
- Main
- Catalog
- News and Media
- Advertising on the Telegram channel «EBS TV»

Advertising on the Telegram channel «EBS TV»
🌐 World Wide News — Breaking stories. Global updates. Real impact. Stay informed with the latest news from every corner of the world — fast, reliable, and all in one channel.
Channel statistics
Full statisticschevron_right
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ኮቾሬ ወረዳ ፍሰሃ ገነት ተብሎ የሚጠራዉ አከባቢ ነዋሪዎች እና " ልጆቻችን ያለ አግባብ ታስረዋል " የሚሉት ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
በአከባቢዉ ማህበረሰብ በተደጋጋሚ ሲጠየቅ የቆየዉን የፍሰሃ ገነት የወረዳ መዋቅርነት ጥያቄ " በማህበራዊ ሚዲያዎች አሰራጭታችኋል " በሚል ወጣቶችን እያሰሱ እያሰሩ ነው ሲሉ ነው ቃላቸውን የሰጡት።
" ስድስት ወጣቶች ያለ ፍ/ቤት ትዕዛዝ ታስረዋል " የሚሉት ነዋሪዎቹ የፍሰሃ ገነት ወረዳ በቀደመዉ ጊዜ የወረዳ መዋቅር የነበረዉ መሆኑንና የመዋቅር ጥያቄዉ የሕብረተሰቡ በመሆኑ እነዚህም ወጣቶች ይህንኑ ሃሳባቸዉን በማህበራዊ ሚዲያ በማሰራጨታቸው ብቻ ከስራና የትምህርት ገበታቸው እየታሰሱ መታሰራቸውንና ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸዉ መደረጉን ገልጸዋል።
" ፖሊስ ልጆቻችንን እንዳናገኝ ከማድረጉም በላይ ' በተባባሪነት አስራችኋለዉ ' እያለ እያስፈራራን ነዉ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የተናገሩት የአከባቢው ወጣቶች " እኛም እየተፈለግን በመሆኑ አከባቢያችንን ለቀን ሸሽተናል " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጌዴኦ ዞንና የኮቾሬ ወረዳ ፖሊስ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገው የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ፈቃደኛ ባለመሆናቸዉ የኮቾሬ ወረዳ አዛዥ ደግሞ ስልካቸዉ ባለመስራቱ ለጊዜው አልተሳካም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ኮቾሬ ወረዳ ፍሰሃ ገነት ተብሎ የሚጠራዉ አከባቢ ነዋሪዎች እና " ልጆቻችን ያለ አግባብ ታስረዋል " የሚሉት ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
በአከባቢዉ ማህበረሰብ በተደጋጋሚ ሲጠየቅ የቆየዉን የፍሰሃ ገነት የወረዳ መዋቅርነት ጥያቄ " በማህበራዊ ሚዲያዎች አሰራጭታችኋል " በሚል ወጣቶችን እያሰሱ እያሰሩ ነው ሲሉ ነው ቃላቸውን የሰጡት።
" ስድስት ወጣቶች ያለ ፍ/ቤት ትዕዛዝ ታስረዋል " የሚሉት ነዋሪዎቹ የፍሰሃ ገነት ወረዳ በቀደመዉ ጊዜ የወረዳ መዋቅር የነበረዉ መሆኑንና የመዋቅር ጥያቄዉ የሕብረተሰቡ በመሆኑ እነዚህም ወጣቶች ይህንኑ ሃሳባቸዉን በማህበራዊ ሚዲያ በማሰራጨታቸው ብቻ ከስራና የትምህርት ገበታቸው እየታሰሱ መታሰራቸውንና ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸዉ መደረጉን ገልጸዋል።
" ፖሊስ ልጆቻችንን እንዳናገኝ ከማድረጉም በላይ ' በተባባሪነት አስራችኋለዉ ' እያለ እያስፈራራን ነዉ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የተናገሩት የአከባቢው ወጣቶች " እኛም እየተፈለግን በመሆኑ አከባቢያችንን ለቀን ሸሽተናል " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጌዴኦ ዞንና የኮቾሬ ወረዳ ፖሊስ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገው የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ፈቃደኛ ባለመሆናቸዉ የኮቾሬ ወረዳ አዛዥ ደግሞ ስልካቸዉ ባለመስራቱ ለጊዜው አልተሳካም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
ከ40 አመት በላይ መምህራንን በማሰልጠን የሚታወቀዉ የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ በመምህርነት በዲግሪና ዲፕሎማ የሚሰለጥኑ ተማሪዎች በወር ለምግብ የሚሰጣቸዉ 760 ብር ለመኖር ስላላስቻላቸዉ ሰዉ ቤት ተቀጥረዉ በቤት ሰራተኝነት ከጫካ ጭራሮ እየለቀሙ የራሳቸውን ምግብ ለማብሰል መገደዳቸውን ገልጸዋል።
ከእነዚህ ተማሪዎች አንዱ በእንጨት ለቀማ ወቅት ሕይወቱ እንዳለፈም ሰልጣኞቹ ተናግረዋል።
በወር የሚከፈላቸው 760 ብር ነው ፤ አንድ እንጀራ ለመግዛት የዋጋውን ውድነት አልቻሉትም ከዚህ ኑሮ ውድነት በመነሳት ወንዶች ኩሽና ተፈቅዶላቸው እንጀራ እየጋገሩ እየኖሩ ናቸው።
ነገ ተማሪዎችን ለማስተማር የሚሰለጥኑ መምህራን የሚማሩትን ሳይሆን የሚበሉትን በማሰብ የማገዶ እንጨት በመልቀም፣ የቀን የጉልበት ሠራተኛ በመሆን፣ እንዲሁም ሊጥ አብኩተው ለምግባቸው የሚሆን እንጀራ በመጋገር ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ ነው የተባለው።
ሰልጣኝ መምህራኑ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ምን አሉ ?
በ760 ብር የምግብ ወርሃዊ ክፍያ የመኖሪያ ቤት ተሰጥቷቸው በኮሌጅ የሚማሩ ተማሪዎች ከትምህርት በኋላ የሚመገቡትን ምግብ ለማብሰል በደሴ ወደሚገኙት የጦሳ፣ አዘዋና ሌሎች እንጨት ለመልቀም ወደሚያስችላቸው ጫካዎች ሲያመሩ ከሞት ጋርም ተጋፍጠዋል፡፡
ለመማር በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ በጦሳ ተራራ እንደዚሁም በአዘዋ ተራራ ካለቀምን በስተቀር እንጨት አይገኝም ብለዋል።
በዚህም አንድ ሳሙኤል የተባለ የእንግሊዝኛ ክፍል የዲግሪ ተማሪ በጦሳ ተራራ እንጨት ሊለቅም ሄዶ ህዳር 28 ቀን ህይወቱ አልፏል፡፡
ችግሩ በተለይ ሴቶች ላይ የጎላ ነው የምትለው ሠልጣኝ ተማሪ የግማሽ ቀን የቤት ሰራተኝነትና በሌሎች ስራዎች እራሳችን እየደጎምን ነው ትምህርት የምንማረው ብላለች፡፡
" የኑሮ ሁኔታ በጣም ከባድ ነው የሚከፈለን ብር 760 ነው፡፡ ባለን አቅም እየሰራንም ነው የምንማረው በትምህርታችን ላይ ውጭ ውለን ስንገባ እየደከመን ማጥናት እንቸገራለን እንጨት ለቅመን ነው የምንማረው ወንዶችም እንጨት እየለቀሙ እየጋገሩ ይማራሉ " ስትል ተናግራለች።
" አሁን አሁንማ ሥራም ጠፍቷል ፤
አሁን የቀን ስራ ሰርተን ለመማር የማንችልበት ጊዜ ላይ እንገኛለን " የሚለው ተማሪ " ወቅታዊ ሁኔታው ተጨማሪ ስራ ሰርተን ለመማር አላስቻለንም " ብሏል።
" ሴቶች የግማሽ ቀን ስራ ካገኙ ይሰራሉ ወንዶች ቅዳሜና እሁድ ይሰራሉ። ዘንድሮ ግን የለም፤ መስራት አትችልም የተግባር ልምምድ ስለምንሄድ ትንሽ ከበድ ይላል። ባለፈው አመት ይሻላል ውጭ ላይም ትንሽ አስፈሪ ነው ሰዓቱ " ሲል ገልጿል።
በትምህርቱ ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ ነው መባሉን
የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ መምህር የሆኑት መምህር አበበ ደሴ እንደሚገልፁት ተማሪዎች የዕለት ኑሯቸውን በማሰብ ስለሚጠመዱ ትምህርት የመቀበል አቅማቸው ውስን ሆኗል ብለዋል፡፡
" ግማሾች የቀን ስራ ሰርተው ነው የሚኖሩት። ሴቶችም ቢሆኑ በእንጀራ ጋጋሪና ካፍቴሪያ ውስጥ ተቀጥረው እየሰሩ ነው። ክፍል ውስጥም ገብተው ስታይ በአብዛኛዉ ከሚማሩበት የሚያንቀላፉበት ነው የሚበልጠው። ወጥተው የሚመገቡት የለም " ሲሉ አስረድተዋል።
የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ሀሰን ወርቁ በበኩላቸው ተማሪዎቹ ያሉበት ችግር ለመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል።
ወርሃዊ የምግብ ክፍያቸውም ከ760 ብር ከፍ እንዲል ለክልሉ ትምህርት ቢሮ/ጥያቄ መቅረቡን አመልክተዋል።
" በአብዛኛው ከመማር ማስተማሩ ይልቅ ስለ እሚበሉት ፣የሚጠጡት ነው የሚያስቡት በትምህርት ላይ ተፅዕኖ አለው። ይህንን ታሳቢ አድርገን ክልል ላይም ጥያቄ እያቀረብን ነው፡፡ " ብለዋል።
Credit - ዶቼ ቨለ ሬድዮ
@tikvahethiopia
ከ40 አመት በላይ መምህራንን በማሰልጠን የሚታወቀዉ የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ በመምህርነት በዲግሪና ዲፕሎማ የሚሰለጥኑ ተማሪዎች በወር ለምግብ የሚሰጣቸዉ 760 ብር ለመኖር ስላላስቻላቸዉ ሰዉ ቤት ተቀጥረዉ በቤት ሰራተኝነት ከጫካ ጭራሮ እየለቀሙ የራሳቸውን ምግብ ለማብሰል መገደዳቸውን ገልጸዋል።
ከእነዚህ ተማሪዎች አንዱ በእንጨት ለቀማ ወቅት ሕይወቱ እንዳለፈም ሰልጣኞቹ ተናግረዋል።
በወር የሚከፈላቸው 760 ብር ነው ፤ አንድ እንጀራ ለመግዛት የዋጋውን ውድነት አልቻሉትም ከዚህ ኑሮ ውድነት በመነሳት ወንዶች ኩሽና ተፈቅዶላቸው እንጀራ እየጋገሩ እየኖሩ ናቸው።
ነገ ተማሪዎችን ለማስተማር የሚሰለጥኑ መምህራን የሚማሩትን ሳይሆን የሚበሉትን በማሰብ የማገዶ እንጨት በመልቀም፣ የቀን የጉልበት ሠራተኛ በመሆን፣ እንዲሁም ሊጥ አብኩተው ለምግባቸው የሚሆን እንጀራ በመጋገር ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ ነው የተባለው።
ሰልጣኝ መምህራኑ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ምን አሉ ?
በ760 ብር የምግብ ወርሃዊ ክፍያ የመኖሪያ ቤት ተሰጥቷቸው በኮሌጅ የሚማሩ ተማሪዎች ከትምህርት በኋላ የሚመገቡትን ምግብ ለማብሰል በደሴ ወደሚገኙት የጦሳ፣ አዘዋና ሌሎች እንጨት ለመልቀም ወደሚያስችላቸው ጫካዎች ሲያመሩ ከሞት ጋርም ተጋፍጠዋል፡፡
ለመማር በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ በጦሳ ተራራ እንደዚሁም በአዘዋ ተራራ ካለቀምን በስተቀር እንጨት አይገኝም ብለዋል።
በዚህም አንድ ሳሙኤል የተባለ የእንግሊዝኛ ክፍል የዲግሪ ተማሪ በጦሳ ተራራ እንጨት ሊለቅም ሄዶ ህዳር 28 ቀን ህይወቱ አልፏል፡፡
ችግሩ በተለይ ሴቶች ላይ የጎላ ነው የምትለው ሠልጣኝ ተማሪ የግማሽ ቀን የቤት ሰራተኝነትና በሌሎች ስራዎች እራሳችን እየደጎምን ነው ትምህርት የምንማረው ብላለች፡፡
" የኑሮ ሁኔታ በጣም ከባድ ነው የሚከፈለን ብር 760 ነው፡፡ ባለን አቅም እየሰራንም ነው የምንማረው በትምህርታችን ላይ ውጭ ውለን ስንገባ እየደከመን ማጥናት እንቸገራለን እንጨት ለቅመን ነው የምንማረው ወንዶችም እንጨት እየለቀሙ እየጋገሩ ይማራሉ " ስትል ተናግራለች።
" አሁን አሁንማ ሥራም ጠፍቷል ፤
አሁን የቀን ስራ ሰርተን ለመማር የማንችልበት ጊዜ ላይ እንገኛለን " የሚለው ተማሪ " ወቅታዊ ሁኔታው ተጨማሪ ስራ ሰርተን ለመማር አላስቻለንም " ብሏል።
" ሴቶች የግማሽ ቀን ስራ ካገኙ ይሰራሉ ወንዶች ቅዳሜና እሁድ ይሰራሉ። ዘንድሮ ግን የለም፤ መስራት አትችልም የተግባር ልምምድ ስለምንሄድ ትንሽ ከበድ ይላል። ባለፈው አመት ይሻላል ውጭ ላይም ትንሽ አስፈሪ ነው ሰዓቱ " ሲል ገልጿል።
በትምህርቱ ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ ነው መባሉን
የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ መምህር የሆኑት መምህር አበበ ደሴ እንደሚገልፁት ተማሪዎች የዕለት ኑሯቸውን በማሰብ ስለሚጠመዱ ትምህርት የመቀበል አቅማቸው ውስን ሆኗል ብለዋል፡፡
" ግማሾች የቀን ስራ ሰርተው ነው የሚኖሩት። ሴቶችም ቢሆኑ በእንጀራ ጋጋሪና ካፍቴሪያ ውስጥ ተቀጥረው እየሰሩ ነው። ክፍል ውስጥም ገብተው ስታይ በአብዛኛዉ ከሚማሩበት የሚያንቀላፉበት ነው የሚበልጠው። ወጥተው የሚመገቡት የለም " ሲሉ አስረድተዋል።
የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ሀሰን ወርቁ በበኩላቸው ተማሪዎቹ ያሉበት ችግር ለመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል።
ወርሃዊ የምግብ ክፍያቸውም ከ760 ብር ከፍ እንዲል ለክልሉ ትምህርት ቢሮ/ጥያቄ መቅረቡን አመልክተዋል።
" በአብዛኛው ከመማር ማስተማሩ ይልቅ ስለ እሚበሉት ፣የሚጠጡት ነው የሚያስቡት በትምህርት ላይ ተፅዕኖ አለው። ይህንን ታሳቢ አድርገን ክልል ላይም ጥያቄ እያቀረብን ነው፡፡ " ብለዋል።
Credit - ዶቼ ቨለ ሬድዮ
@tikvahethiopia
የትግራይ ኃይል አባላት ለአምስተኛ ቀን ያካሄዱት የመኪና መንገድ መዝጋት ያካተተ ሰልፍ ተከትሎ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰራዊት አባላት ተጠቃሚ የሚያረጋግጥ ደንብ ማጸደቁ አስታውቋል።
እሁድ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም የጀመረው የትግራይ ኃይል ሰልፍና ተቃውሞ ዛሬ ቀጥሎ ከእንዳስላሰ-ሽረ ፣ አክሱም ፣ ዓድዋና ተምቤንና ሌሎች አከባቢዎች ወደ መቐለ የሚያስገባ መንገድ ተዘግቶ ውሏል።
ይህንን ተከትሎ ዛሬ ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም ከሰዓት በኃላ የፅሁፍ መግለጫ ያወጣው የጊዚያዊ እስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ካቢኔ ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ያወጣው የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ረቂቅ ደንብ ዛሬ ማፅደቁን አመልክተዋል።
ካቢኔው በዛሬው አስቸኳይ ስብሰባው የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ደንብ በዝርዝር ተወያይቶ ተግባራዊ እንዲሆን በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል።
የፀደቀው ደንብ ፦
- መሰረታዊ ፍላጎቶች
- የህክምና አገልግሎት
- የቤት መስሪያ መሬት
- በመንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የሚሰጥ የክብር አገልግሎት
- ትምህርት ስልጠናና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ያካተተ ነው ብሏል ከፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የተሰጠው የፅሁፍ መግለጫ።
" የፀደቀው የትግራይ ፀጥታ ኃይሎች ተጠቃሚነት ደንብ ለረጅም ጊዜ ጥናት የተደረገበት ከፀጥታ አመራሮች ውይይት ሲካሄድበት የቆየ ነው " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ ኃይል አባላት ለአምስተኛ ቀን ያካሄዱት የመኪና መንገድ መዝጋት ያካተተ ሰልፍ ተከትሎ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰራዊት አባላት ተጠቃሚ የሚያረጋግጥ ደንብ ማጸደቁ አስታውቋል።
እሁድ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም የጀመረው የትግራይ ኃይል ሰልፍና ተቃውሞ ዛሬ ቀጥሎ ከእንዳስላሰ-ሽረ ፣ አክሱም ፣ ዓድዋና ተምቤንና ሌሎች አከባቢዎች ወደ መቐለ የሚያስገባ መንገድ ተዘግቶ ውሏል።
ይህንን ተከትሎ ዛሬ ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም ከሰዓት በኃላ የፅሁፍ መግለጫ ያወጣው የጊዚያዊ እስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ካቢኔ ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ያወጣው የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ረቂቅ ደንብ ዛሬ ማፅደቁን አመልክተዋል።
ካቢኔው በዛሬው አስቸኳይ ስብሰባው የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ደንብ በዝርዝር ተወያይቶ ተግባራዊ እንዲሆን በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል።
የፀደቀው ደንብ ፦
- መሰረታዊ ፍላጎቶች
- የህክምና አገልግሎት
- የቤት መስሪያ መሬት
- በመንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የሚሰጥ የክብር አገልግሎት
- ትምህርት ስልጠናና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ያካተተ ነው ብሏል ከፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት የተሰጠው የፅሁፍ መግለጫ።
" የፀደቀው የትግራይ ፀጥታ ኃይሎች ተጠቃሚነት ደንብ ለረጅም ጊዜ ጥናት የተደረገበት ከፀጥታ አመራሮች ውይይት ሲካሄድበት የቆየ ነው " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፈኞች ዛሬም ለአምስተኛ ቀን የመኪና መንገድ ዘግተው ውለዋል።
ትናንት ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም ወደ ዓዳግራት ከተማ የሚያስገቡና የሚያስወጡ በሶስት አቅጣጫ የተዘጉ መንገዶ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ተከፍተዋል።
ዛሬ ከእንዳስላሰ-ሽረ ፣ አክሱም ፣ ዓድዋ ፣ ተምቤንና ሌሎች አከባቢዎች ወደ መቐለ የሚያስገቡ ዋና የመኪና መንገድ በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሃገረ ሰላም ከተማ ነው የተዘጋው።
ከጥዋቱ 1:00 መንገዱ የዘጉ የትግራይ ኃይል አባላት ፦
- " የተሰውት ቤተሰብ አባላት ይደገፉ ! "
- " የቆሰሉት ይታከሙ ! "
- " የሰራዊት ድምፅ ይሰማ ! "
- " የሰራዊር መብት የማያከብር መሪ ይውረድ ! "
- " መሪ ፍረድ ወይ ውረድ ! "
- " የደመወዝ ጥያቄያችን ይመለስ ! "
- " የቤት መስሪያ መሬት ይሰጠን ! "
የሚሉና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።
እሁድ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም የጀመረው የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍና ተቃውሞ ያዳመጠው የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰራዊቱ ጥያቄ ለመመለስ ያስችላል ያለው መመሪያ አውጥቻሎህ ማለቱ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፈኞች ዛሬም ለአምስተኛ ቀን የመኪና መንገድ ዘግተው ውለዋል።
ትናንት ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም ወደ ዓዳግራት ከተማ የሚያስገቡና የሚያስወጡ በሶስት አቅጣጫ የተዘጉ መንገዶ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ተከፍተዋል።
ዛሬ ከእንዳስላሰ-ሽረ ፣ አክሱም ፣ ዓድዋ ፣ ተምቤንና ሌሎች አከባቢዎች ወደ መቐለ የሚያስገቡ ዋና የመኪና መንገድ በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሃገረ ሰላም ከተማ ነው የተዘጋው።
ከጥዋቱ 1:00 መንገዱ የዘጉ የትግራይ ኃይል አባላት ፦
- " የተሰውት ቤተሰብ አባላት ይደገፉ ! "
- " የቆሰሉት ይታከሙ ! "
- " የሰራዊት ድምፅ ይሰማ ! "
- " የሰራዊር መብት የማያከብር መሪ ይውረድ ! "
- " መሪ ፍረድ ወይ ውረድ ! "
- " የደመወዝ ጥያቄያችን ይመለስ ! "
- " የቤት መስሪያ መሬት ይሰጠን ! "
የሚሉና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።
እሁድ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም የጀመረው የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍና ተቃውሞ ያዳመጠው የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰራዊቱ ጥያቄ ለመመለስ ያስችላል ያለው መመሪያ አውጥቻሎህ ማለቱ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚችሉ ተማሪዎች በግልም ሆነ በመንግሥት ተቋማት እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች እንደሆኑ መግለፁ ይታወቃል፡፡
ሚኒስቴሩ የ2018 ትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ መቁረጫ ነጥብን በተመለከተ በቀን 06/02/2018 ዓ.ም ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማብራሪያ ልኳል፡፡
“ 33 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች የሚለው ወደ ቁጥር ሲገለፅ ልዩነት መኖሩ፤ የፐርሰንቱ እና የቁጥሩ አገላለጽ በደንብ clear ለማድረግ“ ማብራራያው ማስፈለጉን የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ማኅበር ሥራ አስኪያጅ ተፈራ ገበየሁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ @tikvahuniversity ተናግረዋል፡፡
የ2018 ትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም መቁረጫ ነጥብ በመንግሥትም ሆነ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ልዩነት የሌለ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የ2018 ትምህርት ዘመን የመቁረጫ ነጥብ ዝርዝር ፦
➡️ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216 ከ 600
➡️ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204 ከ 600
➡️ ታዳጊ ክልሎች እና የአርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ከ 600
➡️ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ከ 600
➡️ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ዓይነ ስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165 ከ 600
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Via @tikvahuniversity
ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚችሉ ተማሪዎች በግልም ሆነ በመንግሥት ተቋማት እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች እንደሆኑ መግለፁ ይታወቃል፡፡
ሚኒስቴሩ የ2018 ትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ መቁረጫ ነጥብን በተመለከተ በቀን 06/02/2018 ዓ.ም ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማብራሪያ ልኳል፡፡
“ 33 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች የሚለው ወደ ቁጥር ሲገለፅ ልዩነት መኖሩ፤ የፐርሰንቱ እና የቁጥሩ አገላለጽ በደንብ clear ለማድረግ“ ማብራራያው ማስፈለጉን የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ማኅበር ሥራ አስኪያጅ ተፈራ ገበየሁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ @tikvahuniversity ተናግረዋል፡፡
የ2018 ትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም መቁረጫ ነጥብ በመንግሥትም ሆነ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ልዩነት የሌለ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የ2018 ትምህርት ዘመን የመቁረጫ ነጥብ ዝርዝር ፦
➡️ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216 ከ 600
➡️ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204 ከ 600
➡️ ታዳጊ ክልሎች እና የአርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ከ 600
➡️ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ከ 600
➡️ የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ዓይነ ስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165 ከ 600
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
Via @tikvahuniversity
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የሪሚዲያል ፕሮግራም #የማያስተናግዱ ዩኒቨርሲቲዎች ፦
1. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
2. አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
3. አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
4. ሲቪል ሰርቪርስ ዩኒቨርሲቲ
5. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
6. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
7. ኮተቤ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ናቸው።
ተማሪዎች የሞሉትን ምርጫ በ student.ethernet.edu.et በኩል ማረጋገጥ የሚችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
Via @tikvahuniversity
ዛሬ በናይሮቢ ካሲራኒ ለቀድሞዉ የኬንያ ጠቅላይ ሚንስትር ራይላ ኦዲንጋ የአስከሬን ሽኝት መርሃግብር ተካሂዷል።
በዚሁ ወቅት በተነሳ ብጥብጥ የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዐይን እማኞች ናይሮቢ ለሚገኘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ባልደረባ ተናግረዋል።
እንደ ዐይን እማኞቹ ገለፃ ሁለት ሰዎች ከፀጥታ ሃይል በተተኮሰ ጥይት የተገደሉ ሲሆን አምስት ሰዎች ተኩሱን ተከትሎ በነበረ ግርግር ሕይወታቸው ማለፉን ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በስፍራው ተገኘቶ እንደተመለከዉ በስታዲየሙ የራይላ ኦዲንጋ አስክሬን ስንብት እየተካሄደ በነበረበት የተወሰኑ ወጣቶች ከፀጥታ አካላት ጋር በፈጠሩት አለመግባባት ጥይት የተተኮሰ ሲሆን አስለቃሽ ጭስም ተወርውሮ ሕዝቡ ከስታዲየሙ እንዲወጣ ተደርጓል።
የሀገሪቱ ሚዲያዎች የሟቾችን ቁጥር ሁለት ብለዉ የዘገቡ ሲሆን ጉዳት ስለደረሰባቸው ሰዎች እስካሁን ምንም የተባለ ነገር የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ናይሮቢ
#TikvahEthiopiaFamilyNairobi
@tikvahethiopia
ዛሬ በናይሮቢ ካሲራኒ ለቀድሞዉ የኬንያ ጠቅላይ ሚንስትር ራይላ ኦዲንጋ የአስከሬን ሽኝት መርሃግብር ተካሂዷል።
በዚሁ ወቅት በተነሳ ብጥብጥ የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዐይን እማኞች ናይሮቢ ለሚገኘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ባልደረባ ተናግረዋል።
እንደ ዐይን እማኞቹ ገለፃ ሁለት ሰዎች ከፀጥታ ሃይል በተተኮሰ ጥይት የተገደሉ ሲሆን አምስት ሰዎች ተኩሱን ተከትሎ በነበረ ግርግር ሕይወታቸው ማለፉን ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በስፍራው ተገኘቶ እንደተመለከዉ በስታዲየሙ የራይላ ኦዲንጋ አስክሬን ስንብት እየተካሄደ በነበረበት የተወሰኑ ወጣቶች ከፀጥታ አካላት ጋር በፈጠሩት አለመግባባት ጥይት የተተኮሰ ሲሆን አስለቃሽ ጭስም ተወርውሮ ሕዝቡ ከስታዲየሙ እንዲወጣ ተደርጓል።
የሀገሪቱ ሚዲያዎች የሟቾችን ቁጥር ሁለት ብለዉ የዘገቡ ሲሆን ጉዳት ስለደረሰባቸው ሰዎች እስካሁን ምንም የተባለ ነገር የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ናይሮቢ
#TikvahEthiopiaFamilyNairobi
@tikvahethiopia
የሩሲያ መንግስት በማንኛውም የትምህርት መስክ በሩሲያ ትምህርት የመከታተል ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች ስኮላርሺፕ ማመቻቸቱን አሳውቋል።
ስኮላርሺፑ የሩሲያ መንግስት ለ155 የባችለር፣ ማስተርስ እና ፒ ኤች ዲ ተማሪዎች በማንኛውም ፊልድ እንዲማሩ የፈቀደው ነው።
ባለፈው አመት ለ100 ተማሪዎች ተፈቅዶ የነበር ስኮላርሺፕ በዘንድሮ አመት ቁጥሩ ወደ 155 ተማሪዎች ከፍ የተደረገ ሲሆን እንደ አመልካቾች ብዛት የሩሲያ መንግስት ቁጥሩን ከእዚህም ከፍ ሊያደርገው እንደሚችል የሩሲያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
የሩሲያ የሳይንስ እና ባህል ማዕከል ወይም በአዲሱ ስያሜው ሩሲያን ሃውስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፤ የስኮላርሺፑ ሙሉ የትምህርት ክፍያ በሩሲያ መንግሥት የሚሸፈን መሆኑን ገልጾ የጉዞ ትኬት እና የኢንሹራንስ ወጪዎችን ብቻ በአመልካቾች የሚሸፈን ይሆናል ብሏል።
የትምህርት ሂደቱ የቆይታው ጊዜ ለባችለር አራት አመት ለማስተርስ ሁለት አመት እንዲሁም ለ ፒ ኤች ዲ አመልካቾች እንደ ትምህርቱ አይነት የቆይታ ጊዜያቸው የሚወሰን ይሆናል ተብሏል።
ስኮላርሺፑን አሸንፈው የሚሄዱ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ከመጀመራቸው በፊት ለአንድ አመት የቋንቋ ትምህርት የሚማሩ ሲሆን እንደ ሩሲያን ሃውስ መረጃ ስኮላርሺፑ የሙሉ የትምህርቱን እና የቋንቋን አንድ አመት ቆይታ ያካተተ ነው።
ተማሪዎች ካመለከቱ በኋላ ለስኮላርሺፑ ብቁ የሆኑትን የማጣራት ሂደት የመጀመሪያው ዙር በሳይንስ ማዕከሉ ከተከናወነ በኋላ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዙር የማጣራት ሂደቶች በሩሲያ ዩኒቨርሲቲዎች እና በሚመለከታቸው አካላት የሚከናወን ይሆናል።
ለስኮላርሺፑ የማመልከት ሂደት ሴፕቴምበር 15 የተጀመረ ሲሆን እስከ ጃንዋሪ 15 የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።
በሩሲያ የሳይንስ እና ባህል ማዕከል የስኮላርሺፑ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ናድር መሃመድ " የራሺያን ስኮላርሺፕ እንዲሳካ እናደርጋለን እያሉ ብር የሚቀበሉ ኤጀንሲዎች እያየን ነው " ያሉ ሲሆን በስኮላርሺፑ ዙሪያ ህጋዊ ሰውነት ያለው እና የሚያስተባብረው የሩሲያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል ብቻ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አተባባሪው አመልካቾች ለማማከር እና ለተጨማሪ መረጃ ከሰኞ እስከ አርብ በስራ ሰአት ወደ ማዕከሉ በመደወል መረጃ በነጻ ማግኘት እንደሚችሉ ገልጸዋል።
ለስኮላርሺፑ ለማመልከት መሟላት ያለባቸው ነገሮች ምንድን ናቸው ?
ፓስፖርት አስፈላጊ ቢሆንም ስኮላርሺፑን ለማመልከት አስገዳጅ አይደለም።
በቀበሌ ወይም በፋይዳ መታወቂያ ማመልከት ይቻላል።
የአመልካቾች የ9 ፣ 10 ፣ 11 እና 12 የትምህርት ማስረጃቸው እንዲያስገቡ ይጠየቃል።
አሁን 12 ክፍል እየተማሩ ያሉ አመልካቾች እስካመለከቱበት ጊዜ ያለውን የትምህርት ማስረጃ አስገብተው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት ደግሞ ሲደርስ መስገባት ይችላሉ።
ለማስተርስ አመልካቾች ዲግሪ እና ግሬድ ሪፖርት አስፈላጊ ነው (ዲግሪው ያልደረሰለት ቴምፖራሪውን ማስገባት ይችላል)።
ለፒ ኤች ዲ አመልካቾች የሪሰርች ፕላናቸው ምን እንደሆነ ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን አስገዳጅ ባይሆንም ፕብሊሽ የተደረገ የጥናታዊ ጽሁፍ ቢኖራቸው ይመከራል።
ባለፈው አመት ስኮላርሺፑ የተሰጠው 50 በመቶ ለባችለር ዲግሪ ፣ 30 በመቶ ለማስተርስ ዲግሪ እና 20 በመቶ ለፒኤች ዲ ዲግሪ ቢሆንም ይህኛው ስኮላርሺፕ እንደ አመልካቹ ቁጥር ብዛት ፐርሰንቱን ሊሸጋሸግ ይችላል።
ጥሩ ውጤት ያላቸው ተማሪዎች የመመረጥ እድላቸው ሰፊ ነው በመሆኑ ቢያመለክቱ ይመረጣል።
ጥሩ ውጤት የሌላቸው ተማሪዎች የስኮላርሺፑ የውድድር ሂደት የተማሪዎችን የትምህርት መረጃ በማስተያየት የሚከናወን በመሆኑ በአንዳንድ ትምህርቶች ጥሩ ውጤት ካላቸው ተማሪዎች የተሻሉ ሆነው ቢገኙ ባላንስ ስለሚያደርግ ማመልከት ይችላሉ።
ስኮላርሺፑን https://www.education-in-russia.com ሊንክ በመጠቀም ቋንቋውን ወደ እንግሊዝኛ በመቀየር ማመልከት ይቻላል።
ለተጨማሪ መረጃ ወደ ሩሲያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል በEmail - [email protected]
ወይም [email protected]
እንዲሁም በስልክ ቁጥር 251 11 155 1343 ማግኘት ይቻላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የሩሲያ መንግስት በማንኛውም የትምህርት መስክ በሩሲያ ትምህርት የመከታተል ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች ስኮላርሺፕ ማመቻቸቱን አሳውቋል።
ስኮላርሺፑ የሩሲያ መንግስት ለ155 የባችለር፣ ማስተርስ እና ፒ ኤች ዲ ተማሪዎች በማንኛውም ፊልድ እንዲማሩ የፈቀደው ነው።
ባለፈው አመት ለ100 ተማሪዎች ተፈቅዶ የነበር ስኮላርሺፕ በዘንድሮ አመት ቁጥሩ ወደ 155 ተማሪዎች ከፍ የተደረገ ሲሆን እንደ አመልካቾች ብዛት የሩሲያ መንግስት ቁጥሩን ከእዚህም ከፍ ሊያደርገው እንደሚችል የሩሲያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
የሩሲያ የሳይንስ እና ባህል ማዕከል ወይም በአዲሱ ስያሜው ሩሲያን ሃውስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፤ የስኮላርሺፑ ሙሉ የትምህርት ክፍያ በሩሲያ መንግሥት የሚሸፈን መሆኑን ገልጾ የጉዞ ትኬት እና የኢንሹራንስ ወጪዎችን ብቻ በአመልካቾች የሚሸፈን ይሆናል ብሏል።
የትምህርት ሂደቱ የቆይታው ጊዜ ለባችለር አራት አመት ለማስተርስ ሁለት አመት እንዲሁም ለ ፒ ኤች ዲ አመልካቾች እንደ ትምህርቱ አይነት የቆይታ ጊዜያቸው የሚወሰን ይሆናል ተብሏል።
ስኮላርሺፑን አሸንፈው የሚሄዱ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ከመጀመራቸው በፊት ለአንድ አመት የቋንቋ ትምህርት የሚማሩ ሲሆን እንደ ሩሲያን ሃውስ መረጃ ስኮላርሺፑ የሙሉ የትምህርቱን እና የቋንቋን አንድ አመት ቆይታ ያካተተ ነው።
ተማሪዎች ካመለከቱ በኋላ ለስኮላርሺፑ ብቁ የሆኑትን የማጣራት ሂደት የመጀመሪያው ዙር በሳይንስ ማዕከሉ ከተከናወነ በኋላ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዙር የማጣራት ሂደቶች በሩሲያ ዩኒቨርሲቲዎች እና በሚመለከታቸው አካላት የሚከናወን ይሆናል።
ለስኮላርሺፑ የማመልከት ሂደት ሴፕቴምበር 15 የተጀመረ ሲሆን እስከ ጃንዋሪ 15 የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።
በሩሲያ የሳይንስ እና ባህል ማዕከል የስኮላርሺፑ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ናድር መሃመድ " የራሺያን ስኮላርሺፕ እንዲሳካ እናደርጋለን እያሉ ብር የሚቀበሉ ኤጀንሲዎች እያየን ነው " ያሉ ሲሆን በስኮላርሺፑ ዙሪያ ህጋዊ ሰውነት ያለው እና የሚያስተባብረው የሩሲያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል ብቻ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አተባባሪው አመልካቾች ለማማከር እና ለተጨማሪ መረጃ ከሰኞ እስከ አርብ በስራ ሰአት ወደ ማዕከሉ በመደወል መረጃ በነጻ ማግኘት እንደሚችሉ ገልጸዋል።
ለስኮላርሺፑ ለማመልከት መሟላት ያለባቸው ነገሮች ምንድን ናቸው ?
ፓስፖርት አስፈላጊ ቢሆንም ስኮላርሺፑን ለማመልከት አስገዳጅ አይደለም።
በቀበሌ ወይም በፋይዳ መታወቂያ ማመልከት ይቻላል።
የአመልካቾች የ9 ፣ 10 ፣ 11 እና 12 የትምህርት ማስረጃቸው እንዲያስገቡ ይጠየቃል።
አሁን 12 ክፍል እየተማሩ ያሉ አመልካቾች እስካመለከቱበት ጊዜ ያለውን የትምህርት ማስረጃ አስገብተው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት ደግሞ ሲደርስ መስገባት ይችላሉ።
ለማስተርስ አመልካቾች ዲግሪ እና ግሬድ ሪፖርት አስፈላጊ ነው (ዲግሪው ያልደረሰለት ቴምፖራሪውን ማስገባት ይችላል)።
ለፒ ኤች ዲ አመልካቾች የሪሰርች ፕላናቸው ምን እንደሆነ ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን አስገዳጅ ባይሆንም ፕብሊሽ የተደረገ የጥናታዊ ጽሁፍ ቢኖራቸው ይመከራል።
ባለፈው አመት ስኮላርሺፑ የተሰጠው 50 በመቶ ለባችለር ዲግሪ ፣ 30 በመቶ ለማስተርስ ዲግሪ እና 20 በመቶ ለፒኤች ዲ ዲግሪ ቢሆንም ይህኛው ስኮላርሺፕ እንደ አመልካቹ ቁጥር ብዛት ፐርሰንቱን ሊሸጋሸግ ይችላል።
ጥሩ ውጤት ያላቸው ተማሪዎች የመመረጥ እድላቸው ሰፊ ነው በመሆኑ ቢያመለክቱ ይመረጣል።
ጥሩ ውጤት የሌላቸው ተማሪዎች የስኮላርሺፑ የውድድር ሂደት የተማሪዎችን የትምህርት መረጃ በማስተያየት የሚከናወን በመሆኑ በአንዳንድ ትምህርቶች ጥሩ ውጤት ካላቸው ተማሪዎች የተሻሉ ሆነው ቢገኙ ባላንስ ስለሚያደርግ ማመልከት ይችላሉ።
ስኮላርሺፑን https://www.education-in-russia.com ሊንክ በመጠቀም ቋንቋውን ወደ እንግሊዝኛ በመቀየር ማመልከት ይቻላል።
ለተጨማሪ መረጃ ወደ ሩሲያ ሳይንስ እና ባህል ማዕከል በEmail - [email protected]
ወይም [email protected]
እንዲሁም በስልክ ቁጥር 251 11 155 1343 ማግኘት ይቻላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Reviews channel
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «EBS TV» is a Telegram channel in the category «Новости и СМИ», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 4.7K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 7.2, with 0 reviews and an average score of 0.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.2 ₽, and with 0 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий