
- Main
- Catalog
- Religion & Spirituality
- Advertising on the Telegram channel «የክርስትና መልስ»
Advertising on the Telegram channel «የክርስትና መልስ»
ሙስሊሞች በክርስትና ላይ የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች በመጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት የሚመልስ ቻናል ነው።
Channel statistics
በነገረ መለኮት ትምህርት ውስጥ "አብ ያለ ወልድ ቃልነት መናገር አይችልም፣ ወልድ ያለ አብ ልብነት ማሰብ አይችልም፣ ወይም ያለ መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት መኖር አይችሉም" የሚለው አገላለጽ ሲነሳ፣ ብዙዎች ይህ "አለመቻል" በመለኮት ዘንድ ያለን ጉድለት ወይም ድክመት የሚያመለክት ሊመስላቸው ይችላል። ይህ "አለመቻል" መለኮታዊ ድክመትን ሳይሆን፣ መለኮታዊ ፍጹምነትንና ባሕርያዊ አንድነትን የሚያረጋግጥ ቀመር ነው።
እግዚአብሔር እንደ ፍጡር የተሰባሰበ (Composite) አይደለም። እኛ ሰዎች ለማሰብ አእምሮ፣ ለመናገር ጉሮሮ፣ ለመኖር ደግሞ እስትንፋስ የሚያስፈልገን "ጎደሎ" ፍጡራን በመሆናችን ነው። እነዚህ መሣሪያዎች ከሌሉን "አንችልም" የምንለው ከውጭ እርዳታ ስለምንፈልግ ነው። አምላክ ግን ሁልጊዜም በራሱ ሙሉና ዘላለማዊ ንቁ ህልውና ያለው ነው (Pure Act)። እርሱ እንደ እኛ ሰብአዊ ፍጡራን ታስቦበት የሚደረግ ሥራ ወይም ጊዜ የሚፈጅ ሂደት የለበትም። በእርሱ ዘንድ ማሰብ፣ መናገርና መኖር የባሕርዩ ዘላለማዊ መገለጫዎች ናቸው እንጂ ቆይተው የሚመጡ ድርጊቶች አይደሉም። "አብ ያለ ቃሉ (ወልድ) መናገር አይችልም" ስንል፣ ልክ "እሳት ያለ ብርሃን ሊያበራ አይችልም" እንደምንለው ዓይነት ባሕርያዊ መሳ ለመሳነትን መግለጣችን ነው። ብርሃን ለእሳቱ "ረዳት" ሆኖ የመጣ ሳይሆን የእሳቱ ማንነት እንደሆነ ሁሉ፣ ወልድም የአብ የባሕርይ ቃሉ በመሆኑ፣ አብ ያለ ቃሉ ቢኖር ኖሮ "ቃል አልባ" ወይም "ዲዳ" ይሆን ነበር። ይህ ደግሞ በመለኮት ዘንድ የማይታሰብ ጉድለት ነው።
ለእስልምና ወገኖችም የሚሆን ጠንካራ አምክንዮ እዚህ ጋር እናንሳ። አላህ "ተናጋሪ" መሆኑን ሁሉም ሙስሊም ይስማማል። ጥያቄው ግን፦ "አላህ ያለ ቃሉ መናገር ይችላልን?" የሚል ነው። "አይችልም" ካሉ—እኛ የምንለውን "ባሕርያዊ አለመነጣጠል" አረጋገጡ ማለት ነው። "ይችላል" ካሉ ግን—አምላክን ያለ ቃሉ "ዲዳ" እያደረጉት ነው። እኛ "አብ ያለ ቃሉ መናገር አይችልም" ስንል፣ ቃሉ (ወልድ) ከአብ ጋር ዘላለማዊና የማይነጣጠል መሆኑን፣ አምላክም መቼም ቢሆን "ቃል አልባ" ሆኖ እንደማያውቅ ማረጋገጣችን ነው። ይህም አምላክን ፍጹም ያደርገዋል እንጂ አያሳንሰውም። አምላክን "አንድ" ለማድረግ ሲባል ቃሉንና እስትንፋሱን (ሕይወቱን) ከእርሱ መነጠል፣ አምላክን እንደ ድንጋይ ወዳለ ግዑዝ ነገር (ጥይት አልባ መሣሪያ) ይለውጠዋል።
አብ "ልብ"፣ ወልድ "ቃል"፣ መንፈስ ቅዱስ "እስትንፋስ" ናቸው። በሰውነታችን ውስጥ ልብ ያለ ቃልና ያለ እስትንፋስ ሕያው ሊሆን እንደማይችል ሁሉ፣ በመለኮትም አንዱ አካል ያለ ሌላው ህልውና የለውም። ይህ ግንኙነት "አለመቻል" ሳይሆን "አለመነጣጠል" (Inseparability) ይባላል። እያንዳንዱ አካል በባሕርይው ሙሉ አምላክ ቢሆንም፣ ይህ ሙሉነቱ የሚገኘው በሦስትነቱ ውስጥ ባለ አንድነት ነው። አብ "ምንጭ" በመሆኑ፣ ያለ ቃሉና ያለ እስትንፋሱ ምንጭ ሊባል አይችልም። ስለዚህ ወልድና መንፈስ ቅዱስ የአብ የባሕርይ ገንዘቦቹ እንጂ ከውጭ የመጡ የኃይል ምንጮች አይደሉም።
የአካላት ልዩነት በመገኛ ግንኙነት እንጂ በኃይል መበላለጥ አለመሆኑን ይሰመርበት። አብ የቃሉና የእስትንፋሱ "መገኛ" በመሆኑ፣ ያለ እነርሱ አይታሰብም ማለታችን አምላክን ሕያውና ተናጋሪ ያደርገዋል። በእስልምናው "ተውሂድ" አምላክን ከባሕርያቱ ነጥሎ "ብቸኛ" ለማድረግ ሲሞከር፣ አምላክ የፍቅርና የመግባቢያ ቃል የሌለው "ባዶ" አካል ይሆናል። እውነተኛው መለኮታዊ ፍጹምነት ግን አብ ሁልጊዜ በቃሉ (በወልድ) ተናጋሪ፣ ሁልጊዜም በእስትንፋሱ (በመንፈስ ቅዱስ) ሕያው ሆኖ መኖሩ ነው።
"አይችልም" የሚለው ቃል በመለኮት ምስጢር ውስጥ ትርጉሙ "አይሰማማም" (Incompatibility) ማለት ነው። መለኮት ያለ ቃሉ መሆኑ ከባሕርዩ ጋር አይስማማም፤ መለኮት ያለ ሕይወቱ (እስትንፋሱ) መሆኑ ከፍጹምነቱ ጋር አይሄድም። ስለዚህ ሦስቱ አካላት እርስ በርስ የሚመሰረቱ ዘላለማዊ ህልውናዎች ናቸው። ይህ አምላክ በራሱ የተሟላ (Self-sufficient) እና የማይከፈል ሕያው መሆኑን የሚያሳይ ታላቅ ምስጢር ነው።
በአጠቃላይ፣ መለኮት በባሕርይ አንድ ቢሆንም፣ በግብር (በአካል) ግን ሦስት ነው። ሥጋን የመንካትና የመዋሐድ ግብር ደግሞ የቃሉ (የወልድ) ብቻ በመሆኑ፣ እርሱ ሰው ቢሆንም ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለው የባሕርይ አንድነት ግን ጸንቶ ይኖራል።
መለኮት በባሕርይ አንድ ቢሆንም በአካል ሦስት መሆኑን፣ እንዲሁም ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ ብቻ ሰው መሆኑን ለሰው ልጅ አእምሮ በሚመጥን መልኩ በተለያዩ ተፈጥሯዊ ክስተቶች ልናስረዳው እንችላለን። እነዚህ ምሳሌዎች መለኮት ሳይከፋፈል እንዴት አንዱ አካል ብቻ ለዓለም እንደታየ ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ።
በመጀመሪያ የንግግርን ሂደት እንደ ምሳሌ እንውሰድ። አንድ ሰው "አንድ ቃል" ቢናገር፣ ያ ቃል በውስጡ ድምፅን፣ ዜማንና ትርጉምን የያዘ አካል አለው። እነዚህ ሦስቱ ከአንድ እስትንፋስ የሚገኙ የአንድ ቃል ክፍሎች ናቸው። ሆኖም ያ ቃል ወደ ሰሚው ጆሮ ሲደርስ፣ ጆሮን በቀጥታ የሚነካውና የሚጋፋው "ድምፅ" ብቻ ነው። ትርጉሙና ዜማው በድምፁ ውስጥ ሆነው አብረው ቢመጡም፣ ጆሮን ነክተው የሚሰሙት ግን በድምፁ አማካኝነት ነው። ወልድ (ቃለ አብ) ወደ ዓለም መጥቶ ሥጋን ሲዋሐድም የሆነው ይህ ነው፤ አብና መንፈስ ቅዱስ በባሕርይ ከእርሱ ጋር ቢኖሩም፣ በቀጥታ ከሥጋ ጋር የተዋሐደውና በምድር ላይ የታየው ግን "ቃል" የተባለው አካል ብቻ ነው።
ይህንኑ ሐሳብ በጥበብና በጽሕፈት ምሳሌ ይበልጥ ማጥከር ይቻላል። አንድ ሰው በውስጡ ጥበብ ወይም ዕውቀት አለው፤ ያንን ዕውቀቱን በወረቀት ላይ ለመግለጥ ቢፈልግ በቃል አማካኝነት ይጽፈዋል። ቃሉ ወረቀቱ ላይ ሰፍሮ ሲታይ፣ ወረቀቱን የነካውና የታየው ቃሉ ብቻ ነው። በወረቀቱ ላይ ያለው ቃል ግን ከሰውየው ዕውቀትና ከማንነቱ የተለየ አይደለም። በተመሳሳይ መልኩ ወረቀት በሆነው ሥጋ ላይ የሰፈረው ቃል (ወልድ) የአብንና የመንፈስ ቅዱስን መለኮታዊ ዕውቀትና ባሕርይ በሙሉ ይዞ ቢመጣም፣ በሥጋ ወረቀት ላይ ተጽፎ የታየው ግን ወልድ ብቻ ነው።
ሌላው አስደናቂ ምሳሌ የማየት ሂደት ነው። ማየት እንዲቻል ዐይኑ፣ ብርሃኑና የማየት ኃይሉ የግድ ያስፈልጋሉ። እነዚህ ሦስቱ ባይተባበሩ ማየት አይቻልም። ነገር ግን አንድን ነገር ስናይ፣ በነገሩ ላይ አርፎ ነገሩን ገልጦ የሚያሳየን "ብርሃኑ" ብቻ ነው። ዐይን በሩቅ ሆኖ ያያል እንጂ ነገሩ ላይ አያርፍም፤ የማየት ኃይልም በውስጥ ሆኖ ይሠራል እንጂ ነገሩን አይነካም። በዚህም መሠረት ነገሩ ላይ አርፎ የታየው (ሰው የሆነው) ብርሃኑ (ወልድ) ብቻ ነው። ነገር ግን ዐይኑ (አብ) እና ኃይሉ (መንፈስ ቅዱስ) ከብርሃኑ ተለይተው ስለማይኖሩ፣ በሥራው ሁሉ አብረውት አሉ። ሦስቱም ተባብረው "አንድ እይታን" እንደሚፈጥሩ ሁሉ፣ በመለኮትም አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ አንድ ሕልውና፣ አንድ ፈቃድና አንድ አምላክነት ያላቸው አንድ መለኮት ናቸው።
በመጨረሻም በቤተ መቅደስ ውስጥ ያለውን የጽናና የዕጣን ምሳሌ እንመልከት። በጽና ውስጥ የሚቃጠል ፍም (አብ) አለ፤ ያ ፍም የሚያወጣው ብርሃን (ወልድ) እና ከእርሱ የሚወጣው መዓዛ (መንፈስ ቅዱስ) በአንድ ጽና ውስጥ ይገኛሉ። የዕጣኑ መዓዛ ቤቱን በሙሉ ሞልቶ ልብሳችንን በሚለክፈው ጊዜ፣ ልብስህን የነካውና የሸተተው "መዓዛው" ብቻ ነው። መዓዛው ልብስህን ስለለመደ ግን ፍሙ ወይም ብርሃኑ ልብስህ ላይ አረፈ አይባልም። መለኮትም አንድ ቢሆንም፣ ወደ እኛ መጥቶ ሥጋን የለበሰውና የሰውን ባሕርይ (ልብሳችንን) የነካው ወልድ ብቻ ነው። እርሱ ግን ከፍሙ (አብ) እና ከብርሃኑ (መንፈስ ቅዱስ) ሳይለይ እንደመጣ እናምናለን።
እነዚህ ሁሉ ምሳሌዎች የሚያረጋግጡት አንድ እውነትን ነው፦ መለኮት በባሕርይ አንድ፣ በግብርና በአካል ሦስት እንደሆነና ሰው የመሆን ምስጢር ደግሞ የቃሉ (የወልድ) ብቻ መሆኑን ነው። ይህም መለኮትን ሳይከፋፍል፣ አምላክን ለሰው ልጆች በሚታይና በሚዳሰስ መልኩ እንዲገለጥ አድርጎታል።
የሥላሴ ትምህርት የሚያስተምረው እግዚአብሔር አንድ የማይከፈል መለኮታዊ ባሕርይ (Ousia) መሆኑን ነው። ይህ አንድ ባሕርይ በሦስት ልዩ አካላት (Hypostases) ማለትም በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፍጹም ሆኖ ይኖራል። እነዚህ አካላት በባሕርይ አንድ (Consubstantial) በመሆናቸው፣ እያንዳንዱ አካል ያለ መከፋፈልና ያለ መደባለቅ የተሟላው አንድ አምላክ ነው። በእግዚአብሔር ዘንድ እንደ ቁስ የሚቆራረስ "የተከፋፈለ አካል" ወይም እንደ ገመድ የሚበጠስ "መካከለኛ ባሕርይ" የለም። አካላት በአንዱ ረቂቅና ወሰን በሌለው ባሕርይ ውስጥ ያሉ ዘላለማዊ ግንኙነቶች እንጂ እንደ ሰው አካል የሚበታተኑ ብልቶች አይደሉም።
አካላት እርስ በርስ የሚለዩት በግንኙነታቸው (አብ ወላጅ፣ ወልድ ተወላጅ፣ መንፈስ ቅዱስ ሠራጺ) እንጂ በባሕርይ አይደለም። ስለዚህ በአንዱ አካል ላይ የሚደርስ ድርጊት—ለምሳሌ ሰው መሆን—ወደ ሌሎቹ አካላት አይፈስም፤ ምክንያቱም አካላት የባሕርይ "ክፋዮች" ሳይሆኑ የባሕርዩ ሙሉ መገለጫዎች በመሆናቸው ነው። ሰው መሆን (ሥጋዌ) የመለኮታዊ ባሕርይ ለውጥ ሳይሆን፣ በወልድ አካል ብቻ የተከናወነ አካላዊ ተዋሕዶ (Hypostatic Union) ነው። ወልድ በተለየ አካሉ ፍጹም የሰውነትን ባሕርይ ከራሱ ጋር አዋሐደ፤ ይህም ተዋሕዶ ያለ መለወጥና ያለ መከፋፈል የተፈጸመ ነው። "ግማሽ መለኮት ሰው ሆነ" ሊባል አይችልም፤ ወልድ በሙሉነቱ የማይከፈል አምላክ በመሆኑ መለኮታዊ ባሕርዩ ሳይለወጥ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ሙሉ ሆኖ ይኖራል።
ብዙውን ጊዜ የእስልምና ወገኖች "ሥላሴ አምላክን ይከፋፍላል" የሚል የተሳሳተ ትችት ይሰነዝራሉ። እውነታው ግን ተቃራኒው ነው፤ ትክክለኛው የሥላሴ ትምህርት የመለኮትን አለመከፋፈልና አለመወሰን የሚያረጋግጥ ብቸኛው መንገድ ሲሆን፣ የእስልምናው "ተውሂድ" ግን አምላክን ወይ ወደ "ፍጡርነት" ወይም ወደ "ባዶነት" የሚለኩስ ድክመት አለበት። እኛ የምናመልከው አምላክ ረቂቅ፣ የማይወሰንና በሁሉ የሞላ ሕያው መለኮት ነው። አንድ ነገር "ሕያው" ለመባል የግድ ልባዊነት (ሀልዎ)፣ ቃላዊነት (ነባቢነት) እና ሕያውነቱ (እስትንፋሱ) ሊኖሩት ይገባል። እነዚህ ከሌሉት ወይ ሕልውና የለውም፣ ወይም ደግሞ እንደ ድንጋይ ያለ "ጉዑዝ" ነው ማለት ነው። መለኮት የማይከፈል በመሆኑ ቃሉ ባለበት ሁሉ ልቡና እስትንፋሱ አሉ። እያንዳንዱ ባሕርዩ ሙሉውን መለኮታዊ "እኔነት" ስለሚወክሉ ሦስቱም "እኔ" የሚሉ አካላት ናቸው እንላለን።
ለእስልምና ወገኖች የምናቀርበው ጥያቄ ይህ ነው፦ "አላህ ልብ፣ ቃልና እስትንፋስ አለው ወይስ የለውም?" የለውም ካሉ አላህ ሕልውና የሌለው ጉዑዝ ጣዖት መሆኑን አምነው መቀበል አለባቸው። አለው ካሉ ግን ከሦስቱ "እኔ" የሚለው ማነው? ቃሉ ብቻ "እኔ" የሚል ከሆነ መለኮት በቃሉ ተወስኗል ማለት ነው ስለዚህ አምላክ እንደፍጡር ውስን የሆነ ያደርገዋል ፤ ይህም አምላክን እንደ ፍጡር የተከፋፈለ ያደርገዋል። ቃሉም ልቡም "እኔ" የሚሉ ከሆነ ግን እኛ የምንለውን "ሦስት አካላት" ማረጋገጥ ነው።ምክንያቱም እኛ አካል የምንለው እኔነትን እንጂ ቁሳዊ አካል አይደለም። አላህ "ቃል" ካለው ያ ቃሉ አምላክ ነው ወይስ አይደለም? አይደለም ካሉ አላህ ከቃሉ ውጭ "ዲዳ" ነበረ ወይም ቃሉ ፍጡር ነው ማለት ይሆናል፤ አምላክ ነው ካሉ ደግሞ ሁለት አላህ ሊሉ ነው? ወይስ እንደ እኛ "አንድ መለኮት በቃሉ የታወቀ አካል" የሚለውን ይቀበላሉ?
የእስልምናው አምላክ ትርጓሜ ምክንያታዊነት ይጎድለዋል። አምላክን አንድ ለማድረግ ሲሉ "ባሕርይ አልባ" ያደርጉታል፤ ባሕርይ ለመስጠት ሲሞክሩ ደግሞ "የተከፋፈለና ውስን" ያደርጉታል። "ቃሉን ወይም ልቡን ለይቶ ነው ወይስ በአንድነት የሚያመልኩት?" ብለን ስንጠይቅ፤ ለይተን አናመልክም ካሉ ልቡ ባለበት ቃሉ ስላለ ሦስትነትን ያረጋግጣሉ። አንዱን ብቻ እንመርጣለን ካሉ ግን መለኮትን ከፈሉት ማለት ነው። እውነተኛው መለኮት ግን የማይከፈል ሕያው በመሆኑ፣ ልቡ በቃሉ፣ ቃሉ በሕይወቱ የታወቀና የተገለጠ ሥላሴ ነው። የእስልምናው "አላህ" ግን ወይ በቦታ የሚወሰን ፍጡር፣ ወይም ሕይወት የሌለው ጣዖት ሆኖ ያርፋል። ስለዚህ "እስልምና ጣዖት አምላኪነት ነው" ብንል፣ አምላክን "ቁስ" እና "ውስን" ከማድረግ የሚመነጭ እውነት ነው።
ብዙውን ጊዜ "መለኮት አንድ ከሆነ ለምን ሦስቱም አካላት ሰው አልሆኑም? መለኮታዊ ባሕርይ ሥጋን ከተዋሐደስ ሦስቱም ተዋሐዱ ማለት አይደለምን?" የሚሉ ጥያቄዎች ይነሳሉ። ለእነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ይሆን ዘንድ በሰውነታችን ውስጥ ያለውን የልብ፣ የቃልና የእስትንፋስ አንድነትና ልዩነት እንደ ምሳሌ መመልከት እንችላለን።
አንተ በልብህ የምታስበውን ቃል በድምፅ ብታወጣው፣ ያ ድምፅ የሰውን ጆሮ ይነካል። በዚህ ድርጊት ውስጥ ጆሮን የነካው "ድምፅህ ወይም ቃልህ" ብቻ ነው። ቃልህ ጆሮን ስለነካ ብቻ ልብህና እስትንፋስህ አብረው ጆሮን ነኩ አይባልም። ነገር ግን ቃልህ ጆሮን ሲነካ የቃልህ ባሕርይ ብቻውን መጥቶ አይደለም፤ ምክንያቱም ያለ ልብ መነሻነትና ያለ እስትንፋስ ኃይል ቃል "ድምፅ" ሆኖ ሊገለጥ አይችልምና። ስለዚህ ጆሮን በነካው ቃል ውስጥ የልብህና የእስትንፋስህ ባሕርይ (ሕልውና) ቢኖርም፣ የነካው አካል ግን ድምፅህ ብቻ ነው።
የእግዚአብሔር ወልድ ሰው መሆንም (ሥጋዌ) ትርጉሙ ይህ ነው። መለኮታዊ ባሕርይ የማይከፈል (Indivisible) በመሆኑ፣ ወልድ ሥጋን ሲዋሐድ የመለኮት ባሕርይ ሙሉ በሙሉ በእርሱ ዘንድ አለ። ሆኖም ሥጋን የተዋሐደው ግን የመለኮት "ቃል" (ወልድ) ብቻ ነው። ቃሉ ሥጋን ስለተዋሐደ የአብና የመንፈስ ቅዱስ ባሕርይ ከእርሱ ተለይቷል ማለት አይደለም። ልክ ድምፅህ ጆሮን ሲነካ ከልብህና ከእስትንፋስህ ባሕርይ ሳይለይ፣ ነገር ግን ራሱ ብቻ ጆሮን እንደሚነካው ማለት ነው። "የሰውነትህ ባሕርይ ጆሮን ነካ" ለማለት ድምፅህ ጆሮን መንካቱ በቂ እንደሆነ ሁሉ፣ መለኮታዊ ባሕርይ ሥጋን ተዋሐደ ሲባልም በአብና በመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ያለው ያው አንዱ የመለኮት ባሕርይ በወልድ አካል አማካኝነት ከሥጋ ጋር አንድ ሆነ ማለት ነው።
ይህ ተዋሕዶ ወልድን "ሰው" ሲያደርገው፣ አብንና መንፈስ ቅዱስን ግን ሰው አያደርጋቸውም። ምክንያቱም እንደ ቃል (እንደ ድምፅ) የመገለጥና የመነካት ግብር የቃሉ (የወልድ) ብቻ ነው። ቃልህ ከልብህና ከእስትንፋስህ ሳይለይ ወጥቶ ጆሮን እንደሚነካ ሁሉ፣ ወልድም ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ መጥቶ ሥጋን ተዋሐደ፤ ሰው የሆነው ግን ቃሉ ብቻ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስን እንደ እግዚአብሔር ቃል የምንቀበለው በጭፍን እምነት ሳይሆን፣ አእምሯዊና ታሪካዊ መረጃዎችን መሠረት አድርገን ነው። ለዚህም የሚከተሉትን ዋና ዋና ማስረጃዎች መመልከት ይቻላል፦
1. አስደናቂው አንድነትና የታሪክ ትክክለኛነት
መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በ1,600 ዓመታት ጊዜ ውስጥ በተለያዩ የኑሮ ደረጃ ላይ በነበሩ (እንደ ነገሥታት፣ እረኞች፣ ዓሣ አጥማጆችና ሐኪሞች ባሉ) 40 በሚሆኑ ሰዎች ነው።
💥 እነዚህ ሁሉ ሰዎች በተለያዩ ዘመናትና ቦታዎች ሆነው ቢጽፉም፣ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ግን አንድ ወጥ የሆነ መልእክትና ታሪክ አላቸው። ይህ መለኮታዊ አመራር ካልታከለበት በቀር በሰው ድካም ብቻ ሊመጣ የማይችል "አስደናቂ አንድነት" ነው።
💥ለምሳሌ የባቢሎን መውደቅ ከተማዋ ከመያዟ ከመቶ ዓመታት በፊት በኢሳይያስ መጽሐፍ ላይ በዝርዝር ተተንብዮ ነበር። እንዲሁም በዳንኤል መጽሐፍ ላይ የተገለጹት የኃያላን መንግሥታት መቀያየር በታሪክ በትክክል ተከስተዋል።
2. የሐዋርያት ሕይወትና የደማቸው ምስክርነት
💥ማንም ሰው ለውሸት ወይም ለፈጠራ ታሪክ ብሎ ሕይወቱን አሳልፎ አይሰጥም። ሐዋርያት ግን ያዩትና የዳሰሱት እውነት ስላላቸው ብቻ መከራን ተቀብለዋል።
💥 ትንሣኤውን የሰሙት በወሬ ሳይሆን "በዓይናችን አይተናል፣ በእጃችንም ዳስሰናል" (1 ዮሐንስ 1:1) በማለት ነው። አንድ ሰው ውሸት የሚዋሸው ለገንዘብ፣ ለሥልጣን ወይም ለዝና ነው። ሐዋርያት ግን ክርስቶስ ተነሥቷል በማለታቸው ያገኙት መከራንና ሞትን ብቻ ነው።
💥ክርስቶስ ሲያዝ ፈርተው የሸሹት ሐዋርያት፣ ከትንሣኤው በኋላ ግን በሞት ፊት እንኳን ሳይበገሩ መመሥከራቸው "አስገራሚ ነገር" እንዳዩ ትልቁ ማረጋገጫ ነው። የሰው ልጅ ለሚያምንበት እውነት ይሞታል እንጂ፣ ራሱ ለፈጠረው ውሸት አይሞትም። የሐዋርያት ደም የመጽሐፍ ቅዱስ እውነተኝነት ትልቁ ማኅተም ነው።
3. አሳማኝ የታሪክ ምስክሮች
የትንሣኤው ታሪክ "ተረት" እንዳይሆን የሚያደርጉት ሦስት መሠረታዊ የታሪክ እውነታዎች አሉ፦
💥የ500 ምስክሮች መኖር፦ ሐዋርያው ጳውሎስ ክርስቶስ በአንድ ጊዜ ለ500 ሰዎች እንደታየ ሲጽፍ (1 ቆሮንቶስ 15:6)፣ በወቅቱ በሕይወት ያሉ ምስክሮችን ጠቅሶ ነው። "ካላመናችሁኝ ሄዳችሁ የዓይን ምስክሮቹን ጠይቁ" የሚል ዓይነት ድፍረት የነበረው እውነት ስለያዘ ብቻ ነው።
💥አንድ ድምፅ በተለያዩ ቦታዎች፦ ቶማስ ወደ ሕንድ፣ ማርቆስ ወደ ግብፅ፣ ማቴዎስ ወደ ተለያዬ ቦታ ቢበታተኑም፤ ሁሉም ሳይገናኙ የሰበኩት ግን "ክርስቶስ ሞቷል፣ ተነስቷልም" የሚል አንድ ወጥ መልእክት ነው።
💥ባዶው መቃብር፦ ድርጊቱ የተፈጸመው ጠላቶቻቸው በሞሉባት በኢየሩሳሌም መሃል ነበር። መቃብሩ ባዶ መሆኑን ባያውቁ ኖሮ፣ ጠላቶቻቸው አስከሬኑን በማሳየት ወሬያቸውን በቀላሉ ማጋለጥ በቻሉ ነበር።
💥በእስልምና ትምህርት መሠረት ሐዋርያት (ሐዋርይዩን) የአላህ ታማኝ አገልጋዮች ተደርገው ይታያሉ። ታዲያ አምላክ የመረጣቸው እነዚህ ታማኝ ሰዎች፣ አምላክ በሰቀለው "ሌላ ሰው" ተታልለው ለዘመናት "ኢየሱስ ተሰቅሎ ተነስቷል" ብለው በስህተት እንዲያስተምሩና በዚያው ስህተት ምክንያት እንዲገደሉ አምላክ ይፈቅዳል? ይህ የአምላክን ፍትሃዊነትና ሰዎችን አለማታለል (አምላክ ሰዎችን አያታልልምና) ጥያቄ ውስጥ ይጥላል። ይልቁኑ ሐዋርያት ያዩትን እውነት ሰበኩ፣ አምላክም ለእውነቱ እንዲቆሙ አደረጋቸው ማለት የበለጠ ምክንያታዊ ነው።
Reviews channel
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «የክርስትና መልስ» is a Telegram channel in the category «Религия и духовность», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 4.0K subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 7.2, with 0 reviews and an average score of 0.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 60.0 ₽, and with 0 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий