
- Main
- Catalog
- News and Media
- Advertising on the Telegram channel «4-3-3 WORLD NEWS»
Advertising on the Telegram channel «4-3-3 WORLD NEWS»
ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው!
Channel statistics
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ብሪታንያ የቻጎስ ደሴቶችን ለሞሪሸስ ለመስጠት መወሰኗ ዋሽንግተን ግሪንላንድን ለመቆጣጠር ከፈለገችባቸው ምክንያቶች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል። የግል ንብረታቸው በሆነው ትሩዝ ሶሻል ላይ ባጋሩት መልዕክት፣ የዩናይትድ ኪንግደም የቻጎስ ደሴቶችን ሉዓላዊነት ለሞሪሺየስ ለማስረከብ ያቀደችው እቅድ “የታላቅ የሞኝነት ተግባር ነው” ብለዋል።
በሚያስደነግጥ ሁኔታ፣ የእኛ “ብሩህ” የኔቶ አጋር፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ በአሁኑ ጊዜ የዲዬጎ ጋርሺያ ደሴትን፣ ወሳኝ የአሜሪካ ወታደራዊ ቤዝ ጣቢያን ለሞሪሸስ ለመስጠት አቅዳለች፣ እናም ይህንን ያለምክንያት ያደርጋሉ ብለዋል። ቻይና እና ሩሲያ ይህንን የድክመት ተግባር እንዳስተዋሉ ምንም ጥርጥር የለውም። እነዚህ ጥንካሬን ብቻ የሚያውቁ ዓለም አቀፍ ኃያላን ናቸው፣ ለዚህም ነው ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ በእኔ መሪነት ከአንድ ዓመት ወዲህ ከመቼውም ጊዜ በላይ እተከበረች ነው ሲሉ ተደምጠዋል።
የትራምፕን ንግግር የብሪታኒያ መንግስት ተቃዋሚዎች ደግፈዋል። የመንግስት የቻጎስ ስምምነት “ራስን በራስ ማጥፋት” ነው ሲሉ የገለጹት የኮንሰርቫቲቭ መሪ ወይዘሮ ኬሚ ባደናች ናቸው። ባዳናች ከፕሬዚዳንቱ መልእክት ምስል ጎን ለጎን በኤክስ ላይ ባስተላለፉት መልእክት “የቻጎስ ደሴቶችን ለማስረከብ መወሰን የሞኝነት ተግባር ብቻ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ራስን ማጥፋት ነው ብለዋል። "በዚህ ጉዳይ ላይ ግልፅ ነኝ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ትክክል ናቸው ሲሉ ተደምጠዋል። "የኬይር ስታርመር የቻጎስ ደሴቶችን የመስጠት እቅድ የዩናይትድ ኪንግደም ደህንነትን የሚያዳክም እና ሉዓላዊ ግዛታችንን የሚወስድ አስከፊ ፖሊሲ ነው።
በስምዖን ደረጄ
@Ethionews433et @Ethionews433et
አንድ የታይዋን ሰው ለ20 አመታት ያህል በየቀኑ ተመሳሳይ የሙቀት መጠጫ ኩባያ ፔርሙዝ ለቡና ይጠቀም የነበረ ሲሆን በሊድ መመረዝ ህይወቱን በአሳዛኝ ሁኔታ አጥቷል።
ስሙ ያልተገለፀው ይህው ሰው በ50ዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ እና ከ30 አመት በላይ የማሽከርከር ልምድ ያለው ቢሆንም በቅርቡ ወደ ስራው ሲሄድ መኪናው ከሱቅ ጋር ተጋጭቶ ፍሬን መያዝ ሳይችል እንኳን ክፉኛ ተጎድቷል።
በመጀመሪያ በተደረጉት ምርመራዎች በከባድ የደም ማነስ፣ ኮርቲካል አትሮፊ እና ያልተለመደ የኩላሊት ተግባር መዛባት እንዳጋጠመው አረጋግጠዋል። ለተጨማሪ ምርመራዎች ወደ ኔፍሮሎጂ ክፍል ተላልፏል።የኔፍሮሎጂስት ሀንግ ዩንግ-ህሲያንግ በቅርቡ በታይዋን በሚገኝ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ላይ የግለሰቡን ጉዳይ እንደ ማስጠንቀቂያ አቅርበው ሰዎች የውሃ ጠርሙሶችን ወይም የሙቀት መጠጫዎችን በየጊዜው እንዲቀይሩ አስጠንቅቀዋል።
ታካሚው በቅርብ ጊዜ ድካም እያጋጠመው እንደነበረ እና ጣዕም እንደተቀየረበት ብዙ ጊዜ ሲመገብ ምግቡ በቂ ጨዋማ እንዳልሆነ ይሰማው ነበር። እነዚህ ሁሉ ምልክቶች በሊድ መመረዝ ያመለክታሉ፤ ይህ ሁኔታ በደም ምርመራው የተረጋገጠ ነው።ዶክተሮች የመመረዙን ምንጭ ለማወቅ ሲሞክሩ ሰውዬው በየቀኑ ማለት ይቻላል ለሁለት አስርት ዓመታት ያህል ተመሳሳይ ቴርሞስን ሲጠቀም እንደነበር ደርሰውበታል። የማጉ ውስጠኛው ሽፋን ዝገት የተነሳ አሲዳማው ሊድ ወደ ቡናው በየቀኑ እየተቀላቀለ መሆኑ ታውቋል።
በስምዖን ደረጄ
@Ethionews433et @Ethionews433et
👇👇
ቴዎድሮስ በጽሁፉ እንዳረጋገጠው፣ ሰይፉ ፋንታሁን አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በህይወት እንዲቆይ ከማንም በላይ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ ከነበሩት ጥቂት የቅርብ ሰዎች አንዱ ነው።
ከአንድ ዓመት በፊት አርቲስት ነጻነት ለህክምና ወደ ህንድ ሲጓዝ፣ ሰይፉ ፋንታሁን ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አድርጓል። በቅርቡም ነጻነት ሲታመም፣ ሰይፉ ከውጭ ሀገር (አሜሪካ) ዶክተር በማስመጣት እና አስፈላጊውን ወጪ ሁሉ በመሸፈን አርቲስቱ እንዲድን የቻለውን ሁሉ አድርጓል።
ደራሲው እንዳስነበበው፣ ሰይፉ ለነጻነት "የሚያስፈልገውን ወጪ ሁሉ እኔ አመጣለሁ፤ አንተ ብቻ ተረጋግተህ ህክምናህን ተከታተል" በማለት በተደጋጋሚ ሲለምን እና ሲደግፍ ነበር።
ሰይፉ ለምን አልተናገረም?.... በቀብሩ ዕለት ሰይፉ ወደ መድረክ ወጥቶ ንግግር ያላደረገበት ምክንያት፣ የንቀት ወይም የቸልተኝነት ሳይሆን "ጥልቅ የሆነ የልብ ስብራት እና ቁጭት" ውጤት መሆኑን ቴዎድሮስ ገልጿል።
"ሰይፉ እና ጥቂት ወዳጆቹ የትናንቱ የቀብር ዕለት እንዳይመጣ አቅማቸው የፈቀደውን እና ከዚያም በላይ አድርገዋል" ያለው ጸሐፊው፣ የልፋታቸው ውጤት መና ቀርቶ አርቲስቱ በማረፉ የተሰማቸው ጥልቅ ሀዘን እና ቁጭት ዝምታን እንዲመርጡ እንዳደረጋቸው አመላክቷል።
ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ የሰይፉን ሰብእና ሲገልጽ፣ "ሰይፉ ቧልተኛ ቢመስልም፣ በድብቅ የእውነት ክርስትናን የሚኖር ሰው ነው" ብሏል። ብዙውን ጊዜ እርዳታ ሲያደርግ "ከአሜሪካ አንድ ወዳጄ የላከው ነው፣ ስሜ አይጠቀስ ብሏል" በማለት የራሱን ገንዘብ ለሌላ ሰው ስም ሰጥቶ የሚረዳ፣ የሰውን ክብር የማይነካ እና በችግር ላይ የማይጨፍር ሰው መሆኑ ተመስክሮለታል።
ጸሐፊው ሲያጠቃልልም፣ "በቀብራችሁ ላይ ማቅ ለብሰው ከተገኙት ይልቅ፣ ሳትሞቱ በህይወት እያላችሁ የደራረሱላችሁ እና ዝም ያሉት የእናንተ ጠቃሚ ወዳጆች ናቸው" ሲል አስተማሪ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ምንጭ- ዘሐበሻ
@Ethionews433et @Ethionews433et
❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️
🫶🫶🫶🫶🫶🫶🫶🫶🫶🫶🫶🫶
😘😘😘😘😘😘😘😘😘😘😘😘
▶️የቱርክ ፊልም JOIN 👈 ይንኩ
▶️የአሜሪካ ፊልም JOIN 👈 ይንኩ
▶️ የህንድ ፊልም JOIN 👈 ይንኩ
▶️የቻይና ፊልም JOIN 👈 ይንኩ
▶️የአማርኛ ፊልም JOIN 👈 ይንኩ
▶️ተከታታይ ፊልሞች JOIN 👈 ይንኩ
▶️ አኒሜሽን ፊልሞች JOIN 👈 ይንኩ
▶️አክሽን ፊልሞች JOIN 👈 ይንኩ
▶️የጫካ ፊልሞች JOIN 👈 ይንኩ
▶️የፍቅር ፊልሞች JOIN 👈 ይንኩ
▶️የsex ፊልሞች JOIN 👈 ይንኩ
✅ እንደ ምርጫው መርጦ ይቀላቀሉ ✅
JOIN
ይቀላቀሉ ይቀላቀሉ
⚡️ Waver 👉 @wase_vip1
የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ።
በስርዓተ ቀብሩ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የኪነ ጥበብ ቤተሰቦች፣ አድናቂዎቹ እንዲሁም ወዳጅ ዘመዶቹ ተገኝተዋል።
ባደረበት ህመም ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት፣ በፊልም ደራሲነትና አዘጋጅነት፣ በተዋናይነት እና በሌሎች የጥበብ ስራዎቹ በኪነ ጥበቡ ቤተሰብ ዘንድ ይታወቃል።
ሁለገቡ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ለበርካታ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈውን የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ በመሆን አገልግሏል።
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በፊልም እና በቴአትር ስራዎቹ እጅግ ተወዳጅ የነበረ ሲሆን፤ ሲቲ ቦይስ፣ ሳልነግራት፣ ያንቺው ሌባ፣ ኤፍቢአይ፣ ሚስተር ኤክስ፣ ቾምቤ እና ሌሎችም ድንቅ ብቃቱን ያሳየባቸው ፊልሞች ናቸው።
ፍሬሽ ማን ከህዝብ ጋር ያስተዋወቀው የቴአትር ስራው ነው።
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ባለትዳርና የ3 ልጆች አባት ነበር።💔💔💔
@Ethionews433et @Ethionews433et
የፑንትላንድ የጸጥታ ኃይሎች በሰሜናዊ ሶማሊያ ባካሄዱት መጠነ ሰፊ የካልሚስካድ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር የዋሉ የውጭ ሀገር የISIS ታጋዮችን ዝርዝር ይፋ አድርገዋል በዚህ መረጃ መሠረት በቁጥጥር ስር ከዋሉት ታጋዮች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ማለትም ሀያ ሶስቱ ኢትዮጵያውያን መሆናቸው ታውቋል
ይህም ዓለም አቀፍ አሸባሪ ቡድኑ ISIS በኢትዮጵያ ውስጥ ሰፊ የቅጥር እና የማደራጀት ስራ እየሰራ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ ማሳያ ነው
በቁጥጥር ስር የዋሉት ኢትዮጵያውያን ስም ዝርዝር እንደሚያሳየው፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ መሆናቸው ስጋቱን ከፍ ያደርገዋል። ከኢትዮጵያውያኑ በተጨማሪ የየመን፣ የቱርክ፣ የሞሮኮ እና የታንዛኒያ ዜጎች በቡድኑ ውስጥ ተሳታፊ ሆነው ተገኝተዋል።
ይህ አሳሳቢ መረጃ እንደሚያመለክተው አክራሪ ኃይሎች በሀገሪቱ ውስጥ በስውር መረባቸውን በመዘርጋት ወጣቶችን ለሽብር ተግባር እያሰለጠኑ ወደ ጎረቤት ሀገራት እያሰማሩ ይገኛሉ
በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግስት በአሁኑ ወቅት በሃይማኖት አክራሪዎች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ በመቀጠል ይህንን ውስጥ ለውስጥ እየተካሄደ ያለን አደገኛ እንቅስቃሴ ከወዲሁ ሊታገለው ይገባል
የሀገሪቱን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅም በስውር የሚንቀሳቀሱ የሽብር መረቦችን የመበጣጠስ ስራ የቅድሚያ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ነው
በመሆኑም መንግስት ከጎረቤት ሀገራት የደህንነት ተቋማት ጋር ያለውን ትብብር በማጠናከር እና በሀገር ውስጥ ያለውን ጥብቅ ክትትል በማስቀጠል ይህንን ስር እየሰደደ የመጣውን የአክራሪነት ስጋት ሳይባባስ ሊያስቆመው እንደሚገባ ተመልክቷል
@Ethionews433et @Ethionews433et
ዛሬ ጥር 10 ቀን በሸገር ከተማ አስተዳደር፣ በኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የፋንታ መድኃኔዓለም ደብር የጥምቀት ከተራ በዓልን ሲያከብሩ እና ሲያስተባብሩ የነበሩ አራት ወጣቶች በኤሌክትሪክ አደጋ ሕይወታቸው አልፏል።
የቤተክርስቲያኑ ምዕመናን ታቦተ ሕጉን አጅበው ወደ ባሕረ ጥምቀት በማቅናት ላይ እያሉ፣ በሚጓዙበት ሰረገላ እና በኤሌክትሪክ መስመር መካከል በተፈጠረ ንክኪ የ4 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ አልፏል።
@Ethionews433et @Ethionews433et
ዋሽንግተን ዲ.ሲ — የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ በላኩት ይፋዊ ደብዳቤ፣ አሜሪካ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ (GERD) ዙሪያ በሚደረገው ድርድር ላይ ዳግም ጣልቃ ገብታ ለመሸምገል ዝግጁ መሆኗን አስታወቁ።
January 16 ቀን 2026 ዓ.ም (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር) የተፃፈው ይህ ደብዳቤ፣ በናይል ወንዝ የውሃ አጠቃቀም ላይ ያለውን የቆየ አለመግባባት "አንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ" ለመፍታት ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
1. ፕሬዝዳንት ትራምፕ ግብፅ በእስራኤል እና በሃማስ መካከል ለተደረገው የተኩስ አቁም ስምምነት ላደረገችው ሽምግልና ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
2. የአባይ ውሃ ክፍፍል" ጥያቄን በኃላፊነት ስሜት ለመፍታት የአሜሪካ ሽምግልና እንዲቀጥል ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።
3. ፕሬዝዳንቱ በደብዳቤያቸው ላይ "ማንኛውም የቀጠናው ሀገር የናይልን ውድ ሀብት ብቻውን መቆጣጠር የለበትም፤ ጎረቤቶቹንም መጉዳት የለበትም" ሲሉ የአሜሪካን አቋም አረጋግጠዋል።
4. ስምምነቱ ለግብፅ እና ለሱዳን በድርቅ ወቅት አስተማማኝ የውሃ ፍሰት እንዲኖር የሚያረጋግጥ፣ ለኢትዮጵያ ደግሞ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ዕድል የሚሰጥ መሆን እንዳለበት ጠቁመዋል።
5. እንዲያውም ኢትዮጵያ የምታመነጨውን ኃይል ለግብፅ እና ለሱዳን ልትሸጥ ወይም በነፃ ልትሰጥ የምትችልበትን ሁኔታ ጠቅሰዋል።
6. በትራምፕ አገላለጽ በግድቡ (DAM!) ዙሪያ ያለው ውጥረት ወደ ከፍተኛ ወታደራዊ ግጭት እንዳያመራ ስጋታቸውን ገልጸው፣ ጉዳዩ በአጀንዳቸው አናት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
7. ይህ ደብዳቤ ግልባጭ (CC) የተደረገላቸው ለኢትዮጵያው ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ፣ ለሱዳኑ ጄኔራል አል-ቡርሃን፣ እንዲሁም ለሳውዲ አረቢያ እና ለተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መሪዎች ነው።
ይህም ትራምፕ የቀጠናውን ሀያላን ሀገራት በማሳተፍ አዲስ የዲፕሎማሲ ጫና ለመፍጠር ማቀዳቸውን ያሳያል።
የቀድሞው የትራምፕ አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ በወሰደው ጠንካራ አቋም የሚታወስ ሲሆን፣ ይህ አዲስ ደብዳቤ በኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን መካከል ለዓመታት ተቋርጦ የነበረውን የሶስትዮሽ ድርድር ወዴት ሊያመራው እንደሚችል የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
እናንተስ በዚህ ጉዳይ ምን ትላላችሁ❓
Via The White House
ጉርሻ page
@Ethionews433et @Ethionews433et
Reviews channel
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «4-3-3 WORLD NEWS» is a Telegram channel in the category «Новости и СМИ», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 16.4K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 12.5, with 1 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 4.8 ₽, and with 1 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий