም አልኩኝ ።
እኔ ሀብታም ሰዎች አርቴፊሻል ነገር የሚጠቀሙም አይመስለኝም ነበር ፊቴ ላይ ትወረውረው ይሆን እንዴ እያልኩ እየፈራሁ ነበር የሰጠዋት ።
ከጠበኩት በተቃራኒው ግን በጣም እንደወደደችው እየነገረችኝ በፍቅር አይን እያየችኝ
" አመሠግናለሁ በጣም " አለችኝ ።
ኡፍፍፍ የኔ እናት እርጋታዋ ደርባባነቷ በጣም ነው ደስ የሚለው ።
ረጅምና ለስላሳ ፀጉሯ ሁለት ቦታ እንደተሰራ የቆየ ይመስላል ።
ያ ቀይ ፊቷ በቁስል እና በተቧጨረ ነገር ተሞልቷል ሲመስለኝ ሲያማት ራሷን ለማጥቃት ትሞክራለች መሠለኝ !!!
ግን የተፈጥሮ ውበቷ ያስታውቃል በዛ ላይ ያን ያህል ትልቅ አይደለችም ወጣት የምትባል ሰው ናት !!!
እኔ በሷ ተፈጥሮ እየተመራመርኩ ለካ ሳሚ እያወራ ምን እንዳለ ሳልሰማው " እናመሠግናለን " ሲል ብቻ ሰማሁት ።
ምን ይበል ምን ባላውቅም አረ አይባል ሳሚ ብዬ ፈገግ አልኩኝ ።
ከዛ እዛ ሀብሉን ልታረገው ስትል
አይ አይ እንደዚ አይደለም መጀመሪያ አንዱን ልዕልና አንዱን ሳሚ ፀጉርሽን ይፈቱታል ከዛ ረጅም ሰአት የሚፈጅ ሻውር ከባለቤትሽ ጋ ትወስጃለሽ ቀስ ብሎ ያጥብሻል ከዛ ልብስ ትቀይሪና ጌጥሽን አድርገሽ ዛሬ ከእኔ ጋር ነው ምሳ የምንበላዎ እንጠብቅሻለን አልኳት መልሷ ምንም ቢሆነን ለመጋፈጥ እየተዘጋጀሁ ።
እንዳሰብኩትም ማልቀስ ጀመረች ስቅስቅ ብላ ካለቀሰች ቡሀላ ወደኔ ተጠግታ ጭምቅ አድርጋ አቀፈችኝና
" የምር እንዳልከው ማረግ እችላለሁ እ ??" ብላ በጥያቄ ፊት አየችኝ ።
እኔም በደስታ ተሞልቼ አዎ አዎ በደንብ ትችያለሽ በጣም ቀላል ነገር ነው እኮ ትችያለሽ !!!!
ብዬ ለማነቃቃት ሞከርኩኝ ተመቻችታ ተቀምጣ ዞር ብላ ሳሚን አየችው ።
እሱም እሺ የምትል ስላልመሠለው ችላ ብሎ ተቀምጦ የነበረ ቢሆንም ስታየው በደስታ ተነስተው ሁለቱም እንደ እንቁላል እየተንከባከቡ በቀስታ ፈቷት ።
በጣም ተጎድቶ ራሱ የሚያምር ፀጉር አላት ።
ከዛም ወደ ሳሎን ተመልሰን እኔና ልዕልና ቁጭ ብለን ሁሉም ሰላም እንዲሆን እየፀለይን ቆየን ።
ከዛም ቀራርቦ የነበረው ምግብ አንዳንዶቹን እያነሳች ማሞቅ እና ሰላም በፊት ላይ ትወዳቸው የነበሩ ምግቦችና ጁስ መጨመር ጀመረች ።
ልዕልና በጣም ጨንቋት ስትቆም ስትቀመጥ ስትነሳ ስትጨነቅ ነበር እውነት ለመናገር እኔም በጣም ፈርቻለሁ !!!
የሆነ ነገር እንደሚቀየር እያሰብኩ ተጨንቄ ነበር ።
እዛው ተቀምጠን ከ አንድ ሰአት ከሀምሳ ደቂቃ በላይ ቆየን !!
አዲስ ነገር ብንጠብቅም ቆዩብን።እስከዛ ሰአት ሰላም መሆናቸው ትንሽ አረጋግቶኝ ልክ ቁጭ ስል የሚረብሽ ጩኸት ሰማንና ሁለታችንም ለሩጫ እንደተዘጋጀ አትሌት በሩጫ ወደመታጠቢያ ቤት ሮጥን .........
✍✍✍✍fidel.....
........ ከማያ ጋ ተገጣጠምኩ ። በፊት ላይ አግኝቻትም የማላቃት ልጅ አሁን በዚህ ልክ መገጣጠማችን በጣም እያስገረመኝ ነው ።
አሁን አልተሳሳትኩም ራሴን እንደምንም ተቆጣጥሬ አለፍኳት ።
የሆነ አካሌ ግን ያዛት ያዛት ይለኛል ??
ከዛም ምን እንደሚያያዝ ባላውቅም ሀብታም ቤት ሙዝ ይዤ አልሄድም ብዬ ገበያ ውስጥ ስዟዟር የሆነ የሚያምር ጌጣጌጥ ቤት ተመለከትኩኝ ።
አርቴፊሻል ቢሆንም የሚያማምር ሀብልና የእጅ ጌጥ አየሁኝ ።
እና ሚኪ በጣም አስተዋይና አሳቢ ሰው ስለሆነ የሷን መንፈስ የሚያድሱና እሷን የሚያስደስቱ ነገሮች መግዛት ይሻላል ብዬ አሰብኩኝና በሌለኝ ብር መከራከር እንኳን አልችል የሚያምር ሀብልና የእጅ ጌጥ ገዝቼ በእቃ ላይ አስደርጌ ወደነ ሳሚ ቤት ሄድኩኝ ።
ልክ እኔ ስደርስ የሳሚ መኪና ስትገባ ተገጣጠምን ።
ስራ ጨርሶ ምሳ ለመብላት መምጣቱ ነበር ።
እኔም እግር ጥሎኝ እያልኩኝ በአይነት የቀረበው ምግብ ላይ ደረስኩኝ ።
ሚኪ ከባድ የራስ መተማመን ተጭኖታል ።
መኝታ ቤቷን ቆልፋ የምትኖረውን የልዕልናን እናት ሰላምን ጤነኛ ሰው ለማረግ ሀላፊነት ወስዷል ።
ልዕልናም እጇን ተጣጥባ ስትመጣ ከኔ ጋ አይን ለአይን ተገጣጠምን ።
እየሮጠች መታ ጥምጥም ብላ አቀፈችኝ ። ደነገጥኩኝ ክው ብዬ እስክትለቀኝ መጠበቅ ጀመርኩኝ ።
" ትላንት እኮ እናቴን አወራዋት ከስንት ጊዜ ቡሀላ አወራችኝ ስታለቅስ አየዋት በጣም ነው የምናመሠግነው እሺ ደግሞ ስለ አንተ ነግሪያታለሁ እኮ አስተዋውቅሻለሁ ብያታለሁ " ብላ ጉንጬን ሳመችኝ ።
ክው ነው ያልኩት !!! ደንግጬ ፍዝዝ ብዬ ሳያት ምንም ሳትል ዞራ ምግቡ ጋ ቁጭ አለች ።
ወዲያው አንድ የሚገርም ሀሳብ መጣልኝ ቀጥታ ወደ ሳሚ ዞርኩኝና
አንድ ሀሳብ አለኝ !! አልኩ ፈገግ ብዬ
" ምንድነው እሺ " አለኝ ሳሚ ወንበሩ ላይ እየተቀመጠ ።
ወደ ምግብ ከመግባታችን በፊት አንዴ ሰላምን እንያት አልኳቸው ።
ቤቱ በአበቦች ነፈካ ስለሆነ ከማስቀመጫው ላይ አበባ ሳብ ሳብ አርጌ ሁለት አወጣሁ እና ይሄን ይዘን አልኳቸው ።
" አሁን ምሳ ሊቀርብላት ነው ትብላና እናወራለን ከፈለክ " አለኝ ሳሚ በተጨናነቀ ፊት ።
አይ አይ አይሆንም ምግብም አብረን ልንበላ እንችላለን ማን ያውቃል አልኳቸው ።
በጣም ደስ እያለኝ ነው ሀሳቤን የነገርኳቸው !!! ሳስበው ሚኪ ጥሩ የስነ ልቦና ሀኪም መሆን የሚችል ይመስላል !!!
በጣም አስተዋይ ሆኛለሁ ሲጀመር እዚህ ቤት ስመጣ ሌላ የማላቀውን ሰው ነው የምሆነው ። ብቻ ግን መልሳቸውን ስጠብቅ ልዕልና ቀደም ብላ
" ጥሩ ሀሳብ አይመስለኝም " አለች ሳሚም እሷን ተከትሎ
" አዎ አትልፋ አይሆንም እሺ አትልም " አለኝ
ከየት እንዳመጣሁት ባላቅም
ይሆናል !!! ባይሆንም እንሞክረዋ ከሆነ ይሆናል ካልሆነ ቀጣይ ይሆናል ባለፈው ቀን እኮ አምንሀለሁ ብለከኛል እንደምታምነኝ አሳየኛ !!! አልኩት ።
ሳሚም አላሳፈረኝም እሺታውን ለመግለፅ ከተቀመጠበት ተነሳ ።
ልዕልና ሀሳቡን እንዳታስቀይረው ፈርቼ በእጄ ግትቼ ላነሳት ስሞክር ገና እንደያስኳት የሆነ የንዝረት ስሜት ስለተሰማኝ ደንግጬ ቶሎ ለቀኳት ።
ከዛም አበባውን ለሁለቱም ሰጠዋቸውና እናንተ ግቡና እመጣለሁ ብያቸው ወደዃላ ቀረሁ ።
ከዛም ወደ ልዕልና ጠጋ ብዬ
ገብተሽ በደንብ አውሪያትና ከዛ እንግዳ ላስተዋውቅሽ ብለሽ ጥሪኝ አልኳት ቀስ ብዬ እሷም እሺ ብላኝ ወደ ክፍሏ ሄድን ።
ሁለቱም ከመፍራታቸው የተነሳ በሩ ላይ ሲደርሱ ሁለቱም በረጅሙ ተንፍሰው አማትበው ወደ ውስጥ ገቡ ።
ውጪ እያለች ልዕልና በጣም ፈርታ የነበረ ቢሆንም ቀበጥ መሆኗ ጠቀማት መሠለኝ ፍልቅልቅ እያለች
" ማማ አየሽ ምን እንዳመጣንልሽ አበባ ላንቺ ነው እኮ ናፍቀሽን ነበር " አለቻት እቅፏ ውስጥ እየገባች።
ሳሚ ቃላት ማውጣት ስለከበደው በፀጥታ ተውጦ ግንባሯን ሳማትና ፊት ለፊቷ ቁጭ አለ ።
ከዛም ልዕልና ቶሎ ብላ
" እማ የማስተዋውቅሽ ሰው አለ " ብላ በምልክት ጠራችኝ ።
እስካሁን እነሱን ሲመክርና ሲያበረታታ የነበርኩ ልጅ ለመግባት ራሱ ፈራሁ ከዛ ግን ሳማትብ ለቀቀኝና ፈገግ ብዬ ገና እግሬን ሳስገባ ወደዃላ እየሸሸች መፍራትና መንቀጥቀጥ ጀመረች የሆነ መንፈስ እንዳየ ሰው አረጋት ።
" ከነገርኩህ ጊዜ ጀምሮ ሰው ትፈራለች የማታቀውን ሰው አትወድም ትሸሻለች ነግሬህ ነበር እኮ እንደማይሆን " አለኝ ሳሚ ከተቀመጠበት ተነስቶ በቀስታ ።
የነበረኝ ትልቅ በራስ መተማመን ይጥቀመኝ ይጉዳኝ ባላውቅም በራሴ ተማምኜ
ሊሆን ይችላል ብዬ ወደሷ ቀርቤ ከአልጋው ስር በርከክ ብዬ ስቀመጥ በትልቅ ፍራቻ ታየኝ ጀመር ።
እኔ በሌለኝ ብር አውጥቼ የገዛውት ስጦታ ልሰጣት ከሁዴዬ ውስጥ ፌስታሉን ሳወጣ እሪሪሪ ብላ ጮኸች መረበሽ ጀመረች ትራሶቹን ወረወረችብኝ ማልቀስ ጀመረች .........
በጣም ደነገጥኩ ሳሚ እጄን እየጎተተ እንደወጣ ቢነግረኝም እዛው ቆሜ ቀረሁ .......
✍✍✍✍fidel ....
ክፍል አስራ አምስት
......... እጇን ጭምቅ አድርጌ ያስኩት ። ልጅቷ ስርአት ያላት ፈሪና ጭምት ሰው ናት ። ስይዛት ከመደንገጧ የተነሳ እጆቿ እየተንቀጠቀጡ ነበር ።
ግራ ቢገባት ቀና ብላ እንኳን ሳታየኝ
" ምንድነው ችግር አለ ?" አለችኝ በታፈነና ቀስ ባለ ድምፅ ።
ምን እያሰብኩ እንደነበር አላውቅም እንደመባነን ብዬ እጇን ለቀኳትና በጣም መርበትበት ጀመርኩኝ ።
እ.... እ .... እያልኩኝ ወደፊት ወደዃላ መርበትበት ጀመርኩኝ ።
ምን እንደሆንኩና ምን እየተሰማኝ እንዳለ ማወቅ አለመቻሌ የበለጠ ግራ አጋባኝና እረበሸኝ !!!
ከዛ በላይ ከፊት ለፊቷ ቆሜ መጋፈጥ ስላልቻልኩኝ የሌለብኝን ከአንገቴ ጎንበስ ብዬ ይቅርታ ብያት ፖሊስ እንዳባረረው ሌባ በሩጫ ከቦታው ራኩኝ ።
ቀጥታ ወደቤት ሄድኩ ።
ስገባ እናቴ ቡና እያፈላች ነበር ።
" ምሳ ስጠብቅህ ቆየህብኝ እኮ ልጄ በሰላም ነው ሰሞኑን ከቤት መራቅ አበዛክብኝ " አለችኝ ።
እውነት ለመናገር ልክ ናት ወይ ቤት አይደለሁም ወይ ደግሞ ቁጭ ብዬ ስለ ልዕልናና ስለ ቤተሰቧ እያሰብኩ አመሻለሁ በቃ !!!
የዛሬው ለየት የሚያረገው ግን የእናቴን ስፔሻል ምግብ ድንይ በሽሮ ከበላሁና ድካም የሚያጠፋው ቡናዋን ከጠጣሁ ቡሀላ ገብቼ ስለ ማያ ማሰብ ጀመርኩኝ ።
በርግጥ ስሟንም የማውቀው አንድ ትምህርት ቤትና አንድ ክፍል በመሆናችን ነው ።
የክላሱ ቀለሜ እና ዝምተኛ የፊት ወንበር ወዳጅ እንደሆነች ባውቅም ትኩረት ሰጥቻትም ሆነ በስህተት እንኳን አውርቻት የማላቃት ልጅ አንድ ቀን በራሴ የፈጠርኳት ካራክተር ከመሆኗ ብሶ እንዴት ሆኖ አሁን ላይ የሚሰማኝ ስሜት እንደተፈጠረ አልገባ ብሎኛል ።
ምሽቱን ሙሉ ከአይምሮዬ ማውጣት ከብዶኝ ተጨነኩ !!!
ጠዋት በጠዋት ተነስቼ እንደተለመደው ተሳልሜ ኸደ ስፖርት ሄድኩኝ ።
ሀሳቤን የሚያስረሳኝ ይመስል በጣም ለረጅም ሰአት ስሰራ ቆየሁ ።
ረጅምም ሰአት ከመስራቴ የተነሳ በጣም ደክሜ ትንፋሼ መቆራረጥ ጀምሮ ነበር ቆይቼ አስተዋልኩት እንጂ !!
አሰልጣኙ መቶ እንዳቆሚ ስነግረኝ ነበር ትዝ ያስተዋልኩትም !!!!
ከዛ ወጥቼ ቀጥታ ወደ ቤት ሄድኩኝ ። መንገዱን ሙሉ ፊት ለፊት እንዳላገኛት እየፈራሁ እንደሰረቀ ሰው ዙሪያዬን እያማተርኩ በሰቀቀን ስጓዝ ከፈራሁት በበለጠ እናቴ መስከረም እና ማያ አንድ ላይ ፊት ለፊቴ ሲመጡ አየዋቸው ።
ወደ ግራሞ ወደቀኝም ብመለከት መታጠፊያ የሚባል የለም መሀል ግድግዳዎች ናቸው ።
ወደዃላ ተመልሼ ልሄድ እያሰብኩ እያለ ከሩቅ እናቴ ፈገግ ስትል አየዋት ደ
ያ ማለት ደግሞ አይታኛለች ማለት ነው ብዬ ስላሰብኩ ቀጥ ብዬ ቆምኩኝ ።
የሚያናደው ደግሞ አጠገቤ እየቀረቡ ሲመጡ ነበር ያስተዋሉኝና የዛኔ ነበር የእናቴንና የመስከረምን ተገርሞ እኔን ማየትና የማያን ቀድንጋጤ ቀጥ ብሎ መቆም ያስተዋልኩት ።
ምናለ ቀጥ ብዬ ብመለስ ያልኩት !!! ምክንያቱም ገና ሲቀርቡኝ ሌቤ መረበሹና እንግዳ ስሜቶችን ማስተናገድ የጀመርኩት ።
አጠገቤ እንደደረሱ እንደሁሌው እናቴ አገላብጣ ሳመችኝና
" ልጄ ስጠብቅህ ስትቆይብኝ እኮ ነው የወጣሁት " አለችኝ ቀበል አድርጋም መስከረም እንደናቴ ከሰማችኝ ቡሀላ
" ጎረምሳው አሁንማ እየጠገብክ ነው እንደልጅነትህም አይደለህ " አለችኝ ።
እሷ ስታወራ ሲያስጨንቀኝ የነበረው ግን ሰላም ልበላት አልበላት እያልኩ ግራ ስጋባ ነበር !!!
እጇን መንካት ፈራሁ ሁላ ብቻ
አረ እንዴት እናንተ ላይ ይጠገባል አንድ ላይ አሳድጋችሁኝ ... ምናምን ብዬ ነገሩን ለመደባበስ ሞከርኩኝ ።
"" የመስኪዬ ልጅ ናት እኩ ሰላም በላት እንጂ " የሚለው የእናቴ ንግግር ነበር ቆሌዬን የገፈፈው ።
ምን እንደማረግ ግራ ገብቶኝ እናቴን ስመለከታት ቆየሁኝ ። በአይኗ ቁጣዋን ስታሳየኝ ደንግጬ እጄን ዘረጋሁላት እሷ ፈርታለች ቶሎ እጄን ነካ አድርጋ ሰበሰበችው ።
ምንም ባላመጣው እኔን መንካት ደብሯት ነው ! በዬ ተናደድኩኝ ።
ሳስበው ስናደድ ነው መሠለኝ ወደ እራሴ የምመለሰው ኮስተር ብዬ
ሰላም ዋሉ ብዬ ማያን ገፍተር አድርጊያት አልፌ ሄድኩኝ ።
ቤት ገብቼ ሻውር ወስጄ ጨርሼ ራሱ መናደዴን ማስቆም አልቻልኩኝም የሆነ ያለመከበር ያለመፈለግ አይነት ስሜት ነው የተሰማኝ !!!
በእራሴና በሁኔታዎች እየተናደድኩኝ ነበር ።
ከዛ ቁርሴን በልቼ ጨርሼ ለጥ አልኩኝ ።
ደክሜ ስለነበር ቶሎ እንቅልፍ ወሰደኝ ለረጅም ሰአት ተኝቼ ተነሳሁኝ ።
ከዛ ስነቃ ሳሚ ትዝ አለኝ ።
ብር ማስቀመጫዬ ላይ ሳይ ትንሽ ብር ነበረችኝና ህመምተኛ ለመጠየቅ በሚል ሰበብ ለመሄድ አሰብኩ ከዛ ለባብሼ ከቤት ወጣሁ ልክ ስወጣ ከማያ ጋ ተገጣጠምኩ ......
✍✍fidel.....
ክፍል አስራ አምስት
......... ከተቀመጥኩበት ተነሳሁ ። እሷም ክው ብሓ እርምጃዋን ገታችው ???
እየተፈጠረ ያለው ነገር ከኔ አልፎ ያስጨነቀው ሳሚ
" ምነው ልጄ ችግር አለ ?" ብሎ እጄን ሲይዘኝ ከገባሁበት ሰመመን ባነን ብዬ
ይቅርታ ሳሚ የሆነ ነገር ትዝ ብሎኝ ነው !! ብዬ ንግግሬን ገታ አደረኩት ።
እሷም የበለጠ ነጠላውን እየተሸፋፈነች አንገቷን ደፍታ ቄሱን ተከትላ ሄደች ።
ምን እንደተፈጠረና ምን እንደሆንኩ ያልገባኝ እኔ በሀሳብ ተውጬ እያለ ነበር ሳሚ
" ልትነግረኝ ካልፈለክ ተወው በቃ " ያለኝ ።
ለካስ ስለ እራሴ እንድነግረው ሲጠይቀኝ ስለነበር ይሄ ድንጋጤ የተፈጠረው ማውራት ያልፈለኩ መስሎት ነበር ።
እኔም አረ በጭራሽ እንደዛ አይደለምዐበምነግርህ ህይወት ለመገረም ተዘጋጅ እንጂ ነግርሀለሁ አልኩት ።
በመጀመሪያ ትክክለኛ ስሜ ሚኪያስ አይደለም ሀብታሙ ነው ብዬ መናዘዝ ጀመርኩ ።
ገና ሳልነግረው የተገረመ ፊት አሳየኝ ። እኔም ፈገግ ብዬ
እኔ የደሀ ልጅ ሆኜ ስሜ ሀብታሙ መሆኑን ስለማልወደው ነው ያስቀየርኩት ።
እና ደግሞ እናቴም አባቴም በጣም ደሀ ከተባለ ቤተሰብ ወተው ደሀ ቤተሰብ መስርተው ይኖራሉ ።
የቤቱ ብቸኛ ልጅ ነኝ ። አባቴ የመጠጥ ሱሰኛ ነው አንድ ካቲካላ ጎንጨት ካላለ የሎብ ምት እንደቆመ ሰው ያረገዋል ።
ሲጠጣ ደግሞ ታርዳ እንደተጣለች ዶሮ ያንፈራግጠዋል !!!
ከልጅነቴ ጀምሮ በድህነት ህይወት ውስጥ ነው ያደኩት ።
እናቴ ጉልት ሰርታ ነው ያሳደገችኝ አባቴ አልፎ አልፎ ይሰራል ችግሩ እዛው በካቲካላ ይጨርሳታል ።
እናቴን ያን ያህል ጠባየ ግዛትም እንደገቢያችን ወጪም የለንም እኔ ከጠገብኩ አለም ሁሉ ሰላም ውሎ ያደረ የሚመስላት ምስኪን እናት ናት ያለችኝ ።
" አልጠራጠርም " አለ ሳሚ ጣልቃ ገብቶ ።
በቃ አሁን ላይ የምታነው ሀብታሙን የገነባችው እናቴ ናት ሚኪን ለመገንባት ደግሞ በትንሹ የራሴ ጥረትም አለበት ።
እና አጋጣሚ ከእናንተ ጋር አስተዋወቀኝ እኔ መኖር አለመኖሩንም የማላቀውን አይነት ህይወት ነው የምትኖሩት ።
ደግሞ በፈጣሪ ስም የምምልልክ እኔ በገንዘብ የምገዛ ሰውም አይደለሁም እና ለገንዘብ ብዬ የቀረብኳችሁ ምናምን እንዲመስላችሁ አልፈልግም እኔ በትምህርቴም ደካማ አይደለሁም በጉልበትም ጠንካራ ነኝ በራሴ ሰርቼ ማግኘት የምችል ሰው ነኝ ነገሮች አልመቻች ብለውኝ ነው አልኩት ።
ከሱ ጋ ሳወራ ከልቤ ነው የማወራው እና ለረጅም ደቂቃ በጣም ብዙ ነገር አወራን ከሱ የምደብቅበት ምክንያት የለኝም ለልዕልና ይንገራት አይንገራትም አላሳሰበኝም ሁሉንም ነገር ነገርኩት ።
በጣም ለብዙ ሰአት ነው ያወራነው ደስ የሚለው እሱም በእኔ ላይ ሙሉ እምነት እንዳለው እስከመጨረሻው አብረን እንደምንዘልቅ እኔን እንደ ልጅም እንደ ጓደኛም እንደተቀበለኝ ሙሉ በሙሉ እንደሚያምነኝ ስለ ድህነት ስለ ሀብት እሱም በፊት ላይ ምን አምነት ህይወት እንደነበረው ብቻ በጣም ብዙ ነገር አወራን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በዚህ ልክ የውጪ ሰው ሳወራ ።
ከሰው ብጣላም ከአስተማሪ ብጣላም በድህነት ብከፋም ብቻ ምንም አይነት ነገር ቢኖር እናቴ እቅፍ ውስጥ ገብቼ ነው የማለቅሰው ሌላ የማወራውም የለኝም ።
ከረጅም የግል ንግግር ስንነቃ ነበር ቤተክርስቲያን ውስጥ መሆናችንም የታወቀኝ ።
ከዛ ተሳልመን ከዛ ወጣን ።
እኔ ተመልሼ ወደነሱ ቤት መሄድ አልፈለኩኝም ። ሳሚ ደግሞ አብረን እንድንሄድ አስቦ ነበር ግን ስራ አለኝ ብዬ ግግም አልኩበት ።
በስተመጨረሻም ቅዳሜ መጥቼ ጠይቃታለሁ ብዬ ቃል ገብቼ እኔም ወደቤቴ በእግሬ መሄድ ጀመርኩ ሳሚም በመኪናው ተመለሰ ።
መንገድ ላይ ሆኜ በርካታ ሀሳቦች ሲመላለሱብኝ ነበር !!!!!
ማያን ሳያት ለምን እንደደነገጥኩ ራሴን ጠየኩት ።
አይ ለልዕልና ያወራሁትንና እሷን ስላሰብኩ ስህተት ስለሆነ ነው ብዬ አሰብኩኝና ቀጥ ብዬ መንገዴን ቀጠልኩኝ ።
ከሳሚ ጋር ስላወራሁ የሆነ ነገር ቅልል ብሎኛል ።
ስለድህነቴ ለልዕልና ነገራት አልነገራት ብዬ አለመጨነቄ ግን ትንሽ አስጨንቆኛል !!!
ዙሪያ ጥምጥም አድርጌ በሩቅ መንገድ አርጌ ብቻዬን እያወራሁ ነበር እየሄድኩ የነበርው ።
የመጨረሻው የኛ ቤት መታጠፊያ ቀጭኗ መንገድ ጋር ስደርስ ግን ከየት መጣች ሳልላት ከፊት ለፊቴ ማያ ስትመጣ አየዋት ።
ሳላስበው ቀጥ ብዬ ቆምኩኝ ።
ለምን እንደሆነ አላቅም ሳያት ሰውነቴ መታዘዝ ያቆም ይመስል የማስበውን ማረግ ከብዶኛል ። ቅድም ለምን እንደቆምኩም ሆነ አሁን መራመድ ለምን እንደከበደኝ አላቅም !!!
ስታየኝ እሷም መደንገጧ ደግሞ የኔን ሀሳብና ጭንቀት አጋጋለብኝ ።
ከሩቅ ስትመጣ ጀምሮ እያየዋት ነበር !!!
ያን ያህል ቆንጆ መሆኗን ያየሁት የዛኔ ነበር ቁመት አቋም ቀሚስ ለባሽ ከእርጋታ ጋር አነውባት ።
ቀስ በቀስ ረጠገቤ ደረሰች እሷ አውርቻትም ሆነ ቼክ አድርጊያት ስለማላቅ እንደሁሌው አንገቷን ደፍታ እያለፈች ነበር ።
ያቺ ቀጭን መንገድ ግን አቀራርባናለች እና እጄ አልታዘዝ ብሎኝ በሰላም እየሄደች የነበረችውን ልጅ ሳላስበው ቀሚሶቿን ሰብስባ የያዘችበት እጇን ጭምቅ አድርጌ ያስኩት ?????
✍✍fidel.....
ክፍል አስራ አራት
.......... አቀፋት ። አምልጦኝ እንደተቆጣጣሪ አባት ማነው ምንሽ ነው ?? ብዬ ልሟገታት ምንም አልቀረኝ ማለት ይቻላል ግን እንደምንም ራሴን ተቆጣጥሬ በዝምታ ከበሩ ገለል አልኩኝ ።
መን ፈልጋ እንደሆነ አላቅም ዲቦራ ተብዬዋ ተከተለችኝ ።
" አንዴ ስልክህን ስጠኝ " አለችኝ ።
ደፋር እንኳን ቁጥሬን በዘዴ ልትቀበል ስልክም እንደሌለኝ ማን በነገረልኝ እያልኩ በውስጤ
የለኝም ብዬ ንግግሩን በአጭሩ ለመቋጨት ሞከርኩኝ ።
" ልደውል እኮ ነው ""አለች ላለማስነቃት ፊቷን አኮሳትራ ።
በቅርቡ ሰረቁኝ የለኝም አልኩሽ እኮ አልኳትና ፊቴን ዘፈዘፍኩት ።
ትንሽ ደቂቃ በሩ ላይ ቆመው ምን እንዳወሩ ባላቅም ቆየት ብለው ወደኛ መጡ ።
ዲቦራንም አቅፎ ሰላም ካላት ቡሀላ
" ሄይ ሚኪያስ እባላለሁ " ብሎ የራሴን ሁለተኛ ስም ደግሞ ነገረኝ ።
ገና ሳየው አልወደድኩትም ከሱ ጋ ብዙ ላለማውራት እኔም ብዬ ሰላምታውን መልሼ ዝም አልኩኝ ።
" ኑ ግቡ "" ብላ ልዕልና ከፊት ቀደመች እሱም ተከትሏት ሶፋው ላይ ተቃቅፈው ልበል ተዛዝለው ብቻ ተሸካክመው ተቀመጡ ።
ምንም ያህል የምትወደው ፍቅረኛዋ ቢሆን እኛ ፊት የተጋነነ ሁኔታ ማሳየታቸው የምር አናዶኛል ከልቤ !!!
ከዛ ግን ምንም እንዳልመሠለው ለመሆን የማረገው ሳጣ በጥሩ ሰአት ሳሚ ከክፍሉ ሲወጣ አየውት ። ኀለእኔ በጣም አሪፍ ነገር ነው ።
ሳየው ከተቀመጥኩበት ብድግ አልኩኝ አመጣጡ ያስፈራል ነገር !!!!
እኔ ምንም አይነት ጩኸት ስላልሰማሁ ነገሩ ሁሉ ሰላም መስሎኝ ነበር !!!
ፈራሁ በማያገባኝ ገብቼ ነገር ያበላሸው መስሎኝ በጭንቀት ድፍት ልል ስል ቀጥታ መቶ ላዬ ላይ ተጠመጠመብኝ ።
ይሄን እቅፍ አላውቀውም !!!!! bcha gn des mil neger alewu !!!
ሲያቅፈኝ ተረጋጋሁም ተጨነኩም ግራ ገብቶኝ ነበር !!!!
ለደቂቃዎች ካቀፈኝ ቡሀላ ለቀቀኝና በእጆቹ እጄን አጥብቆ ይዞ
" የኔ ልጅ አንተ ማለት ከፈጣሪ የተላክ ስጦታ ነክ ና እንውጣ ላወራክ እፈልጋለሁ ና " ብሎ እጄን እየጎተተ ሊወስደኝ ሲል
ያ ሴታሴት
" እንዴ ሳም " አለ ።
የሚገርመው ያንን ያህል ሰአት ልጁን አላስተዋለውም ነበር ደንገጥ እያለ
" እንዴ ናቲ " ብሎ ጨበጠውና ሰላምታ ከተቀያየሩ ቡሀላ
" ና በቃ ልጅ ሚኪ " ብሎ ወደ ውጪ ገሰገሰ ።
እናውራ ሲል ጊቢ ውስጥ መስሎኝ የነበረ ቢሆንም የውጪውን በር ከፍቶ መኪናውን አመጣና ውስጥ እንድገባ ነግሮኝ ይዞኝ ሄደ ።
ቤት ውስጥ ምን እንደተፈጠረ አለመስማቴ እየረበሸኝ ነው ።
ደግነቱ በጣም ቅርብ ቦታ ነው የሄድነው የሰፈራችን ድምቀት አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ነበር የወሰደኝ ።
የኔ ከጫጫታ ማምለጫዬ መደገፊያዬ መጠለያዬ የልብ ጓደኛዬ... ብቻእዛ መሄዳችን አስደስቶኛል !!!
ሳሚ ተንበርክኮ ያለማቋረጥ ምስጋናን ያቀርባል !!!!
ፀሎቱን እስኪጨርስ ሸሸች ብዬ የራሴን ፀሎት አደረስኩኝ ።
ከዛም ከረጅም ደቂቃዎች ቡሀላ ወደኔ መቶ ከአጠገቤ ተቀመጠ ።
ሰአቱ ቀትር አካባቢ ስለነበር ብዙም ሰው የለም እና ጥጋችንን ይዘን ተቀመጥን ።
እስከሚያወራ እየጠበኩት ነበር !!
" ታውቃለህ ልጄ አንተን ለምን እንደቀረብኩህ ከዚ በፊት ነግሬካለሁ !!!
ታማኝነትህን ስለወደድኩትና ወንድ ልጅ እንዲኖረኝ ብመኝም ስላላገኘው አንተን ሳይህ ስለወደድኩህ ብቻ ነው !!!! በጊዜው ሌላ ሀሳብም አልነበረኝም ግን ታውቃለህ ሳስበው ፈጣሪ ነው ወደኔ የላከህም ሆነ ከኔ ጋ ያገናኘህ !!!!" አለኝ ደስታውጰፊቱ ላይ እየታየ ።
ምን እንዳገኘና ለምን በዚህ ልክ ደስተኛ እንደሆነ የማቀው ነገር ባይኖርም ፈገግ ሲል አብሬው ፈገግ እያልኩ ነበር ።
ከዛም ተሳካልን እንዴ ?? አልኩት ምን እንደምል ግራ ገብቶኝ ።
" በደንብብብ ከስንት ጊዚያት ቡሀላ እኮ አወራችኝ የሚስቴን ድምፅ ሰማሁት " አለኝ ።
ተመስገን አልኩ በልቤ ።
ከዛ ወዲያው መለስ አርጎ
" ልጄ አንተ ልክ ነበርክ የሚያወራትና አዳማጭ ነበር ያጣችው ።!!!
ገና ስታየን እሪ ስለምትል ስለምትጮኽ ስለምታለቅስ እፈራለሁኝ ለዛ ነበር የማላወራት " አለኝ ።
እኔ እንደማስበው መታ ካላየቻችሁና ካላወራቻችሁ በር ከፍታ ካልወጣች ገብታችሁ አታወሯትም አይደል ? አልኩኝ ።
ከሳሚ ጋ ስሆን የሚመጣው አሳቢ አስተዋይና ቁም ነገረኛ ልጅ ማን እንደሆነ ባላቅም በንግግር የበሰለ ሰው እያረገኝ ነው ። ሳሚም ለጠቅ አድርጎ
" እሷ ብዙ ጊዜ የእንቅልፍ ና ሌሎች መድሀኒቶች ትወስዳለች እና ስንገባ የምትታመም ስለሚመስለን ስለምንፈራ ፈልጋን ካልመጣች ዝም ነው የምንለው " አለኝ ።
አየክ አይደል እንጀዛ ስትርቋት ደግሞ እሷዐስለታመመች የተዋችዋትና የጠላቹዋት መስሎ ይሰማታል እና ፈልገሀት ክፍሏን ከፍተህ ስገባ ያለመጠላትና የተፈላጊነት ስሜት ተሰምቷት ነው !! አልኩት ።
" በጣም የሚገርም እይታ ነው ጎበዝ ልጅ ነህ " አለኝ ።
የምርም ግን በእራሴ ንግግር ራሴ እየኮራሁ ነበር ።
ለካ አዳማጭ ካለ ጥሩ ተናጋሪ ይወጣል ማለት ጀመርኩኝ !!!
ከአምላኬና ከእናቴ ውጪ የማወራው አንድም ሰው ስለሌለ ማውራት እንደምችል ራሱ ራሴን እንድጠራጠረው ያደርገኛል !!!
" ታውቃለህ ገና ስገባ እንደናፈቅት ነገረችኝ ብቸኝነት እንደጎዳትና ራሷን እንድጠላ እንዳደረጋት ነገረችኝ ( እንባውን ከአይኑ እየጠራረገ ) ታውቃለህ እኔ እንደማስበው እኔን ሳይሆን ራሷን ጥፋተኛ ነው የምታደርገው ቤተሰባችሁን ደስታችሁን ወጣትነትህን ስለነጠኳችሁ ይቅርታ አለችኝ እኮ ( ያለቅሳል ) የመጨረሻ ቃሏ ደግሞ እርዳኝ አለችኝ እኮ !!! ከፈጣሪ ቀጥሎ የአንተ እርዳታ ያስፈልገኛል እባክህ " አለኝ ።
እኔ በምን ልረዳህ እችላለሁ ሳሚ ?? አልኩት ግራ ገብቶኝ ።
" አሁን እንደረዳከኝ እርዳኝ በቃ ፈጣሪ መርቆ ጥበበኛ ልጅ አርጎሀል እሲ ጥበቡን ይገልጥልሀል ብቻ የቤተሰቤን ጤና እና ደስታ እንድመልስ አግዘኝ " አለኝ በድጋሜ ፊቱ ላይ የሚያንዣብበውን እንባ እየጠረገ ።
ወዲያው ማሰብ ጀመርኩኝ ።
" ከዛ በፊት ግን ....." ብሎ ዝም አለ ።
ግን ምን ሳሚ አልኩት እኔም
" ስለ አንተ ሁሉንም ነገር ማወቅ እፈልጋለሁ እውነታውን !!" አለኝ ።
ስለኔ አልኩት ደንግጬ እንኳን የሚወራ የሚነገር ታሪክ ሊኖረኝ በህይወት መኖሬም የአምላክ ስራ ነው !!!!
እንዲህ ነው የምለው ታሪክ የለኝም ብዬው ቀና ስለ ከፊት ለፊቴ ከደብሩ አንድ አባት ጋር ረጅም ቀሚስ ሻሽና ነጠላ እንደለበሰች ወደኛ መስመር ሲመጡ አየዋቸው ።
ሳላስበው ደነገጥኩ ልቤ ላይ የሆነ እንግዳ ስሜት ሲሰማኝ ነበር ።
እንደዛ ሆና ሳያት ለካ እንደዚ ቆንጆ ናት እንድል አደረገችኝ ።
የሚገርመው የልዕልናና የኔ የፍቅረኛ ማሳየት ውድድር ባይኖር እኮ ጭራሽ ልብ ብዬም አይቻት የማላቀው ልጅ ናት !!!
ምን እንዳሏት ባላውቅም በነጠላው አፏን አፈን እያደረገች ስትስቅ አየዋት ።
ልቤ ላይ ያለውን አላስፈላጊ የልብ ምትና ያልታወቀ ስሜት ግራ አጋባኝ ድንገት ቀና ስትል አይን ለአይን ግጥምጥም አልን !!!
ክው ብዬ ሳላስበው ከተቀመጥኩት ተነሳሁ ????
✍✍✍fidel ......
ማምሸትና አለመልቀቅ ሳይሆን ስለታሪኩ ___
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ፊደል✍✍» is a Telegram channel in the category «История», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 1.8K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 6.1, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 18.0 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий