
Monetize Telegram Mini App with Telega.io
Connect your app, set CPM, and watch your revenue grow!
Start monetizing
22.8

Advertising on the Telegram channel «የእምነት ጥበብ»
5.0
Religion & Spirituality
Language:
English
0
0
"የኦርቶዶክስ ክርስትና ጥልቅ ትምህርቶችን እና ጊዜ የማይሽረው እውነቶችን እወቅ።በእምነት ጥበብ በእምነታችን ላይ የተመሰረቱ ትርጉም ያላቸው መልሶችን እናካፍላለን። በመንፈሳዊ ጉዞዎ ላይ እድገትን፣ ግልጽነትን እና የሚያበረታቱ ትርጉም ላለው ንግግሮች እና ግንዛቤዎች ይቀላቀሉ
Share
Add to favorite
Buy advertising in this channel
Placement Format:
keyboard_arrow_down
- 1/24
- 2/48
- 3/72
- Native
- 7 days
- Forwards
1 hour in the top / 24 hours in the feed
Quantity
%keyboard_arrow_down
- 1
- 2
- 3
- 4
- 5
- 8
- 10
- 15
Advertising publication cost
local_activity
$2.40$2.40local_mall
0.0%
Remaining at this price:0
Recent Channel Posts
✨ርእሲ- "ደም እንተይፈሰሰ ስርየት የለን" - ንምንታይ⁉️
❓ሕቶ፦ መፅሐፍ ቅዱስ "ደም እንተይፈሰሰ ስርየት የለን" ይብል። እሞ አዳ ከምዚ እንተኮይኑ ንምንታይ እዩ ደም ምፍሳስ አድልዩ? ፈጣሪ ናይ ደም መስዋዕቲ ይደሊ ድዩ ኮይኑ?
📌መልሲ
እዚ ሕቶ ብክልተ መንገድታት ንመልከቶ⚡️
1. ካብ ክርስቶስ አንፃር✝️
• ፈለማ ምሉእ ናይቲ መፅሐፍ ምዕራፍ ተንተንብቦ መልሱ አብኡ ጳውሎስ ይነግረና። ዕብራውያን 9:10 ከምዚ ይብል
"እዙይ ናይዚ ዘመንዚ ምሳሌ እዩ"ኢሉ ይዛረበና። ጎይታና ኢየሱስ ቅድሚ ምምፅኡ ሰባት ንዕኡ ንክርድእዎን ንክቅበሉዎን ምሳሌ አቀዲሙ ከቅምጥ አድላዪ ነይሩ። ንዕኡ እዩውን ጳውሎስ ናይ ብሉይ ኪዳን ስርዓት ብምጥቃስ ምምሃር ዘድለዮ እምበር እግዚአብሔር ናይ እንስሳት ደም ዝደሊ ኮይኑ እንተይኮነስ ነቲ ክመፅእ ዘለዎ ማለት'ውን ነቲ ንኩሉ ወድሰብ ክብል ደሙ ከፍስስ ዘለዎ አካል ምሳሌ ምእንቲ ክኾኖ እግዚአብሔር ብደም እንስሳት ይቅረ ከም ዝብለሎም ንክስውኡ ኣዘዞም። • አብ ብሉይ ኪዳን ንስርየት ሓጥያት ናይ እንስሳት ደም ይቀርብ ነይሩ። እዚ መስዋዕቲ ድማ ናይ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍፁም መስዋዕቲ የመላኽት። ኢየሱስ "ናይ ዓለም ሓጥያት ዘርሕቅ ናይ እግዚአብሔር በጊዕ" ተባሂሉ ተፀዊዑ እዩ። (ዮሐ 1:29) •እስራኤላውያን ካብ ናይ ግብፂ ባርነት ነፃ ዝወፁሉ ናይ ፋሲካ በዓል አብ ዘብዕልኩ ግዘ እቲ ንመስዋዕቲ ዝቀርብ በጊዕ ናይ ኢየሱስ መስዋዕትነት ዘመልኽት እዩ። ናይቲ በጊዕ ደም አብ ናይ እስራኤላውያን ገዛ ብምቅባእ ሞት ካብኣቶም ንክሓልፍ ከም ዝገበሮ፤ እዚ ደምዚ ናይ ኢየሱስ ምሳሌ እዩ ነይሩ። ናይ ኢየሱስ ደም ካብ ናይ ሓጥያት ሞት ነፃ ይገብር እዩሞ። አብ ኢሳይያስ 53:5
ንሱ ግና ብሰንኪ ሓጢኣትና ቘሰለ፤ ብሰንኪ በደልናውን ደቐቐ፤ ምእንቲ ድሕንነትና፥ መቕፃዕቲ ናብኡ ወረደ፤ ንሕናውን ብቝስሉ ተፈወስና።"ከም ዝብል ጎይታ ኢየሱስ ሰብ ብምኳን ከምኡ'ውን ሞይቱ ንደቂ-ሰባት ደሙ ብምፍሳስ ንደቂ-ሰባት ከድሕን ግድን ነይሩ። •እግዚአብሔር ብዘይ ምፍሳስ ደም ከድሕን ይክእል ነይሩዶ? ዝብል ሰብ እንተልዩ ድማ መልሱ እወ ይክእል ነይሩ ግን ድማ እቲ ጉዳይ ስለ ምኽኣልን ዘይምኽአል አይኮነን። አዳም ብዝሰርሖ ሓጥያት ምኽንያት ሞት ንደቂ-ሰብ ተፈሪድዎ እዩ። እግዚአብሔር ብዘይ ምንም ቅፅዓት ንሰባት እንተ ዘድሕን ነይሩ ናይ አምላክ ፍትሓዊነት ናብ ሕቶ ዘእቱ እዩ ነይሩ። ብዘይም ምፍሳስ ደም ስርየት (ይቅርታ) እንተትርከብ ናይ ሓጥያት ክብደት ብቀሊሉ ዝረአ ነገር እዩ ዝኸውን። •ናይ ደም መስዋዕትነት ናይ ሓጥያት ክፍኣትን ናይ ህይወት ዋጋን የርኢ። ስለዚ ብዘይ ደም ምፍሳስ ስርየት እንተትግበር ናይ ሓጥያት ክፍኣት ምርኣይ ክሰኣነና ነይሩ እዩ። እግዚአብሔር ብዘይ ምንም መስዋዕቲ ንሰባት እንተተድሕን ነይሩ ናቱ ምሕረት ብቀሊሉ ዝረአ ነገር እዩ ዝኸውን። ከምኡ'ውን እግዚአብሔር አቀዲሙ ኣብ ልዕሊ አዳም ናይ ሞት ፍርዲ አውፂኡ እዩ፤ እዚ ፍርዲ ብዘይ ምንም ቅፅዓት እንተ ስዒርዎ ቃሉ ዘፍረሰ ይኸውን። •ብመሰረት መፅሐፍ ቅዱስ ሓጥያት ካብ እግዚአብሔር ይፈልየና ሞት'ን የምፅአልና። •ደም ናይ ህይወት ምልክት እዩ። ስለዚ ናይ ሓጥያት ዋጋ ህይወት እዩ። •እዚ ማለት ድማ ሓጥያት አዝዩ ከቢድ ካብ ምኳኑ ዝተልዓለ መስዋዕቲ ህይወት እዩ ዝሓትት። •እግዚአብሔር ንደቂ-ሰባት ስለ ዝፎቱ ካብ ሓጥያት ባርነት ነፃ ከውፅኦም ደለየ። ነገር ግን እግዚአብሔር ፍትሓዊ አምላኽ ስለ ዝኮነ ንሓጥያት ካሕሳ ክቀርብ ግድን ነበረ። •ኢየሱስ ክርስቶስ ናይ ደቂ-ሰባት ሓጥያት ብምሽካም ናይ እግዚአብሔር ፍቅርን ፍትሕን ብሓደ ግዘ አርእዩ እዩ። •ኢየሱስ ክርስቶስ ሓጥያት ዘይብሉ ፍፁም አምላኽን ሰብን ብምኳኑ ናይ ደቂ-ሰባት ሓጥያት ክሽከም ከኣለ። •ናይ ኢየሱስ ደም ምፍሳስ ሰባት ምስ እግዚአብሔር ንክዕረቁ በሪ ዝኸፈተ እዩ። •ናይ ክርስቶስ መስዋዕቲ ፍፁምን መተካእታ ዘይብሉን እዩ። ካብዚ ዝተልዓለ ድማ "ደም እንተይፈሰሰ ስርየት የለን" የብሃለ። 2. ብአንፃር አንሕና ደቂ-ሰባት👦👩👶 •እግዚአብሔር ናይ እንስሳት ደም አይደልን። ነገር ግን ናይ ልብና ንስሓን ንዕኡ ክንእዘዝን ይደሊ። •አብ ውሽጥና ዘሎ ክፉእ ባህሪ ንክነወግድ መንፈሳዊ ቃልሲ ክንገብር አለና። •"እቲ ናይ መንፈስ ሰይፊ ዝኮነ ቃለ እግዚአብሔር" ብምጥቃም ካብ ሓጥያት ንክንርሕቅ ተፀዊዕና ኢና። •"ደም እንተይፈሰሰ ስርየት የለንሞ" ከም ዝብል ስጋን ደምን ናይ እግዚአብሔር መንግስቲ ክወርሱ ስለ ዘይክእሉ እቲ ናይ እግዚአብሔር ቃል ዝኮነ ናይ መንፈስ ሰይፊ እዩ ዘድልየና። •ከምቲ ነብይ ኤርምያስ ዝተዛረቦ
"ንሰይፉ ድማ ካብ ደም ዝኽልክል ዝተረገመ ይኹን" ኤር 48:10እዚ ሰይፊ ዘወግዶ ናይ ሓጥያት particle ዘለዎ ክፉእ ደም ዘፍስስን አብ ውሽጢ ነፍስና ዝዓበየ ምድራዊን ስጋዊን ክፋእነት እዩ። •ስለዙይ ናይ እግዚአብሔር ቃል ዝገብረና ንሓጥያት ሞይትና ንእግዚአብሔር ሕያዋን ንክንከውን እዩ። እዚ ንዘልአለማዊ ደስታ ዝመርሕ ህያው መንገዲ እዩ። •ንሰይፊ ካብ ደም ምክልካል ማለት ንሓጥያት ካብ ምቅታል ምኽልካል ማለት እዩ። ነዚ ሰይፊዚ ድማ "ሰይፈይ ስጋ ትበልዕ" ተባሂሉ እዩ። •ደም ዝተብሃለ ናይ ስጋ ስራሕ ሓጥያት እዩ። መፅሐፍ ደማ ከምዚ ይብል
"እቶም ብስጋ ዘለዉ ንእግዚአብሔር ከሐጉስዎ አይክእሉን" ----ሮም 8:8
282
16:50
20.08.2025
💦ኢየሱስም ስለምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።" ማር. 10:18
➡️ሙስሊሞች ይሄን ጥቅስ በመያዝ ጌታ ኢየሱስ አምላክ አይደለም ለማለት ይጠቀሙበታል።
✨ምን ማለት እንደው እንይ እስኪ
መጀመሪያ ማወቅ ያለብን ቸር የሚለው ቃል ለሰው እራሱ የሚያገለግል ነው አስፈላጊ ከሆነ ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መጥቀስ እንችልአለን።
ጌታ ኢየሱስ ሰዎዬውን ጥያቄ ጠየቀው እንጅ እኔ ቸር አይደለሁም አላለም
ጌታ ኢየሱስ ይህንን ጥያቄ የጠየቀው "መምህር" ብሎ የጠራው ሰው ኢየሱስን እንደ አንድ ተራ ሰው ወይም መምህር አድርጎ ስላየው ነው። ጌታም በዚያ መልኩ ተራ ሰው እንዳልሆነ፣ ነገር ግን ከእግዚአብሔር አብ ጋር አንድ መሆኑን ለማስተማር ፈልጓል።
ጌታ ኢየሱስ በራሱ ውስጥ ያለውን አምላካዊ ባሕርይ ለሰውየው ግልጽ ለማድረግ ፈለገ። እርሱ ራሱ ቸርነቱ ምንጩና ባለቤቱ መሆኑን ለማሳየት፣ "ለምን ቸር ትለኛለህ?" ብሎ ጠየቀ። የሰውየውም መልስ "አንድ እግዚአብሔር ብቻ ቸር ነው" መሆን ነበረበት፣ ይህም ለኢየሱስም ሆነ ለጠያቂው ሰው የኢየሱስን አምላካዊነት የሚያረጋግጥ ነበር።
ኢየሱስ "ቸር ለምን ትለኛለህ?" በማለት ጥያቄ ያቀረበው ሰውን ለማስተማር ነው። የጠየቀው ሰው እውነተኛ ማንነቱን ማለትም ከእግዚአብሔር አብ ጋር ያለውን አንድነት እንዲረዳው ነው። ሰውየው ኢየሱስን እንደ ሌላ ሰው ቢያየውም፣ ኢየሱስ ግን እርሱ ራሱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን እያሳየው ነበር።
ጌታ ኢየሱስ "ቸር" መሆኑን የሚያረጋግጡ ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አሉ።
✨የዮሐንስ ወንጌል 10፡11 ላይ፣ “እኔ መልካም እረኛ ነኝ...” በማለት ራሱን ገልጿል። “መልካም” (ቸር) የሚለው ቃል የኢየሱስን ቸርነት፣ ፍቅር እና ለበጎቹ ያለውን አሳቢነት ያሳያል።
✨ የሐዋርያት ሥራ 10፡38 ላይ፣ ሐዋርያው ጴጥሮስ “እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስና በኃይል ቀብቶታልና፣ እርሱም መልካም(ቸርነትን) እያደረገ ለዲያብሎስ የተገዙትንም ሁሉ እየፈወሰ ዞረ” በማለት የመሰከረለት ቸርነቱ የሚያረጋግጡ ተግባራትን ነው።
✨2 Corinthians 8 አማ - 2ኛ ቆሮንቶስ
9: የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።
በመጨረሻም፣ ጌታ ኢየሱስ “ለምን ቸር ትለኛለህ?” ብሎ የጠየቀው የሰውየው እምነት የቱ ጋ እንደደረሰ ለማረጋገጥ እና በእርሱ ማንነት ውስጥ ያለውን አምላካዊ ቸርነት ለመግለጽ ነው። እርሱ የእግዚአብሔር አብ ልጅ እንደመሆኑ መጠን፣ የአብ ቸርነት በእርሱ ውስጥ ነው። ስለዚህም ቸር ነው።
210
22:28
21.08.2025
imageImage preview is unavailable
ከተመቸኝ ትንሽ እጽፍላችሁ ይሆናል😊
242
08:22
22.08.2025
ስለ ክርስቲያኖች ትክክለኛ ሕይወት
እናም እርሱ እንዳስተማረው የማይኖሩ ሰዎች፣ በከንፈራቸው የክርስቶስን ትምህርቶች ቢመሰክሩም፣ ክርስቲያኖች እንደማይባሉ ይረዱ፤ ምክንያቱም በቃላቸው የሚመሰክሩት ሳይሆኑ፣ ሥራውን የሚሠሩት ይድናሉና፣ እንደ ቃሉ፡- “ጌታ ሆይ፣ ጌታ ሆይ፣ የሚለኝ ሁሉ ወደ መንግሥተ ሰማያት አይገባም፣ ነገር ግን በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ። እኔን የሚሰማኝ እና ቃሌን የሚጠብቅ ሁሉ የላከኝን ይሰማል። እና ብዙዎች ‘ጌታ ሆይ፣ ጌታ ሆይ፣ በስምህ አልበላንም እና አልጠጣንም፣ እናም ድንቅ ሥራ አልሰራንም?’ ይሉኛል። እናም ከዚያ በኋላ፣ ‘እናንተ ዓመፀኞች፣ ከእኔ ራቁ’ እላቸዋለሁ። ከዚያም ጻድቃን እንደ ፀሐይ በሚያበሩበት ጊዜ፣ እና ክፉዎች ወደ ዘላለም እሳት በሚላኩበት ጊዜ፣ ዋይ እና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል። ምክንያቱም ብዙዎች በበግ ለምድ ተጎናጽፈው፣ ነገር ግን ውስጣቸው ነጣቂ ተኩላዎች ሆነው በስሜ ይመጣሉ። በሥራቸው ታውቋቸዋላችሁ። እናም መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል እና ወደ እሳት ይጣላል።” እናም እነዚህን ትምህርቶቹን ተከትለው የማይኖሩ፣ እና በስም ብቻ ክርስቲያን የሆኑትን ሁሉ፣ በእናንተ ዘንድ እንዲቀጡ እንጠይቃለን።Justin Martyr
The First Apology
Chapter XVI.—Concerning patience and swearing.
200
09:10
22.08.2025
ስለምን ቸር ትለኝ አለህ?
በክፍል ሦስት
ምን አልባት ሉቃስ እና ማርቆስ ከማቴዎስ ጋር ይቀረናሉ ሊሉ ይችላሉ ብዬ መጣው በዚያውም ሃሳብ ለመጨመር😁
በንግግራቸው ውስጥ አንዳንድ ልዩነት ያለ ይመስላል፣ ምክንያቱም ቃላቱ በማቴዎስ መሠረት “ስለ መልካሙ ለምን ትጠይቀኛለህ?” ሲሆኑ፣ እንደ ሌሎቹ ግን “ለምን ቸር ትለኛለህ?” የሚሉ ናቸው። “ስለ መልካሙ ለምን ትጠይቀኛለህ?” የሚለው ዓረፍተ ነገር፣ ሰውየው “ምን መልካም ነገር ላድርግ?” ብሎ ጥያቄ ሲያቀርብ ከተገለጸው ጋር በይበልጥ የሚያያዝ ነእ። ምክንያቱም በዚያ ላይ መልካም የሚለው ስም ለክርስቶስ ተሰጥቷል፣ ጥያቄውም ቀርቧል። ነገር ግን “ቸር መምህር” የሚለው አነጋገር ብቻውን ጥያቄውን አያስተላልፍም። ስለዚህ፣ እሱን ለመፍታት የተሻለው መንገድ “ለምን ቸር ትለኛለህ?” እና “ስለ መልካሙ ለምን ትጠይቀኛለህ?” የሚሉት ሁለቱም ዓረፍተ ነገሮች ጌታ ተናግሯቸዋል ስለዚህ ሉቃስ እና ማርቆስ የጌታን አንዱን ዓረፍተ ነገር ሲናገሩ ማቴዎስ ደግሞ ሌላውን ተናገረ ።
ስለዚህ የእግዚአብሔር ቸርነት
ግን እንደ ሰው የተገደበ ወይም የተወሰነ ሳይሆን ፍጹም ቸርነት ያለው ነው። ስለዚህም ነው ጌታችን 'አምላክ
መሆኔን ክደህ ስለምን ቸር ትለኛለህ?..."የመለሰለት።
እስኪ አንድ አባት ለእነዚህ ሰዎች የጠየቃቸውን እንጠይቃቸው።
በመጀመሪያ፣ እነዚህን አሳሳች ሰዎችን “ጌታን መልካም/ቸር መባልን እንደተቃወመ ታስባላችሁን?” ብለን እንጠይቃቸው። “ለምን መልካም/ቸር ብለህ ትጠራኛለህ?” በሚሉት ቃላት እንደሚገለጽ፣ ክፉ መባልን ይመርጥ ነበርን? እርሱ ራሱ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበዳችሁ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፣ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን ተሸከሙ፣ ከእኔም ተማሩ፤ እኔ የዋህና በልቤ ትሑት ነኝና፣ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ። ቀንበሬ ቀላልና ሸክሜ ቀላላ ነውና” ብሎ የተናገረውን፣ የክፋት ንግግርን ለእርሱ የሚመድብ ማንም ሰው ምክንያታዊ ነው ብዬ አላስብም። እርሱ የዋህና ትሑት እንደሆነ ይናገራል፡- ታዲያ ቸር/መልካም ተብሎ በመጠራቱ ተቆጥቶ ነበር ብለን ማመን እንችላለን? ሁለቱ ሀሳቦች ወጥነት የላቸውም። የራሱ መልካምነት ምስክር የሆነ፣ የመልካምነትን ስም አይቀበልም። እንግዲያውስ፣ ጥሩ በመባሉ አልተቆጣም ማለት ግልጽ ነው፡- እናም ጥሩ መባሉን እንደተቃወመ ማመን ካልቻልን፣ ምን እንደተባለ እንጠይቅ፣ ያንን ግን ተቃወመ።
እንግዲያውስ፣ ጥያቄ አቅራቢው እርሱን ጥሩ ከማለት ውጪ እንዴት እንደጠራው እንመልከት። “ቸር መምህር፣ መልካም ነገር ምን ላድርግ?” አለ። “ጥሩ” ከሚለው ማዕረግ በተጨማሪ “መምህር” የሚለውን ጨመረ። ክርስቶስ እንግዲህ ጥሩ በመባሉ ካልገሰጸ፣ “ቸር መምህር” በመባሉ ሊሆን ይገባል። በተጨማሪም፣ የመገሰጹ መንገድ የመምህርነትን ወይም የጥሩነትን ስም ሳይሆን፣ የጠያቂውን አለማመን እንደተቃወመ ያሳያል። ሕጉን በመጠበቁ የሚኩራራ፣ ነገር ግን የሕጉ ፍጻሜ የሆነውን ክርስቶስን የማያውቅ፣ በሥራው እንደጸደቀ የሚያስብ፣ ክርስቶስ ወደ እስራኤል ቤት የጠፉ በጎች እንደመጣ እና ሕጉ በጽድቅ እምነት ማዳን እንደማይችል ለማያምኑት እንደመጣ ያልተገነዘበ ወጣት፣ የሕጉ ጌታ፣ አንድያ አምላክ የሆነውን እንደ ተራ የሕግ መምህርና ጽሑፍ መምህር አድርጎ ጠየቀው። ነገር ግን ጌታ፣ እንደ ሕግ መምህር አድርጎ የሚጠራውን ይህንን የማያከብር አለማመንን በመጥላት፣ “ለምን ጥሩ ብለህ ትጠራኛለህ?” ሲል መለሰ። እናም እርሱን እንዴት ጥሩ ልንለው እንደምንችል ለማሳየት፣ “ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ማንም ጥሩ የለም” ብሎ አክሏል፣ ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር ከሆነ የመልካምነትን ስም አልካደም።
ጌታ“እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፣ መልካምም ትላላችሁ፣ እንደዚያ ነኝና፤” እና በሌላ ጊዜ ደግሞ፣ “መምህር አትባሉ ተመልከቱ እሱ እራሱን ተራ ሰው አድርጎ አይቶ እያውቅም ሌሎች መምህር አትብሉ ያሉ ጌታ ለራሱ ሲሆን ግን ነኝና መልካምም ትላላችሁ እያለ ሲናገር ስታዩ እሱ ተራ ሰው አልነበረምና።
ቸር ልትለኝ ከፈለግህ፣ እኔን እንደ እግዚአብሔር እወቅ” ከማለት ሌላ ምን ማለት ነው?
243
11:14
22.08.2025
ጌታ ስለምን ቸር ትለኝ አለህ ? ስላለው
ክፍል ሁለት
በኮመንት መስጭ የተነሳ ሃሳብ ስለነበር በደንብ ግልጽ ለማድረግ በክፍል ሁለት መጣው😊
ሃሳቡ ምንድነው ጌታ ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር የለም ብሎ ዘግቶታል የሚል ነው ።
እውነት ነው አወ ዘግቶታል የዘጋው ግን ጥያቄው እንዳለ አድርጎ ነው የዘጋውም ሰውዬ ጌታ በነገረው መልኩ አስቦ እድመልስለት ነው ።ጌታ ኢየሱስ ተራ ሰው ቢሆን ለምን ቸር ትለኝ አለህ ብሎ አይጠይቀውም ነበር። ምክንያቱም ቸር መባል ለሰው የተገባ ስለሆነ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚል
Matthew 12 አማ - ማቴዎስ 35: መልካም ሰው ከልቡ መልካም መዝገብ መልካም ነገርን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከክፉ መዝገብ ክፉ ነገርን ያወጣልእንድል ። ቸር ማለት መልካም ማለት ነው ለዚህም መጽሐፍ ቅዱሳችን በማቴዎስ ወንጌል የዚህን ሰው ጥያቄ እንድህ ይለዋል
Matthew 19 አማ - ማቴዎስ 17: እርሱም፦ “ስለ መልካም ነገር ለምን ትጠይቀኛለህ? መልካም የሆነ አንድ ነው፤ ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ፡” አለው።ነገር ግን ጌታ እኔ መልካም እረኛ ነኝ እንዳለ ከላይ ባለው ጽሑፍ አይተናል እዚህ ላይ ግን መልካም የሆነ አንድ ነው ይላል። ይሄ ብቻ አይደለም
John 10 አማ - ዮሐንስ 28: እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።ያለ ጌታ ቸር መባልን ተቃወመ ማለት የማያስኬድ ነው ጌታ ስለራሱ እኔ እያለ ለአምላክ የሚገቡ ነገሮችን ብዙ ጊዜተናግሯል ። ታድያ ምን ማለት ነው የሚለውን በድንብ ግልጽ እንድሆንላችሁ በምሳሌ እንይ ሰውዬው ወደ ኢየሱስ የመጣው እንደ አንድ መልካም መምህር አድርጎ በመቁጠር ነበር። ኢየሱስም የዚህን ሰው ግምት በመገንዘብ “ቸር ትለኛለህ?” ብሎ ጠየቀው። ይህም “አንተ የምትለኝን 'ቸር' የሚለውን ቃል ተራ አትቁጠረው፤ በባሕርይ የእግዚአብሔር ብቻ ነው” የሚል መልእክት አለው። ስለዚህ በምን መልኩ ነው እያልከኝ ያለኸው ነው። ምሳሌ፦ አንድ ሰው አንበሳ ብሎ ሲጠራህ፣ አንተም “ለምን አንበሳ ትለኛለህ? አንበሳ ብርቱና ንጉሥ ነው” ብትለው፣ “አንበሳ” የሚለው ስም ምን ያህል ከባድና ትርጉም ያለው እንደሆነ እያስተማርከው ነው ስለዚህ ሰውዬው አንበሳ ያለህ ገብቶት ከሆነ ሊመልስልህ የምችለው አወ አንበሳ ብርቱ ነው አንተም ብርቱና ንጉሥ ነህ በማለት ለምን እንዳለው በደንብ በማስረዳት ይገልጽለታል ። በተመሳሳይ መልኩ፣ ኢየሱስም “ቸር” የሚለው ባሕርይ የእግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ በማስረዳት የራሱን አምላካዊ ማንነት ገልጿል።ማለትም ሰውዬው ጠንካራ ቢሆን በእምነቱ እንድሁም ገብቶት ቢሆን ጌታ የጠየቀው ለእግዚአብሔር ቸር በሚባልበት መልኩ ለምን ቸር እንዲያለው ተረድቶ እንድህ ስል በማለት የሰውዬውም መልስ አወ ቸር እግዚአብሔር ብቻ ነው ስለዚህ አንተ ቸር እግዚአብሔር ስለሆንክ ነው እንደዚያ ያልኩህ ነበር መሆን የነበረበት ። እንጅ እንደ ተራ ሰው ቸር ለመባልማ ይሄን ጥያቄ ባላነሳ ነበር ሙስሊሞች ይሄን ጥያቄ ባለማወቅ ቢያነሱትም ጌታ ኢየሱስ አምላክነቱን ያሳየበት እንደው ሲያቁ እንደማያነሱት እርግጥ ነው እንደውም ይሄን ጥቅስ ማንሳት ያለብን እኛ ነን የጌታን አምላክነት ለማሳዬት ይቆየን የተሻለ ሃሳብ የሚያነሳ ካለ በክፍል ሦስት እመጣለው 😊
163
11:14
22.08.2025
ለሰንበት ትምህርት ቤት መምህራን
እንደ ሃሳብ ሰንበት ትምህርት ሊማር መጥቶ ጥያቄ ሲጠዩቃችሁ እንዴት እንደዚህ አይነት ጥያቄ ትጠይቃልህ/ሽ ብላችሁ አሸማቃችሁ ድጋሜ እንዳይመለስ የምታደርጉ ልጆቹም መልስ ቢያጡ ነው ብለው ወደሌላ ቤተ እምነት እየሄዱ ስለሆነ እንደ ሃሳብ ቤታችሁ ብትቀመጡ😁
የምሬን ነው መመለስ ካልቻላችሁ ደግሞም መምህር ነኝ ብላችሁ ቁማችሁ እናንተ ራሳችሁን ሁሉን ነገር እንደምታቁ አድርጋችሁ አላቀውም ሌላ ጊዜ ጠይቄ እመልሳለው እንደማለት የእናንተን አለማወቅ ሰውን በማሸማቀቅ ከምትሸፍኑ ቤታችሁ ቁጭ በሉ ጥሩ ምክር ነው በእናንተ ምክንያት ሰው ከሚጠፋ😁
2204
15:06
22.08.2025
በገነት የተተከለች የሕይወት ዛፍ አረገች፣ እርሷም በምሥጢር ለብርሃን እናት ምልክት ናት
350
13:39
22.08.2025
“አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው #እንዲሁ ደግሞ ለወልድ #በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታልና።” (ዮሐንስ 5:26)ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የክርስትናን መሠረታዊ አስተምህሮ በጥልቅ የሚገልጽ ሲሆን፥ ለአንዳንዶች ደግሞ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ አይደለም ለማለት ይጠቀሙበታል ። እስኪ ሁሌ ማብራሪያ ከምንሰጥ ግን አንዳንዴም እንጠይቃቸው😊 ሙስሊሞች እስኪ ከፍጡር ልክ እንደ አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው የተሰጠው አንድ ጥቅሱ የትኛውም ፍጡር በራሱ ሕይወት የለውም ለዚያውም ልክ እንደ አብ በራሱ ሕይወት ያለው አስባችሁታል ፍጡር ልክ እንደ አብ ሕይወት ሲኖረው እንደ አብ ሕይወት ኖረው ማለት አብ ሕይወት ሰጭነውና ለፍጡር ሕይወት ይሰጣል ከፍጡር እንደዚያ አሳዩን ? የምትጠቅሱትን አለማወቃችሁ ይገርመኛል ብታቁ ኑሮ ይሄን ጥቅስ አጠቅሱትም ነበር። ማብራሪያውን ሌላ ጊዜ 😊
172
10:46
24.08.2025
በዮሐንስ ወንጌል 5፡26 ላይ ያለው
“አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው፣ እንዲሁ ለወልድም በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታልና።”ሙስሊሞች ይሄን ባለማወቅ ጌት አምላክ አይደለም ለማለት ይጥቀሙበታል ግን የጌታን አምላክነት የሚያሳይ እንጂ አምላክ አለምሆኑን ፈጽሞ አያሳይም።። የዚህን ጥቅስ ትክክለኛ ትርጉም ለመረዳት በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ከፍለን ማየት እንችላለን። ሀ. “አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው...” ይህ የመጀመሪያው ሐረግ የእግዚአብሔርን መሠረታዊ ባሕርይ ይገልጻል። “በራሱ ሕይወት” መኖር ማለት፡- * ምንጩ ራሱ ነው፡ ሕይወቱ ከሌላ አካል የተገኘ ወይም የተቀዳ አይደለም። እርሱ የሕይወት ሁሉ ምንጭ ነው እንጂ የእርሱ ሕይወት ምንጭ የለውም። * ፍጡር አይደለም፡ ሕልውናው መጀመሪያ የለውም። “ያልነበረበት ጊዜ ነበር” ሊባል አይችልም። * በማንም ላይ አይመሰረትም፡ ለመኖር በሌላ ነገር ላይ ጥገኛ አይደለም። ይህ አምላካዊ ባህርይ (Divine Simplicity) ይባላል። ሕይወት ከማንነቱ የተለየ ባህሪ ሳይሆን፣ ማንነቱ ራሱ ነው። ስለዚህ "አብ በራሱ ሕይወት አለው" ማለት፣ የአብ ሕልውና ፍጹም፣ ያልተከፋፈለ፣ ዘላለማዊና የማንም ድጋፍ የማይሻ መሆኑን ያረጋግጣል። ለ. “...እንዲሁ ለወልድም በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታልና።” “እንዲሁ” የሚለው ቃል “እንደዚሁ”፣ “በተመሳሳይ መንገድ”፣ “በዚያው ልክ” ወይም “ልክ እንደ” ማለት ነው። ይህ ቃል አንድን ነገር ከሌላ ነገር ጋር እኩል ወይም ተመሳሳይ መሆኑን ለማሳየት ያገለግላል። በዚህ ጥቅስ ውስጥ “እንዲሁ” የሚለው ቃል በአብና በወልድ መካከል ያለውን ተመሳሳይነት ያሳያል። * የመጀመሪያው ንጽጽር (አብ): አብ በራሱ ሕይወት አለው። ይህ ማለት እግዚአብሔር አብ የሕይወት ምንጭ ሲሆን፣ ሕይወቱን ከማንም አላገኘም። እርሱ ራሱ ሕይወት ነው። * ሁለተኛው ንጽጽር (“እንዲሁ” የወልድ): “እንዲሁ” አብ ለወልድ በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታል። ይህ ማለት አብ በራሱ ያለውን ልዩ እና ዘላለማዊ የሕይወት ባሕርይ ለወልድ ሰጥቶታል ማለት ነው። “በራሱ ሕይወት” ማለት ራሱን የቻለ፣ ከማንም ያልተገኘና ከማንኛውም ሌላ አካል ነፃ የሆነ የመኖር ባሕርይ (aseity) ማለት ነው። ይህ አባባል ከመጀመሪያው የነበረውንና ያልተፈጠረውን የሕይወት ሙላት የሚያመለክት ሲሆን፣ ይህ ባሕርይም የእግዚአብሔር ብቻ ነው። ስለዚህ ጌታ ኢየሱስ ይህን “በራሱ የመኖር” ባሕርይ ልክ እንደ አብ የተሰጠው ስለሆነ እርሱ እግዚአብሔር ነው። ከእግዚአብሔር ውጭ ማናቸውም ፍጡር “በራሱ ሕይወት” የለውም። በራሱ የሚኖረው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ስለዚህ “ሰጠው” የሚለውን በሁለት ከፍለን እንየው፦ 1. የመጀመሪያው ልደት (ከመጀመሪያው): እግዚአብሔር የማይከፋፈል (simple) በመሆኑ፣ የባሕርዩን “ክፍል” ወይም “ድርሻ” ሊሰጥ አይችልም። ስለዚህ አብ ለወልድ ሕይወትን “ሲሰጥ”፣ የሚሰጠው ከፊል ኃይልን ሳይሆን መላ ማንነቱን፣ ሙሉ ባሕርዩን ነው። ይህ ድርጊት ዘላለማዊ ልደት (Eternal Generation) ይባላል። አብ ለዘላለም አባት እንደሆነ፣ ወልድም ለዘላለም ልጅ ነው። አብ ለወልድ ሕይወትን “የመስጠት” ተግባር እርሱን ዘላለማዊ በሆነ መንገድ የመውለድ ተግባር ሲሆን፣ በዚህም ወልድ አብ በያዘው መንገድ የመለኮትን ሙላት ይይዛል። ልክ የብርሃን ጨረር ከራሱ ብርሃን ጋር ዘላለማዊ እና የማይነጣጠል እንደሆነ ሁሉ፣ ወልድም ከአብ ጋር ዘላለማዊ እና የማይነጣጠል ነው። ጨረሩ በብርሃን የተሠራ ፍጥረት አይደለም፤ ነገር ግን የብርሃን ባሕርይ ራሱ ነው። የወልድን ዘላለማዊ ልደት መካድ፣ አብ አብ ያልነበረበት ጊዜ ነበር ማለት ነው፤ ይህም ዘላለማዊ ማንነቱንና መለኮታዊ ማንነቱን ይነጥቀዋል። ስለዚህ “ሰጠው” የሚለው ከመወለድ ጋር አንድ የሆነ አብ ለወልድ ልብነቱን መስጠቱን ያመላክታል። እግዚአብሔር (መለኮት) አንድ ባህርይ ነው። አንድ መለኮት ሦስቱን “ከዊናት” ለሦስቱ አካላት ሰጥቷል፦ ልብነቱን ለአብ፤ ቃልነቱን ለወልድ፤ ሕይወትነቱን ለመንፈስ ቅዱስ። 2. ሁለተኛው ልደት (ሰው ከመሆኑ አንፃር): የወልድ ዘላለማዊና ያልተፈጠረ “በራሱ ሕይወት” መያዝ፣ ለሌሎች ሕይወት ለመስጠት ያለውን መካከለኛ ሥልጣን የሚያስችል መሠረታዊ የሕልውና ቅድመ ሁኔታ ነው። የእግዚአብሔርን ሥራ ለመሥራት ወልድ በመጀመሪያ እግዚአብሔር መሆን አለበት። ይህ አቀራረብ ኢየሱስ ሕይወትን ስለ መስጠትና ስለ መፍረድ የሚናገርበትን የቁጥር 21 እስከ 27 ያለውን ክፍል በሙሉ ፍጹም የሆነ ንባብ ይሰጣል። ለዚህም የቅዱስ ቄርሎስን ቃል እንመልከት፦
“አንድያው (ወልድ)፣ በሥጋው ባሕርይ ሰው በመሆኑና በምድርም ላይ በሥጋ ሳለ እንደ እኛ ሆኖ በመታየት፣ አይሁድን ስለ ድኅነት በሚመለከቱ ጉዳዮች በብዙ መንገድ ሲያስተምር፣ ለመለኮት የሚገቡ ሁለት ነገሮችን ክብር ለራሱ ተጎናጸፈ። ምክንያቱም ሙታንን እንደሚያስነሣና በፍርዱ ዙፋን ፊትም ለፍርድ እንደሚያቆማቸው በግልጽ አረጋግጧልና። ነገር ግን ሰሚዎቹ፣ "እግዚአብሔር አባቴ ነው" በማለት ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላስተካከለ፣ በዚህ ነገር ተበሳጭተው በምክንያት እንደሚከሱት እጅግ ይጠበቅ ነበር። ስለዚህ፣ ለመለኮት የሚገባውን ሥልጣንና ግርማ ከሰው ባሕርይ ጋር ከሚሄድ አነጋገር ጋር በማደባለቅ፣ ከሚገባው በላይ በትሕትናና ራሱን ዝቅ አድርጎ በመናገር የቁጣቸውን ክብደት ያለዝባል፤ እንዲህም ይላል፦ "አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው፣ እንዲሁ ለወልድም በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታል።" (እርሱም እንዲህ የሚል ይመስላል፦) "እኔ፣ አሁን እንደ እናንተ ሆኜ እንደ ሰው የምታየኝ፣ ሙታንን አስነሣለሁ ብልና ለፍርድም አቀርባቸዋለሁ ብል አትደነቁ፤ አብ ሕይወትን እንድሰጥ ኃይልን ሰጥቶኛል፣ በሥልጣንም እንድፈርድ ሰጥቶኛል።" በዚህ መንገድ በቀላሉ የሚሰናከለውን የአይሁድን ጆሮ ከፈወሰ በኋላ፣ ለሚከተለው ነገር ጥቅምም ትጋት የተሞላበት ጥንቃቄ ያደርጋል። ይህን ሥልጣን እንደተቀበለ ለምን እንደተናገረም ወዲያው ሲያብራራ፣ "የሰው ልጅ ስለሆነ" በማለት የሰው ባሕርይ በራሱ ምንም እንደሌለው ይገልጻል።”ስለዚህ ሥጋ ሕይወት ሰጭነትን ገንዘብ አደረገ እናም እንደ አብ ሕይወትን እንደሚሰጥ ተናገረ። ጌታ ኢየሱስ ሕይወትን እንደሚሰጥ ተናግሯል፤ ቃል ሕይወት ነውና ሕይወት ሰጭነትን ሥጋ ገንዘቡ አድርጎ ሥጋ ለሰዎች የዘላለም ሕይወት ይሰጣል። “ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው” እንዳለ ጌታ።
98
15:24
25.08.2025
close
Reviews channel
keyboard_arrow_down
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
5.0
1 reviews over 6 months
Excellent (100%) In the last 6 months
c
**ffeennew@******.io
On the service since June 2022
24.06.202518:11
5
Everything is fine. Thank you!

የእምነት ጥበብ
On the service since August 2024
26.06.202513:25
Thank you
Show more
New items
Channel statistics
Rating
22.8
Rating reviews
5.0
Сhannel Rating
2
Subscribers:
20.8K
APV
lock_outline
ER
1.6%
Posts per day:
3.0
CPM
lock_outlineSelected
0
channels for:$0.00
Subscribers:
0
Views:
lock_outline
Add to CartBuy for:$0.00
Комментарий