
Advertising on the Telegram channel «Orthodox Tewahdo new»
#Orthodox_Tewahdo_new Ethiopian Orthodox Tewahdo Church is a channel that broadcasts current news and teachings to the Christian public. የመዝሙር ቻናል👉
Channel statistics
ሰው ጨካኝ ሲሆን እግዚአብሔር ግን ሁሉን የሚወድ ቸርና ርህርህ ነው፡፡
ለዚህም ነው ንጉስ ዳዊት ከሦስቱ ቅጣቶች መካከል አንዱን እንዲመርጥና አማራጩ ሲቀርብለት የተናገረው ቃል ድንቅ ነው፡፡
" ምህርቱ ብዙ ነውና በእግዚአብሔር እጅ እንውደቅ በሰው እጅ ግን አልውደቅ፡፡"
2ኛ ሳሙ 24 ፥ 14፡፡
ጻድቁ እዮብም በሦስቱ ባልደረበቹ እጅ በወደቀ ጊዜና እነርሱም እርሱን መውቀሳቸውን ባላቋረጡ ጊዜ እንዲህ ነበር ያላቸው ፡- "ነፍሴን የምትነዘንዙ በቃልስ የምታደቅቁኝ እስከ መቼ ነው? ይኸውም ስትሰድቡኝ አሥር ጊዜ ነው፡፡"
ኢዮ 19 ፥ 2 - 3፡፡
እግዚአብሔር ግን ከሰው በእጅጉ በተለየ መልኩ መሐሪና ርህርህ መሆኑን በሚከተሉት ውስጥ እንመለከታለን፡፡
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|•✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
📖የግዕዝ ትምህርት ጀምሯል ቤተሰብ ተጀምሯል ቮይስ ቻት ግቡ🙏
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=28139bd52b72e2e60ድ
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=28139bd52b72e2e60d
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
ለኑሮ ሰላማዊ፣ ለንግድዎ ስኬታማ የሆነውን የቤትና የሱቅ ባለቤት የመሆን ዕድል አሁኑኑ ይጠቀሙ። ደስታዎ እዚህ ይጀምራል!
🏠 ለመኖሪያ በተመረጡ የካሬ አማራጮች፦
* ባለ 1 መኝታ፦ ከ77 ካሬ ጀምሮ
* ባለ 2 መኝታ፦ ከ111 ካሬ ጀምሮ
* ባለ 3 መኝታ፦ ከ150 ካሬ ጀምሮ
* ባለ 4 መኝታ፦ ከ190 ካሬ ጀምሮ
* ፔንት ሃውስ (Penthouse)፦ ከ169 እስከ 295 ካሬ ድረስ
🛒 ለንግድ ሱቆች፦ ከ27 ካሬ ጀምሮ።
💰 ልዩ የክፍያ አማራጮች፦
* በ 10% ቅድመ ክፍያ ብቻ ውል ይጀምሩ።
* የ 60% የባንክ ብድር ተመቻችቶለት፣ እስከ 25 ዓመታት ድረስ ቀስ እያሉ የሚከፍሉበት።
* ሙሉ ለሚከፍሉ 35% ታላቅ ቅናሽ (እስከ 3,000,000 ብር እውነተኛ ቅናሽ!) ቅደመው ለሚመጡ ዝቅተኛ ፍሎር አለ
💎 ሙሉ ምቾቶች የተሟሉለት፦
🏊♂️ መዋኛ ገንዳ |
🏃♂️ የመሮጫ ትራክ |
🏋️ ጂም |
🛒 ሱፐር ማርኬት
🅿️ ሰፊ ፓርኪንግ |
💧 የከረሰ ምድር ውሃ |
⚡ አውቶማቲክ ጄኔሬተር
📍 አድራሻ፦ ለቡ መብራት ኃይል (በሁለት ታላላቅ ተቋማት መካከል)
"የነገ ቅርሶን ዛሬ ይገንቡ፤ በብዙ ያተርፋሉ!"
📞 አሁኑኑ ይደውሉና ሳይቱን ይጎብኙ፦
0918965096
ዲ ኤም ሲ ሪል እስቴት
ደስታዎ እዚህ ይጀምራል
@henokab2730
https://t.me/henokdmcreal
✞የካቲት 23 ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
😇 አዋጁን ካስነገሩ በኋላ ከዚያም ተነሥቶ ወደ ትግራይ ክፍለ አገር ዘመቱና ከትግራይ አውራጃ አንዷ የምትሆን አድዋ የምትባል አገር ደረሱ፡፡ የሣህለ ማርያም (ዳግማዊ ምኒልክ) ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) በንጉሡ ትዕዛዝ ታቦተ ጊዮርጊስን አስይዘው ከሊቀ ጳጳሱ ከአባ ማቴዎስ እንዲሁም ከቀሳውስቱና ከመነኰሳቱ ጭምር ከንጉሡ ጋር ወደ ጦርነቱ ተጓዘች፡፡ በዚያም ጊዜ የአክሱም ጽዮን መነኰሳትና ካህናት የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሡ ወደ ምኒልክ መጥተው ከሊቀ ጳጳሱ ከነአቡነ ማቴዎስ ጋር ተቀላቀሉ ከዚያም ሌሊቱን ሙሉ ጸሎት ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ።
🤩 በዚህም ዕለት ይኸውም የካቲት ሃያ ሦስት ቀን በሮማውያንና በኢትዮጵያውያን መካከል ከፍተኛ ጦርነት ሆነ በዚህም ጊዜ በሰማይ ታላቅ ተአምር ተደረገ። ማለትም የቀስተ ደመና ምልክት ታየ ከዚያም ከቀስተ ደመናው ውስጥ መልኩ አረንጓዴ የመሰለ ጢስ ይወጣ ነበር፡፡ ከዚህም ጢስ ውስጥ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ያለ ድምጽ ተሰማ፡፡ ከዚህም የነጐድጓድ ድምጽ የተነሳ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ሽብር ሆነ ለመዋጋት አልቻሉም፡፡ ይልቁኑ ኃያሉ ገባሬ ተአምር ማር ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ላይ ፈረሱ ተቀምጦ ከነፋስ ሩጫ ይልቅ እየተፋጠነ በአየር ላይ በተገለጸ ጊዜ በግንባራቸው ፍግም እያሉ ወደቁ፡፡ "የኢትዮጵያ ህዝብ አምላካቸው ሊረዳቸው መጣ እንግዲህ ማን ያድኅነናል" አሉ ምድርም ጠበበቻቸው በዚህን ጊዜ የኢትዮጵያ ሠራዊት የሮምን የጦር ሠራዊት ፈጁዋቸው የተረፉትንም ማረኳቸው ፈጽመውም እስኪያጠፏቸው ድረስ በሮማውያን ላይ በእግዚአብሔር ሥልጣን የኢትዮጵያውያን እጅ እየበረታ ሄደ፡፡ ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) በእግዚአብሔር ኃይልና በተአምራት አድራጊው በቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳይነት የሮማውያንን የጦር ሠራዊት ድል አድርገው የድል አክሊል ተቀዳጅተው ተመለሱ፡፡
👉 የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ምኒልክ ከአደዋ ጦርነት ከተመለሱ በኋላ በአዲስ አበባ በምትበል ከተማው መካከል በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ቤተክርስቲያን አሠራ። ስሟንም ገነተ ጽጌ ብለው ሰየሟት። ቅዱስ ጊዮርጊስ በጦርነት ቦታ ሁሉ ይረዳው ነበርና። ልመና ክብሩ በኛ ለዘላለሙ በዕውነት ይደረግል።
(ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተአምር 17)
🤩 "የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"☦️ ምሳ 1፥33📕
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
ከ ቄራ ወደ ሜክሲኮ የሚወስደው ዋና አስፋልት ከመብራቱ አለፍ ብሎ
ከ ባለ 1 መኝታ ቤት እስከ ባለ 3 መኝታ ቤት
📍ባለ 1 መኝታ ቤት 60ካሬ
📍ባለ 2 መኝታ ቤት 90 -116 ካሬ
📍ባለ 3 መኝታ ቤት 125-157 ካሬ
✅ቅድመ ክፍያ 20%
✅100% ለሚከፍል 30% ቅናሽ ይደረጋል፡፡
ከ 7ኛ ፎቅ እስከ 13 ፎቅ የፍሎር አማራጭ አላቸው ፡፡
ከ ግራውንድ እስከ 5ኛ ፎቅ የንግድ ሱቆች
6ኛ ፎቅ የጋራ መገልገያ
👉ባለ 1 መኝታ ቤት 60ካሬ
አጠቃላይ ክፍያ = 6,900,000
20% ቅድመ ክፍያ = 1,380,000
👉100% ለሚከፍል 30%ቅናሽ ተደርጎ የሚከፍለው ክፍያ = 4,830,000
👉 ሱቆችን ደግሞ በፒያሳ፣በገላን እንዲሁም በቡልጋሪያ ከፈለጉ
ቅድመ ክፍያ ለ ንግድ ሡቆች:
👉Ground 3,500,000
1st :- 2,500,000
3rd :- 1,300,000
5th Floor :- 900,000
ፈጥነው ይያዙ❗️
👉ማሳስቢያ ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ አናደርግም
🏗️ ቀሪውን ክፍያ በ 3 አመት በግንባታ ሂደት የሚከፍሉት ይሆናል፡፡
☎️+251974163592
https://t.me/yichalemtilahun
በዚች ቀን የክቡር ፋሲለደስ ልጅ የከበረ አውሳብዮስ በሰማዕትነት ሞተ።
ይህም የከበረ ፋሲለደስ ለአንጾኪያ መንግሥት የሠራዊት አለቃ ነው ለመንግሥት ልጆችም አባታቸው ነው እርሱም ከፋርስ ሰዎች ጋር በጦርነት ውስጥ እያለ ዲዮቅልጥያኖስ የክብርባለቤት ጌታችንን ክርስቶስን ክዶ ጣዖትን እንዳመለከ ሰማ።
እጅግ አዝኖ ወደ ልጁ ወደ አውሳብዮስ ልኮ ይህን ነገረው የከበሩ የቤተ መንግሥት ሰዎች ዘመዶቹን ዳግመኛ ጠራቸው እነርሱም የንጉሥ ልጅ ዮስጦስ አባዲር ገላውዴዎስና ቴዎድሮስ ከእርሳቸውም ጋር ያሉትን ጠርቶ ስለ ከሀዲው ንጉሥ ነገራቸው።
ሁሉም እጅግ አዘኑ ዳግመኛም እንዲህ አላቸው እኔ ስለ ፈጣሪዬ ስለ ክርስቶስ ስም ደሜን አፈሳለሁ ሁሉም በዚህ በጎ ምክር ተስማምተው እርስ በርሳቸው ተማማሉ።
ጠላቶቻቸውንም ድል አድርገው ወደ ሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ ንጉሡ ከሠራዊቱ ጋር ወጥቶ በደስታ ተቀበሏቸው።
ከዘህም በኋላ የቅዱስ ፊቅጦር አባት ህርማኖስ ለቅዱሳኑ ጣዖትን እንዲአቀርብላቸውና አንዲሰግዱለት ንጉሡን መከረው ንጉሡም ህርማኖስ እንደ መከረው አደረገ ። በዚያንም ጊዜ ቅዱሳንን ጠርቶ እነዲህ አላቸው እኔ እጅግ እንደምወዳችሁ እናንተ ታውቃላችሁ አሁንም ለአጵሎን ሰግዳችሁ ልቤን ደስ ታሰኙ ዘንድ ከእናንተ እሻለሁ።
ቅዱሳንም ሰምተው እጅግ ተቆጡ አውሳብዮስም ንጉሡን ሊገድል ሰይፉን መዘዘ ንጉሡም ሸሽቶ ተሸሸገ ከንጉሥም ባለሟሎች ብዙዎችን ሠራዊቱንም ጭምር ገደለ የከበረ ፋሲለደስም ባይከለክላቸው ከንጉሥ ቤት ምንም ሰው ባልቀራቸው ነበር።
ከዚህም በኋላ ደግሞ አውሳብዮስን ወደ ግብጽ አገር ወስደው በዚያ ይገድሉት ዘንድ ህርማኖስ ንጉሡን መከረው እርሱ በዚች ሀገር ከኖረ ያገር ሰዎችን በላይህ ያስነሣብሃልና ያሰብከውን ምንም ምን መሥራት አትችልም አለው።
ንጉሡም ቅድስ አውሳብዮስን ጽኑዕ ሥቃይን ያሠቃዩት ዘንድ ወደ ግብጽ አገር ወደ ቅፍጥ ገዥ ሉልያኖስ ዘንድ እንዲወስዱት ጻፈ ወደ መኰንን ሉልያኖስም በደረሰ ጊዜ በመንኰራኵር ሕዋሳቱን በመቁራረጥ በግርፋት አሰቃዩት።
ደግመኛም በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት ጌታችንም መልአኩን ልኮ ከመከራው ሁሉ አዳነው አጽናንቶና አረጋግቶ ያለ ጉዳት አስነሣው።
ነፍሱንም ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ወሰዳት የጻድቃንና የሰማዕታትንም መኖሪያ አየ ለርሱና ለአባቱ ለዘመዶቹም ያዘጋጀላቸውን ቦታዎች አይቶ ነፍሱ እጅግ ደስ አላት።
ከዚህም በኋላ ወደ እሳት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ መኰንኑ አዘዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአከ ወርዶ እሳቱን እንደ ጠል አቀዝቅዞ ያለ ጥፋት የከበረ አውሳብዮስን አወጣው።
መኳንንቱም እንዲህ ብለው መከሩት መኰንን ሆይ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ እዘዝ ከእርሱም ትግል ታርፋለህ እርሱም የአውሳብዮስን የከበረች ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ
ምንጭ፦
😇 "የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ📖 📖 🌟 ፥🌟 🌟
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
#የምስራች በ እ ግ ዚ አ ብ ሔ ር : ቸ ር ነ ት : የ የ ካ ቲ ት : ቅ ዱ ስ ጊ : ዮ ር ጊ ስ : ዕ ለ ት : ኢ ጣ ሊ ያ ን ን : ድ ል : አ ድ ር ጌ መ ታ ሁ ት : አ ም ላ ክ : ኃ ያ ላ ን : ረ ድ ቶ ኝ : ፈ ጀ ሁ ት : ደ ስ : ብ ሎ ኛ ል : ደ ስ : ይ በ ል ህ ። #እንኳን_አደረሰን
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
ምኩራብ ማለት ምን ማለት ነው??
መምህር ገብተዋል ትምህርት ተጀምሯል ላይቭ ግቡ
ትምህርቱ ተጀምሯል ቮይስ ቻት ግቡ
ከታች በተላከላችሁ ሊንክ በመጫን ሊንኩን በመንካት ወደ ትምህርት ትምህርት ወደ ምሰጥበት ግሩፕ ይቀላቀሉ👇👇👇
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
‹‹እለ ሐሙ በእንተ ስሙ፤ ምድር ሠናይት ርስቶሙ
ስለስሙ መከራን የተቀበሉት፤ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናት››
(ማቴ 5÷51 ፤ ቅዱስ ያሬድ)
ከዚህ በፊት በአርሲ ሀገረ ስብከት በተለያዩ ወረዳዎች የበርካታ ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ሕይወት በመጥፋቱና ከሞት የተረፉትም ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ወደ አጎራባች ከተሞች ተሰደው ለረሀብና ለእርዛት ተጋልጠው እየኖሩ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ቀደም ሲል በተለያዩ ጊዜያት፣ በደረሰው ሞትና ስደት ምእመናን እያዘነ ባሉበት፣ እኛም ከኃዘናችን ባልተጽናናንበት ሁኔታ ጥቃቱ በአዲስ መልኩ ቀጥሎ የ21 ንጹሐን ወገኖቻችን ሕይወት በግፍ ማለፉን፣ በሕይወት የተረፉትም በታጣቂዎቹ መታገታቸውንና የደረሱበት አለመታወቁን፣ h10 የሚበልጡ አባውራዎች ቤትና ንብረት እንደተቃጠለ በመግለጽ ከሀገረ ስብከቱ የቀረበውን ሪፖርት የተመለከትነው ጥልቅ በሆነ ኃዘን ነው፡፡
አገር ሰላም ብለው በሚኖሩት ከምንም ጉዳይ ጋር ንክኪ በሌላቸው ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን ላይ ይህን አስነዋሪ ድርጊት የፈጸሙት አካላትም ግድያውን በሃይማኖት ስም ይፈጽሙት እንጂ የሃይማኖት ስዎች ግን አይደሉም፡፡ ዓላማቸውም በሀገራችን ለረዥም ዘመናት ተከባብረው አብረው በኖሩት የሃይማኖት ተቋማት መካከል ግጭትን መፍጠር ነውና የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና ሕዝበ ክርስቲያኑ በጋራ ልናወግዛቸው ይገባል፡፡
በመሆኑም በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ በሕዝበ ክርስቲያኑ ዕለታዊ ኑሮ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥር፣ በቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ በሰው ልጅ ሰብአዊ አኗኗር ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው አጸያፊ ድርጊት በመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በጽኑ አውግዞታል፡፡
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በተደጋጋሚ እየተፈጸመ ያለው ሞትና መፈናቀልም ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን በየትኛውም የሀገራችን ክፍል በነጻነት ሠርተው የመኖርና ሥርዓተ አምልኮ የመፈጸም ሕገ መንግሥታዊ መብታቸውን የሚጋፋ በመሆኑ የክልሉና የፌዴራል መንግሥት ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ ተከታትለው አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡበት ቋሚ ሲኖዶስ በጥብቅ ያሳስባል፣
ፍርድን በመሻት የሚጮኸው ስለስሙ መከራን የተቀበሉት የንጹሐን ደም ተገቢውን ፍትሕ ይፈልጋልና ይህን አስነዋሪ ድርጊት የፈጸሙት አካላት በሕግ እንዲጠየቁ፣ ወደፊትም ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት እንዳይጠፋ፣ የዜጐች ሀብትና ንብረት እንዳይወድም መንግሥት የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ተግባሩን እንዲያከናውን ቋሚ ሲኖዶስ ጥሪውን በአጽንኦት ያስተላልፋል፤
በደረሰው አደጋ ዙሪያ ተነጋግሮ ተገቢውን ውሳኔ ለማስተላለፍ የተሰበሰበው ቋሚ ሲኖዶስም የአካባቢው ችግር አስተማማኝ በሆነ መንገድ ተፈትቶ ዘላቂ ስላም እስኪገኝ ድረስ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የተሰየመው የሀገር ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ዐቢይ ኮሚቴ ከፌደራልና ከክልሉ መንግሥት ጋር በመነጋገር ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥልና የሚመለከታቸውም አካላት በየድርሻቸው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ቋሚ ሲኖዶስ በክብር ያሳስባል፡፡
የክልሉ መንግሥትና የአካባቢው መስተዳድርም ችግሩን ለመፍታት እያደረገ ያለው ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥልና ወደፊትም ችግሩ እንዳይደገም ከመሠረቱ መፍታት የሚያስችል እርምጃ እንዲወስድ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ትጠይቃለች፡፡
በመጨረሻም ስለስሙ በሥጋቸው መከራን በመቀበል ሕይወታቸውን በአጡት ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን የተሰማንን መሪር ኃዘን እየገለጽን ልዑል እግዚአብሔር ዕረፍተ ነፍስን እንዲሰጥልን፣ ቤተሰቦቻቸውንም እንዲያጽናናልን እንጸልያለን፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ
የካቲት 2018 ዓ/ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯
Reviews channel
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «Orthodox Tewahdo new» is a Telegram channel in the category «Образование», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 180K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 7.5, with 0 reviews and an average score of 0.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 9.6 ₽, and with 0 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий