
Get clients in any niche!
Delegate the launch of advertising to us — for free
Learn more
30.2

Advertising on the Telegram channel «እንማር»
5.0
11
Share
Add to favorite
Buy advertising in this channel
Placement Format:
keyboard_arrow_down
- 1/24
- 2/48
- 3/72
- Native
- 7 days
- Forwards
1 hour in the top / 24 hours in the feed
Quantity
%keyboard_arrow_down
- 1
- 2
- 3
- 4
- 5
- 8
- 10
- 15
Advertising publication cost
local_activity
$18.00$18.00local_mall
0.0%
Remaining at this price:0
Recent Channel Posts
✨✨ፍቅር ቅብ-16✨✨
ዮናስ ደጄን ከረገጠበት ቀን ጀምሮ መመንመን የጀመርኩ መሰለኝ.....ጉንጮቼ በሁለት ቀን የሰመጡ አጥንቶቼም የተንኮታኮቱ ...ፀጉሬ ሳልነካው ተነቅሎ ያለቀ አይኔም ያለመነፅር አሻፈረኝ የሚል መሰለኝ....ከበሽታ በላይ እርጅና ተሰማኝ....
ምግብ የሚባል እምቢ አለኝ....በትግል የበላሁትም ወዲያው ይወጣል....አኳሀኔ የታመመም....ያረገዘም.....ያረጀም ሰው አይነት ነበር.....
የመክብብ ጓደኛ ጋር መሄድ አልፈለግኩም....ምንም ቢሆን የመክብብ ጓደኛ ነው....ዛሬ እንደታማሚ በቅንነት ቢያነጋግረኝ ነገ ላይ የመክብብ የሆነ ነገር ሆኜ ቢያየኝ ጣቱን ለመቀሰር አንደኛ ነው.....
ምንም ባደርግ ሊለቀኝ ያልቻለው መክብብ ላይ ያለኝ ተስፋ ነው....እንዲህ ነው ብሎ አፍ አውጥቶ አልነገረኝ ነገር.....ፍቅር ይኑርበት ሀዘኔታ በውል አለየሁት ነገር....ነገ ኖረም አልኖረም ግን ውስጤ የሚጠነቀቅለት ብቸኛው ሰው ነው....
*****
"ከባለቤቴ ጋር ስንተዋወቅ ጀምሮ ቫይረሱ ነበረበት....አልነገረኝም.....እንኳን ይሄ ቫይረስ ጉንፋን አሞት የሚያውቅም አይመስልም ነበር....በጣም እንደሚወደኝ በአስር ጣቴ የምፈርምለት ሰው ነበር....ወደ አልጋ ሲገፋኝ በጄ አላልኩትም ነበር.....እንደሚወደኝ እና ከኔ ሌላ ማግባት እንደማይፈልግ ....ከኔ ሌላ ማንንም እንደማያልም እያለቀሰ ነገረኝ.....ትዝ ይለኛል አለቃቀሱ....ያሳሳ ነበር....ግን ስላለቀሰ አልነበረም ያመንኩት.....እንዲሁ ዝም ብዬ ነው ያመንኩት....
ከሱ ጋር በተኛሁ ማግስት ህዳር ሚካኤል ነበር......ሌላ ጊዜ ማህሌት አድሬ ቅዳሴን አስቀድሼ እስኪያልበኝ የምዘምረው ልጅ አዳሩን እስኪያልበኝ ባለግኩ.....
የሆነ አፋፍ ላይ ቆሜ በርቀት ታቦት ሸኘሁ.....በርቀት አለቀስኩበት....
ቀናት ወራትን ሲወልዱ በእንባ ተለምኜ የሰጠሁትን ገና ሲጠጋኝ ማቀበል ጀመርኩ....ሀጥያት ሲለመድ ፅድቅ ይመስላል...ማፈር ስናቆም ውድቀታችን "ሀ" ብሎ ይጀምራል.....
"ሀ" አልኩኝ....
ልክ ያልሆነ ስራ እየሰራሽ የሚሰማሽ ልክነት ካለ አእምሮሽ ሚዛኑን እየሳተ ነው.....የሰው ልጅ ይለምዳል.....ደግነትንም ክፋትንም....ሀጥያትንም ፅድቅንም....ጉብዝናንም ስንፍናንም.....መልበስንም መራቆትንም....ማግኘትንም ማጣትንም.....ቤተ እምነቱንም ክለቡንም.....ሁሉንም ይለምዳል.....
ጭንቅላት ሞኝም ብልጥም ነው....ያስብልሻልም አያስብልሽምም......ያስለመድሽውን ይለምዳል.....ስታስቀሪበት እንደራበው ህፃን ልጅ ያጣድፍሻል.....ጭንቅላት ባለጌም ጨዋም ነው.....ሁሉንም ይለምዳል.....ጭንቅላት የልብ ወዳጅ ነው አይገምትሽም.....ጭንቅላት ከአባት ገዳይ የከፋ ጨካኝም ነው.....ሲበቃው በቃው ነው።
ባለቤቴ እንክርዳድ የሌለበት ስንዴ ነበረ....የተለቀመ ስንዴ.....እንዲህ ነው ብለሽ እንከን የማታወጪለት አይነት ሰው.....
ከሰጠኝ በሽታ በላይ የሄደበት መንገድ አቆሰለኝ....የሞኝ ውሳኔ ቢሆንም ቫይረሱ እንዳለበት ቢነግረኝ እንደማልተወው ነው የምነግርሽ.....ይሄ ለኔ ልክ ያልሆነ ልክነት ነው.....አልተወውም ነበር....የሄደበት አቋራጭ መንገድ ግን እኔን በአካል ሰጥቶ በመንፈስ ነጠቀው......
ምክንያቱ "እወድሻለሁ" ነበር....ውስጠ ምስጢሩ ጎን ራስ ወዳድነት ነበር....አይገርምም ሁሉም ለራሱ ነው....ሲወድሽ እራሱ ለራሱ ነው....ላንቺ ብሎ የሚወድሽ አምላክሽ ብቻ ነው።
በሽታውን ሲሰጠኝ አስቦበት እንደነበር ሲነግረኝ አላፈረም....ምናል ባይነግረኝ.....ሁሉም መነገር የለበትም አይደል.....ምናል ድንገት ስሜታዊ ሆኜ ምናምን ቢለኝ....."ይሄን በሽታ ካሲያዝኳት ጥላኝ አትሄድም ብዬ ነው ያደረግኩት....ደሞም ልክ ነበርኩ አልሄድሽም.....".....ነበር ያለኝ.....ሞኝ ሆኖ እንጂ ሄጃለሁ....".....አለችኝ እና መጣሁ ያለ እንባዋን በአውራ ጣቷ ወደጎን አሽቀነጠረችው......ልመረመር ከሄድኩበት ክሊኒክ ህመምተኛ መቀበያ ወንበር ላይ የተቀመጠች ጎልማሳ ሴት ታሪክ ነው.....
"ሰው ሲከፋው ከድንጋይ ጋርም ያወራል...."....አለችኝ በትኩረት እያየችኝ.....መገረሜ በታሪኳ ብቻ ሳይሆን እንዴት ዘርግፋ ነገረችኝ በሚለውም ስለነበር ማስተዋሏ ገረመኝ።
ከሰፈር በጣም ርቄ የሄድኩበት ክሊኒክ ነው....ከሰፈር መራቄ ሀፍረቴን የሚቀንስልኝ መስሎኝ ነበር....አልቀነሰም።
"እድል ሰጠኝ....."......ስሜ ከውስጥ ተጠራ.....
እንደስሜ እድል እንዲሰጠኝ እየተመኘሁ ወደውስጥ ዘለቅኩ።
ከዶክተሩ ጋር አንድ አንድ አንድ ነገር ተነጋገርንና ሌላም ምርመራ ጨምሮ ወደ ላብራቶሪ ክፍል ላከኝ....
ላብራትሪስቷ ደሜን ቀዳች......የገላመጠችኝ መሰለኝ.....ለነገሩ በሶስት ታክሲ ስመጣ ሶስተኛው ታክሲ ውስጥ ጋቢና የተቀመጠው ሰውዬ ራሱ አስተያየቱ ስራዬን እንደሚያውቅ ነገር ነው....ከታክሲ ስወርድ ያየኃቸው አሮጊት አይነ ውሀቸው አላማረኝም....የክልኒኳ ፅዳት ሰራተኛ በምታፀዳው መሬት ፈንታ እኔን ብታፀዳኝ ደስ እንደሚላት አይኗ ነግሮኛል....ዶክተሩም ስራ ሆኖበት ነው.....
አባዬ ደወለ....ባነሳው "አንቺ ባለጌ...." የሚለኝ መሰለኝ....አላነሳሁትም....
የራሴን ስሜት ሰው ሁሉ ላይ እያየሁት ስሸበር ወጣ ብዬ ተነፈስኩ...."ተረጋጊ እድል ማንም አያውቅም ተረጋጊ.....".....አልኩኝና የቅድሟን ሴትዮ ጥዬ ወደመጣሁበት ወንበር አመራሁ.....የለችም።
ተመልሼ ወጥቼ ሰማዩ ላይ አፈጠጥኩበት.....ደመና ነበር....ወደላይ አንጋጥጬ "አደራህን አምላኬ አደራህን" አልኩት.....
ዮናስ ደጄን ከረገጠበት ቀን ጀምሮ መመንመን የጀመርኩ መሰለኝ.....ጉንጮቼ በሁለት ቀን የሰመጡ አጥንቶቼም የተንኮታኮቱ ...ፀጉሬ ሳልነካው ተነቅሎ ያለቀ አይኔም ያለመነፅር አሻፈረኝ የሚል መሰለኝ....ከበሽታ በላይ እርጅና ተሰማኝ....
ምግብ የሚባል እምቢ አለኝ....በትግል የበላሁትም ወዲያው ይወጣል....አኳሀኔ የታመመም....ያረገዘም.....ያረጀም ሰው አይነት ነበር.....
የመክብብ ጓደኛ ጋር መሄድ አልፈለግኩም....ምንም ቢሆን የመክብብ ጓደኛ ነው....ዛሬ እንደታማሚ በቅንነት ቢያነጋግረኝ ነገ ላይ የመክብብ የሆነ ነገር ሆኜ ቢያየኝ ጣቱን ለመቀሰር አንደኛ ነው.....
ምንም ባደርግ ሊለቀኝ ያልቻለው መክብብ ላይ ያለኝ ተስፋ ነው....እንዲህ ነው ብሎ አፍ አውጥቶ አልነገረኝ ነገር.....ፍቅር ይኑርበት ሀዘኔታ በውል አለየሁት ነገር....ነገ ኖረም አልኖረም ግን ውስጤ የሚጠነቀቅለት ብቸኛው ሰው ነው....
*****
"ከባለቤቴ ጋር ስንተዋወቅ ጀምሮ ቫይረሱ ነበረበት....አልነገረኝም.....እንኳን ይሄ ቫይረስ ጉንፋን አሞት የሚያውቅም አይመስልም ነበር....በጣም እንደሚወደኝ በአስር ጣቴ የምፈርምለት ሰው ነበር....ወደ አልጋ ሲገፋኝ በጄ አላልኩትም ነበር.....እንደሚወደኝ እና ከኔ ሌላ ማግባት እንደማይፈልግ ....ከኔ ሌላ ማንንም እንደማያልም እያለቀሰ ነገረኝ.....ትዝ ይለኛል አለቃቀሱ....ያሳሳ ነበር....ግን ስላለቀሰ አልነበረም ያመንኩት.....እንዲሁ ዝም ብዬ ነው ያመንኩት....
ከሱ ጋር በተኛሁ ማግስት ህዳር ሚካኤል ነበር......ሌላ ጊዜ ማህሌት አድሬ ቅዳሴን አስቀድሼ እስኪያልበኝ የምዘምረው ልጅ አዳሩን እስኪያልበኝ ባለግኩ.....
የሆነ አፋፍ ላይ ቆሜ በርቀት ታቦት ሸኘሁ.....በርቀት አለቀስኩበት....
ቀናት ወራትን ሲወልዱ በእንባ ተለምኜ የሰጠሁትን ገና ሲጠጋኝ ማቀበል ጀመርኩ....ሀጥያት ሲለመድ ፅድቅ ይመስላል...ማፈር ስናቆም ውድቀታችን "ሀ" ብሎ ይጀምራል.....
"ሀ" አልኩኝ....
ልክ ያልሆነ ስራ እየሰራሽ የሚሰማሽ ልክነት ካለ አእምሮሽ ሚዛኑን እየሳተ ነው.....የሰው ልጅ ይለምዳል.....ደግነትንም ክፋትንም....ሀጥያትንም ፅድቅንም....ጉብዝናንም ስንፍናንም.....መልበስንም መራቆትንም....ማግኘትንም ማጣትንም.....ቤተ እምነቱንም ክለቡንም.....ሁሉንም ይለምዳል.....
ጭንቅላት ሞኝም ብልጥም ነው....ያስብልሻልም አያስብልሽምም......ያስለመድሽውን ይለምዳል.....ስታስቀሪበት እንደራበው ህፃን ልጅ ያጣድፍሻል.....ጭንቅላት ባለጌም ጨዋም ነው.....ሁሉንም ይለምዳል.....ጭንቅላት የልብ ወዳጅ ነው አይገምትሽም.....ጭንቅላት ከአባት ገዳይ የከፋ ጨካኝም ነው.....ሲበቃው በቃው ነው።
ባለቤቴ እንክርዳድ የሌለበት ስንዴ ነበረ....የተለቀመ ስንዴ.....እንዲህ ነው ብለሽ እንከን የማታወጪለት አይነት ሰው.....
ከሰጠኝ በሽታ በላይ የሄደበት መንገድ አቆሰለኝ....የሞኝ ውሳኔ ቢሆንም ቫይረሱ እንዳለበት ቢነግረኝ እንደማልተወው ነው የምነግርሽ.....ይሄ ለኔ ልክ ያልሆነ ልክነት ነው.....አልተወውም ነበር....የሄደበት አቋራጭ መንገድ ግን እኔን በአካል ሰጥቶ በመንፈስ ነጠቀው......
ምክንያቱ "እወድሻለሁ" ነበር....ውስጠ ምስጢሩ ጎን ራስ ወዳድነት ነበር....አይገርምም ሁሉም ለራሱ ነው....ሲወድሽ እራሱ ለራሱ ነው....ላንቺ ብሎ የሚወድሽ አምላክሽ ብቻ ነው።
በሽታውን ሲሰጠኝ አስቦበት እንደነበር ሲነግረኝ አላፈረም....ምናል ባይነግረኝ.....ሁሉም መነገር የለበትም አይደል.....ምናል ድንገት ስሜታዊ ሆኜ ምናምን ቢለኝ....."ይሄን በሽታ ካሲያዝኳት ጥላኝ አትሄድም ብዬ ነው ያደረግኩት....ደሞም ልክ ነበርኩ አልሄድሽም.....".....ነበር ያለኝ.....ሞኝ ሆኖ እንጂ ሄጃለሁ....".....አለችኝ እና መጣሁ ያለ እንባዋን በአውራ ጣቷ ወደጎን አሽቀነጠረችው......ልመረመር ከሄድኩበት ክሊኒክ ህመምተኛ መቀበያ ወንበር ላይ የተቀመጠች ጎልማሳ ሴት ታሪክ ነው.....
"ሰው ሲከፋው ከድንጋይ ጋርም ያወራል...."....አለችኝ በትኩረት እያየችኝ.....መገረሜ በታሪኳ ብቻ ሳይሆን እንዴት ዘርግፋ ነገረችኝ በሚለውም ስለነበር ማስተዋሏ ገረመኝ።
ከሰፈር በጣም ርቄ የሄድኩበት ክሊኒክ ነው....ከሰፈር መራቄ ሀፍረቴን የሚቀንስልኝ መስሎኝ ነበር....አልቀነሰም።
"እድል ሰጠኝ....."......ስሜ ከውስጥ ተጠራ.....
እንደስሜ እድል እንዲሰጠኝ እየተመኘሁ ወደውስጥ ዘለቅኩ።
ከዶክተሩ ጋር አንድ አንድ አንድ ነገር ተነጋገርንና ሌላም ምርመራ ጨምሮ ወደ ላብራቶሪ ክፍል ላከኝ....
ላብራትሪስቷ ደሜን ቀዳች......የገላመጠችኝ መሰለኝ.....ለነገሩ በሶስት ታክሲ ስመጣ ሶስተኛው ታክሲ ውስጥ ጋቢና የተቀመጠው ሰውዬ ራሱ አስተያየቱ ስራዬን እንደሚያውቅ ነገር ነው....ከታክሲ ስወርድ ያየኃቸው አሮጊት አይነ ውሀቸው አላማረኝም....የክልኒኳ ፅዳት ሰራተኛ በምታፀዳው መሬት ፈንታ እኔን ብታፀዳኝ ደስ እንደሚላት አይኗ ነግሮኛል....ዶክተሩም ስራ ሆኖበት ነው.....
አባዬ ደወለ....ባነሳው "አንቺ ባለጌ...." የሚለኝ መሰለኝ....አላነሳሁትም....
የራሴን ስሜት ሰው ሁሉ ላይ እያየሁት ስሸበር ወጣ ብዬ ተነፈስኩ...."ተረጋጊ እድል ማንም አያውቅም ተረጋጊ.....".....አልኩኝና የቅድሟን ሴትዮ ጥዬ ወደመጣሁበት ወንበር አመራሁ.....የለችም።
ተመልሼ ወጥቼ ሰማዩ ላይ አፈጠጥኩበት.....ደመና ነበር....ወደላይ አንጋጥጬ "አደራህን አምላኬ አደራህን" አልኩት.....
2700
19:34
05.05.2025
⚡️ ከሌላው ምን ይለየናል
👉 ባሉበት ሆነው ባመችዎት ሰዐት መከታተል የሚችሉት ስልጠና።
👉 ያለ አስተማሪ በራስዎት ፍጥነት መውሰድ የሚችሉበት አማራጭ ያካተተ።
👉ሙሉ በሙሉ በተግባር የሚሰጥ መሆኑ።
👉 ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ ከ ፕሮፌሽናል ሰርተፍኬት በተጨማሪ portfolio website የሚኖርዎት መሆኑ።
⚡️ ስልጠናው ምን ምን ያካትታል ?
💥 Graphics design with Canva basics
💥International payment cards
💥Shopify and WordPress website development
💥Upwork
⚡️ ስልጠናው በምን ያክል ጊዜ ይጠናቀቃል ?
With instructor:- በ 1 ወር
self-paced :- depending on your pace from 1 week to 4 weeks.
ሰልጥነው እንደጨረሱ፦
🔥Professional Certificate እና
🖥 ሰልጣኞች የሰሯቸዉን ስራዎች የሚያሳዩበት portfolio website
🌼 ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ቀድመው ይመዝገቡ!
🔗 ለበለጠ መረጃ:
➡️ Customer Support
አድራሻ:- 22 ማዞሪያ KW ህንፃ 1ኛ ፎቅ
✨ Umi technilogies ✨
Website | Telegram | Linkdin | Telegram bot
4400
14:14
05.05.2025
👇English Grammar Rule Quiz 👇
Every sentence must have a subject and___.
Every sentence must have a subject and___.
1600
13:23
05.05.2025
imageImage preview is unavailable
የእድሜያችን ጉዳይ!
(“ምርጫና ውሳኔ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ ውስጥ የተወሰደ ታሪክ)
☑️ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቴን በጀመርኩባት በመጀመሪያዋ ቀን ፕሮፌሰራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ራሱን ካስተዋወቀ በኋላ፣ እኛም በተራችን ሁላችንም እርስ በርሳችን እንድንተዋወቅ አበረታታን፡፡ ከወንበሬ ተነስቼ የምተዋወቀውን ሰው ለመፈለግ ወዲህና ወዲያ በማለት ቃኘት ሳደርግ ከጀርባዬ አንድ እጅ በስሱ ዳበስ አደረገኝ፡፡ ማን እንደነካኝ ለማየት ዘወር ስል ከፈገግታዋ የተነሳ ሁለንተናዋ የሚያበራ አንዲት ፊቷ እጅጉን የተጨማደደ በእድሜ የገፋች ሴት ነች፡፡
☑️ “ መልከ መልካም ሆይ፣ እንዴት ነህ? ስሜ ሮዝ ይባላል፡፡ የሰማንያ ሰባት አመት ሴት ነኝ፡፡ እቅፍ አድርጌ ሰላም ልልህ እችላለሁ?” በማለት ያልጠበኩትን ሰላምታ አቀረበችልኝ፡፡
☑️ ፈገግ ካልኩኝ በኋላ በታላቅ ጉጉት፣ “በሚገባ” አልኳት፡፡ እቅፍ አድርጋ ሰላም ካለችኝ በኋላ ጊዜ ሳላባክን አንድ ጥያቄ አቀረብኩላት፡፡
“ለምንድን ነው በዚህ ለጋና የዋህ እድሜሽ ዩኒቨርሲቲ ለመማር የመጣሽው?” በማለት ቀለድኳት፡፡
እርሷም በቀልድ፣ “እዚህ የመጣሁት ሃብታም ባል ባገኝ ላገባውና ሁለት ልጆች ለመውለድ ነው” አለችኝ፡፡
“እየቀለድኩኝ እኮ አይደለም” አልኳት፣ በዚህ እድሜዋ ለትምህርት ያነሳሳት ምን እንደሆነ ለማወቅ ፍላጎት ስላደረብኝ፡፡
“ሁል ጊዜ የኮሌጅ ዲግሪ እንዲኖረኝ ሕልሙ ነበረኝ፣ አሁን ጊዜው ደርሶ ይኸው ዲግሪዬን ልይዝ ነው” አለችኝ፡፡
☑️ ክፍለ ጊዜው ካለቀ በኋላ ወደ ተማሪዎች መዝናኛው ሕንጻው አቅጣጫ በቀስታ እየተራመድን የሚጠጣ ነገር ተገባበዝን፡፡ ለሚቀጥሉት ሶስት ወራት ከትምህርት ሰዓት በኋላ አብረን በማሳለፍ እንነጋገር ነበር፡፡ በእነዚህ ጊዜያት ያካፈለችኝ በእድሜ ያገኘችው ጥበብና ልምምዷ እጅግ አስገራሚ ነበር፡፡
በቀጣዮቹ አመታት ሮዝ የትምህርት ቤቱ ታዋቂ ሴት ወደ መሆን መጣች፡፡ በሄደችበት ቦታ ሁሉ በቀላሉ ወዳጆችን ታፈራ ነበር፡፡ ዝንጥ ብላ መልበስን ታዘወትር ነበር፡፡ ሴሚስተሩ መጨረሻ ላይ በነበረን የኳስ ጨዋታ ግብዣ ላይ ንግግር እንድታደርግ ጋበዝናት፡፡ ወደ መድረኩ ተጋብዛ ንግግር ስታደርግ ያስተማረችንን በፍጹም አልዘነጋውም፡፡
“መጫወት የምናቆመው በእድሜ ስላረጀን አይደለም፣ መጫወት ስላቆምን ነው የምናረጀው፡፡ ደስተኞችና ስኬታማዎች መሆን ከፈለጋችሁ፣ ምስጢራቱ ግልጽ ናቸው፡፡ በየቀኑ የሚያስቅ ነገር ፈልጋችሁ ማግኘት አለባችሁ፡፡ የምትከታተሉት ሕልም ሊኖራችሁ ይገባል፣ ምክንያቱም ሕልማችሁን ስታጡ ትሞታላችሁ፡፡ በዙሪያችን በርካታ ሰዎች ሞተው እንኳን እንደሞቱ አልገባቸውም፡፡ በማርጀትና በማደግ መካከል ትልቅ ልዩነት አለ፡፡ የአስራ ዘጠኝ አመት ወጣት ሆነህ አመቱን ሙሉ ምንም ሳትሰራ በአልጋ ላይ ካሳለፍክ ሃያ አመት ወደ መሆን መምጣትህ አይቀርም፡፡ እኔ ደግሞ ሰማንያ ሰባት ዓመቴ ሆኖ አመቱን ሙሉ በአልጋዬ ላይ ባሳልፍ፣ ሰማንያ ስምንት ወደመሆን መምጣቴ አይቀርም፡፡
በአድሜ መግፋት ለሁሉም የተሰጠ እውነታ ነው፡፡ እድሜን መቁጠር ምንም አይነት ልዩ ስጦታና ችሎታ አይጠይቅም፡፡ ለማለት የፈለኩት በሚከናወኑት የሕይወት ለውጦች ውስጥ ሁሉ ያለንን እድል በመጠቀም ማደግ ይኖርብናል ነው፡፡ እኛ በእድሜ የገፋን ሰዎች ያለፈውን ሕይወታችንን አስመልክቶ በአብዛኛው የሚኖርብን ጸጸት ስላደረግናቸው ነገሮች ሳይሆን ስላላደረግናቸው ነገሮች ነው፡፡ ማርጀትንና መሞትን የሚፈሩ ሰዎች ብዙ ጸጸት ያለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡
በዲግሪ በተመረቀች በአንድ ሳምንት ውስጥ ሮዝ በሰላም ከዚህ አለም ተሰናበተች፡፡ በቀብር ስነስርአቷ ላይ የተገኘን ተማሪዎች በሙሉ፣ መሆንና ማድረግ የምንፈልገው ደረጃ ለመድረስ ከፈለግን በማንኛውም ጊዜ ያንን ማድረግ እንደምንችል ስናስታውስ ዋልን፡፡
ዶክተር እዮብ ማሞ
➡️ @Enmare1988
➡️ @Enmare1988
➡️ @Enmare1988
(“ምርጫና ውሳኔ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ ውስጥ የተወሰደ ታሪክ)
“ለምንድን ነው በዚህ ለጋና የዋህ እድሜሽ ዩኒቨርሲቲ ለመማር የመጣሽው?” በማለት ቀለድኳት፡፡
እርሷም በቀልድ፣ “እዚህ የመጣሁት ሃብታም ባል ባገኝ ላገባውና ሁለት ልጆች ለመውለድ ነው” አለችኝ፡፡
“እየቀለድኩኝ እኮ አይደለም” አልኳት፣ በዚህ እድሜዋ ለትምህርት ያነሳሳት ምን እንደሆነ ለማወቅ ፍላጎት ስላደረብኝ፡፡
“ሁል ጊዜ የኮሌጅ ዲግሪ እንዲኖረኝ ሕልሙ ነበረኝ፣ አሁን ጊዜው ደርሶ ይኸው ዲግሪዬን ልይዝ ነው” አለችኝ፡፡
በቀጣዮቹ አመታት ሮዝ የትምህርት ቤቱ ታዋቂ ሴት ወደ መሆን መጣች፡፡ በሄደችበት ቦታ ሁሉ በቀላሉ ወዳጆችን ታፈራ ነበር፡፡ ዝንጥ ብላ መልበስን ታዘወትር ነበር፡፡ ሴሚስተሩ መጨረሻ ላይ በነበረን የኳስ ጨዋታ ግብዣ ላይ ንግግር እንድታደርግ ጋበዝናት፡፡ ወደ መድረኩ ተጋብዛ ንግግር ስታደርግ ያስተማረችንን በፍጹም አልዘነጋውም፡፡
“መጫወት የምናቆመው በእድሜ ስላረጀን አይደለም፣ መጫወት ስላቆምን ነው የምናረጀው፡፡ ደስተኞችና ስኬታማዎች መሆን ከፈለጋችሁ፣ ምስጢራቱ ግልጽ ናቸው፡፡ በየቀኑ የሚያስቅ ነገር ፈልጋችሁ ማግኘት አለባችሁ፡፡ የምትከታተሉት ሕልም ሊኖራችሁ ይገባል፣ ምክንያቱም ሕልማችሁን ስታጡ ትሞታላችሁ፡፡ በዙሪያችን በርካታ ሰዎች ሞተው እንኳን እንደሞቱ አልገባቸውም፡፡ በማርጀትና በማደግ መካከል ትልቅ ልዩነት አለ፡፡ የአስራ ዘጠኝ አመት ወጣት ሆነህ አመቱን ሙሉ ምንም ሳትሰራ በአልጋ ላይ ካሳለፍክ ሃያ አመት ወደ መሆን መምጣትህ አይቀርም፡፡ እኔ ደግሞ ሰማንያ ሰባት ዓመቴ ሆኖ አመቱን ሙሉ በአልጋዬ ላይ ባሳልፍ፣ ሰማንያ ስምንት ወደመሆን መምጣቴ አይቀርም፡፡
በአድሜ መግፋት ለሁሉም የተሰጠ እውነታ ነው፡፡ እድሜን መቁጠር ምንም አይነት ልዩ ስጦታና ችሎታ አይጠይቅም፡፡ ለማለት የፈለኩት በሚከናወኑት የሕይወት ለውጦች ውስጥ ሁሉ ያለንን እድል በመጠቀም ማደግ ይኖርብናል ነው፡፡ እኛ በእድሜ የገፋን ሰዎች ያለፈውን ሕይወታችንን አስመልክቶ በአብዛኛው የሚኖርብን ጸጸት ስላደረግናቸው ነገሮች ሳይሆን ስላላደረግናቸው ነገሮች ነው፡፡ ማርጀትንና መሞትን የሚፈሩ ሰዎች ብዙ ጸጸት ያለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡
በዲግሪ በተመረቀች በአንድ ሳምንት ውስጥ ሮዝ በሰላም ከዚህ አለም ተሰናበተች፡፡ በቀብር ስነስርአቷ ላይ የተገኘን ተማሪዎች በሙሉ፣ መሆንና ማድረግ የምንፈልገው ደረጃ ለመድረስ ከፈለግን በማንኛውም ጊዜ ያንን ማድረግ እንደምንችል ስናስታውስ ዋልን፡፡
ዶክተር እዮብ ማሞ
5100
10:47
05.05.2025
imageImage preview is unavailable
Ads
😌 😌 ዛሬ ማታ ትልቅ GIVEAWAY አለ የSTAR, የTON ወይም ብር የምንሸልም ይሆናል ማንም እንዳይቀር ✌️ FAMILY😌 😌
#Ads
GIVEAWAY ላይ ለመሳተፍ በቅድሚያ የዚህን CHANNEL JOIN ማለት አለባችሁ😏 @UNIQUECRYPTO_24l7😮
GIVEAWAY?🤝 @UNIQUECRYPTO_24l7 👈 JOIN HERE
#Ads
GIVEAWAY ላይ ለመሳተፍ በቅድሚያ የዚህን CHANNEL JOIN ማለት አለባችሁ
GIVEAWAY?
5000
08:50
05.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-15✨✨
"በሁለተኛ እድል ታምናለህ....."......አልኩት መክብብን ምሳ የምንበላበት ሬስቶራንት ተቀምጠን....
"እንደ ሁኔታው ይለያያል...."....አለኝና ለአፌ መጥኖ አጎረሰኝ.....ቀጥሎም "እየበላሽ አይደለም ምን ሆነሻል....."....አለኝ።
"ምንም አልሆንኩም....".....አልኩትና ያጎረሰኝን ውጬ እጄ ላይ ሳድበለብል የቆየሁትንም ደገምኩና እየበላሁ መሆኔን አስመሰከርኩ....
"ኧረ....ረ እንዲህ ከሆነማ ሁሌ ነው ምጋብዝሽ....አበላልሽ ኪስ አይጎዳም...."....አለና ያን ምትሀት ጥርሱን ገለጥ አደረገው።
"ስለ ሁለተኛ እድል እያወራሁህ ነበር.....".....አልኩት ለማስታወስ ያህል....
"ያው ሁለተኛ እድል እንደቦታው እና እንደሁኔታው ይለያያል....ለምሳሌ አንድ ነብስ ያጠፋ ወንጀለኛ...."....ከማለቱ አቋርጬው ከፍርድ ቤት ህግና መሰል ነገሮች የወጣ መልስ እንደምፈልግ ነገርኩት....
"specific አርጊልኛ.....እንዲሁ ሁለተኛ እድል የሚባል ነገር የለም እኮ እድሌ....."....አለኝ....እድሌ ስላለኝ ልቤ ሰላሳ ሁለት ጥርሱን አሳየ....ቢሆንም ግን ዮናስ የነገረኝን ነገር ሳስታውስ መክብብን ከሩቅ የማየው እንጂ የማልዳስሰው.....የማልነካው የእኔ የማልለው 'የማይበላ ወፍ' እንደሆነ ትዝ አለኝ።
"ስለ HIV አስበህ ታውቃለህ....."......አልኩት ድንገት....እንዳልኩት ያወቅኩት ካልኩት በኃላ ነበር።
"እኔንጃ ያው በሽታ ነው....ግን እንዴት አስበዋለሁ....አንዳንዴ በዙሪያሽ ያለ ሰው ሲታመም ነው በሽታውን የምታስተውይው አልያም 'በሽታ' የሚባል ነገር መኖሩን የምታስታውሽው እና እንደሚሞት ሰው የምትኖሪው....".....አለኝና አንድ ጉርሻ ደገመኝ።
"የሚሞት ሰው እንዴት ነው ሚኖረው...."....አልኩት አጣድፌ ጉርሻውን ከዋጥኩ በኃላ.....
"በርግጥ ሁላችንም ሟቾች ነን....ነገር ግን እንደሚሞት ሰው የሚኖረው በቁጥር ነው....ብዙ ሰው ግን እንደሚሞት የሚያስታውሰው ሲታመም ነው....እንደምትሞቺ ስታስቢ ለነገ የምታስቀምጪው ደስታ የለም....'ነገ' የምትይው ስራም ምግብም አይኖርም....እንደምትሞቺ ስታስቢ ነው መግቢያሽ የሚያሳስብሽ....የመጨረሻዎቹ ደይቃዎች ላይ ነው የነብስሽን ድምፅ የምትሰሚው....."
"ማን ታሞ ነው....?....."....አለኝ ቀጠል አድርጎ......"እኔ" አይባል ነገር ሆኖብኝ "አንድ ጓደኛዬ ታማ ነው..."....አልኩት....
"እንዴት ያዛት....".....ሲለኝ ደነገጥኩ....
"እንዴት ይይዛታል....እንደተለመደው ነዋ.... ትንሽ ስህተት ነበር ከፍቅር ጓደኛዋ ተጋብቶባት...."....አልኩትና ፊት ለፊቴ ያለውን ውሀ ባንድ ትንፋሽ ጨለጥኩት....
"ትንሽ ስህተት እንኳን አይደለም....ህይወት የሚያስከፍል 'ትንሽ' የለም....እንዴት ብዬ የጠየቅኩሽም እንዳልተለመደውም የሚታመሙ ሰዎች ስላሉ ነው....."
"ማለት....."...
"በደም ንክኪ..."....ሲለኝ የኢለመንተሪ ተማሪ የሆኖኩ መሰለኝ....ትንሽ ቆይቶ ስለ ሶስቱ የ'መ' ህጎች ሊያስተምረኝም ይችላል....እኔ ጭንቀቴ እንጂ እንዲህ የሚያስለፈልፈኝ ከመክብብ ጋር ሲጀመር ስለ በሽታ አይወራም....ከሱ ጋር መወራት ያለበት ስለ እሱ ብቻ ነበር....ስለ እሱ ውበት....ስለ ጥርሶቹ....ስለ አይኖቹ....ነፍስ ድረስ ስለሚሰማው ስለሚያረሰርሰው ድምፁ....ስለ መዳፎቹ....በቃ መወራት ያለበት ይሄ ነው.....
ድሮ ድሮ መልክ የበዛበት ወንድ አልወድም ነበር....ጭንቅላቴ ምን ሲል ይሄን መልክ የተትረፈረፈለት ወንድ እንደከጀለ አላውቅም.....
ከዮናስ የሰማሁትን ሰምቼ አልቅሼ አልወጣልኝም....አልወጣልኝም....እዚህ ከመክብብ ጋር ቁጭ ብሎ ምሳ ለመብላት ምን ያሀል እንደታገልኩኝ የማውቀው እኔ ነኝ....ስሜቱን ይሄ ነው ብዬ የምገልፀው አይነት አይደለም....
"ስለ HIV እናውራ...."....አልኩት ስለዩንቨርሲቲ ቆይታው ሲያጫውተኝ...ፊቱ ላይ ግርታ አነበብኩ።
"በጣም ተጨንቀሻል በጓደኛሽ ጉዳይ...."....ሲለኝ በአዎንታ አንገቴን ነቀነቅኩለት...
"ቆይ ሀኒም ታውቃታለች...."....ሲለኝ "ቀላል" ልለው ከአፌ ነው የመለስኩት.....
"አይ አታውቃትም....."..
"አንድ ዶክተር ጓደኛ አለኝ....ስልኩን እሰጥሽና መጠየቅ የምትፈልጊውን ጠይቂው...."
"..በርግጥ በጣም rare ኬዝ ነው....normally ግን በዚህ ፍጥነት ይሄን ያሀል weight loss አታደርግም...." የሚለኝ የደወልኩለት ዶክተር ነው.....'ከእኔ ጋር ከተለያየ በኃላ ነው የያዘው' ብዬ ለመቀበል የቻልኩትን እያደረግኩ ነው....ዶክተሩ የመለሰልኝ መልስ ተስፋዬን አሟጦ ጣለው.....
"ጓደኛሽ ቲቢ endemic area move አርጋ ነበር....?...."....አለኝ ቀጠል አድርጎ...
"አላውቅም ምነው...."...አልኩትና መልሱን በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ።
"ምን አልባት እንደዚያ አካባቢ ከሄደች እና እንደ ቲቢ ባሉ ተጓዳኝ በሽታ የመጠቃት እድል ከነበራት በተጨማሪም immunityዋ የሞተ ከሆነ significant weight loss በዚህ ፍጥነት ሊኖራት ይችላል።" ሲለኝ ትንሽ ልቤ ተስፋ ጫረ....የዮናስ አከሳስ የዘመናት ታማሚ እንጂ የቅርብ አላስመሰለውም ነበር።
ትንሽ እፎይ አልኩ.....
"ለማንኛውም ነገ እኔ ክሊኒክ ትምጣና ልያት...አንድ አንዴ misdiagnosed የመደረግ ሁኔታም ስለሚኖር ድጋሚ ትታይ".... አለኝና ተሰነባበትን.......
ጭንቀቴን መደበቅ እንዳቃተኝ የታወቀኝ ታናሽ እህቴን ክፉኛ ሳመናጭቃት ነበር....
አላለቀም....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
"በሁለተኛ እድል ታምናለህ....."......አልኩት መክብብን ምሳ የምንበላበት ሬስቶራንት ተቀምጠን....
"እንደ ሁኔታው ይለያያል...."....አለኝና ለአፌ መጥኖ አጎረሰኝ.....ቀጥሎም "እየበላሽ አይደለም ምን ሆነሻል....."....አለኝ።
"ምንም አልሆንኩም....".....አልኩትና ያጎረሰኝን ውጬ እጄ ላይ ሳድበለብል የቆየሁትንም ደገምኩና እየበላሁ መሆኔን አስመሰከርኩ....
"ኧረ....ረ እንዲህ ከሆነማ ሁሌ ነው ምጋብዝሽ....አበላልሽ ኪስ አይጎዳም...."....አለና ያን ምትሀት ጥርሱን ገለጥ አደረገው።
"ስለ ሁለተኛ እድል እያወራሁህ ነበር.....".....አልኩት ለማስታወስ ያህል....
"ያው ሁለተኛ እድል እንደቦታው እና እንደሁኔታው ይለያያል....ለምሳሌ አንድ ነብስ ያጠፋ ወንጀለኛ...."....ከማለቱ አቋርጬው ከፍርድ ቤት ህግና መሰል ነገሮች የወጣ መልስ እንደምፈልግ ነገርኩት....
"specific አርጊልኛ.....እንዲሁ ሁለተኛ እድል የሚባል ነገር የለም እኮ እድሌ....."....አለኝ....እድሌ ስላለኝ ልቤ ሰላሳ ሁለት ጥርሱን አሳየ....ቢሆንም ግን ዮናስ የነገረኝን ነገር ሳስታውስ መክብብን ከሩቅ የማየው እንጂ የማልዳስሰው.....የማልነካው የእኔ የማልለው 'የማይበላ ወፍ' እንደሆነ ትዝ አለኝ።
"ስለ HIV አስበህ ታውቃለህ....."......አልኩት ድንገት....እንዳልኩት ያወቅኩት ካልኩት በኃላ ነበር።
"እኔንጃ ያው በሽታ ነው....ግን እንዴት አስበዋለሁ....አንዳንዴ በዙሪያሽ ያለ ሰው ሲታመም ነው በሽታውን የምታስተውይው አልያም 'በሽታ' የሚባል ነገር መኖሩን የምታስታውሽው እና እንደሚሞት ሰው የምትኖሪው....".....አለኝና አንድ ጉርሻ ደገመኝ።
"የሚሞት ሰው እንዴት ነው ሚኖረው...."....አልኩት አጣድፌ ጉርሻውን ከዋጥኩ በኃላ.....
"በርግጥ ሁላችንም ሟቾች ነን....ነገር ግን እንደሚሞት ሰው የሚኖረው በቁጥር ነው....ብዙ ሰው ግን እንደሚሞት የሚያስታውሰው ሲታመም ነው....እንደምትሞቺ ስታስቢ ለነገ የምታስቀምጪው ደስታ የለም....'ነገ' የምትይው ስራም ምግብም አይኖርም....እንደምትሞቺ ስታስቢ ነው መግቢያሽ የሚያሳስብሽ....የመጨረሻዎቹ ደይቃዎች ላይ ነው የነብስሽን ድምፅ የምትሰሚው....."
"ማን ታሞ ነው....?....."....አለኝ ቀጠል አድርጎ......"እኔ" አይባል ነገር ሆኖብኝ "አንድ ጓደኛዬ ታማ ነው..."....አልኩት....
"እንዴት ያዛት....".....ሲለኝ ደነገጥኩ....
"እንዴት ይይዛታል....እንደተለመደው ነዋ.... ትንሽ ስህተት ነበር ከፍቅር ጓደኛዋ ተጋብቶባት...."....አልኩትና ፊት ለፊቴ ያለውን ውሀ ባንድ ትንፋሽ ጨለጥኩት....
"ትንሽ ስህተት እንኳን አይደለም....ህይወት የሚያስከፍል 'ትንሽ' የለም....እንዴት ብዬ የጠየቅኩሽም እንዳልተለመደውም የሚታመሙ ሰዎች ስላሉ ነው....."
"ማለት....."...
"በደም ንክኪ..."....ሲለኝ የኢለመንተሪ ተማሪ የሆኖኩ መሰለኝ....ትንሽ ቆይቶ ስለ ሶስቱ የ'መ' ህጎች ሊያስተምረኝም ይችላል....እኔ ጭንቀቴ እንጂ እንዲህ የሚያስለፈልፈኝ ከመክብብ ጋር ሲጀመር ስለ በሽታ አይወራም....ከሱ ጋር መወራት ያለበት ስለ እሱ ብቻ ነበር....ስለ እሱ ውበት....ስለ ጥርሶቹ....ስለ አይኖቹ....ነፍስ ድረስ ስለሚሰማው ስለሚያረሰርሰው ድምፁ....ስለ መዳፎቹ....በቃ መወራት ያለበት ይሄ ነው.....
ድሮ ድሮ መልክ የበዛበት ወንድ አልወድም ነበር....ጭንቅላቴ ምን ሲል ይሄን መልክ የተትረፈረፈለት ወንድ እንደከጀለ አላውቅም.....
ከዮናስ የሰማሁትን ሰምቼ አልቅሼ አልወጣልኝም....አልወጣልኝም....እዚህ ከመክብብ ጋር ቁጭ ብሎ ምሳ ለመብላት ምን ያሀል እንደታገልኩኝ የማውቀው እኔ ነኝ....ስሜቱን ይሄ ነው ብዬ የምገልፀው አይነት አይደለም....
"ስለ HIV እናውራ...."....አልኩት ስለዩንቨርሲቲ ቆይታው ሲያጫውተኝ...ፊቱ ላይ ግርታ አነበብኩ።
"በጣም ተጨንቀሻል በጓደኛሽ ጉዳይ...."....ሲለኝ በአዎንታ አንገቴን ነቀነቅኩለት...
"ቆይ ሀኒም ታውቃታለች...."....ሲለኝ "ቀላል" ልለው ከአፌ ነው የመለስኩት.....
"አይ አታውቃትም....."..
"አንድ ዶክተር ጓደኛ አለኝ....ስልኩን እሰጥሽና መጠየቅ የምትፈልጊውን ጠይቂው...."
"..በርግጥ በጣም rare ኬዝ ነው....normally ግን በዚህ ፍጥነት ይሄን ያሀል weight loss አታደርግም...." የሚለኝ የደወልኩለት ዶክተር ነው.....'ከእኔ ጋር ከተለያየ በኃላ ነው የያዘው' ብዬ ለመቀበል የቻልኩትን እያደረግኩ ነው....ዶክተሩ የመለሰልኝ መልስ ተስፋዬን አሟጦ ጣለው.....
"ጓደኛሽ ቲቢ endemic area move አርጋ ነበር....?...."....አለኝ ቀጠል አድርጎ...
"አላውቅም ምነው...."...አልኩትና መልሱን በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ።
"ምን አልባት እንደዚያ አካባቢ ከሄደች እና እንደ ቲቢ ባሉ ተጓዳኝ በሽታ የመጠቃት እድል ከነበራት በተጨማሪም immunityዋ የሞተ ከሆነ significant weight loss በዚህ ፍጥነት ሊኖራት ይችላል።" ሲለኝ ትንሽ ልቤ ተስፋ ጫረ....የዮናስ አከሳስ የዘመናት ታማሚ እንጂ የቅርብ አላስመሰለውም ነበር።
ትንሽ እፎይ አልኩ.....
"ለማንኛውም ነገ እኔ ክሊኒክ ትምጣና ልያት...አንድ አንዴ misdiagnosed የመደረግ ሁኔታም ስለሚኖር ድጋሚ ትታይ".... አለኝና ተሰነባበትን.......
ጭንቀቴን መደበቅ እንዳቃተኝ የታወቀኝ ታናሽ እህቴን ክፉኛ ሳመናጭቃት ነበር....
አላለቀም....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
5900
20:00
04.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-15✨✨
"በሁለተኛ እድል ታምናለህ....."......አልኩት መክብብን ምሳ የምንበላበት ሬስቶራንት ተቀምጠን....
"እንደ ሁኔታው ይለያያል...."....አለኝና ለአፌ መጥኖ አጎረሰኝ.....ቀጥሎም "እየበላሽ አይደለም ምን ሆነሻል....."....አለኝ።
"ምንም አልሆንኩም....".....አልኩትና ያጎረሰኝን ውጬ እጄ ላይ ሳድበለብል የቆየሁትንም ደገምኩና እየበላሁ መሆኔን አስመሰከርኩ....
"ኧረ....ረ እንዲህ ከሆነማ ሁሌ ነው ምጋብዝሽ....አበላልሽ ኪስ አይጎዳም...."....አለና ያን ምትሀት ጥርሱን ገለጥ አደረገው።
"ስለ ሁለተኛ እድል እያወራሁህ ነበር.....".....አልኩት ለማስታወስ ያህል....
"ያው ሁለተኛ እድል እንደቦታው እና እንደሁኔታው ይለያያል....ለምሳሌ አንድ ነብስ ያጠፋ ወንጀለኛ...."....ከማለቱ አቋርጬው ከፍርድ ቤት ህግና መሰል ነገሮች የወጣ መልስ እንደምፈልግ ነገርኩት....
"specific አርጊልኛ.....እንዲሁ ሁለተኛ እድል የሚባል ነገር የለም እኮ እድሌ....."....አለኝ....እድሌ ስላለኝ ልቤ ሰላሳ ሁለት ጥርሱን አሳየ....ቢሆንም ግን ዮናስ የነገረኝን ነገር ሳስታውስ መክብብን ከሩቅ የማየው እንጂ የማልዳስሰው.....የማልነካው የእኔ የማልለው 'የማይበላ ወፍ' እንደሆነ ትዝ አለኝ።
"ስለ HIV አስበህ ታውቃለህ....."......አልኩት ድንገት....እንዳልኩት ያወቅኩት ካልኩት በኃላ ነበር።
"እኔንጃ ያው በሽታ ነው....ግን እንዴት አስበዋለሁ....አንዳንዴ በዙሪያሽ ያለ ሰው ሲታመም ነው በሽታውን የምታስተውይው አልያም 'በሽታ' የሚባል ነገር መኖሩን የምታስታውሽው እና እንደሚሞት ሰው የምትኖሪው....".....አለኝና አንድ ጉርሻ ደገመኝ።
"የሚሞት ሰው እንዴት ነው ሚኖረው...."....አልኩት አጣድፌ ጉርሻውን ከዋጥኩ በኃላ.....
"በርግጥ ሁላችንም ሟቾች ነን....ነገር ግን እንደሚሞት ሰው የሚኖረው በቁጥር ነው....ብዙ ሰው ግን እንደሚሞት የሚያስታውሰው ሲታመም ነው....እንደምትሞቺ ስታስቢ ለነገ የምታስቀምጪው ደስታ የለም....'ነገ' የምትይው ስራም ምግብም አይኖርም....እንደምትሞቺ ስታስቢ ነው መግቢያሽ የሚያሳስብሽ....የመጨረሻዎቹ ደይቃዎች ላይ ነው የነብስሽን ድምፅ የምትሰሚው....."
"ማን ታሞ ነው....?....."....አለኝ ቀጠል አድርጎ......"እኔ" አይባል ነገር ሆኖብኝ "አንድ ጓደኛዬ ታማ ነው..."....አልኩት....
"እንዴት ያዛት....".....ሲለኝ ደነገጥኩ....
"እንዴት ይይዛታል....እንደተለመደው ነዋ.... ትንሽ ስህተት ነበር ከፍቅር ጓደኛዋ ተጋብቶባት...."....አልኩትና ፊት ለፊቴ ያለውን ውሀ ባንድ ትንፋሽ ጨለጥኩት....
"ትንሽ ስህተት እንኳን አይደለም....ህይወት የሚያስከፍል 'ትንሽ' የለም....እንዴት ብዬ የጠየቅኩሽም እንዳልተለመደውም የሚታመሙ ሰዎች ስላሉ ነው....."
"ማለት....."...
"በደም ንክኪ..."....ሲለኝ የኢለመንተሪ ተማሪ የሆኖኩ መሰለኝ....ትንሽ ቆይቶ ስለ ሶስቱ የ'መ' ህጎች ሊያስተምረኝም ይችላል....እኔ ጭንቀቴ እንጂ እንዲህ የሚያስለፈልፈኝ ከመክብብ ጋር ሲጀመር ስለ በሽታ አይወራም....ከሱ ጋር መወራት ያለበት ስለ እሱ ብቻ ነበር....ስለ እሱ ውበት....ስለ ጥርሶቹ....ስለ አይኖቹ....ነፍስ ድረስ ስለሚሰማው ስለሚያረሰርሰው ድምፁ....ስለ መዳፎቹ....በቃ መወራት ያለበት ይሄ ነው.....
ድሮ ድሮ መልክ የበዛበት ወንድ አልወድም ነበር....ጭንቅላቴ ምን ሲል ይሄን መልክ የተትረፈረፈለት ወንድ እንደከጀለ አላውቅም.....
ከዮናስ የሰማሁትን ሰምቼ አልቅሼ አልወጣልኝም....አልወጣልኝም....እዚህ ከመክብብ ጋር ቁጭ ብሎ ምሳ ለመብላት ምን ያሀል እንደታገልኩኝ የማውቀው እኔ ነኝ....ስሜቱን ይሄ ነው ብዬ የምገልፀው አይነት አይደለም....
"ስለ HIV እናውራ...."....አልኩት ስለዩንቨርሲቲ ቆይታው ሲያጫውተኝ...ፊቱ ላይ ግርታ አነበብኩ።
"በጣም ተጨንቀሻል በጓደኛሽ ጉዳይ...."....ሲለኝ በአዎንታ አንገቴን ነቀነቅኩለት...
"ቆይ ሀኒም ታውቃታለች...."....ሲለኝ "ቀላል" ልለው ከአፌ ነው የመለስኩት.....
"አይ አታውቃትም....."..
"አንድ ዶክተር ጓደኛ አለኝ....ስልኩን እሰጥሽና መጠየቅ የምትፈልጊውን ጠይቂው...."
"..በርግጥ በጣም rare ኬዝ ነው....normally ግን በዚህ ፍጥነት ይሄን ያሀል weight loss አታደርግም...." የሚለኝ የደወልኩለት ዶክተር ነው.....'ከእኔ ጋር ከተለያየ በኃላ ነው የያዘው' ብዬ ለመቀበል የቻልኩትን እያደረግኩ ነው....ዶክተሩ የመለሰልኝ መልስ ተስፋዬን አሟጦ ጣለው.....
"ጓደኛሽ ቲቢ endemic area move አርጋ ነበር....?...."....አለኝ ቀጠል አድርጎ...
"አላውቅም ምነው...."...አልኩትና መልሱን በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ።
"ምን አልባት እንደዚያ አካባቢ ከሄደች እና እንደ ቲቢ ባሉ ተጓዳኝ በሽታ የመጠቃት እድል ከነበራት በተጨማሪም immunityዋ የሞተ ከሆነ significant weight loss በዚህ ፍጥነት ሊኖራት ይችላል።" ሲለኝ ትንሽ ልቤ ተስፋ ጫረ....የዮናስ አከሳስ የዘመናት ታማሚ እንጂ የቅርብ አላስመሰለውም ነበር።
ትንሽ እፎይ አልኩ.....
"ለማንኛውም ነገ እኔ ክሊኒክ ትምጣና ልያት...አንድ አንዴ misdiagnosed የመደረግ ሁኔታም ስለሚኖር ድጋሚ ትታይ".... አለኝና ተሰነባበትን.......
ጭንቀቴን መደበቅ እንዳቃተኝ የታወቀኝ ታናሽ እህቴን ክፉኛ ሳመናጭቃት ነበር....
አላለቀም....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
"በሁለተኛ እድል ታምናለህ....."......አልኩት መክብብን ምሳ የምንበላበት ሬስቶራንት ተቀምጠን....
"እንደ ሁኔታው ይለያያል...."....አለኝና ለአፌ መጥኖ አጎረሰኝ.....ቀጥሎም "እየበላሽ አይደለም ምን ሆነሻል....."....አለኝ።
"ምንም አልሆንኩም....".....አልኩትና ያጎረሰኝን ውጬ እጄ ላይ ሳድበለብል የቆየሁትንም ደገምኩና እየበላሁ መሆኔን አስመሰከርኩ....
"ኧረ....ረ እንዲህ ከሆነማ ሁሌ ነው ምጋብዝሽ....አበላልሽ ኪስ አይጎዳም...."....አለና ያን ምትሀት ጥርሱን ገለጥ አደረገው።
"ስለ ሁለተኛ እድል እያወራሁህ ነበር.....".....አልኩት ለማስታወስ ያህል....
"ያው ሁለተኛ እድል እንደቦታው እና እንደሁኔታው ይለያያል....ለምሳሌ አንድ ነብስ ያጠፋ ወንጀለኛ...."....ከማለቱ አቋርጬው ከፍርድ ቤት ህግና መሰል ነገሮች የወጣ መልስ እንደምፈልግ ነገርኩት....
"specific አርጊልኛ.....እንዲሁ ሁለተኛ እድል የሚባል ነገር የለም እኮ እድሌ....."....አለኝ....እድሌ ስላለኝ ልቤ ሰላሳ ሁለት ጥርሱን አሳየ....ቢሆንም ግን ዮናስ የነገረኝን ነገር ሳስታውስ መክብብን ከሩቅ የማየው እንጂ የማልዳስሰው.....የማልነካው የእኔ የማልለው 'የማይበላ ወፍ' እንደሆነ ትዝ አለኝ።
"ስለ HIV አስበህ ታውቃለህ....."......አልኩት ድንገት....እንዳልኩት ያወቅኩት ካልኩት በኃላ ነበር።
"እኔንጃ ያው በሽታ ነው....ግን እንዴት አስበዋለሁ....አንዳንዴ በዙሪያሽ ያለ ሰው ሲታመም ነው በሽታውን የምታስተውይው አልያም 'በሽታ' የሚባል ነገር መኖሩን የምታስታውሽው እና እንደሚሞት ሰው የምትኖሪው....".....አለኝና አንድ ጉርሻ ደገመኝ።
"የሚሞት ሰው እንዴት ነው ሚኖረው...."....አልኩት አጣድፌ ጉርሻውን ከዋጥኩ በኃላ.....
"በርግጥ ሁላችንም ሟቾች ነን....ነገር ግን እንደሚሞት ሰው የሚኖረው በቁጥር ነው....ብዙ ሰው ግን እንደሚሞት የሚያስታውሰው ሲታመም ነው....እንደምትሞቺ ስታስቢ ለነገ የምታስቀምጪው ደስታ የለም....'ነገ' የምትይው ስራም ምግብም አይኖርም....እንደምትሞቺ ስታስቢ ነው መግቢያሽ የሚያሳስብሽ....የመጨረሻዎቹ ደይቃዎች ላይ ነው የነብስሽን ድምፅ የምትሰሚው....."
"ማን ታሞ ነው....?....."....አለኝ ቀጠል አድርጎ......"እኔ" አይባል ነገር ሆኖብኝ "አንድ ጓደኛዬ ታማ ነው..."....አልኩት....
"እንዴት ያዛት....".....ሲለኝ ደነገጥኩ....
"እንዴት ይይዛታል....እንደተለመደው ነዋ.... ትንሽ ስህተት ነበር ከፍቅር ጓደኛዋ ተጋብቶባት...."....አልኩትና ፊት ለፊቴ ያለውን ውሀ ባንድ ትንፋሽ ጨለጥኩት....
"ትንሽ ስህተት እንኳን አይደለም....ህይወት የሚያስከፍል 'ትንሽ' የለም....እንዴት ብዬ የጠየቅኩሽም እንዳልተለመደውም የሚታመሙ ሰዎች ስላሉ ነው....."
"ማለት....."...
"በደም ንክኪ..."....ሲለኝ የኢለመንተሪ ተማሪ የሆኖኩ መሰለኝ....ትንሽ ቆይቶ ስለ ሶስቱ የ'መ' ህጎች ሊያስተምረኝም ይችላል....እኔ ጭንቀቴ እንጂ እንዲህ የሚያስለፈልፈኝ ከመክብብ ጋር ሲጀመር ስለ በሽታ አይወራም....ከሱ ጋር መወራት ያለበት ስለ እሱ ብቻ ነበር....ስለ እሱ ውበት....ስለ ጥርሶቹ....ስለ አይኖቹ....ነፍስ ድረስ ስለሚሰማው ስለሚያረሰርሰው ድምፁ....ስለ መዳፎቹ....በቃ መወራት ያለበት ይሄ ነው.....
ድሮ ድሮ መልክ የበዛበት ወንድ አልወድም ነበር....ጭንቅላቴ ምን ሲል ይሄን መልክ የተትረፈረፈለት ወንድ እንደከጀለ አላውቅም.....
ከዮናስ የሰማሁትን ሰምቼ አልቅሼ አልወጣልኝም....አልወጣልኝም....እዚህ ከመክብብ ጋር ቁጭ ብሎ ምሳ ለመብላት ምን ያሀል እንደታገልኩኝ የማውቀው እኔ ነኝ....ስሜቱን ይሄ ነው ብዬ የምገልፀው አይነት አይደለም....
"ስለ HIV እናውራ...."....አልኩት ስለዩንቨርሲቲ ቆይታው ሲያጫውተኝ...ፊቱ ላይ ግርታ አነበብኩ።
"በጣም ተጨንቀሻል በጓደኛሽ ጉዳይ...."....ሲለኝ በአዎንታ አንገቴን ነቀነቅኩለት...
"ቆይ ሀኒም ታውቃታለች...."....ሲለኝ "ቀላል" ልለው ከአፌ ነው የመለስኩት.....
"አይ አታውቃትም....."..
"አንድ ዶክተር ጓደኛ አለኝ....ስልኩን እሰጥሽና መጠየቅ የምትፈልጊውን ጠይቂው...."
"..በርግጥ በጣም rare ኬዝ ነው....normally ግን በዚህ ፍጥነት ይሄን ያሀል weight loss አታደርግም...." የሚለኝ የደወልኩለት ዶክተር ነው.....'ከእኔ ጋር ከተለያየ በኃላ ነው የያዘው' ብዬ ለመቀበል የቻልኩትን እያደረግኩ ነው....ዶክተሩ የመለሰልኝ መልስ ተስፋዬን አሟጦ ጣለው.....
"ጓደኛሽ ቲቢ endemic area move አርጋ ነበር....?...."....አለኝ ቀጠል አድርጎ...
"አላውቅም ምነው...."...አልኩትና መልሱን በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ።
"ምን አልባት እንደዚያ አካባቢ ከሄደች እና እንደ ቲቢ ባሉ ተጓዳኝ በሽታ የመጠቃት እድል ከነበራት በተጨማሪም immunityዋ የሞተ ከሆነ significant weight loss በዚህ ፍጥነት ሊኖራት ይችላል።" ሲለኝ ትንሽ ልቤ ተስፋ ጫረ....የዮናስ አከሳስ የዘመናት ታማሚ እንጂ የቅርብ አላስመሰለውም ነበር።
ትንሽ እፎይ አልኩ.....
"ለማንኛውም ነገ እኔ ክሊኒክ ትምጣና ልያት...አንድ አንዴ misdiagnosed የመደረግ ሁኔታም ስለሚኖር ድጋሚ ትታይ".... አለኝና ተሰነባበትን.......
ጭንቀቴን መደበቅ እንዳቃተኝ የታወቀኝ ታናሽ እህቴን ክፉኛ ሳመናጭቃት ነበር....
አላለቀም....
✍ሸዊት
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
https://t.me/shewitdorka
5900
20:00
04.05.2025
ፍቅር እና ቁጥር
ስንግባባ ሰሞን እኔ መላመድን ለማምለጥ የምባትል ባተሌ ነበርኩ። የተጣመርኩት ባይኖርም ራሴን ብቻዬን እወደዋለሁ።
የማልደራደርበት ማንነት ነበረኝ። ሌሎችን የማደንቅበትና የማከብርበት የማንነት መለኪያያዎችም ነበሩኝ።
እሱ ---- አላውቅም የሱን ፍላጎት........ ብቻ አላጣደፈኝም። የተለየ ፍላጎት እንዳለውም ሊያሳየኝ አልተፍጨረጨረም። የሰው ፍላጎት እና ሀሳብ ሲጫንብኝ እንደማልወድ ገብቶታል።
ማባበሉ አጥንቶ የቀመረበት ነበር። ጆሮዬ ከአንዴም ሁለቴ ከድቶኛል እና በተቆለጳጰሰ የፍቅር ዓረፍተ ነገር የሚደነግጥ ልብ እንደሌለኝ አውቋል። ቀስ በቀስ ለፍፅምና የተጠጋ እሱነቱን ነው የጋተኝ።
በገንዘብ ተተምነው ውድ የሆኑ ስጦታዎች እየገዛ አይደለም ያቀበጠኝ፤ በአንድ አንጎል የምናስብ እስኪመስለኝ ድረስ የሚያስፈልገኝን እና ለልቤ የቀረቡ ስጦታዎችን ነበር የሰጠኝ። ውደጂኝ አላለኝም። እንድወደው ምንም አስተዋፅኦ እንዳላደረገ ዓይነት፣ .....የቀን ተቀን እሱነቱን እየኖረ እንደሆነ ዓይነት
፣....... እኔን ለመማረክ የጨመረው ምናምኒት ትጋት እንደሌለ ፣.......... ለሃጬ እስኪዝረበረብ በሱሱ ለመተብተቤ ያበረከተው ምንም እንደሌለ ሁላ ......ከደሙ ነፃ ነኝ...... እኔ የእለት ተእለት እኔነቴን ነው የኖርኩት ዓይነት እጁን ተለቀለቀ።
የሰው ልጅ አዘቦታዊ ማንነት እንዴት እንዲህ እንከን አልባ ይሆናል ብዬ አልጠየቅኩም። በየእለቱ እየገለጠ ያስነበበኝን የማንነቱን ምሰሶዎች ሰብስቤ እሱ ነው ያልኩትን እሱን በልቤ ገነባሁ ፣ በአዕምሮዬ ሳልኩ። ለዚህ ማንነት እጅ ሰጠሁ።
እዚህ ጊዜ ላይ
ፍቅሩን ፣ ጊዜውን ፣ ጆሮውን ፣ ልቡን ፣ ገላውን ፣ትኩረቱን ያልሰጠኝ የለም። 100% እሱነቱን ያለስስት ነበር የሰጠኝ። እስክበስል ማገዶ እንደምፈጅ ገብቶታል። አልተጣደፈም። ከሞከኩኝ ኋላ እስክበሰብስ እንደምታሽ ገብቶታል።
ሱሴ የሆነ ጊዜ ላይ ....... ያለእርሱ ትንፋሽ እንደሚያጥረኝ የገባው ሰዓት ላይ .......
የሂሳብ ቀመሩን ይጫወት ጀመረ። ቀስ በቀስ ከመቶ እሱነቱ ይገምሰው ገባ። ፍቅሩንም ጊዜውንም ጆሮውኑም ልቡንም ገላውንም ትኩረቱንም በግማሽ ቦደሰው። 50% !! ልቤ የምትደገፈው ምርኩዝ ስታስስ የነጠቀኝን ትንሽ ይጨምርበታል። 75%!! ........ ጨዋታው ይሄ ነው። 100 እንደነበር ይጠፋኛል።
ካጣሁት ግማሽ ይልቅ የተጨመረልኝ እሩብ ያስቦርቀኛል። ልቤ መልሳ እሱን ማምለኳን ትቀጥላለች። መልሶ ከ75% ወደ 25% ሲወርድብኝ የአየር ቧንቧዬ የጠበበ ያህል ደረቴን ያፍነኛል። መልሶ 25% እሱን ይጨምርልኛል። ግማሽ እሱነቱን እንደነሳኝ አላላዝንም። የጨመረልኝ ያስደንሰኛል።
አንድ ቀን ገላውን ለሌላ ሴት አዋሰብኝ። እዚህ ጊዜ ላይ ከሙሉ እሱነቱ 5% ፐርሰንቱን እንኳን አልሰጠኝም።
በብዙ ትዕግስት እና ጥበብ ውስጤ የገነባው እሱነቱ ግን አሁንም አልተገመሰም። ወይም በቀላሉ እንዳይፈርስ አድርጎ ከዓለት ገንብቶታል። ወይም ማመን አልፈልግም። ፍንክች አይልም።
አልካደኝም። በእንባ ታጅቦ ይቅርታ ጠየቀኝ። ይቅርታውን በአግቢኝ ጥያቄ እና ቀለበት አጀበው። የምለው ገባችሁ? ከአምስት 25% ነዳው አይደል? ያደረገውን ሳይሆን ያደረገልኝን እያሰብኩ ተፍለቀለቅኩ። ስለሚወደኝ አይደል አዳራሽ ሙሉ ህዝብ ጠርቶ ፕሮፖዝ ያደረገኝ?
ሶስት ቀን የት እንዳለ እንኳን ሳይነግረኝ ዘግቶኝ ይከርምና በአራተኛው ቀን ለእናቴ ከክርስታል የተሰራ የአበባ ማስቀመጫ ገዝቶ ከች ይላል። ሶስቱን ቀን ረስቼ ለእናቴ ላሳያት ፍቅር እሸነፋለሁ።
እሱ ከሚያሳየኝ የዘቀጠ ማንነት ይልቅ በልቤ ያነገስኩት ማነነት ላይ ሙጭጭ አልኩ። በሂሳብ ቀመሩ ተወናበድኩ።
የእሱን ስዕል ከልቤ ከማፍረሴ ብዙ ቀን ቀድሞ እኔ ፈረስኩ። የእሱን እውነተኛ ማንነት አምኜ ከመቀበሌ ከብዙ ቀናት ቀድሞ የራሴ ማንነት ጠፋኝ።
መላመድን ላመልጠው የምሸመጥጥ አትሌት አልነበርኩ? እሱ ከልቤም ከህይወቴም ሲወጣ ለመሮጥም ለማምለጥም ለማሰብም የተረፈ አቅም አልነበረኝም።
*
ውብ ቀን ምሽት አምሹልኝ!!♥️❤️♥️❤️
ሜሪ ፈለቀ
ስንግባባ ሰሞን እኔ መላመድን ለማምለጥ የምባትል ባተሌ ነበርኩ። የተጣመርኩት ባይኖርም ራሴን ብቻዬን እወደዋለሁ።
የማልደራደርበት ማንነት ነበረኝ። ሌሎችን የማደንቅበትና የማከብርበት የማንነት መለኪያያዎችም ነበሩኝ።
እሱ ---- አላውቅም የሱን ፍላጎት........ ብቻ አላጣደፈኝም። የተለየ ፍላጎት እንዳለውም ሊያሳየኝ አልተፍጨረጨረም። የሰው ፍላጎት እና ሀሳብ ሲጫንብኝ እንደማልወድ ገብቶታል።
ማባበሉ አጥንቶ የቀመረበት ነበር። ጆሮዬ ከአንዴም ሁለቴ ከድቶኛል እና በተቆለጳጰሰ የፍቅር ዓረፍተ ነገር የሚደነግጥ ልብ እንደሌለኝ አውቋል። ቀስ በቀስ ለፍፅምና የተጠጋ እሱነቱን ነው የጋተኝ።
በገንዘብ ተተምነው ውድ የሆኑ ስጦታዎች እየገዛ አይደለም ያቀበጠኝ፤ በአንድ አንጎል የምናስብ እስኪመስለኝ ድረስ የሚያስፈልገኝን እና ለልቤ የቀረቡ ስጦታዎችን ነበር የሰጠኝ። ውደጂኝ አላለኝም። እንድወደው ምንም አስተዋፅኦ እንዳላደረገ ዓይነት፣ .....የቀን ተቀን እሱነቱን እየኖረ እንደሆነ ዓይነት
፣....... እኔን ለመማረክ የጨመረው ምናምኒት ትጋት እንደሌለ ፣.......... ለሃጬ እስኪዝረበረብ በሱሱ ለመተብተቤ ያበረከተው ምንም እንደሌለ ሁላ ......ከደሙ ነፃ ነኝ...... እኔ የእለት ተእለት እኔነቴን ነው የኖርኩት ዓይነት እጁን ተለቀለቀ።
የሰው ልጅ አዘቦታዊ ማንነት እንዴት እንዲህ እንከን አልባ ይሆናል ብዬ አልጠየቅኩም። በየእለቱ እየገለጠ ያስነበበኝን የማንነቱን ምሰሶዎች ሰብስቤ እሱ ነው ያልኩትን እሱን በልቤ ገነባሁ ፣ በአዕምሮዬ ሳልኩ። ለዚህ ማንነት እጅ ሰጠሁ።
እዚህ ጊዜ ላይ
ፍቅሩን ፣ ጊዜውን ፣ ጆሮውን ፣ ልቡን ፣ ገላውን ፣ትኩረቱን ያልሰጠኝ የለም። 100% እሱነቱን ያለስስት ነበር የሰጠኝ። እስክበስል ማገዶ እንደምፈጅ ገብቶታል። አልተጣደፈም። ከሞከኩኝ ኋላ እስክበሰብስ እንደምታሽ ገብቶታል።
ሱሴ የሆነ ጊዜ ላይ ....... ያለእርሱ ትንፋሽ እንደሚያጥረኝ የገባው ሰዓት ላይ .......
የሂሳብ ቀመሩን ይጫወት ጀመረ። ቀስ በቀስ ከመቶ እሱነቱ ይገምሰው ገባ። ፍቅሩንም ጊዜውንም ጆሮውኑም ልቡንም ገላውንም ትኩረቱንም በግማሽ ቦደሰው። 50% !! ልቤ የምትደገፈው ምርኩዝ ስታስስ የነጠቀኝን ትንሽ ይጨምርበታል። 75%!! ........ ጨዋታው ይሄ ነው። 100 እንደነበር ይጠፋኛል።
ካጣሁት ግማሽ ይልቅ የተጨመረልኝ እሩብ ያስቦርቀኛል። ልቤ መልሳ እሱን ማምለኳን ትቀጥላለች። መልሶ ከ75% ወደ 25% ሲወርድብኝ የአየር ቧንቧዬ የጠበበ ያህል ደረቴን ያፍነኛል። መልሶ 25% እሱን ይጨምርልኛል። ግማሽ እሱነቱን እንደነሳኝ አላላዝንም። የጨመረልኝ ያስደንሰኛል።
አንድ ቀን ገላውን ለሌላ ሴት አዋሰብኝ። እዚህ ጊዜ ላይ ከሙሉ እሱነቱ 5% ፐርሰንቱን እንኳን አልሰጠኝም።
በብዙ ትዕግስት እና ጥበብ ውስጤ የገነባው እሱነቱ ግን አሁንም አልተገመሰም። ወይም በቀላሉ እንዳይፈርስ አድርጎ ከዓለት ገንብቶታል። ወይም ማመን አልፈልግም። ፍንክች አይልም።
አልካደኝም። በእንባ ታጅቦ ይቅርታ ጠየቀኝ። ይቅርታውን በአግቢኝ ጥያቄ እና ቀለበት አጀበው። የምለው ገባችሁ? ከአምስት 25% ነዳው አይደል? ያደረገውን ሳይሆን ያደረገልኝን እያሰብኩ ተፍለቀለቅኩ። ስለሚወደኝ አይደል አዳራሽ ሙሉ ህዝብ ጠርቶ ፕሮፖዝ ያደረገኝ?
ሶስት ቀን የት እንዳለ እንኳን ሳይነግረኝ ዘግቶኝ ይከርምና በአራተኛው ቀን ለእናቴ ከክርስታል የተሰራ የአበባ ማስቀመጫ ገዝቶ ከች ይላል። ሶስቱን ቀን ረስቼ ለእናቴ ላሳያት ፍቅር እሸነፋለሁ።
እሱ ከሚያሳየኝ የዘቀጠ ማንነት ይልቅ በልቤ ያነገስኩት ማነነት ላይ ሙጭጭ አልኩ። በሂሳብ ቀመሩ ተወናበድኩ።
የእሱን ስዕል ከልቤ ከማፍረሴ ብዙ ቀን ቀድሞ እኔ ፈረስኩ። የእሱን እውነተኛ ማንነት አምኜ ከመቀበሌ ከብዙ ቀናት ቀድሞ የራሴ ማንነት ጠፋኝ።
መላመድን ላመልጠው የምሸመጥጥ አትሌት አልነበርኩ? እሱ ከልቤም ከህይወቴም ሲወጣ ለመሮጥም ለማምለጥም ለማሰብም የተረፈ አቅም አልነበረኝም።
*
ውብ ቀን ምሽት አምሹልኝ!!♥️❤️♥️❤️
ሜሪ ፈለቀ
6100
17:23
04.05.2025
ፍቅር እና ቁጥር
ስንግባባ ሰሞን እኔ መላመድን ለማምለጥ የምባትል ባተሌ ነበርኩ። የተጣመርኩት ባይኖርም ራሴን ብቻዬን እወደዋለሁ።
የማልደራደርበት ማንነት ነበረኝ። ሌሎችን የማደንቅበትና የማከብርበት የማንነት መለኪያያዎችም ነበሩኝ።
እሱ ---- አላውቅም የሱን ፍላጎት........ ብቻ አላጣደፈኝም። የተለየ ፍላጎት እንዳለውም ሊያሳየኝ አልተፍጨረጨረም። የሰው ፍላጎት እና ሀሳብ ሲጫንብኝ እንደማልወድ ገብቶታል።
ማባበሉ አጥንቶ የቀመረበት ነበር። ጆሮዬ ከአንዴም ሁለቴ ከድቶኛል እና በተቆለጳጰሰ የፍቅር ዓረፍተ ነገር የሚደነግጥ ልብ እንደሌለኝ አውቋል። ቀስ በቀስ ለፍፅምና የተጠጋ እሱነቱን ነው የጋተኝ።
በገንዘብ ተተምነው ውድ የሆኑ ስጦታዎች እየገዛ አይደለም ያቀበጠኝ፤ በአንድ አንጎል የምናስብ እስኪመስለኝ ድረስ የሚያስፈልገኝን እና ለልቤ የቀረቡ ስጦታዎችን ነበር የሰጠኝ። ውደጂኝ አላለኝም። እንድወደው ምንም አስተዋፅኦ እንዳላደረገ ዓይነት፣ .....የቀን ተቀን እሱነቱን እየኖረ እንደሆነ ዓይነት
፣....... እኔን ለመማረክ የጨመረው ምናምኒት ትጋት እንደሌለ ፣.......... ለሃጬ እስኪዝረበረብ በሱሱ ለመተብተቤ ያበረከተው ምንም እንደሌለ ሁላ ......ከደሙ ነፃ ነኝ...... እኔ የእለት ተእለት እኔነቴን ነው የኖርኩት ዓይነት እጁን ተለቀለቀ።
የሰው ልጅ አዘቦታዊ ማንነት እንዴት እንዲህ እንከን አልባ ይሆናል ብዬ አልጠየቅኩም። በየእለቱ እየገለጠ ያስነበበኝን የማንነቱን ምሰሶዎች ሰብስቤ እሱ ነው ያልኩትን እሱን በልቤ ገነባሁ ፣ በአዕምሮዬ ሳልኩ። ለዚህ ማንነት እጅ ሰጠሁ።
እዚህ ጊዜ ላይ
ፍቅሩን ፣ ጊዜውን ፣ ጆሮውን ፣ ልቡን ፣ ገላውን ፣ትኩረቱን ያልሰጠኝ የለም። 100% እሱነቱን ያለስስት ነበር የሰጠኝ። እስክበስል ማገዶ እንደምፈጅ ገብቶታል። አልተጣደፈም። ከሞከኩኝ ኋላ እስክበሰብስ እንደምታሽ ገብቶታል።
ሱሴ የሆነ ጊዜ ላይ ....... ያለእርሱ ትንፋሽ እንደሚያጥረኝ የገባው ሰዓት ላይ .......
የሂሳብ ቀመሩን ይጫወት ጀመረ። ቀስ በቀስ ከመቶ እሱነቱ ይገምሰው ገባ። ፍቅሩንም ጊዜውንም ጆሮውኑም ልቡንም ገላውንም ትኩረቱንም በግማሽ ቦደሰው። 50% !! ልቤ የምትደገፈው ምርኩዝ ስታስስ የነጠቀኝን ትንሽ ይጨምርበታል። 75%!! ........ ጨዋታው ይሄ ነው። 100 እንደነበር ይጠፋኛል።
ካጣሁት ግማሽ ይልቅ የተጨመረልኝ እሩብ ያስቦርቀኛል። ልቤ መልሳ እሱን ማምለኳን ትቀጥላለች። መልሶ ከ75% ወደ 25% ሲወርድብኝ የአየር ቧንቧዬ የጠበበ ያህል ደረቴን ያፍነኛል። መልሶ 25% እሱን ይጨምርልኛል። ግማሽ እሱነቱን እንደነሳኝ አላላዝንም። የጨመረልኝ ያስደንሰኛል።
አንድ ቀን ገላውን ለሌላ ሴት አዋሰብኝ። እዚህ ጊዜ ላይ ከሙሉ እሱነቱ 5% ፐርሰንቱን እንኳን አልሰጠኝም።
በብዙ ትዕግስት እና ጥበብ ውስጤ የገነባው እሱነቱ ግን አሁንም አልተገመሰም። ወይም በቀላሉ እንዳይፈርስ አድርጎ ከዓለት ገንብቶታል። ወይም ማመን አልፈልግም። ፍንክች አይልም።
አልካደኝም። በእንባ ታጅቦ ይቅርታ ጠየቀኝ። ይቅርታውን በአግቢኝ ጥያቄ እና ቀለበት አጀበው። የምለው ገባችሁ? ከአምስት 25% ነዳው አይደል? ያደረገውን ሳይሆን ያደረገልኝን እያሰብኩ ተፍለቀለቅኩ። ስለሚወደኝ አይደል አዳራሽ ሙሉ ህዝብ ጠርቶ ፕሮፖዝ ያደረገኝ?
ሶስት ቀን የት እንዳለ እንኳን ሳይነግረኝ ዘግቶኝ ይከርምና በአራተኛው ቀን ለእናቴ ከክርስታል የተሰራ የአበባ ማስቀመጫ ገዝቶ ከች ይላል። ሶስቱን ቀን ረስቼ ለእናቴ ላሳያት ፍቅር እሸነፋለሁ።
እሱ ከሚያሳየኝ የዘቀጠ ማንነት ይልቅ በልቤ ያነገስኩት ማነነት ላይ ሙጭጭ አልኩ። በሂሳብ ቀመሩ ተወናበድኩ።
የእሱን ስዕል ከልቤ ከማፍረሴ ብዙ ቀን ቀድሞ እኔ ፈረስኩ። የእሱን እውነተኛ ማንነት አምኜ ከመቀበሌ ከብዙ ቀናት ቀድሞ የራሴ ማንነት ጠፋኝ።
መላመድን ላመልጠው የምሸመጥጥ አትሌት አልነበርኩ? እሱ ከልቤም ከህይወቴም ሲወጣ ለመሮጥም ለማምለጥም ለማሰብም የተረፈ አቅም አልነበረኝም።
*
ውብ ምሽት አምሹልኝ!!♥️❤️♥️❤️
ሜሪ ፈለቀ
➡️ @Enmare1988
➡️ @Enmare1988
➡️ @Enmare1988
ስንግባባ ሰሞን እኔ መላመድን ለማምለጥ የምባትል ባተሌ ነበርኩ። የተጣመርኩት ባይኖርም ራሴን ብቻዬን እወደዋለሁ።
የማልደራደርበት ማንነት ነበረኝ። ሌሎችን የማደንቅበትና የማከብርበት የማንነት መለኪያያዎችም ነበሩኝ።
እሱ ---- አላውቅም የሱን ፍላጎት........ ብቻ አላጣደፈኝም። የተለየ ፍላጎት እንዳለውም ሊያሳየኝ አልተፍጨረጨረም። የሰው ፍላጎት እና ሀሳብ ሲጫንብኝ እንደማልወድ ገብቶታል።
ማባበሉ አጥንቶ የቀመረበት ነበር። ጆሮዬ ከአንዴም ሁለቴ ከድቶኛል እና በተቆለጳጰሰ የፍቅር ዓረፍተ ነገር የሚደነግጥ ልብ እንደሌለኝ አውቋል። ቀስ በቀስ ለፍፅምና የተጠጋ እሱነቱን ነው የጋተኝ።
በገንዘብ ተተምነው ውድ የሆኑ ስጦታዎች እየገዛ አይደለም ያቀበጠኝ፤ በአንድ አንጎል የምናስብ እስኪመስለኝ ድረስ የሚያስፈልገኝን እና ለልቤ የቀረቡ ስጦታዎችን ነበር የሰጠኝ። ውደጂኝ አላለኝም። እንድወደው ምንም አስተዋፅኦ እንዳላደረገ ዓይነት፣ .....የቀን ተቀን እሱነቱን እየኖረ እንደሆነ ዓይነት
፣....... እኔን ለመማረክ የጨመረው ምናምኒት ትጋት እንደሌለ ፣.......... ለሃጬ እስኪዝረበረብ በሱሱ ለመተብተቤ ያበረከተው ምንም እንደሌለ ሁላ ......ከደሙ ነፃ ነኝ...... እኔ የእለት ተእለት እኔነቴን ነው የኖርኩት ዓይነት እጁን ተለቀለቀ።
የሰው ልጅ አዘቦታዊ ማንነት እንዴት እንዲህ እንከን አልባ ይሆናል ብዬ አልጠየቅኩም። በየእለቱ እየገለጠ ያስነበበኝን የማንነቱን ምሰሶዎች ሰብስቤ እሱ ነው ያልኩትን እሱን በልቤ ገነባሁ ፣ በአዕምሮዬ ሳልኩ። ለዚህ ማንነት እጅ ሰጠሁ።
እዚህ ጊዜ ላይ
ፍቅሩን ፣ ጊዜውን ፣ ጆሮውን ፣ ልቡን ፣ ገላውን ፣ትኩረቱን ያልሰጠኝ የለም። 100% እሱነቱን ያለስስት ነበር የሰጠኝ። እስክበስል ማገዶ እንደምፈጅ ገብቶታል። አልተጣደፈም። ከሞከኩኝ ኋላ እስክበሰብስ እንደምታሽ ገብቶታል።
ሱሴ የሆነ ጊዜ ላይ ....... ያለእርሱ ትንፋሽ እንደሚያጥረኝ የገባው ሰዓት ላይ .......
የሂሳብ ቀመሩን ይጫወት ጀመረ። ቀስ በቀስ ከመቶ እሱነቱ ይገምሰው ገባ። ፍቅሩንም ጊዜውንም ጆሮውኑም ልቡንም ገላውንም ትኩረቱንም በግማሽ ቦደሰው። 50% !! ልቤ የምትደገፈው ምርኩዝ ስታስስ የነጠቀኝን ትንሽ ይጨምርበታል። 75%!! ........ ጨዋታው ይሄ ነው። 100 እንደነበር ይጠፋኛል።
ካጣሁት ግማሽ ይልቅ የተጨመረልኝ እሩብ ያስቦርቀኛል። ልቤ መልሳ እሱን ማምለኳን ትቀጥላለች። መልሶ ከ75% ወደ 25% ሲወርድብኝ የአየር ቧንቧዬ የጠበበ ያህል ደረቴን ያፍነኛል። መልሶ 25% እሱን ይጨምርልኛል። ግማሽ እሱነቱን እንደነሳኝ አላላዝንም። የጨመረልኝ ያስደንሰኛል።
አንድ ቀን ገላውን ለሌላ ሴት አዋሰብኝ። እዚህ ጊዜ ላይ ከሙሉ እሱነቱ 5% ፐርሰንቱን እንኳን አልሰጠኝም።
በብዙ ትዕግስት እና ጥበብ ውስጤ የገነባው እሱነቱ ግን አሁንም አልተገመሰም። ወይም በቀላሉ እንዳይፈርስ አድርጎ ከዓለት ገንብቶታል። ወይም ማመን አልፈልግም። ፍንክች አይልም።
አልካደኝም። በእንባ ታጅቦ ይቅርታ ጠየቀኝ። ይቅርታውን በአግቢኝ ጥያቄ እና ቀለበት አጀበው። የምለው ገባችሁ? ከአምስት 25% ነዳው አይደል? ያደረገውን ሳይሆን ያደረገልኝን እያሰብኩ ተፍለቀለቅኩ። ስለሚወደኝ አይደል አዳራሽ ሙሉ ህዝብ ጠርቶ ፕሮፖዝ ያደረገኝ?
ሶስት ቀን የት እንዳለ እንኳን ሳይነግረኝ ዘግቶኝ ይከርምና በአራተኛው ቀን ለእናቴ ከክርስታል የተሰራ የአበባ ማስቀመጫ ገዝቶ ከች ይላል። ሶስቱን ቀን ረስቼ ለእናቴ ላሳያት ፍቅር እሸነፋለሁ።
እሱ ከሚያሳየኝ የዘቀጠ ማንነት ይልቅ በልቤ ያነገስኩት ማነነት ላይ ሙጭጭ አልኩ። በሂሳብ ቀመሩ ተወናበድኩ።
የእሱን ስዕል ከልቤ ከማፍረሴ ብዙ ቀን ቀድሞ እኔ ፈረስኩ። የእሱን እውነተኛ ማንነት አምኜ ከመቀበሌ ከብዙ ቀናት ቀድሞ የራሴ ማንነት ጠፋኝ።
መላመድን ላመልጠው የምሸመጥጥ አትሌት አልነበርኩ? እሱ ከልቤም ከህይወቴም ሲወጣ ለመሮጥም ለማምለጥም ለማሰብም የተረፈ አቅም አልነበረኝም።
*
ውብ ምሽት አምሹልኝ!!♥️❤️♥️❤️
ሜሪ ፈለቀ
6100
17:23
04.05.2025
imageImage preview is unavailable
ዛሬ ደግሞ የምጠቁማችሁ ቻናል የሚገራርሙ ዓለም አቀፍ እውነታዎችን ሳይኮሎጂዎችን የሚለቅ የሚያስገርሙ ለማመን የሚከብዱ የዓለማችንን ጉዶች የምታገኙበት ትምህርት ምትቀስሙበት ምርጥ ቻናል ነው!
ቻናሉን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ንኩት
👇👇👇
@yegudalem
@yegudalem
@yegudalem
@yegudalem
ቤተሰብ ይሄን ሼር በማድረግ ተባበሩኝ !
ቻናሉን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ንኩት
👇👇👇
@yegudalem
@yegudalem
@yegudalem
@yegudalem
ቤተሰብ ይሄን ሼር በማድረግ ተባበሩኝ !
5900
16:30
04.05.2025
close
Reviews channel
keyboard_arrow_down
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
5.0
8 reviews over 6 months
Excellent (100%) In the last 6 months
f
**biubiu@*****.com
On the service since January 2025
18.03.202518:18
5
Precise task compliance
Show more
New items
Channel statistics
Rating
30.2
Rating reviews
5.0
Сhannel Rating
28
Subscribers:
126K
APV
lock_outline
ER
4.3%
Posts per day:
5.0
CPM
lock_outlineSelected
0
channels for:$0.00
Subscribers:
0
Views:
lock_outline
Add to CartBuy for:$0.00
Комментарий