
Advertising on the Telegram channel «Orthodox Tewahdo new»
#Orthodox_Tewahdo_new Ethiopian Orthodox Tewahdo Church is a channel that broadcasts current news and teachings to the Christian public. የመዝሙር ቻናል👉
Channel statistics
በሸገር ሀገረ ስብከት በሚገኘው የደብረ ፀሀይ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን አገልጋይ ወጣቶች ታቦተ ሕጉን አጅበው ወደ ባሕረ ጥምቀት በማቅናት ላይ እያሉ፣ በሚጓዙበት ሰረገላ እና በኤሌክትሪክ መስመር መካከል በተፈጠረ ንክኪ የ4 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ሊያልፍ መቻሉ ተገልጿል።
በኮዬ ፈጬ የደብረ ፀሀይ መድኃኒዓለም በደረሰው አደጋ ማህተቤን አልበጥስም የተዋህዶ ድምፅ የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እንገልፃለን ለቤተሰቦቻቸው ለወዳጆቻቸው መፅናናትን እንመኛለን ነፍስ ይማር
በሸገር ሀገረ ስብከት በሚገኘው የደብረ ፀሀይ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን አገልጋይ ወጣቶች ታቦተ ሕጉን አጅበው ወደ ባሕረ ጥምቀት በማቅናት ላይ እያሉ፣ በሚጓዙበት ሰረገላ እና በኤሌክትሪክ መስመር መካከል በተፈጠረ ንክኪ የ4 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ሊያልፍ መቻሉ ተገልጿል።
በኮዬ ፈጬ የደብረ ፀሀይ መድኃኒዓለም በደረሰው አደጋ ማህተቤን አልበጥስም የተዋህዶ ድምፅ የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እንገልፃለን ለቤተሰቦቻቸው ለወዳጆቻቸው መፅናናትን እንመኛለን ነፍስ ይማር
✞እንኳን ለብርሃነ ጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ልዩ የከተራ በዓል በማስመልከት የተዘጋጀው ልዩ ፕሮግራማችን ተጀምሯል ቮይስ ቻት ግቡ😍🙏
✨ዝማሬ በተጋባዢ ዘማሪያን
✨ትምህርተ ወንጌል በሊቃዉንት
✨ መንፈሳዊ ጭዉዉትና ግጥም እና ድራማ
✨ሚክረ አበው እና መነባነብ
✨ ትረካ መንፈሳዊ ልቦለድ
✨ ዜና ቤተክርስቲያን
✨ዝማሬ በገና እና በክራር
ተጀምሯል ቮይስ ቻት ግቡ
ተጀምሯል ቮይስ ቻት ግቡ
ተጀምሯል ቮይስ ቻት ግቡ
✞🌹✟ቤተ ቅዱስ ሚካኤል በጎ አድርጎት መንፈሳዊ ማኅበር ✞🌹✟
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=ea270dff3c579ede21
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=ea270dff3c579ede21
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
በዓለ ኤዺፋንያ "በዓለ ጥምቀት "
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ዐሥራ አንድ በዚች ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአጥማቂው ዮሐንስ ዘንድ በዮርዳኖስ ወንዝ ውኃ ተጠመቀ።
ይችም ዕለት በዮናኒ ቋንቋ ኤጲፋንያ ትባላለች ትርጓሜውም መለኮት የተገለጠበት ማለት ነው።
ልዩ የሆነች የሦስትነቱን ምሥጢር ገልጦባታልና አብ ከሰማይሁኖ የምወደው በርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት እያለ ሲመሰክር ወልድም በዮርዳኖስ ወንዝ ቁሞ ሳለ መንፈስ ቅዱስም በነጭ ርግብ አምሳል በወልድ ራስ ላይ ሲቀመጥ ይህ አጥማቂው ዮሐንስ እንደመሰከረ።
እንዲህ ሲል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠምቆ ከውኃ በወጣ ጊዜ ወዲያኑ ሰማይ ተከፈተ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በጌታችን ራስ ላይ ተቀመጠ ከሰማይም እንዲህ የሚል ቃል መጣ ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ነው እርሱንም ስሙት።
በዚች እለት ጌታችን ራሱን ገልጦአልና ከዚህ በፊት ሰላሳ አመት ያህል ራሱን አልገለጠም ነበር ግን በዚች እለት ለእስራኤል ልጆች ራሱን ገለጠ እነሆ የእግዚአብሔር በግ የአለምን ኃጢአት የሚያስወግድ ብሎ መጥምቁ ዮሐንስ እንደገለጠው የከበረ ወንጌል ምስክር ሆነ።
እኔ አላውቀውም ነበር ነገር ግን እስራኤል ያውቁት ዘንድ በውኃ ላጠምቅ ስለዚህ መጣሁ አለ።
በዚህም በዓል የእግዚአብሔር ልጅ የክርስቶስ የጌትነቱ ክብር ተገልጧል እርሱም የአለሙን ሁሉ ኃጢአት ለማስወገድ የሚሠዋ የእግዚአብሔር አማናዊ በግ ነው።
ስለዚህም ይህ በዓል በክርስቲያን ወገኖች ሁሉ ዘንድ የከበረና ከፍ ከፍ ያለ ሆነ በርሱም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጥምቀቱ በአከበረው ውኃ ይነጹበታል የተቀበሉትንም ንጽሕና ጠብቀው ቢኖሩ በውስጡ የኃጢአታቸውን ሥርየት ያገኛሉ።
ስለዚህም ከክፉ ነገር ሁሉ ተጠብቀን የፈጣሪያችንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የቸርነቱን ብዛት ልናመሰግን ይገባናል እርሱ ስለ እኛ ሰው ሆኖ ከኃጢአታችን አድኖናልና።
ምንጭ፦
😇 "የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ📖 📖 🌟 ፥🌟 🌟
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧• ✧══╯
«ከተረ» ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ከበበ፣ ዙሪያውን ያዘ ማለት ነው:: ይኸውም ታቦተ ሕጉ በጳጳሳት፣ በሊቃውንት፣ በቀሳውስት፣ በዲያቆናት እንዲሁም በምእመናን ተከብቦ ታጅቦ መጓዙን የሚያመለክት ገላጭ ቃል ነው::
ዳግመኛም «ከተራ» ማለት ‹‹ከተረ›› ሰበሰበ፣ ዐጠረ ካለው ከግዕዝ ቃል የወጣ ሲሆን ይኸውም ምእመኑ ወራጁን ውኃ ሰብስበው ወይም ገድበው በየሰበካው ቦታ ተለይቶና ተከልሎ ታቦታቱ በዳስ/በድንኳን የሚያድሩበት የተለያዩ የውኃ አካላት ተጠርገው የሚከተሩበት ስለሆነ ነው:: ይህም ስፍራ ‹‹ባሕረ ጥምቀት - የታቦት ማደርያ›› እየተባለ ይጠራል:: የውኃ መሰብሰቢያ ማለት ነው፡፡
መቼ ተጀመረ?
የጥምቀት አከባበር በሀገራችን ታቦት ተሸክሞ ወንዝ ወርዶ የክርስቶስን በዓለ ጥምቀት ማክበር የተጀመረው በአባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ሲሆን ይበልጥ ተጠናክሮ በሜዳና በውኃ ዳር ማክበር የተጀመረው በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት (ከ፭፻፴ - ፭፻፵፬) እንደሆነ ይነገራል። ይኸውም ከቅዱስ ያሬድ (፭፻፭ - ፭፻፸፪) ዜማ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ታቦታቱ በየዓመቱ ጥር ፲፩ ቀን ጠዋት ወደ ወንዝ ወርደው ማታ ወደ መንበረ ክብራቸው እንዲመለሱ ይደረግ ነበር። ከዚህም በኋላ በቅዱስ ላልይበላ ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ምድር እየተመላለሱ በብሕትውናና በስብከተ ወንጌል ተግተው ያገለግሉ የነበሩ ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያ ክፍላተ ሀገር እየተዘዋወሩ ባሕረ ጥምቀቱን ባርከዋል:: ንጉሥ ላልይበላ (ከ፲፩፻፵-፲፩፻፹) ድረስ ሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ለየብቻቸው በተናጠል ሲፈጽሙት የነበረውን ክብረ በዓል አስቀርቶ በምትኩ በአንድ አካባቢ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት በአንድነት ተሰባስበው በአንድ ጥምቀተ ባሕር እንዲያከብሩ ትዕዛዝ አስተላልፏል:: ይህም ተግባራዊ በመሆኑ የበዓሉ አከባበር ሥነ ሥርዓት ቅንጅትና ድምቀት ባለው ሁኔታ እንዲከበር አድርገዋል::
በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት ከ፲፪፻፷ እስከ ፲፪፻፸፭ ዓ.ም ድረስ በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከ፲፪፻፫ እስከ ፲፫፻፬ ዓ.ም ድረስ አሳሳቢነት የተጀመረው ሥርዓተ በዓል ተጠናክሮ እንዲቀጥል በአዋጅ ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡ በመቀጠል ዐፄ ናኦድም የተማሩ ነበሩና በመጽሐፈ ኢያሱ:-
❝የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመው ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት❞
— ኢያ ፫፥፫ ተብሎ የተነገረውን ቃል ንጉሡ ጠንቅቀው የሚያውቁ በመሆናቸው ማንኛውም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ የሆነ ሁሉ ታቦተ ሕጉ ወደ ጥምቀተ ባሕሩ በሚወርድበት ጊዜና ከጥምቀተ ባሕር ወደ ቤተ መቅደሱ በሚመለስበት ጊዜ አጅቦ አውርዶና አጅቦ እንዲመለስ አዋጅ ነግረው በአዋጁ መሠረትም ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ታቦተ ሕጉን በማጀብ በሆታና በዕልልታ እንዲያከብር ተደርጓል::
በመንፈሳዊነታቸውና በደራሲነታቸው የሚታወቁ መጻሐፍትን በመጻፍ ሥርዓትን በመደንገግ ለቤተ ክርስቲያን ትልቅ ውለታ ያበረከቱ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ (፲፬፻፳፮ - ፲፬፻፷ ዓ.ም) ታቦታቱ ወደ ወንዝ ወርደው ዕለቱን እንዳይመለሱ፣ በዚያ ፈንታ በጥምቀት ዋዜማ ጥር ፲ ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርደው እንዲያድሩ ሀገሩን በኪደተ እግር ይባርኩም ዘንድ በሄዱበት መንገድ እንዳይመለሱ በአዋጅ ወሰኑ።
ሃይማኖታዊ ምሥጢሩ ምንድን ነው?
ታቦታተ ሕጉ በወጡበት ቦታ የማይመለሱበት ምክንያት ብዙ ምስጢር አለው። ይኸውም:-
፩.
❝ወተቀደሰት ምድር በኪደተ እግሩ — ምድር በኪደተ እግሩ ተቀደሰች
❞
— እንዳለ ሊቁ ያልተባረከ መሬት እንዲባረክ
፪. ዳግመኛም ያላየው እያየ ያልሰማው እየሰማ ሥርዐቱን አይቶ እንዲያምን ሃይማኖት እንዲሰፋ
፫. ነቢያት በመጡበት እንዳይመለሱ ሥርዓት ነበረና በዚያ ልማድ
፬. ሰብአ ሰገል ጌታን ካገኙ በኋላ በመጡበት ቦታ አልተመለሱምና የዚያ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦታቱም በሕዝብ ጥበቃና ክብካቤ ተደርጎላቸው በየጥምቀተ ባሕሩ እንዲያድሩ ወስነዋል:: አከባበሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ አድማሱም ብሔራዊነትን እየያዘ መጥቷል፡፡ ሕዝቡም ታቦታተ ሕጉን በሆታና በዕልልታ ከቤተመቅደስ አጅቦ ከወጣ በኋላ በባሕረ ጥምቀት ከትሞ ማደር ጀመረ:: ሊቃውንቱም እንዲሁ ለበዓሉ የሚስማማውን ቃለ እግዚአብሔር እያደረሱ ያድሩ ጀመር፡፡
የቃል ኪዳኑን ታቦት ይዞ አክብሮ ወደ ወንዝ መውረድ በብሉይ ኪዳን የነበረ ሥርዐት ነው። ኢያሱ በሙሴ ተተክቶ ሕዝበ እስራኤልን ሲመራ ታቦቱን አሸክሞ ሲሔድና ከዮርዳስ ወንዝ ሲደርስ ባሕሩ ከሁለት ይከፈልና ወራጁም ይቆም እንደነበረ ቅዱስ መጽሐፍ ይናገራል:: እስራኤል ወደ ምድረ ርስት ሲገቡ ታላቁን የዮርዳኖስ ወንዝ ሲሻገሩ ድንኳን ጥለው የቃል ኪዳን ታቦት ድንኳን ውስጥ አድርገው ሌዋውያኑ ዙሪያውን፣ ካህናቱ በውስጥ ሆነው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ እንደተሻገሩ ዛሬም እንደ ዮርዳኖስ ከድህነት ወደ ብልጽግና፣ ከደዌ ወደ ጤና፣ ከከህደት ወደ ሃይማኖት ከድንቁርና ወደ ዕውቀት አላሻግር ያለን ባሕረ ኀጢአት በቃል ኪዳኑ አማካኝነት በጥምቀቱ በረከት ያደርቅልናል (ኢያሱ ፩፥፲፫ ፤ ኢያሱ ፫፥፰)። ሐዋርያው ፊልጶስ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባውን ሊያጠምቀው ወደ ጋዛ ወንዝ የመውረዱ ምሳሌ ነው (ሐዋ ሥራ ፰፥፴፬)።
ዋናው ምሥጢሩ ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐንስን አስከትሎ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመሄዱ ምሳሌ ነው (ማቴ ፫፥፲)። ከጥንት ጀምሮ የቃል ኪዳኑን ታቦት ይዘን ወደ ወንዝ ወርደን በዓለ ጥምቀትን የምናከብረው ከዚህ ታሪክ በመነሣት ነው፡፡
ስለዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ጥር ፲ ቀን ተቀራራቢ የሆኑትን ታቦታትን በየአቅራቢያቸው ወደሚገኘው ወንዝ በአንድነት እያወረደች ከከተራ ዕለት ጀምሮ የጥምቀትን በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ሥርዐት ታከብራለች። ሌሊቱን ከሚያነጋው ሕዝበ ክርስቲያን ጋር በመሆን ያሬዳዊ ማሕሌትና የወንጌል ጉባኤ ተዘርግቶ በመምህራን ወቅታዊ ትምህርት ሲሰጥ ይታደራል ይዋላል፡፡ በበዓለ ጥምቀት ዋዜማ የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድና የባሕረ ጥምቀት መዘጋጀት የሚከተለው ሃይማኖታዊ ታሪክና ምሳሌ አለው::
ታቦቱ - የጌታችን
ታቦቱን አክብሮ የሚሄደው ካህን - የቅዱስ ዮሐንስ
ባሕረ ጥምቀቱ - የዮርዳኖስ ወንዝ
ታቦታቱን አጅበው የሚሄዱትና በዓሉን የሚያከብሩት ምእመናን - ወደ ቅዱስ ዮሐንስ እየመጡ የንስሐ ጥምቀት ሲጠመቁ የነበሩ ሰዎች ምሳሌዎች ናቸው።
ታቦታቱ በጥምቀት ዋዜማ ከመንበራቸው ወደ ጥምቀተ ባሕር መውረዳቸውና በዚያውም ማደራቸው - ጌታችን በእደ ዮሐንስ በፈለገ ዮርዳኖስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ከማታው ጀምሮ መውረዱንና ተሰልፎ ተራውን ሲጠብቅ ማደሩን ያጠይቃል::
ጥምቀት የሞቱ የመቃብሩ አምሳል ነው
ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናም፣ የበረዶ ወራት ነው። እንኳንስ ከወንዝ ዳር ከማናቸውም ቦታ ቢሆኑ ያለ መጠለያ መዋልና ማደር አይቻልም። ስለዚህ ከዮሐንስ ሊጠመቁ የሚሄዱ ሰዎች ሁሉ በዮርዳኖስ ዙሪያ ድንኳናቸውን ተክለው ያርፉ ነበር። ይህንን አብነት አድርገን ዛሬም በባሕረ ጥምቀት ዙሪያ በድንኳኖች የተከለሉ ዳሶች ይጣላሉ:: የከተራ በዓል ጥንት ከነገሥታቱ ጀምሮ የሀገር መሪዎች በቀዳሚነት ተሰልፈው የሚያከብሩት ብሔራዊ በዓል ከመሆኑ የተነሣ ሃይማኖታዊና ባህላዊ የአከባበር ሥርዐት አለው::
እንኳን አደረሰን!
ዲ/ን ኃይለራጉኤል
በዮርዳኖስ ተጠምቀ ፈጺሞ ሕገ ወአስተርአየ ገሃደ፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ
እግዚአብሔር ነግሠ፦
አስተርእዮ ኮነ ዘክርስቶስ ስነ መለኮት፤ ከመ ርግብ ውስተ ምጥማቃት፤ እንዘ ይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር።
ይትባረክ፦
ርእዩከ ማያት እግዚኦ፤ ርእዩከ ማያት ወፈርሑ፤ ደንገጹ ቀላያተ ማያት ማያቲሆሙ።
፫ት፦
አርአየነ ፈቃዶ በከመ ሥምረቱ ለአምላክነ፤ ወረደ ወተወልደ እምብእሲት፤ ወአንሶሰወ ዲበ ምድር፤ ወአስተርአየ ከመ ሰብእ፤ በበህቅ ልህቀ፤ በ፴ ክረምት በዮርዳኖስ ተጠምቀ።
ሰላም
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ
በሰላም አስተርአየ ወልደ አምላክ ፍጹም፤ ወተወልደ በሀገረ ዳዊት፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ ከመ ይቤዝወነ፤ ወልደ አምላክ ፍጹም አስተርአየ።
ክብር ይእቲ
ኲሎሙ ማኅበረ መላእክቲሁ፤ ይሴብሑ ወይዜምሩ ለዘበሥጋ ሰብእ አስተርአየ፤ ንዑ ንስግድ ሎቱ ሃሌ ሉያ።
ዝማሬ
ኅብስተ ሰማያዌ ወጽዋዓኒ ዘእማየ ሕይወት፤ ጠዓሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ።
ዕጣነ ሞገር
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወደሞ ክቡረ መንፈሰ ሕይወት ወቅድሳተ መንፈስ፤ ወሀበነ ማየ መንጽሔ ዚአነ።
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧• ✧══╯
በዚች ዕለት ምእመናን እስከ ምሽት እንዲጾሙት ያዘዙበት ምክንያቱ ይህ ነው፦የልደትና የጥምቀት በዓል በረብዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ኃምሳ የሚበላውን የጥሉላት መብል በጥዋት በመብላት ምእመናን ሁሉ በአሉን እንዲአከብሩ የከበሩ አባቶቻችን ሐዋርያት አዝዘዋል እሊህ ሁለቱ የእግዚአብሔር ታላላቅ በዓሎቹ ናቸውና።እኛ በዚህ በኃላፊው አለም ተድላ ደስታ ደስ የሚለን ለሌሎች እንዳይመስላቸው እንደ አይሁድና እንደ አረማውያን በዓል በመብልና በመጠጥ ብቻ እንዳናደርግ ስለዚህ ከልደትና ከጥምቀት በአል በዋዜማ ያሉትን ሁለቱን እለታት እንድንፆም አዘዙን የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ ላይ በሚሆን ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ እንድንጾማቸው ይገባልና በዚህም ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል የጾም ሥራና የበዓል ማክበር ሥራ ነው።
እንዲሁም በግብጻውያን አብያተ ክርስቲያን የተሠራ ነው
።
በይረሙን በእሑድ ወይም በአይሁድ ሰንበት ቀን ቢሆን ይህም ጌታ የተገለጸበት ጥር ዐሥር ቀን ነው በዋዜማው ዐርብ እስከ ምሽቱ ይጹሙ አስቀድመን እንደተናገርን ጥሉላት አይብሉ የልደትና የጥምቀት በዓልም ሰኞ ቀን ቢሆን በሰንበት ቀን ይጾሙ ዘንድ አይቻልም ነገር ግን ጥሉላትን ከመብላት ይጠበቁ።
በጥምቀትም እለት ከእኩለ ሌሊት በፊት ተነስተው በውኃው ላይ ይጸልዩና ይጠመቁ ሕፃናትም በሚጠመቁ ጊዜ በውኃ እንዳይገድፉ ካህናቱም ከመንጋቱ በፊት ቀድሰው ቁርባኑን ያሳርጉ እጅግም ማልደው በጥዋት ከቤተ ክርስቲያን ይውጡ በከበረ ሥርዓታቸው ጌቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘ
ዙ።
የመለካውያን ወገኖች ግን የልደትና የጥምቀት ዋዜማ በቅዳሜ ቀን ወይም በእሁድ ቀን ቢሆን በሶስት ሰዓት ይቀድሳሉ ከወደዱም የተባረከ ኅብስት ተመግበው ውኃ ይጠጣሉ ከዚህም በኋላ ካህናቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሁነው በየሰአቱ በመጸለይ ለበዓሉ የሚገባውን የነቢያትን ትንቢቶች ያነባሉ በዚያም ቀን በምሽት ይኸውም ጥርዓሥር ነው።
በውኃው ላይ ይጸልያሉ ይህም አባቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙት አልሆነም።
እርሳቸው የኤጲፋንያን በዓል እንዲአከብሩ አዘዋል ይኸውም መድኀኃኒታችን የተገለጠበት ካኑን በሚባል በሮም ሁለተኛ ወር በሰባት ይህም ጥር ዐሥራ አንድ ቀን ነው።
መለካውያን ግን የከበሩ አባቶች የቤተ ክርስቲያን መምህራን ያዘዙትን ይተላለፋሉ በልደትና በጥምቀት በዓል ዓርብም ረቡዕም ቢሆን አስቀድመው በርሱ ፈንታ ሳይጾሙ በጥዋት ተነሥሥተው ይበላሉና።
እኛንም ከበደላችን ያነጻን ዘንድ በዮረዳኖስም ወንዝ እንደ ገለጸ የጌትነቱን ክብር በልቡናችን ይገልጥልን ዘንድ የክብርባለቤት የሆነ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው ጌትነት ክብር ስግደት ለእርሱ ይገባልና።
ሙ አሜን።
#ምንጭ፦
😇 "የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
ምሳ📖 📖 🌟 ፥🌟 🌟
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧• ✧══╯
የዓለምን በደል የሠውን ግፍ አይቶ
ዘጠና ዘጠኙን መላእክቱን ትቶ
አገኘነው ዛሬ በበረት ተኝቶ
የሰላሙ መሪ የሰላሙ ዳኛ
አምላክ ተወለደ ተጠመቀ ለኛ/2/
አዝ
ልጁ በዮርዳኖስ ፅድቅን ሲመሠርት
መጣ በደመና ሰማያዊ አባት
እየመሰከረ የልጁን ጌትነት
የሰላሙ መሪ የሰላሙ ዳኛ
አምላክ ተወለደ ተጠመቀ ለኛ/2/
አዝ
ምድር ስትጨነቅ ተራራው ሲጨፍር
ሰማዩ ሲከፈት ደመናው ሲናገር
ዓለም በዛሬው ቀን አየች ልዩ ምሥጢር
የሰላሙ መሪ የሰላሙ ዳኛ
አምላክ ተወለደ ተጠመቀ ለኛ/2/
አዝ
ባህር ተጨነቀች ጠበባት መሬቱ
ዮርዳኖስም ሸሸ አልቆመም ከፊቱ
እንደ ተናገረው ዳዊት በትንቢቱ
የሰላሙ መሪ የሰላሙ ዳኛ
አምላክ ተወለደ ተጠመቀ ለኛ/2/
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧• ✧══╯
https://t.me/+T4nCtrKz_-DWg9aJ
https://t.me/+T4nCtrKz_-DWg9aJ
Reviews channel
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «Orthodox Tewahdo new» is a Telegram channel in the category «Образование», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 180K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 7.5, with 0 reviews and an average score of 0.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 9.6 ₽, and with 0 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий