
Channel statistics
ክፍል ሰላሳ አራት
.................. መጮህና መሳደብ ጀመረች ። በጣም ደንግጫለሁ በጣም !!!!
ያ ሁላ ፍቅር ሳቅ መግባባት የት ሄዶ ነው አልኩ ፈርቼ ።
ማለት ከቀናቶች በፊት እኮ በጣም ተግባብተን ተመሰጋግነን ነበር የተለያየነው !!
ግራ ገብቶኝ ሳሚን መመልከት ጀመርኩኝ እሱ ደግሞ በጣም ከመፍራቱ የተነሳ ሊያረጋጋት እየሞከረ አይደለም ???
እኔ እንደማስበው ከሆነ ደግሞ ሴት ልጅን ከሚያረጋጉ ነገሮች አንዱ የምትወደው ሰው እቅፍ ውስጥ መቆየት ነው ።
ሳሚ ግራ በመጋባት ስሜት ይመለከተኝ ጀመር ከዛ እጆቼን እያጣመርኩ አቅፎ እንዲያባብላት ነገርኩት።
ሳሚ በዛ ላይ ጎበዝ አልሆነም !!! በስራ በባህሪ በሌሎቹ ነገሮች ላይ ጎበዝ ቢሆንም ግን ፍቅር መስጠት ላይ ደካማ ነው !!!
ስሜቱን መግለፅና ማሳየት ላይ የለበትም !
እንዴት እንደተጋቡ አላቅም በርግጠኝነት በሰላም የፍቅር ሰውነት ይመስለኛል !!!
ለምን እኔን ስታይ እንደተናደደች ሊገባኝ አልቻለም !!
ሳሚን ለማስረዳት ስለረቃኝ አጠገቤ ቆማ የለበስኩትን ጃኬት አጨማዳ ወደያዘችው ልዕልና ዞሬ
እቅፍ ናፍቋታል ቶሎ በይ እሷን ማቀፍ አለብሽ አልኳት ።
ነቄ ነገር ናት ቀልጠፍ ብላ ወደ ሰላም ሄደችና እናቴ እማ የኔ ቆንጆ እያለች እንደ ልጅ ፀጉሯን እየደባበሰች አቀፈቻት ።
እውነትም ናፍቋታል መሰለኝ ተረጋጋች። ስድቡን መግታቷን የተመለከተው ሳሜም ከሰላም እቅፍ ተቀብሎ ያባብላት ጀመር ።
ልዕልና ደግሞ ለአባቷ ካስረከበች ቡሀላ ወደኔ መታ ደረቴ ላይ ልጥፍ አለች ።
በሰአቱ ደስታም ድንጋጤም ነበር በርግጥ ግን ሌላ አማራጭ የለኝም አቅፌ ላባብላት ግድ ነው !!!!
ከስንት ቆይታዎች ቡሀላ ሰላም ተረጋጋችልን ።
ሳሎን ተሰብስበን ቁጭ አልን ብዙም ሳትቆይ ወደራሷ መመለሷ ደስ ይላል ግን ውስጧ እንደቸረበሸ ነው ።
የተፈጠረ አዲስ ነገር አለ እንዴ ? አልኩኝ መልሳ ልትሰድበኝ እንደምትችል እያሰብኩኝ !
" የለም ግን ግን አልቻልኩኝም !!!" አለች ፊቷን ላይ ኮምጣጤ እንደጠጣ ሰው ጉምዝዝ አድርጋ ።
ለምን ?? አልኳት መልሼ
" መንፈሴን አስጨነቀቻት ቅርብ ናት አዎ ይሰማኛል እሷ ቅርቤ ናት ጨርቄን አስጥላኝም አረካችም መሠለኝ ቅርቤ ናት !!!!! ..........????" ማለት ጀመረች።
ሁለቱም ግራ ገብቷቸዋል ደንግጠዋል !!
ችግሩ ግን ምንም ልላቸው አልችልም እኔም ግራ ገብቶኛል ለምን እነዚህ ስሜቶች እንደተፈጠረ ማወቅ እፈልጋለሁ ።
አሁን ላይ የማረገው ነገርና የምሰጠው መፍትሄ ስላልነበረኝ እና ነገ የጊቢ ጉዞ ስላለ ወጣሁ !!!
በዛ ሰአት ላይ ጊብ እንደምንሄድ ሳስብ ወደቤት መሄድ ነበረብኝ ።
በጨዋታ መሀል ለምን እንደተናደደችብኝም ነግራኛለች ።
እ ኔም በቻልኩት አውርቻት ተነስቼ ወጣሁ ።
ወደ ቤት ስመለስ ስጠብቀኝ የነበረችው እናቴን ጠርቻት መቅሰስ በላን !!
በቀጣዩ ቀን የት እንደምንላክ እጣ ወጣና ለማየት ሁላችንም ወደ ትምህርት ቤት ሄድን ።
የዛኔ ደግሞ የመንግስትና የግል አንድ ላይ ስለምንፈተን የምንላክበት ቀንና ቦታ ከነስም ተዘርዝረ።
!!
ከሁሉም የሚያስጠላው ነገር ግን ስም ሳነብ የሶስት ሰው ስም ማንበቤ አስደነገጠኝ
✍✍✍fidel ....
እንደ ሀሳብ ትንሽ ነገር ልበላችሁ ምላሽ ለመስጠት ያህል🙌🙌
በመጀመሪያ እኔን የምታበረታቱኝ የምትደግፉኝ ወዳችሁ ተከታትላችሁ የምታነቡልኝ አመሠግናለሁ !!!🙏🙏
group ላይ በተነሳሁ ሀሳብ ላይ ግን
እኔ ተፈታኝ ነኝ በዛ ላይ ሌላ ኮርስም ተማሪ ነኝ ሴት ነኝ ቤት ውስጥ ስራ ይኖራል .... ምንም ጊዜ የለኝም ለመፃፍ ደግሞ ትኩረት እና ረጅም ሰአት ያስፈልጋል !!
ብዙ ነገሮችን በሰአት አብቃቅቼ ነው የምፅፈው ።
አንደኛ ስለሚያስደስተኝ እና እናንተንም ስለማከብራችሁ እና ከረጅም ውሎ ቡሀላ ትንሽ ረፍት ማድረጊያ ትሆናለች ብዬ ስለማስብ ነው የምፅፈው ።
እኔ ያን ያህል ልምድ የለኝም ተምሬውም አይደለም just መፃፍ ስለምወድ ስለምፈልግ ካየዋቸው ከምሰማቸው ነገሮች ላይ ነው የምፅፈው ።
እና ትኩረት ካልሰጣችሁት አላውቅም እንጂ በፅሁፉ መሀል መሀል ላይ ጠቃሚ የምላቸው ምክሮችና ሀሳቦች እንዲኖሩ አርጌ ነው የምፅፈው ።
በአጠቃላይ ግን በ channel ቅር የተሰኛችሁ ካላችው Leave ማለት መብታችሁ ነው ይቻላል ።
ግን ደግሞ just ሀሳብ መስጠት ፈልጋችሁ ከሆነ ደግሞ እሱም መብታችሁ ነው ማስተካከል የምችለውን ነገር አስተካክላለሁኝ !!
በተረፈ ግን ለምታበረታቱኝ ሁሉ ከግንቦት ቡሀላ አሪፍ አሪፍ ታሪኮችና ሌሎች ነገሮችንም እንደምንጀምርና እንደምትወዱት እርግጠኛ ነኝ !!!
እስከዛው ሼር እያደረጋችሁ ቆዩልኝ እወዳችኋለሁ መልካም አዳር!!!!!!
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ክፍል ሰላሳ ሶስት
....... ከዛ ግን ደስ የሚለው እኔ ከጠበኩትና ከፈራሁት የተሻለ ነበር ።
ጥፊ የለውም ትንሽ የስስት ግፍተራ አለ ከዛ እጆቿን አፏ ላይ አድርጋ ዞር ዞር ብላ አየችና
" ምን ሆነሀል ሰው ቢያየንስ ደግሞ ድገመውና ገድልሀለሁ እሺ " የሚሉ የደስታ ቃላቶችን ተናገረች ።
በጣም ሳቋን ለመቆጣጠር እየሞከረች ነበር
ቢያን በሰአቱ ፊቷ ላይ ቁጣና የመዘግነን ስሜት አለመኖሩ ሰላም ሰቶኛል ።
ሲጀመርም ግልፅ የሆነ ነገር ነበር ዝምታዋ መልስ ሰጠኝ ።
እውነት ለመናገር ያንን ነገር ከየት እንዳሰብኩትም አላቅም ለመጀመሪያ ጊዜ የወንድ ልጅ ስሜት ያየሁባት ሴት እሷ ናት !!!
ባለፈው ማያ በዛ ልክ አውርታኝ ራሱ ምንም ፍላጎትና ስሜት አልነበረኝም ለማያ ሲሆን ግን አመለጠኝ !!!!
አሁን ላይ ሳስበው የዛኔ እንኳንም ተሳሳትኩ እላለሁኝ!!!
በሰአቱ የሆነ አይነት ንዝረትና ከልብ የመነጨ የደስታ ስሜት በየተራ እየተመላለሱብኝ ነበር ።
ለምን እንደሆነም አላውቅም በርግጥ ግን የምር ኩራት ተሰምቶኛል የዛኔ የምርም ወንድ የሆንኩ መሰለኝ ።!!
ከዛም ወደሷ ቤት መሄድ ጀመርን ። እንደስከዛሬው አልነበረችም።
አታየኝም አታወራኝም ቅብጥ ቅብጥ አትልም እጅ በደረት አርጋ ቀስ እያለች መሄድ ጀመረች ።
ሳወራትም በጣም በርጋታ መመለሷ ግራ ቢገባኝ
ደህና ነሽ ልዕልና ችግር አለ አስከፋሁሽ እንዴ ?? አልኳት ።
" እንዴ ማለት ምንም አልሆንኩም አረ " አለችኝ ።
እና ምንድነው በአንዴ የተቀየርሽው ? አልኳት ።
ሳቋ አመለጣት ነገር ግን በነዛ የሚያምሩ እጆቿ ሳቋን ከፊቷ ላይ ተቆጣጠረችና
" አይገባህም እንዴ እንደነገሮች እየተቀየርኩ ነዋ " አለችኝ ።
ንግግሯ የበለጠ ግራ አጋባኝ ። ማለት እንዴት ብዬ መልሷን መጠበቅ ጀመርኩ
" ካሁን ቡሀላ ኩል መሆን አለብኝ ነገሮች ተቀይረዋል ጓደኝነት እና ፍቅር ላይ አንድ አንነት ሰው አልሆንም አንተም የፍቅር ሰው ሁን እስኪ አሁንም ልዕልና ነው የምትለኝ እኮ ???" አለችኝ ።
የኔ አናት ሁኔታዋ በጣም ደስ እንዳላት ፊቷ ላይ ይናገራል !!!!
አልፎ አልፎ ለስላሳ እጇቿን እየያስኩ ወደቤት ሄድን ።
ስንደርስ ሳሚ ምሳ የሚበላበት ጠረንጴዛ ላይ ቁጭ ብሎ በሀሳበ ተውጦ ነበር ደ
ቀበጧ ልጅ
" ደህና ነህ አባዬ እንዴት ዋልክ ችግር አለ? " አለችው ።
ሳሚም በአፀፋው ፈገግታ እያሳየ
" ደህና ነኝ ልጄ ምነው ? አለ ።
" እሺ ታጥቤ መጣሁ " ብላ ወጣች ።
ከዛም ሶስታችንም አንድ ላይ ተቀምጠን ማውራት ጀመርን !!!
ከዛ ከሰአታት በፊት ሰላም ታማ እንደነበርና በስንት መከራ እንደተረጋጋች ነገረን ።
ከዛም ቁጭ ብለን ልክ እንደ ጓደኛ ስናወራ ነበር።
ሳሚን ባየሁት ቁጥር ትዝ የሚለኝ አባቴ ነው ።
ረዝሜ ብልም ሰበር ብዬ ማቀፍ የልብን ማውራት እኛ ቤት እንደ ጎጂ ባህል ነው የሚታየው ።
በሰአቱም ሰላም ድብር ብሏት ወደኛ መጣች ።
ምን እንደነካት አላውቅም ገና ስታየኝ እሪ ማለት ጀመረች ከስከዛሬው ተለየችብኝ እና በጣም መጮህ እና መሣደብ ጀመረች ????
✍✍fidel....
ከመናገርህ በፊት አስብ
ከመፈረምህ በፊት አንብብ
ከማስተማርህ በፊት ተማር
ከመተግበርህ በፊት ሞክር
ከመቁረጥህ በፊት ለካ
ከማጉደልህ በፊት ተካ
ከመዋጥህ በፊት አላምጥ
ከመገንዘብህ በፊት አዳምጥ
ከማመንህ በፊት አረጋግጥ
ከመረከብህ በፊት ቁጠር
ከመወሰንህ በፊት መርምር
ከመስራትህ በፊት አቅድ
ከመተኮስህ በፊት አልም
ከመተቸትህ በፊት አጣራ
ከመብላትህ በፊት ስራ
ከመሞትህ በፊት ቶብት/ንሰሀ ግባ/
ከመሄድህ በፊት ሰንቅ
🫡🫡🫡🫡🫡🫡
....... ወደሷ ስዞር በዝምታ ተመለከተችኝ ።
ይቅርታ እንደምታስቢው አይደለም አልኳት ወደሷ እየቀረብኩ ።
" ሂዳ ተከተላት " አለችኝ አንድ እርምጃ ወደዃላ እየሸሸች ።
ይቅርታ የራሴ ጥፋት ነው እንድትጎዳ ስለማልፈልግ ብቻ ነው ብዬ ላስረዳት ሞከርኩ ።
" ለምን ትጎዳለች ራሱን የሚጠብቅ ኩል የሆነ ባል የሚያከብራት ሰው አላት ለምን ትጎዳለች ??" አለችኝ ።
መጀመሪያ እንደዛ አልመሰለኝም ብዬ ላስረዳት እየሞከርኩኝ እያለ
" ትወዳታለህ ?" የሚል ድርቅ ያለ ጥያቄ ጠየቀችኝ ።
ማያ ማለት ከልጅነት የማቃት ግን የማላቃት ልጅ ናት ሽለሷ ሁሉንም ነግርሻለሁ ከፈለግሽ ግን እወዳታለሁ እንጂ በፍቅር አይደለም እምልልሻለሁ አስብላታለሁ ግን ላፈቅራት አልቻልኩኝም እሷ ጋር ያለው ስሜት ቀስ በቀስ እንደሚጠፋ እርግጠኛ ነኝ አልኳት ።
ያን ያህል የተዋጠላት አትመስልም ።
እውነት ለመናገር ከሆነ ከልቤ ነው ያወራሁት በዛ ላይ በራስ በመተማመን ስሜቴን መግለፄ የሆነ ደስ የሚል አይነት ስሜት አለው የሆነ ነገር ከላዬ ላይ እንደወረደ እየተሰማኝ ነው !!!
እዛ ጋር የነበረውን ድባብ መቀየር ፈልጊያለሁኝ ።
ልዕልና ያን ያህል የምትጨክንብኝ አይመስለኝም ግን አላውቅም ።
በሰአቱ ስሜቷን ለማስተካከል ስለፈለኩኝ ወደሷ ቀረብኩኝና አይን አይኗን መመልከት ጀመርኩኝ ።
በሰአቱ በጣም በራስ መተማመን ላይ ነበርኩኝ ።
በልበ ሙሉንት አታምኚኝም እኔ ልሙት በፍቅር አላስባትም አልኳት።
ከዛም ትንሽ የፍቅር ሰው ለመሆን ስለፈለኩኝ
ግን አንቺስ ? አልኳት ፈገግ ብዬ በጣም እየቀረብኳት።
" እኔ ምን ? " አለችኝ ።
ምንም ሳልናገር በሆነ መንገድ አየዋት ተግባብተናል ግን ላለማመን እየሞከረች ይመስለኛል ።
" ደግሞ ለምንድነው እንደሱ የምታየኝ " አለችኝ አይኖቿን ወደ መሬት እየተከለች ።
ደስ የሚለው ቦታው ብዙም ሰው የማይተላለፍበት ስለነበረ እንጂ እንደዛ ከሴት ጋ ተቀራርቤ ሰው ቢያየኝ ኖሮ ......!!!
ብቻ ግን ወደ ፍቅራችን ስመለስ የሌለኝ ባህሪያትን እያወጣሁ ነው ።
ከሷ ጋ ስሆን የሆኑ ስሜቶች አሉ ።
ላቅፋት እንድታቅፈኝ እንድስማት እንድትስመኝ እጆቿን መያዝ ብቻ ብዙ ነገሮችን እመኛለሁ ።
መቼም ሀብትሽ እንደዛ አያረግም ማያን የተዋወቃት ሚኪ የፍቅር ሰው መሆኑ ተዋቶለታል ።
በእጆቼ አገጯ አካባቢ ይዤ ቀና እያደረኳት
አይኔን እያየሽ ተመልከቺኝ እንጂ ምን ሆነሻል ? አልኳት ።
" አንተ እንደሱ አትመልከተኝ አትቀረበኝም " ብላ ድጋሜ አንድ እርምጃ ከኔ ራቀች ።
ሚኪ ግን ከራሱ ጋ አልነበረም የበለጠ ወደሷ ቀረበና ለምን አላት ።
ውስጤ ያለው ሌላኛው ማንነት ማለቴ ሚኪ በዛ ሰአት አልተቻለም ደ
እሷ ደግሞ ስቀርባት ትደነግጣለች
" ምክንያቱም ውስጤ እንድሳሳት ይገፋፋኛል ልቤ ይመታል እና እንደምትወደኝ ማሰብ እንድጀምር ያረገኛል እረፍ !!" አለችኝ ።
ምን አልባት ልክ ብትሆኚስ እ አስቢ ምን ችግር አለው ደግሞ ለምንድነው ልብሽ የሚመታው እ ታፈቅሪኛለሽ እንዴ ?? አልኳት ጉፍጥጥ ብዬ ።
" ሚኪ ዛሬ ምን ሆነሀል ቅድም አሞክ የነበረው ራስክን ነበር አበድክ እንዴ በዛው ?" አለችኝ ።
አይ አሁን ላይ ከበፊቱ የተሻለ ጤነኛ ሆኛለሁ እሺ ብዬ ፈገግ አልኩኝ ።
ትንሽ ዝም አለችና እንደማፈር እያለች
" ታውቃለህ ሚኪ በቅርብ ስትታይ የበለጠ ቆንጆ ነክ እንድጎዳ ካልፈለክ አንድ እርምጃ ከእኔ ራቅ " አለችኝ ።
ማለት ለምን ትጎጃለሽ እ እኔ ቆንጆ መሆኔ አንቺን ይጓዳል ? ብዬ ተመለከትኳት ።
"" አዎ ምክንያቱም ልቤ በጣም እየመታ ነው " አለችኝ ።
ከዛ ምን እንደሆንኩ አላውቅም ሊከተሉኝ የሚችሉትን ጥፊ ጥሎ መሄድ መጣላት ስድብ ሁሉንም ሳላስብ ስሜቴን መቆጣጠር አልቻልኩኝም ቀና አድርጌ በእጆቼ ጉንጮቿን አቅፌ በማይሆን መንገድ ሳምኳት ??? ከዛ ግን .........
✍✍✍fidel......
ክፍል ሰላሳ አንድ
.........አንዷን አጥብቄ መያዝ ነበረብኝ ግን መወሰን ከብዶኝ መሀል ላይ ቆሜ ስወዛገብ ነበር ።
በዛ መሀል ከየት እንደመጣ አላውቅ የማያ አይኖች እንባ አዝለዋል አሳዛኝ የልዕልና ፊት ደግሞ እግሬን እንዳላንቀሳቅስ አስረውኛል ።
" አዝናለሁ ሀብትሽ እድልክ አልቋል " አለችኝ ።
ማለት ማያ እስኪ ልትረጂኝ ሞክሪ እያልኩ አይን አይኗን ስመለከታት ፈገግ አለች ።
ምንድነው ብዬ ግራ በተጋባ ፊት እየተመለከትኳት እያለ
" ችግር አለ ?" የሚል ድምፅ ሰምቼ ዞር ስል ቀጥታ ወደ ማያ ሄዶ ግንባሯን ሳማት ።
ሰውዬው ፊቱ አዲስ ሆነብኝና ግራ ገብቶኝ ቆሜ እስክታስረዳኝ መጠበቅ ጀመርኩኝ ።
" አረ ምንም ችግር የለም ጓደኞቼ ናቸው ላስተዋውቅህ " ብላ ወደኔ ይዛው መጣችና
" ሀብታሙ ይባላል እንደ ወንድሜ በለው ጓደኛዬ ነው እሷ ደግሞ የሱ ሚስት ናት ያው አልተጋቡም ግን በቅርቡ ሰርጋቸውን እንበላለን " አለችው ።
እሱም እጁን ለሰላምታ እየዘረጋ
" በላይ እባላለሁ ባለቤቷ ነኝ " አለ ።
ጭራሽ አልጠበኩኝም የሰርጉ ቀን ትኩረት ሰጥቼም አላየሁትም ከዚ በፊት በሱፍ ምናምን ተወጣጥሮ አይቼው አቃለሁ ግን በኖርማል አለባበስ ሳየው የተለየ ሰው ሆነብኝ ።
እኔ ሳስብ የነበረው የሆነ ከባድ ሰው ትልቅና የሚያስፈራ ሰው አርጌ ነበር ።
በዛ ላይ አባቱን በደንብ ስለማቀው ልክ እንዳባቱ በገንዘብ የሚያምን ጉረኛ እና አፈር አይንካኝ የሚል አይነት ሰው መስሎኝ ነበርጰ።
አልዋሽም ማያ በጣም ትበዛበታለች !!!!!!! ማያ እና እሱ አይገናኙም በርግጥ በዛ ላይ በእድሜ ቢያንስ አምስት አመት በላይ እንደሚበልጣት እገምታለሁ ግን እንዳሰብኩት አያስጠላም !!!
" በቃ አሁን እንሂዳ ለፈተና ማረፍ አለብሽ ነገ ትሄጃለሽ እኮ " ብሏት እጇቿን ይዞ መሄድ ጀመረ ።
ሲጀመር እኔ ነኝ ጥፋተኛ በሰአቱ አዝኜላት እንጂ አፍቅሪያት አልነበረም ማለት ነው??? ብዬ ማሰብ ጀመርኩኝ !!!!
ከደቂቃዎች በፊት ልትሄድ ስትል ልከተላት እየቃታኝ ነበር የቆየው አሁን ግን አጇን ይዟት ሲሄድ ሳይ ምን አልባት የደስታ እንጂ ሌላ ስሜት አልተሰማኝም ነበር !!!!
አትሂጂ ብዬ ልለምናት ላስቆማትም ሆነ ልከተላት አላሰብኩም ሁላ !!
ለነገሩ ለምን ብዬ ???!!!
ሳስበው ትክክለኛ ነገር እንደሆነ ልቤ ስለሚያቀው ይመስለኛል ያልተከፋሁት !!
በሰአቱ ልጁን ሙሉ በሙሉ በአባቱ አይን ስላየሁት ይጎዳታል ትምህርቷን እንድታቋርጥ ያረጋታል በገንዘብ እንደገዛት ቢሰማውስ ?? እያልኩ እፈራ ስለነበር እንዲሁም ማያ በጣም ቆንጆ እና ጨዋ ምርጥ ባህሪ ያላት ሴት ስለሆነች የማይመጥናት እጅ ላይ ወደቀች ብዬ ስላሰብኩኝ እንዲሁም ደግሞ አሱን ያገባችው በእኔ ጥፋት ነው ብዬ ስላሰብኩ ይመስለኛል ያመመኝና የተጎዳሁት !!!
እንደውም ሳስበው ሴት ልጅ የምትወደውን ብቻ ሳይሆን የሚወዳትን ማግባት በጣም የተሻለ አማራጭ ይመስለኛልም !!!
ቢያንሱ እሱ እንዳየሁት ከሆነ ያከብራታል ያስብላታል ይንከባከባታል በሰው ፊት አያዋርዳትም በዛ ላይ በገንዘብም ቢሆን ሀብታም የሀብታም ልጅ ነው እኔ በስም ብቻ ከተሸከምኩት ይልቅ የተሻለ ነው !!!
ስለዚህ እንኳንም ከሱ ጋር ሆነች እንኳንም አልተሳሳትኩ እንኳንም ስሜት አልኖረኝ ብዬ ፈጣሪዬን አመሰገንኩ ደ
በዛ ሁላ ሀሳብ መሀል ግን ለማያ ብዬ ጥያት ልሄድ የቃጣኝና ማያ ስትሄድ ወደሷ ልመለስ ያሰብኩት ልዕልና ትዝ አለችኝና ወይኔ ጉዴ ብዬ ስዞር በሆነ አይነት አስተያየት እያየችኝ ነበር ።
ይቅርታ ልዕልና ብዬ ወደሷ ስዞር .......
✍✍fidel......
ክፍል ሰላሳ
..........ስትመጣ አየዋት ።
በሰአቱ ሳናስበው ከልዕልና ጋር ተቀራርበን ነበር ።
ከቤቱ ስንወጣ ራሱ እየተሳሳቅን ነበር ።
እና ፊት ለፊቴ እሷን ሳያት ያገጠጠው ጥርሴ ባንዴ ሽሽግ አለ ።
ፊት ለፊት ስንገጣጠም የማያ ፊት ላይ ያየሁት ድንጋጤና የመሰበር ስሜት አስተውዬዋለሁ ።
ከእኔ በላይ ደግሞ ልዕልናን በሆነ አስተያየት ተመለከተቻት !!!
ምን ሆና ነው ብዬ ፈራሁ ።
ከዛ በፈጣጣው ወደኛ መጣች ።
ልዕልና ከዚህ በፊት አይታት ስለማታውቅ መታ ፊት ለፊቴ ስትቆም ግራ በተጋባ ፊት ዞራ አየችኝ ።
እኔም ግራ ገብቶኝዐበዝምታ ስመለከት ነበር ።
" እሷ ናት ልጅቷ ?" አለችኝ ።
ጭራሽ ደግሞ ከኔ መልስ እየጠበቀች ነበር ።
ምን ማለት እንዳለብኝ እንኳን የማላቀው እኔ ሁለቱንም በየተራ ተመለከትኳቸው ።
አይናቸውን እኔ ላይ ተክለው ምላሽ ይጠብቃሉ ።
በዝምታዬ መፅናቴን የተመለከተችው ማያ
" ንገረኛ እሷ ናት አይደል እኔን ሳታድነኝ ጥለህ የመሄድህ ምክንያት ??.
እሷ ናት አይደል በፍቅር የጣለችክ ከእኔ ያራቀችክ ??
እሷ ናት ማለት ነው ክብሬን ማንነቴን ልስጥህ ባልኩኝ እንቢ እንድትል ያደረገችህ ........." የሆነውንም ያልሆነውንም ቀባጠረች ።
የእኔ መልስ አሁንም ዝምታ ቢሆንም ልዕልና ግን በሰማችው ነገር የተደሰተች ይመስል ፍልቅልቅ እያለች ነበር ወይኔ ማያ !!!!
ከእኔ መልስ አለማግኘቷ ሲገባት ራሷ መልሳ
" ለነገሩ ልክ ነህ እሷ ከእኔ በላይ ቆንጆ ናት አይደል በዛ ላይ የሚያምር አለባበስ አላት የሀብታም ልጅ መሆኗን እገምታለሁ በዛ ላይ ደግሞ አንተ እንደምትወዳት እሷም እንደምትወድክ በእይታዋ ያስታውቃል !!!
ግን እምልልሀለሁ አክስቴ ራሱ የእኔን ያህል እንደምትወድህ እጠራጠራለሁ !!!!" ብላኝ አረፈችው ።
አክስቴ የምትለው እናቴን ነው ። ንግግሯ የሆነ ደስ ሚል ነገር ቢኖረውም ግን ልዕልና ትኩረቷንና እምነቷን እኔ ላይ እንድትጥል አድርጓት ነበር ።
እንደምወዳት መተማመን ጀምራለች ።
በጣም የምፈራው ነገር አሁን ባለሁበት ሁኔታ የምሯን ነው ትወደኛለህ ? የሚል ጥያቄ ከልዕልና አፍ መስማት ብቻ ነው !!!!!
ምክንያቱም እንደዛ አለችኝ ማለት ፈጣሪ የሰጠኝን ዳግመኛ እድል ገደል እንደመክተት ነው ።
ብትጠይቀኝ ልክ ማያን እንዳጣዋት እሷንምአጣታለሁ ።
ምክንያቱም እኔ ስሜቴን መግለፅ አልችልምምም!!!!
ወደ ማያ ስመልሳችሁ ግን ሳታስበው እንባዋ አመለጣት ።
እሷ ስታለቅስ ማየት አልፈለኩም አንገቴን ደፋሁ ።
ተጨማሪ ንግግር ሳታደርግ
" መልካሙን ሁሉ እመኝልካለሁ እሺ ትገባሀለች ያዝልቅላችሁ " አለችኝ ።
ወዲያው ደግሞ ወደ ልዕልና ዞራ
" አዎ ቆንጆ ነሽ አምናለሁ ግን ፀባይሽም እንደመልክሽ ይሁን እሺ ገባሽ አይደል !!!
ሀብትሼን በምንም ነገር ብታስከፊው አንቺ አትኖሪም ምክንያቱም ሁሌ በቅርብሽ አለሁ " ብላ ዝታ በመሀላችን አልፋ ሄደች ።
ምን ማረግ እንዳለብኝ አላውቅም ልክ ማያን ተከትዬ ልሄድ ስል ልዕልና በሚያሳዝን ፊት እያየችኝ
" ሚኪ አትወደኝም እኔን ?" አለችኝ ።
ወዲያው ማያ ወደኔ ዞራ ታየኝ ጀመር ። በሁለቱ ሴቶች መሀል ሆኜ በየተራ አየዋቸው ።
ልክ ልሁን አልሁን ባላውቅም የግድ መወሰን አንዷን አጥብቄ መያዝ ነበረብኝና ..........
✍✍fidel.....
........ ስልኩ ጠራ ። ሳሚም ቶሎ ከተቀመጠበት ተነስቶ ለማውራት ሄደ ።
ንዴቴ በአንዴ ቀለል ብሎ በፈገግታ ስመለከታት አይኖተቿ እኔን ላለማየት ማማተር ጀመሩ !
ለኔ ያለሽ ፍቅር አባትሽ ፊት እስከመናዘዝ ነው ማለት ነው ? አልኳት በፈገግታ ተሞልቼ !!
" እ አረ እንደዛ አይደለም " እያለች እያለ ሳሚ ወደኛ መጣ ።
" ልጆች እንግዲህ ይቅርታ በጣም አስፈላጊ ስብስባ ረስቼ ነው መሄድ አለብኝ ።
ስጨርሱ ደውሉልኝና መኪና እልክላይዋለሁ ወደቤት ሂዱ " ብሎን እየተቻኮለ ከኪሱ የሆነ ያህል ብር አውጥቶ ለእኔ ሰጠኝና
" የተጠቀምነውን ክፈሉ ካነሰ ደግሞ ደውሉ " ብሎን እየፈጠነ ሄደ ።
ይሄ ማለት ደግሞ እኔና ልዕልና ብቻችንን አንድ ደስ የሚል አየር ያለው ካፌ ነግር ውስጥ ተቀምጠን እየተፋጠጥን ነው ።
ታውቃላችሁ አንዳንዴ በጣም ራሴን እስከመጥላት የሚያደርስ በራስ አለመተማመን ውስጥ ከቶኛል !!!
ልክ ከማያ ጋር ስሆን ሙሉ በሙሉ ማያን እንደምወዳት ይሰማኛል በማግባቷም ተከፍቻለሁ ግን ልክ ልዕልናን ሳገኛት ሁሉንም ነገር ጥርጣሬ ውስጥ ትከተዋለች !!!!
ሁለታችንም ፋንታችንንም ጨርሰን ቁጭ ብለን ስንፋጠጥ የተመለከተን አስተናጋጅ ወደኛ መቶ
" የሚጨመር ነገር አለ ? " አለን ።
ምንም አያስፈልግም ለማለት ገና ላወራ ስል ቀድም ብላ
" ለእኔ ማኪያቶ አምጣልኝ " አለችው ።
በነገራችን ላይ ያን ያህል ውድ እንዳልሆነ ባውቅም ግን ቀምሼ የማላቀው እኔ እድሌን ለመጠቀም ያህል ለእኔም አልኩት ።
ከትኝሽ ቆይታዎች ቡሀላ ይዞልን መጣና መልካም ጊዜ ብሎን ሄደ ።
ሙሉ ሰአቱን ልዕልና አይኖቿን ከእኔ ለማራቅ የምታረገውን ትግል እየተመለከትኩ ምስጥ ብያለሁ ።
ሴት ልጅ የወደደችውን ወንድ ልጅ አይን በጣም ትፈራለች !!
ሴት ልጅ ከወደደችክ ያንተን አይን ላለማየት አይኖቿን ገደልም ልትከት ትችላለለች !!!!
በመሀላችን ያለውን ዝምታ ቀልድ ለማረግ ያህል
እና ስለ ባልሽ ትንሽ ንገሪኛ ? አልኳት ።
" እ የምን ባል ነው ሚኪ " አለችኝ አሁንም እጆቿን የማኪያቶ ሚንኪያ ላይ አድርጋ ።
" ባል አለኝ ብለሽኝ ነበር እኮ አልኳት እኔም ለማወጣጣት ስለፈለኩኝ ።
"አረ እኔ እየደዛ አይነት ነገሮች ላይ የለሁበትም እኮ " አለችኝ ።
የዛን ቀን ምን እይደነካኝም አላውቅም በጣም ቀልደኜ ሆኜ ነበር ከቤት ስወጣ የበረኩበት ሙዶ እና እዛ እያሳየሁት ያለሁት ሙድ አይገናኝም ሁላ !!!!
ጭራሽ ብሶብኝ
እና እኔ የመጀመሪያሽ ነኛ እ !!! አልኳት እየሳኩኝ ።
ማኪያቶው ጠረንጴዛ ላይ እንደተቀመጠ በመሆኑ ምንም ባጠጣም ምራቋ ያነቃት ይመስል ትን ብሏት ውሀ ጠጥታ የው የለቀቃት ሁላ !!!
እንዴ ምየው ችግር አለ ? አልኳት እሷም ቶሎ ብላ
" አረ የምን ችግር ጠጣና ቶሎ እንውጣ በቃ አለችኝ ።
እሷ እንዳደረገችው አማሰልኩና ቀመስኩት ።
ሀለት የምወዳቸው ነገሮች ድብልቅ ነው በጣም ይጣፍጣል !!!!
ቶሎ መውጣት የፈለገች ትመስላለች ቶሎ ቶሎ መጠጣት ጀመረች እኔም ቶሎ ጨርስኩና ሂሳብ መጣ ።
የመጣው ብር ሳሚ ከሰጠኝ አንፃር ትንሽ ነበር !!!
በእኔ በኩል እናቴ በቀን ለአንድ ጊዜ ምግብ የወር ወጪዋን እንዳወጣን ብሰማ እንደማታናግረኝም አቃለሉ ከሳሚ ብር ላይ ብዙ መትረፉ ግን ደስ አላለኝም ።
ከዛ ቲፕ ኘስቀምጠን ወጣንና በር ላይ እንኪ ለሳሚ ስጪው እሺ ብዬ ብሩን ስሰጣት ልትቀበለኝ ፍቃደኛ እየሆነች አልነበረም !!!!
" አያገባኝም ራስክ ስጥ ሲቀጥል ደግሞ ገና ግብዛው መች አለቀ ትጋብዘኛለህ " ብላኝ አረፈች ።
አስቡት በአባቷ ብር እኔ ስጋብዝ !!!!
መኪና ጥሩ ብሎን ቢሄድም እኔ በየቀኑ በእግሬ የምመላለስበት መንገድ ነውና ቅርብ ነው በዛውም እያወራን እንሄዳለን ብያት መንገድ ጀመርን ።
ልክ የሰፈራችን መተጣጠፊያ መንገድ ላይ ስንደርስ ከሷ ጋ እያወራን ከት ብዬ ስቄ ቀና ስል ማያን ከፊት ለፊቴ ወደኔ ስትመጣ አየዋት !???..........
✍✍fidel
ክፍል ሰላሳ
..........ያሳየችው ፊት ደስ አይልም ነበር!!!
ደስ የሚለው እኔም አፀፋውን እየመለስኩ ፊቴን ከሷ በላይ ከስክሼ
ምነው ልዕልና ? አልኳት ።
ዞር ብላ አባቷን ተመለከተችና
" አይ ገርሞኝ ነው " ብላ በቅጡም ሳትጨርስ ለምን ? ብዬ ቆሌዋን ገፍፈኳት !!!
" አይይይይ....." ብላ ነገሩን አረዘመችው ።
በጣም ንዴት ላይ መሆኔን የተመለከተው ሳሚ ልዕልናን በአይኑ ዝም እንድትል እየነገራት ነበር ።
እኔ ትክክል መሆኔን ስለሚያውቅ ምንም ለማለት አልደፈረም ነበር !!
ለደቂቃዎች ያህል በመሀላችን ዝምታ ከሰፈነ ቡሀላ ልዕልና ቀልጠፍ ብላ እየተቁለጨለጨች
" ይቅርታ አንዴ ላውራ ?" ብላ ሁለታችንንም ተመለከተችን ።
በሰአቱ ሳሚ ምንም እንድታወራ የሚፈልግ አይመስልም !!
ሳስበዎ ነገሮችን እንዳታበላሽ ፈርቶ ይመስለኛል !!!
እኔ ደግሞ በተቃራኒው መጥፎ ንግግር ተናግራኝ እሷን መጥላት እፈልጋለው !!!
ምክንያቱም ልጅቷ በጣም ቆንጅዬና የምታሳሳ ናት !!!
የምጎዳው የምታመመው ለማያ ቢሆንም ሳስበው ግን ልዕልና ለእኔ የማትገባ አይነት የሆነች ልዕልት ትመስለኛለች !!!!
ራሴን በደንብ አረጋግቼ አውሪ ምንም ችግር የለውም አልኳት ቀለል ካላት ብዬ ፊቴን ፈታ እያረኩኝ ።
" ይቅርታ ሚኪ ..."ብላ ወሬዋን ስጀምር ቶሎ ጣልቃ ገብቼ ሀብተትሽ በይኝ ሀብታሙ ነው ስሜ አልኳት ቶሎ ጣልቃ ገብቼ ።
በስሜ እንደማንኛውም ሰው ፈገግ ብላለች !!!
ደስ የሚለው ቅልል ያለች ልጅ ስለሆነች
" አይ እኔ ሚኪ ብልክ ይሻለኛል " አለችኝ !
ሳልፈልግና ሳላስበው ፈገግታዬ አመለጠኝ ።
ስኮሳተር ተጨንቆ የነበረው ሳሚም አብሮኝ ፈገግ እያለ ነበር !!!
" ደሞ አንተን የመሰለ ውብ ልጅ ሀብታሙ የሚል ስም አብሮ አይሄድም እሺ በስመአብ " አለች ቀልድ መሆኑን ለማሳወቅ እየሳቀች !!!
እኔም እኮ እሱን አስቤ ነው የቀየርኩት አልኳት ፈገግ ብዬ ።
" እሺ ወደ ሀሳቤ ልመለስና እኔ አንተ ምንም ብትሆን አይጨንቀኝም !!
ካስቀየምኩህ ይቅርታ ግን እኔ አንተን የሳልኩበትና ያገኘውክ ቦታ ስላልተገጣጠመልኝ ብቻ ነው !!!
እንጂ አንተን የወደድኩህ ማለቴ ( ክው ብላ እጆቿን እያወራጨች )የወደድንህ አንተነትህን ነው !!
እኔ አንተ ስለምትኖርበት ቤት ሰፈር መንደር ምንም አይጨንቀኝም !!!
ሲጀመር ማንም ተንደላቆ የኖረ የለም አባዬ አንተ ካለህበት ሁኔታ የከፋ ቦታ ላይ አድጎ አሁን ላይ ....
አንተ ደግሞ ፈጣሪ ሁሉን አሟልቶ ነው የሰጠቅ እኮ በጣም ውብ ነህ ፀባይክ ለመስራት ፍላጎት አለህ ቋንቋ ትችላለህ ቁመትና አለባበስህ ......." ብላ ዝም አለች ።
ቋንቋ ያለችው እንግሊዝኛ ቋንቋን ቀለል አድርጌ መጠቀም እንደምችል አስታውላ ይመስልኛል !
አለባበስ ቁመት ስትል ሞዴሊንግ እንድማር እየነገረችኝ ይመስለኛል !!!
ግን በጣም ውብ ነህ ሁሉን አሟልቶ የሰጠህ እንዲሁም የወደድኩህ የሚሉት ቃላቶች እኔና ሳሚ ፈገግ ብለን እንድናያት ያደረገው ንግግር ይመስለኛል!!!!
ሳላስበው በንግግሯ ተስቤ ነበር !!!
ህመሜን የምርም ሙሉ በሙሉ የለቀቀኝ ይመስለኛል!!!!!
ደስ እያለኝ ነበር !!!
በተለይ ደግሞ እኔ ትለኛለች ብዬ የጠበኩት ነገር እና እሷ ላይ ያየሁት ነገር ምንም ስላልተገጣጠመ ደስ ብሎኛል !!!
ሀብታሞች እንደዛ ያስባሉ ብዬ ስላላሰብኩኝ ተገርሜ ነበር ።
ሳናስበው ሶስታችንም በፈገግተታ ተሞልተን ሳለ የሳሚ ስልክ ጠራ ......
✍✍fidel......
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «ፊደል✍✍» is a Telegram channel in the category «История», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 1.9K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 6.1, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 18.0 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий