
- Main
- Catalog
- Religion & Spirituality
- Ethio🇪🇹Muslim🇪🇹 Nashida - Menzuma 🎼
Ethio🇪🇹Muslim🇪🇹 Nashida - Menzuma 🎼
Uplifting Islamic content, daily reminders, and beautiful nasheeds. A peaceful space for spiritual growth and halal lifestyle promotion. Ideal for faith-based and modest brands.
Channel statistics
👉ገባ ገባ በሉ ባረከላሁ ፊኩም ⤵⤵
♻️ በዚህ ቀን የአላህ መልእክተኛ አምሳ ሦስት ዓመት በትክክል ሞላቸው። ነብይነታቸውም 13 ዓመታት ሞላው።በወርሃ ረቢዓል አወል 9ኛ ቀን ከዝሆኑ ክስተት በ41ኛው ዓመት ነብይ ተደርገዋል በነዚህ ወገኖች ስሌት መሠረት ነብይ የተደረጉት በዚሁ ዓመት ረመዳን ላይ ነው ለሚሉ ወገኖች ደግሞ በዚህ ቀን ነብይነታቸው 12 ዓመት ከ6 ወራት ከ8ወይም ከ2 ቀናት ነው፡፡🔅 ኢብንል ቀይም እንዲህ ብለዋል በበኒ አምር እና በኒ አውፍ ዘንድ ከፍተኛ ድምጽና ተክቢራ ተሰማ፡ በመልእክተኛው ﷺ መምጣት በመደስት ሙስሊሞች ተክቢራ አሰሙ። እንግዶችን ለመቀበልም ወጡ። ለነብያዊ ክብራቸው ተገቢ የሆነ አቀባበልና ሰላምታም አቀረቡላቸው። በአድናቆት እየተመለከቱም ዙሪያውን ከበቧቸው። በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያሉ ነቢዩ ﷺ እርጋታ ስፈነባቸው። እንዲህ የሚል ወሀይም ወረደላቸው፡፡
إِن تَتُوبَا إِلَى اللَّهِ فَقَدْ صَغَتْ قُلُوبُكُمَا ۖ وَإِن تَظَاهَرَا عَلَيْهِ فَإِنَّ اللَّهَ هُوَ مَوْلَاهُ وَجِبْرِيلُ وَصَالِحُ الْمُؤْمِنِينَ ۖ وَالْمَلَائِكَةُ بَعْدَ ذَٰلِكَ ظَهِيرٌ ወደ አላህ ብትመለሱ ልቦቻችሁ በእርግጥ ተዘንብለዋልና (ትስማማላችሁ)፡፡ በእርሱም ላይ ብትረዳዱ አላህ እርሱ ረዳቱ ነው፡፡ ጂብሪልም ከምእምናንም መልካሙ ከዚህም በኋላ መላእክቱ ረዳቶቹ ናቸው፡፡(ተህሪም 04)🕗 ኡርወት ቢን ዙበይር እንዲህ ሲል አውግቷል፤ የመዲና ነዋሪዎች ነቢዩን በደመቀ ሁኔታ ተቀበሏቸው። እርሳቸውም ወደ ቀኝ አቅጣጫ ሄደው ከበኒ አምር ቢን አውፍ ዘንድ ሰፈሩ። ይህም የሆነው በወርሃ ረቢአል አወል ሰኞ ቀን ነው" አቡበክር ቆሙ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ግን ዝም ብለው ተቀመጡ። የአላህን መልእክተኛ ﷺ አንሷሮች ከአቡበክር ዘንድ እየመጡ ሰላምታ አቀረቡ፡፡ ጸሐይዋ ከመልእክተኛው ላይ ስታርፍና ስታቃጥላቸው አቡበክር ለነቢዩ በኩታቸው ጥላ ሲያደርጉላቸው ሰዎች ሲመለከቱ የአላህ መልእክተኛ " እርሳቸው መሆናቸውን አወቁ የመዲና ነዋሪዎች መልእክተኛውን ለመቀበል ከየቤታቸው በገፍ ወጥተዋል። እጅግ ታሪካዊ ቀን ነበር። መዲና በታሪክ ውስጥ እንደዚህ አይነት ድንቅ ቀን አይታ አታውቅም። አይሁዶች የሚከተለው የእንባቆም ትንቢት በእውን ሲፈጸም ተመለከቱ፤
እግዚአብሔር ከቴማን፤ ቅዱሱም ከፋራን ተራራ ይመጣል»🔹 የአላህ መልእክተኛ ﷺ ቁባእ ላይ ከኩልሱም ቢን ሐዳም ዘንድ አረፉ" በሌላ ዘገባ ከሰእድ ቢን ኸይሰም ዘንድ ማረፋቸው ተዘግቧል" የመጀመሪያው ይበልጥ አስተማማኝ ነው። 🔅 ዓሊ ቢን አቢ ጧሊብ መካ ውስጥ የአላህ መልእክተኛ " በአደራ ያስቀመጡትን ንብረት ለባለቤቶቹ ሲመልሱ፤ ሦስት ቀናት አሳለፉ። ከዚያም በእግራቸው በመጓዝ ቁባ ላይ አገኙዋቸው" ከኩልሱም ቢን ሐዳም ዘንድም አረፉ።" የአላህ መልእክተኛ በቁባ ለአራት ቀናት ቆዩ።ሰኞ፣ ማክሰኞ፣ ረቡእና ሐሙስ፡ በዚህ ቆይታቸው የቁባእን መስጊድ መሠረቱ" ከውስጡም ሰገዱ" ይህም ከነብይነታቸው በኋላ በ«ተቅዋ» መሠረት ላይ የታነጸ የመጀመሪያው መስጅድ ነው። ♨️ በአምስተኛው ቀን ጁሙዓ በአላህ ትእዛዝ ወደ መዲና ጋለቡ" አቡበክር ተጎዳኟቸው። ወደ አጎታቸው ወደ በኒ ነጃር መልእክት ላኩ። እነርሱም ሰይፎቻቸውን ታጥቀው መጡ። ነቢዩን አጅበው ወደ መዲና አቅጠጫ ተጓዙ። ከበኒ ሰሊም ቢን አውፍ ቀዬ ሲደርሱ የጁሙዓ ሰላት ደረሰ። ከሸለቆው መሐል ሰበሰቧቸው እና ሶላቱን ፈጸሙ። ሁሉም ወንዶች ሲሆኑ፣ ቁጥራቸው መቶ ነበር። 🔹 ወደ መዲና መግባት ♻️ ከጁሙዓ በኋላ መዲና ገቡ። ከዚያች እለት ጀምሮ የስሪብ መዲና»(የመልእክተኛው ﷺፐከተማ) በመባል ትታወቃለች። ይሀ እለት እጅግ ታሪካዊ ነበር። እያንዳንዱ ጎጆና የከተማዋ መንገዶች ሁሉ በምስጋናና በውዳሴ ተሞሉ። የአንሷር እንስቶች የሚከተለውን ግጥም እያዜሙ ደስታቸውን ገለጹ፡
እልል እሰየው ጨረቃ ወጣልን ከሰንየቱል ወዳእ» አበራ ደመቀልን ምስጋና ይግባው ለርሱ የበዛ በያይነቱ ቅን ጎዳና ሊመራን ከሩቅ ቀዬ በመምጣቱ የነብያት አይነታ የተነሳህ ከኛው መሐል ይዘህልን መጥተሐል ጉልህ እውነት ማይታበል ሊታዘዙት የሚገባ፤ አመጽን ማይቀበል♨️ አንሷሮች ይህን ያህል የሚጠቀስ ሐብት ባይኖራቸውም የአላህን መልእክተኛ ﷺ ለማስተናገድ ሁሉም ይመኙ ነበር። ነቢዩ በቤታቸው አጠገብ ባለፉ ቁጥር የግመላቸውን ልጓም ይይዙና እዚህ ይግቡ" በቂ ትጥቅ፣ የስው ሐይልና ጥበቱ አለ።» ይላሉ። መልእክተኛውም፡ «ተዋት፣ ታዛዥ ናት» ይላሉ። ግመሏ ስትጓዝ ቆይታ አሁን የነቢዩ መስጂድ ካረፈበት ቦታ ላይ ስትደርስ ተንበረከከች" አልወረዱም። ጥቂት ቆይታ ተነሳች። ትንሽ ተጓዘች። ዞራ በመመለስም መጀመሪያ ከተንበረከከችበት ተንበረከከች። እርሳቸውም ወረዱ። ይህ ቦታ ከበኒ ነጃር ማለትም ከአጎቶቻቸው ቀዬ ውስጥ ነው። ይህ የአላህ ማመላከት ነው። እርሳቸውም ከአጎቶቻቸው ዘንድ ቢያርፋ ይወዱ ነበር። ሰዎች የአላህን መልእክተኛ ﷺ ለማስተናገድ ተሽቀዳደሙ። አቡ አዩብ, አንሷሪ ፈጥኖ ጓዛቸውን በመያዝ ወደቤቱ አስገባው" እርሳቸውም «ሰውየው ከጓዙ ጋር መሆን አለበት» አሉ፡፡ አስዓድ ቢን ዙራራህ : የግመላቸውን ልጓም ቀድሞ ጨበጠ፡፡ 🕗 ቡኻሪ አነስን በመጥቀስ እንደዘገቡት የአላህ መልእክተኛ ፡ ﷺ የማንኛችሁ ቤት ቀረብ ይላል?» ሲሉ ጠየቁ። አቡ አዩብም የኔ ይቀርባል። ቤቴ ይህ ነው። በሩም ይኸውና።» በማለት ፈጥኖ ወደቤቱ ገባ። ማረፊያም አዘጋጀልን። «በአላህ : በረከት ተነሱ አለንም ። ♻️ ከቀናት በኋላ ባለቤታቸው ሰውዳእ፣ ልጆቻቸው ፋጡማና ኡምኩልሱም፣ እንደዚሁም ኡሳማ ቢን ዘይድና ኡም አይመን ደረሱ። አብደላህ ቢን አቡበክር የአቡበክርን ቤተሰቦች አኢሻን ጨምሮ በመያዝ አብሯቸው ተጓዘ። ዘይነብ ግን ከአበል ዓስ ጋር ቀረች። ለመሰደድ ሁኔታዎች አላመቿትም ነበር። ከበድር ዘመቻ በኋላ ተሰደደች።” ⚜️ የአላህ መልእክተኛ መዲና ሲደርሱ አቡበክር እና ቢላል ታመሙ። ከነርሱ ዘንድ ገባሁና፡ «አባቴ ሆይ፣ እንዴት ነህ?» ስል ጠየቅኳቸው። ለአላህ መልእክተኛም መታመማቸውን ነገርኳቸው። እርሳቸውም፡ «አላህ ሆይ፣ መካን የምንወደውን ያሀል ወይም ከዚያ በላይ መዲናን እንድንወድ አድርገን። ጤና*አድርግልን። ምግቧን ባርክልን። ሕመሟን ወስደህ ከጀሀፋህ (ጉድጓድ) ውስጥ ጣልልን።» በማለት ዱዓ አደረጉ። @Aymen_Muhammed01
<<ISLAMIC>> waveመግባት የምትፈልጉ
ISLAMIC CHANNEL OWNER'Sኑ በነፃ ቻነል እናሳድጋለን ፈጥነው ያስመዝግቡ ለ ተወሰኑ ቻነሎች ብቻ ቦታ አለን
👇የቻናል ባለቤቶች👇
የኡም መእበድን ድንኳን በጸጋ የሞሉ ቤቷን በሰላም አርፈው የሄዱ ወደሚሹት የነጎዱ ምንኛ ተሳካለት ዳነ የመሐመድ ባልንጀራ የሆነ ቁሰይ ትልቅ ክብር አጣ በኒ ከእብ ታደለ አማኞችን በመታደግ የልቅና ማድ ጣለ እህታችሁን ጠይቋት ፍየል እቃዋም ይመስክሩ ሙሐመድ በቀያቸው ምን ታምር እንደሰሩ።♻️ አስማ እንዲህ ብላለች የአላህ መልእክተኛ ወደ የት አቅጣጫ እንዳመሩ አላወቅንም ነበር። አንድ ጋኔን ከመካ በታች በኩል መጥቶ እነዚህን ግጥሞች አነበነበ። ሰዎች ተከተሉት። ድምጹን ይስሙት ነበር። ግን አላዩትም። እየጮኸ በላይኛው በኩል ወጣ። ንግግሩን ስንሰማ የአላህ መልእክተኛ : የሄዱበት አቅጣጫ ወደ መዲና መሆኑን አወቅን። ⓹) ነቢዩ ﷺ መንገድ ላይ አባ በሪደት ቢን ሐቢብ አልአስለሚን ከሰባ አባወራ ጋር አገኙትና ስለመ። አብረውት የነበሩ ሁሉም ስለሙ" የአላህ መልእክተኛ የመጨረሻውን (የጉዞ) ኢሻእ ሲሰግዱ ተከትለዋቸው ስገዱ" በራዳህ ከኡሁድ ዘመቻ በኋላ ወደ አላህ መልእክተኛ እስከመጣበት እለት ድረስ ከወገኖቹ ጋር ቆየ። ⚜️ አብደላህ ቢን በሪዳህ እንዳስተላለፉት ነቢዩ ተስፈኛ ነበሩ። በክፉ ገድ አያምኑም። በሩዳህ ከወገኖቹ ከበኒ ሰሀም የሆኑ ሰባ ጋላቢዎች አስከትሎ ሲሄድ ነቢዩን ፡አገኛቸው። ከየት ነው?» አሉት። «ከአስለም» አላቸው" ለአቡበከር «ሰሊምና» (ሰላም ሆንን) አሉ። ከማን ወገን ነህ?» ሲሉም ጠየቁት። ከበኒ ሰሀም» አላቸው" እጣህ ወጣ» አሉ።" ♨️ በሪዳህ አወጣጡ ነቢዩንና አቡበክርን ይዞ ለቁረይሽ በመስጠት የ200 ግመል ሽልማት ለማግኘት እንደሆነ የታሪክ ጸሐፍት ጽፈዋል። አላህ ግን ለቅን ጎዳና አበቃው። ⓺) መንገድ ላይ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ዙበይርን አገኙ። ከሙስሊሞች ቅፍለት ጋር ነበር። ለንግድ ካደረጉት የሻም ጉዞ እየተመለሱ ነበር።ዙበይር የአላህን መልእክተኛ ﷺ እና አቡበክርን ነጭ ልብስ አለበሳቸው።!!! @Aymen_Muhammed01
🔻የ<<በህሉል >>መሳጭ ታሪክ ክፍል❷ ተለቀቀ✨ 👉ገባ ገባ በሉ ባረከላሁ ፊኩም ⤵⤵
Reviews channel
2 total reviews
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Ethio🇪🇹Muslim🇪🇹 Nashida - Menzuma 🎼 is a Telegram channel in the category «Религия и духовность», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 15.0K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 39.0, with 2 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 1.2 ₽, and with 5 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий