
🔥 Spring Deals: Final Week
Up to 70% off + 3.5% extra discount with promo code MAYFINAL!
Go to Catalog
17.6

Advertising on the Telegram channel «መጽሐፍ ቤት Bookstores»
5.0
Books, Audiobooks & Podcasts
Language:
English
443
0
Share
Add to favorite
Buy advertising in this channel
Placement Format:
keyboard_arrow_down
- 1/24
- 2/48
- 3/72
- Native
- 7 days
- Forwards
1 hour in the top / 24 hours in the feed
Quantity
%keyboard_arrow_down
- 1
- 2
- 3
- 4
- 5
- 8
- 10
- 15
Advertising publication cost
local_activity
$12.00$12.00local_mall
0.0%
Remaining at this price:0
Recent Channel Posts
ረጅም ፀሎት ኖሮኝ አያውቅም.....ይሄ በህይወት ዘመኔ የፀለይኩት ሁለተኛ ፀሎቴ ነው.....አንደኛው "እናቴን ቤቷ መልስልኝ...."....ነበር.....
ውጤቴ እስኪደርስ ከዚህ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ ዝብርቅርቅ ስሜት ተጫወተብኝ.....
የምፅአት ቀን እራሱ እንደዚህ የሚርቅ አይመስለኝም።
"እድል ሰጠኝ......".....ተጠራሁ።
አላለቀም.....
🫳ሸዊት
400
12:05
20.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-16✨✨
ዮናስ ደጄን ከረገጠበት ቀን ጀምሮ መመንመን የጀመርኩ መሰለኝ.....ጉንጮቼ በሁለት ቀን የሰመጡ አጥንቶቼም የተንኮታኮቱ ...ፀጉሬ ሳልነካው ተነቅሎ ያለቀ አይኔም ያለመነፅር አሻፈረኝ የሚል መሰለኝ....ከበሽታ በላይ እርጅና ተሰማኝ....
ምግብ የሚባል እምቢ አለኝ....በትግል የበላሁትም ወዲያው ይወጣል....አኳሀኔ የታመመም....ያረገዘም.....ያረጀም ሰው አይነት ነበር.....
የመክብብ ጓደኛ ጋር መሄድ አልፈለግኩም....ምንም ቢሆን የመክብብ ጓደኛ ነው....ዛሬ እንደታማሚ በቅንነት ቢያነጋግረኝ ነገ ላይ የመክብብ የሆነ ነገር ሆኜ ቢያየኝ ጣቱን ለመቀሰር አንደኛ ነው.....
ምንም ባደርግ ሊለቀኝ ያልቻለው መክብብ ላይ ያለኝ ተስፋ ነው....እንዲህ ነው ብሎ አፍ አውጥቶ አልነገረኝ ነገር.....ፍቅር ይኑርበት ሀዘኔታ በውል አለየሁት ነገር....ነገ ኖረም አልኖረም ግን ውስጤ የሚጠነቀቅለት ብቸኛው ሰው ነው....
"ከባለቤቴ ጋር ስንተዋወቅ ጀምሮ ቫይረሱ ነበረበት....አልነገረኝም.....እንኳን ይሄ ቫይረስ ጉንፋን አሞት የሚያውቅም አይመስልም ነበር....በጣም እንደሚወደኝ በአስር ጣቴ የምፈርምለት ሰው ነበር....ወደ አልጋ ሲገፋኝ በጄ አላልኩትም ነበር.....እንደሚወደኝ እና ከኔ ሌላ ማግባት እንደማይፈልግ ....ከኔ ሌላ ማንንም እንደማያልም እያለቀሰ ነገረኝ.....ትዝ ይለኛል አለቃቀሱ....ያሳሳ ነበር....ግን ስላለቀሰ አልነበረም ያመንኩት.....እንዲሁ ዝም ብዬ ነው ያመንኩት....
ከሱ ጋር በተኛሁ ማግስት ህዳር ሚካኤል ነበር......ሌላ ጊዜ ማህሌት አድሬ ቅዳሴን አስቀድሼ እስኪያልበኝ የምዘምረው ልጅ አዳሩን እስኪያልበኝ ባለግኩ.....
የሆነ አፋፍ ላይ ቆሜ በርቀት ታቦት ሸኘሁ.....በርቀት አለቀስኩበት....
ቀናት ወራትን ሲወልዱ በእንባ ተለምኜ የሰጠሁትን ገና ሲጠጋኝ ማቀበል ጀመርኩ....ሀጥያት ሲለመድ ፅድቅ ይመስላል...ማፈር ስናቆም ውድቀታችን "ሀ" ብሎ ይጀምራል.....
"ሀ" አልኩኝ....
ልክ ያልሆነ ስራ እየሰራሽ የሚሰማሽ ልክነት ካለ አእምሮሽ ሚዛኑን እየሳተ ነው.....የሰው ልጅ ይለምዳል.....ደግነትንም ክፋትንም....ሀጥያትንም ፅድቅንም....ጉብዝናንም ስንፍናንም.....መልበስንም መራቆትንም....ማግኘትንም ማጣትንም.....ቤተ እምነቱንም ክለቡንም.....ሁሉንም ይለምዳል.....
ጭንቅላት ሞኝም ብልጥም ነው....ያስብልሻልም አያስብልሽምም......ያስለመድሽውን ይለምዳል.....ስታስቀሪበት እንደራበው ህፃን ልጅ ያጣድፍሻል.....ጭንቅላት ባለጌም ጨዋም ነው.....ሁሉንም ይለምዳል.....ጭንቅላት የልብ ወዳጅ ነው አይገምትሽም.....ጭንቅላት ከአባት ገዳይ የከፋ ጨካኝም ነው.....ሲበቃው በቃው ነው።
ባለቤቴ እንክርዳድ የሌለበት ስንዴ ነበረ....የተለቀመ ስንዴ.....እንዲህ ነው ብለሽ እንከን የማታወጪለት አይነት ሰው.....
ከሰጠኝ በሽታ በላይ የሄደበት መንገድ አቆሰለኝ....የሞኝ ውሳኔ ቢሆንም ቫይረሱ እንዳለበት ቢነግረኝ እንደማልተወው ነው የምነግርሽ.....ይሄ ለኔ ልክ ያልሆነ ልክነት ነው.....አልተወውም ነበር....የሄደበት አቋራጭ መንገድ ግን እኔን በአካል ሰጥቶ በመንፈስ ነጠቀው......
ምክንያቱ "እወድሻለሁ" ነበር....ውስጠ ምስጢሩ ጎን ራስ ወዳድነት ነበር....አይገርምም ሁሉም ለራሱ ነው....ሲወድሽ እራሱ ለራሱ ነው....ላንቺ ብሎ የሚወድሽ አምላክሽ ብቻ ነው።
በሽታውን ሲሰጠኝ አስቦበት እንደነበር ሲነግረኝ አላፈረም....ምናል ባይነግረኝ.....ሁሉም መነገር የለበትም አይደል.....ምናል ድንገት ስሜታዊ ሆኜ ምናምን ቢለኝ....."ይሄን በሽታ ካሲያዝኳት ጥላኝ አትሄድም ብዬ ነው ያደረግኩት....ደሞም ልክ ነበርኩ አልሄድሽም.....".....ነበር ያለኝ.....ሞኝ ሆኖ እንጂ ሄጃለሁ....".....አለችኝ እና መጣሁ ያለ እንባዋን በአውራ ጣቷ ወደጎን አሽቀነጠረችው......ልመረመር ከሄድኩበት ክሊኒክ ህመምተኛ መቀበያ ወንበር ላይ የተቀመጠች ጎልማሳ ሴት ታሪክ ነው.....
"ሰው ሲከፋው ከድንጋይ ጋርም ያወራል...."....አለችኝ በትኩረት እያየችኝ.....መገረሜ በታሪኳ ብቻ ሳይሆን እንዴት ዘርግፋ ነገረችኝ በሚለውም ስለነበር ማስተዋሏ ገረመኝ።
ከሰፈር በጣም ርቄ የሄድኩበት ክሊኒክ ነው....ከሰፈር መራቄ ሀፍረቴን የሚቀንስልኝ መስሎኝ ነበር....አልቀነሰም።
"እድል ሰጠኝ....."......ስሜ ከውስጥ ተጠራ.....
እንደስሜ እድል እንዲሰጠኝ እየተመኘሁ ወደውስጥ ዘለቅኩ።
ከዶክተሩ ጋር አንድ አንድ አንድ ነገር ተነጋገርንና ሌላም ምርመራ ጨምሮ ወደ ላብራቶሪ ክፍል ላከኝ....
ላብራትሪስቷ ደሜን ቀዳች......የገላመጠችኝ መሰለኝ.....ለነገሩ በሶስት ታክሲ ስመጣ ሶስተኛው ታክሲ ውስጥ ጋቢና የተቀመጠው ሰውዬ ራሱ አስተያየቱ ስራዬን እንደሚያውቅ ነገር ነው....ከታክሲ ስወርድ ያየኃቸው አሮጊት አይነ ውሀቸው አላማረኝም....የክልኒኳ ፅዳት ሰራተኛ በምታፀዳው መሬት ፈንታ እኔን ብታፀዳኝ ደስ እንደሚላት አይኗ ነግሮኛል....ዶክተሩም ስራ ሆኖበት ነው.....
አባዬ ደወለ....ባነሳው "አንቺ ባለጌ...." የሚለኝ መሰለኝ....አላነሳሁትም....
የራሴን ስሜት ሰው ሁሉ ላይ እያየሁት ስሸበር ወጣ ብዬ ተነፈስኩ...."ተረጋጊ እድል ማንም አያውቅም ተረጋጊ.....".....አልኩኝና የቅድሟን ሴትዮ ጥዬ ወደመጣሁበት ወንበር አመራሁ.....የለችም።
ተመልሼ ወጥቼ ሰማዩ ላይ አፈጠጥኩበት.....ደመና ነበር....ወደላይ አንጋጥጬ "አደራህን አምላኬ አደራህን" አልኩት.....
380
12:03
20.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-15✨✨
"በሁለተኛ እድል ታምናለህ....."......አልኩት መክብብን ምሳ የምንበላበት ሬስቶራንት ተቀምጠን....
"እንደ ሁኔታው ይለያያል...."....አለኝና ለአፌ መጥኖ አጎረሰኝ.....ቀጥሎም "እየበላሽ አይደለም ምን ሆነሻል....."....አለኝ።
"ምንም አልሆንኩም....".....አልኩትና ያጎረሰኝን ውጬ እጄ ላይ ሳድበለብል የቆየሁትንም ደገምኩና እየበላሁ መሆኔን አስመሰከርኩ....
"ኧረ....ረ እንዲህ ከሆነማ ሁሌ ነው ምጋብዝሽ....አበላልሽ ኪስ አይጎዳም...."....አለና ያን ምትሀት ጥርሱን ገለጥ አደረገው።
"ስለ ሁለተኛ እድል እያወራሁህ ነበር.....".....አልኩት ለማስታወስ ያህል....
"ያው ሁለተኛ እድል እንደቦታው እና እንደሁኔታው ይለያያል....ለምሳሌ አንድ ነብስ ያጠፋ ወንጀለኛ...."....ከማለቱ አቋርጬው ከፍርድ ቤት ህግና መሰል ነገሮች የወጣ መልስ እንደምፈልግ ነገርኩት....
"specific አርጊልኛ.....እንዲሁ ሁለተኛ እድል የሚባል ነገር የለም እኮ እድሌ....."....አለኝ....እድሌ ስላለኝ ልቤ ሰላሳ ሁለት ጥርሱን አሳየ....ቢሆንም ግን ዮናስ የነገረኝን ነገር ሳስታውስ መክብብን ከሩቅ የማየው እንጂ የማልዳስሰው.....የማልነካው የእኔ የማልለው 'የማይበላ ወፍ' እንደሆነ ትዝ አለኝ።
"ስለ HIV አስበህ ታውቃለህ....."......አልኩት ድንገት....እንዳልኩት ያወቅኩት ካልኩት በኃላ ነበር።
"እኔንጃ ያው በሽታ ነው....ግን እንዴት አስበዋለሁ....አንዳንዴ በዙሪያሽ ያለ ሰው ሲታመም ነው በሽታውን የምታስተውይው አልያም 'በሽታ' የሚባል ነገር መኖሩን የምታስታውሽው እና እንደሚሞት ሰው የምትኖሪው....".....አለኝና አንድ ጉርሻ ደገመኝ።
"የሚሞት ሰው እንዴት ነው ሚኖረው...."....አልኩት አጣድፌ ጉርሻውን ከዋጥኩ በኃላ.....
"በርግጥ ሁላችንም ሟቾች ነን....ነገር ግን እንደሚሞት ሰው የሚኖረው በቁጥር ነው....ብዙ ሰው ግን እንደሚሞት የሚያስታውሰው ሲታመም ነው....እንደምትሞቺ ስታስቢ ለነገ የምታስቀምጪው ደስታ የለም....'ነገ' የምትይው ስራም ምግብም አይኖርም....እንደምትሞቺ ስታስቢ ነው መግቢያሽ የሚያሳስብሽ....የመጨረሻዎቹ ደይቃዎች ላይ ነው የነብስሽን ድምፅ የምትሰሚው....."
"ማን ታሞ ነው....?....."....አለኝ ቀጠል አድርጎ......"እኔ" አይባል ነገር ሆኖብኝ "አንድ ጓደኛዬ ታማ ነው..."....አልኩት....
"እንዴት ያዛት....".....ሲለኝ ደነገጥኩ....
"እንዴት ይይዛታል....እንደተለመደው ነዋ.... ትንሽ ስህተት ነበር ከፍቅር ጓደኛዋ ተጋብቶባት...."....አልኩትና ፊት ለፊቴ ያለውን ውሀ ባንድ ትንፋሽ ጨለጥኩት....
"ትንሽ ስህተት እንኳን አይደለም....ህይወት የሚያስከፍል 'ትንሽ' የለም....እንዴት ብዬ የጠየቅኩሽም እንዳልተለመደውም የሚታመሙ ሰዎች ስላሉ ነው....."
"ማለት....."...
"በደም ንክኪ..."....ሲለኝ የኢለመንተሪ ተማሪ የሆኖኩ መሰለኝ....ትንሽ ቆይቶ ስለ ሶስቱ የ'መ' ህጎች ሊያስተምረኝም ይችላል....እኔ ጭንቀቴ እንጂ እንዲህ የሚያስለፈልፈኝ ከመክብብ ጋር ሲጀመር ስለ በሽታ አይወራም....ከሱ ጋር መወራት ያለበት ስለ እሱ ብቻ ነበር....ስለ እሱ ውበት....ስለ ጥርሶቹ....ስለ አይኖቹ....ነፍስ ድረስ ስለሚሰማው ስለሚያረሰርሰው ድምፁ....ስለ መዳፎቹ....በቃ መወራት ያለበት ይሄ ነው.....
ድሮ ድሮ መልክ የበዛበት ወንድ አልወድም ነበር....ጭንቅላቴ ምን ሲል ይሄን መልክ የተትረፈረፈለት ወንድ እንደከጀለ አላውቅም.....
ከዮናስ የሰማሁትን ሰምቼ አልቅሼ አልወጣልኝም....አልወጣልኝም....እዚህ ከመክብብ ጋር ቁጭ ብሎ ምሳ ለመብላት ምን ያሀል እንደታገልኩኝ የማውቀው እኔ ነኝ....ስሜቱን ይሄ ነው ብዬ የምገልፀው አይነት አይደለም....
"ስለ HIV እናውራ...."....አልኩት ስለዩንቨርሲቲ ቆይታው ሲያጫውተኝ...ፊቱ ላይ ግርታ አነበብኩ።
"በጣም ተጨንቀሻል በጓደኛሽ ጉዳይ...."....ሲለኝ በአዎንታ አንገቴን ነቀነቅኩለት...
"ቆይ ሀኒም ታውቃታለች...."....ሲለኝ "ቀላል" ልለው ከአፌ ነው የመለስኩት.....
"አይ አታውቃትም....."..
"አንድ ዶክተር ጓደኛ አለኝ....ስልኩን እሰጥሽና መጠየቅ የምትፈልጊውን ጠይቂው...."
"..በርግጥ በጣም rare ኬዝ ነው....normally ግን በዚህ ፍጥነት ይሄን ያሀል weight loss አታደርግም...." የሚለኝ የደወልኩለት ዶክተር ነው.....'ከእኔ ጋር ከተለያየ በኃላ ነው የያዘው' ብዬ ለመቀበል የቻልኩትን እያደረግኩ ነው....ዶክተሩ የመለሰልኝ መልስ ተስፋዬን አሟጦ ጣለው.....
"ጓደኛሽ ቲቢ endemic area move አርጋ ነበር....?...."....አለኝ ቀጠል አድርጎ...
"አላውቅም ምነው...."...አልኩትና መልሱን በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ።
"ምን አልባት እንደዚያ አካባቢ ከሄደች እና እንደ ቲቢ ባሉ ተጓዳኝ በሽታ የመጠቃት እድል ከነበራት በተጨማሪም immunityዋ የሞተ ከሆነ significant weight loss በዚህ ፍጥነት ሊኖራት ይችላል።" ሲለኝ ትንሽ ልቤ ተስፋ ጫረ....የዮናስ አከሳስ የዘመናት ታማሚ እንጂ የቅርብ አላስመሰለውም ነበር።
ትንሽ እፎይ አልኩ.....
"ለማንኛውም ነገ እኔ ክሊኒክ ትምጣና ልያት...አንድ አንዴ misdiagnosed የመደረግ ሁኔታም ስለሚኖር ድጋሚ ትታይ".... አለኝና ተሰነባበትን.......
ጭንቀቴን መደበቅ እንዳቃተኝ የታወቀኝ ታናሽ እህቴን ክፉኛ ሳመናጭቃት ነበር....
አላለቀም....
✍ሸዊት
490
07:46
19.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-14✨✨
ከዮናስ ጋር ከተለያየን ስድስተኛ ወር አልፎ ሰባተኛውን ይዘናል...ጊዜው እንዴት ይሮጣል.....ፍቅር ቅብ የነበረው አብሮነታችን አንድ አመት ከመንፈቅ የቆየ ነበር....በዚ ሁሉ ጊዜ ውስጥ ዮናስ እንዲህ ነብስ ውጪ ነብስ ግቢ ሆኖ ያሳለፈበትን ቀን አላስታውስም።
"ምንድን ነው ንገረኝ እንጂ....".....አልኩት የተጋባብኝን ፍርሀት ለማባረር እየታገልኩ።
"እ....እ....".....አለና ተጨማሪ ሲንግል አዘዘ።
"ኧረ በፈጠረህ ዮናስ.....".....አልኩት ቆጣ ብዬ።
"አሞኛል.....".....አለኝ ያልጨረሰው ንግግር እንዳለ በሚያሳብቅ አስተያየት....በግንባሩ እያየኝ ነበር።
"ምንህን.....ሲቀጥል እኔ ምን ቤት ነኝ.....?.....".....ግራ ገባኝ።
"እ....አንቺም ሳያምሽ አይቀርም....."....አለና ትልቅ ሸክም ከላዩ እንዳራገፈ ነገር ተነፈሰ....
"ምንድን ነው የምትለው....ምንድን ነው በሽታዬ....ዝም ብሎ ታመሻል አለ እንዴ....."....አልኩት አይኔን በእንባ አቁሬ.....'እንዲህ ነው' ብሎ ባይናገረውም እያለ ያለው ነገር ገብቶኛል....ግን የገባኝ እንኳን ውሸት እንዲሆን በውስጤ እየፀለይኩ ነው....
"ቫይረሱ በደሜ ውስጥ አለ.....".....ሲለኝ ነብስና ስጋዬ ተላቀቀ....ሰውነቴ በደነብኝ.....ሁሉም ነገር ጭው አለብኝ....እያንዳንዱ ድምፅ "ፅፅፅፅፅፅፅ" ብቻ ሆኖ ይሰማኝ ደመር.....ጆሮዬ የሆነ ጩኧት እያወጣ ራሱን ብቻ መስማት ጀመረ....አንደበቴ ተሳሰረ...."እንዴት....መቼ....ለምን....."...... ሌላ የሚጠየቁም የማይጠየቁም ጥያቄዎች ቢመጡብኝም ራሴን አረጋግቼ መጠየቅ አልቻልኩም.....
ተነስቼ ስወጣ ተከተለኝ......
ብዙ ብዙ ነገር ይለፈልፋል....እኔ ግን አልሰማውም.....የሚሰማኝ የጭንቅላቴ ጭውታ ነው....."ፅፅፅፅፅፅፅ".....ይሄ ብቻ ነው የሚሰማኝ።
"ድር እኮ መድሀኒትነት አለው....ቁስልን ለዘብ ያደርጋል....ላፅዳህ ብትዪውም በጄ ይልሻል.....የዘመናት ቆሻሻን ዘወር ብታደርጊው እንኳን ጠረኑ ከርቤም አይበቃውም....."....ያልኳት እህቴ ትዝ አለቺኝ....አፌ ልክ ነበረ....ያልፀዳ ቆሻሻ.....ያልለቀቀ እድፍ ተሸክሜ አፌን እንዳሽሞነሞንኩ አታውቅም እሷ.....
የምናወራውን ብንኖር የት በደረስን....ውስጣችን ጠልሽቶ አፋችንን ማሽሞንሞናችን ምን ጥቅም...ከረፈደ ማስተዋል እንዴት ይቀፋል....ኪሳራ!
***
ፍጥነቴን በእጥፍ ጨምሬ ገሰገስኩ....."ዘወር በልልኝ አውሬ" አልኩት አብሮኝ የሚሯሯጠውን ዮናስ....
"እኔም በቅርቡ ነው ያወቅኩት.....እመኚኝ እድሌ.....".....አለኝ እየተርበተበተ....
"እድሌ አትበለኝ....."....ብዬ አንዴ ሳንባርቅበት ባለበት ቆመ።
እንደሰከረ ሰው እየተንገዳገድኩ ቤቴ ደረስኩ....
አባዬ ቀዝቀዝ ብሎ ጠበቀኝ.....
"ፀጉርሽን ልትሰሪ አልነበር...."....ጠየቀኝ።
"መ....መብራት የለም...."....ብዬው ተስፈንጥሬ መኝታ ቤቴ ገባሁ....
"ምን ሆናለች ልጅቷ...."....አለና ተከተለኝ...."ንገሪኝ እስቲ ምንድን ነው....እኔ አባትሽም ጓደኛሽም ነኝ አይደል...."....አለኝ ትክ ብሎ እያየኝ.....
"ሞኝ ማለት አንድ ስህተትን ደግሞ ደጋግሞ የሚሰራ ነው....".....የሚል አባባል አቃጨለብኝ....ሞት ቢመጣ ለአባዬ አንድ ነገር አልነግረውም ያልኩበት አጋጣሚ ትዝ አለኝ....እንደ እናት መሆን እንዳለበት ሲሰማው የሆንኩትን ይጠይቀኛል.....የሳትኩትን ያለፍርሀት እንዳብራራ ይገፋፋኛል.....እኔም የልብ ልብ ተሰምቶኝ የሆዴን ከዘረገፍኩ በኃላ አባትነቱ ይመጣበታል.....
ነገሩ እንዲህ ነው....
አስራ ሁለተኛ ክፍል ነበርኩኝ....ኢንትራንስ ልንፈተን አካባቢ የነበረ እረፍት ነው....ፕሮቲን ለጭንቅላት ጥሩ ነው ያለው ማን እንደሆነ ባላውቅም አባዬ በጠዋት እየተነሳ በስጋ ፍርፍርና በእንቁላል ያጨናንቀኝ ጀመር.....አብልቶ መክሮ ወደ ላይብረሪ ይልከኛል....ታዲያ ስመለስ የሚጠብቀኝ መክሰስ ልዩ ነበር.... የሚሰራልኝን ምግብ እንዳይቀርብኝ ፈተናው እንዲራዘም እፀልይ ነበር....ለሊት ድንች ጠብሶ ሻይ አፍልቶ ይቀሰቅሰኛል.....እኔ ሳጠና እሱ ጋቢውን ለብሶ ፊት ለፊቴ ይቀመጥና ያንቀላፋል.....
ታዲያ በአንዱ ቀን ጠዋት ቁርሳችንን እየበላን ጨዋታ አነሳ....."እኔ አባትሽ እንዴት ያለሁ የድሮ አራዳ መሰልኩሽ.....".....ብሎ ጀምሮ ከእናቴ በፊት ስለጠበሳቸው አስራ ስድስት ሴቶች ነገረኝ....አብዛኞቹን በእኔ እድሜ እያለ እንዳበሰላቸው እና የዘር ፍሬውን በአግባቡ ቢጠቀምበት አንድ ቀበሌ የሚያህል ልጆች እንደሚኖሩት ነገረኝ.....
ከዚ በኃላ ነው " እንደ አባት እና ልጅ ሳይሆን እንደ ጓደኛ ንገሪኝ እስቲ እስካሁን ምንም የለም....?....".....ብሎ የጠየቀኝ።
"ኧረ የለም....".....አልኩት አንገቴን ቀብሬ።
"ኧረ ተይ ስድስት በመውለጃ እድሜሽ....".....ብሎኝ ሲስቅ ተፍታታሁ....ቀጥዬም ስለ ሁለቱ ኤክሶቼና በሰአቱ ስለነበረው ፍቅረኛዬ የነገርኩት....
ከዛ በኃላ ነው አባትነቱ የመጣው....አንዴ በጥፊ ሲያዞርብኝ ለወራት ያጠናሁት ትምህርት ከአእምሮዬ ብን ብሎ ወጣ....(ለዛ ነው መሰለኝ ፈተናውን ያላለፍኩት)....ነገሩ በዚህ አላበቃም ውጤት ከወጣ እና መውደቄ ከተረጋገጠ በኃላ ነገሩ ባሰ......
"ለነገሩ ከማንም ጋር አሸሸ ገዳሜ እያልሽ ብታልፊ ነበር የሚገርመኝ ኪሳራ....."....."አቤት አቤት 'ፍቅር' አልቀረብሽም ኩክኒያም".....የሚሉ ስድቦችን ከቀበቶው ጋራ ስጠጣ ከረምኩ.....ከዛ በኃላ ነው ለእሱ መንገር እርም ያልኩት።
አሁን አጠገቤ ቁጭ ብሎ "እንደ ጓደኛ" ይለኛል.....የወጋ ቢረሳ ነው ነገሩ.....
****
ሀኒ በጣም አስፈለገችኝ.....እንዲህ ያለ ዱብዳ ወድቆብኝ ለማን አወራዋለሁ.....ባንድ በኩል ደግሞ መክብብ አለ....ሀኒ ለመክብብ ያላትን ስሜት ካነበብኩ በኃላ እሷ ላይ ነፃነቴ ጠፍቷል....
እንዲህ በራሴ ሀሳብ ሰክሬ ስልኬ ነዘረኝ....
"የምሳው ቀጠሮ እንዳለ ነው አይደል.....".....የሚል መልዕክት ነው።
አልመለስኩለትም።
አላለቀም.....
✍ሸዊት
525
09:49
18.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ -13✨✨
መኝታ ቤቴ እንደገባሁ ጥቁር ልብሴን አራገፍኩ....ሀዘን ማርዘም አልፈለግኩም.... ሽሮ መልክ ቢጃማዬን ለብሼ መክብብን ማሰብ ጀመርኩ.....ሰላም።
*
ከሞት የማይተናነስ እንቅልፍ ውስጥ ሆኜ ነበር ስልኬ የቀሰቀሰኝ....መክብብ ሊሆን ይችላል ብዬ ተንደርድሬ ስልኬን ማታ ከወረወርኩበት አነሳሁ....ዮናስ ነበር።
የዘጋሁትን ፋይል መክፈት ላይ ጎበዝ አይደለሁም....ቢሆንም ግን ስልኩን ማንሳት ጨዋነት ነው ብዬ ስላሰብኩ ብቻ አንስቼ የሚለኝን ለመስማት ጆሮዬን አመቻቸው....
"ሄ...ሄለው"....አለኝ የሱ በማይመስል ድምፅ....
"አቤት" አልኩት ቆፍጠን ብዬ....
"እድል....?"....አለኝ እርግጠኛ ለመሆን በሚመስል ድምፀት።
"አዎ ማን ልበል.....".....አልኩት ሳቄን አፍኜ....ሲያስነጥስ ብቻ ሰምቼ ድምፁን እለየዋለሁ.....ሲያስል ብሰማው በሆዱ ያሰበውን አውቃለሁ....
"አላወቅሽኝም....ዮ...ዮናስ ነኝ....".....አለኝ በተቆራረጠ ድምፅ።
"ብዙ ዮናስ አውቃለሁ.....".....አልኩት በቅድሙ ድምፅ።
"ጊቢያችሁ ጋር ነኝ.....ነይ ውጪ የማወራሽ ጥብቅ ጉዳይ አለኝ...."
"ይቅርታ አልችልም።"
"አንቺ ካልወጣሽ ይሄንኑ ጉዳይ ከአባትሽ ጋር እነጋገራለሁ.....".....አለኝ ደንደን ብሎ።
"ምንድን ነው የምትነጋገረው....ምን ቀረን...."....አልኩት ሳላስበው ድምፄን ከፍ አድርጌ.....የምሬን ነበር....ምን ቀረን....የዘር ፍሬውን እኔ ጋር ያስቀመጠው ካልመሰለው በስተቀር እኔን የሚፈልግበት ቁም ነገር የለውም....አልያም ማርሽ አልነሳ ብሎት እንቁ ቀያይሮ ሊሞክር ካልሆነ በቀር እኔ ዘንድ አይመጣም....እንዲያስ ቢሆን እኔ ጋር ከመምጣት መሪጌታ ጋር ቢሄድ አይቀልም ነበር...?
ከብዙ መጯጯህ በኃላ በረንዳ ላይ ዳዊት እየደገመ ያለ አባቴን ጉንጭ ስሜ ፌስታል አንጠልጥዬ ወጣሁ....
ዮናስ ሳር አክሎ ከጊቢያችን ፊት ለፊት ካለው ስልክ እንጨት ጋር ተጣብቋል....'እድል' ብሎ ባይጠራኝ እንሽላሊት መስሎኝ ላልፈው ነበረ።
ሳየው አመዴ ቡን አለ....አዲስ ለያዛት ፍቅረኛው አክሱሙን ሳይሆን ስጋውን እየቆረሰ የሚሰጣት እስኪመስል ድረስ ላልቷል....ፀጉሩ እና ፂሙ ያለልክ አድጎ ሽፍታ አስመስሎታል.....ልብሱ ላዩ ላይ ከመስፋቱ የተነሳ ለለቅሶ የተደኮነ ድንኳን ውስጥ ጋቢ ለብሶ የተቀመጠ የኔቢጤ አስመስሎታል.....የጫማውን አተላለቅ እና የእሱን አከሳስ ላየ ሳሙና ላይ የቆመ ሰንደል ነው ይላል እንጂ ስጋ ለባሽ ሰው ነው አይልም።
እንዳየኝ እንደፋርማሲ እባብ ተጠመጠመብኝ....."ኡኡቴ አልቀረብህም ትናንት እንዴት እንደታቀፍኩ ብታይ ...."....አልኩ በሆዴ....እውነቱን ለመናገር አየር እንጂ ሰው ያቀፈኝ አልመሰለኝም ነበር....
"እንዴት ነሽ" አለኝ ከእግር እስከራሴ እየገረመመ....
"ደህና ነኝ ክብሩ ይስፋ.....".....አልኩትና እንዴት ነህም ሳልለው የሚለኝን መጠባበቅ ያዝኩ።
"የሆነ ካፌ እንቀመጥ እና እንነጋገር.....".....እንዳለኝ አባቴ የጊቢያችንን በር ከፍቶ ወጣ....ፊት ለፊት ተፋጠጥን....ቄሱም ዝም መፅሀፉም ዝም ማለት ይሄኔ ነው።
"ሂድ ዮናስ ሂድ....ቦሀላ እደውልልሀለሁ አባዬ ነው.....".....አልኩትና እሱን በተቃራኒው አቅጣጫ መርቼ ወደ አባቴ ሄድኩ።
"በሰው የምጠላውን ምነው እድል.....አንቺ አጥር ላጥር በጠራራ ጠሀይ እየታከክሽ እህትሽ ምን ትማር ...".....አለኝ በትኩረት እያየኝ....
"አልታከኩም አባ....ኮሌጅ የማውቀው ልጅ ነው....ለሆነ ጉዳይ ፈልጎኝ....."....ከማለቴ አቋረጠኝ።
"ይሄ በልቶ የማያድር የመሰለ ሱሪው የሰፋው ወጠጤ ሀምን ይፈልግሻል....ኧረ በየተራ አቃጥላችሁ ልትደፉኝ ነው....እናታችሁስ....."....ከማለቱ በተራዬ አቋረጥኩት።
"በየሰበቡ ስሟን አትጥራ አባዬ....ለአንተ ሚስት የነበረችው ሴት ለእኛ እናታችን ነበረች....አካልህ የነበረችው ሴት ደሟ ደማችን ውስጥ አለ....ተው አባዬ....ተው".....ብዬው በከፈተው በር ቀድሜው ገባሁ።
ንገሩኝ እስቲ ተመሳሳይ ህመም ይወዳደራል እንዴ....ተመሳሳይ ቁስል እግር እና እጅ ላይ ቢወጣ እግር እኔ ብሳለሁ ይላል....እጅስ እግርን የእኔን ማን አየ እየለገምክ እንጂ እንደ እኔ አልታመምክም ይለዋል....በጭራሽ....ሁላችንም የየራሳችንን ስንታመም ነው መዳኛችንን የምናቀርበው እንጂ 'የኔ ህመም ይብስ' በማለታችን የሚጠጋን ጤና የለም...
ተፈናጥሬ ገብቼ መኝታ ቤቴን ዘጋሁት.... ማልቀስ አልፈለግኩም....ስልኬን አንስቼ ሰላም ወደማገኝበት ቦታ ልደውል እጄን ከመላኬ ሁለት የፅሁፍ መልዕክት ገባልኝ.....
አንዱ ከገነት....አንዱ ደግሞ ከገሀነም።
"እንዴት አደርሽ እድል...."....የሚል የመክብብ መልዕክት እና......
"ዞሮ መግቢያዬ ካፌ እየጠበቅኩሽ ነው....".....የሚል የዮናስ መልዕክት.....ይዙርብህ አቦ ብዬ የመክብብን መልዕክት መለስኩ...
"ዛሬስ ምሳ አታባዪኝም....?"....አለኝ ቀጣዩ መልዕክት....
"ኧረ አባላሀለሁ.....".....አልኩት እንደሚያየኝ ነገር ሸኮርመም እያልኩ።
ትናንት ጨምድጄ ወደቁምሳጥን የላኩትን ቀይ ቀሚሴን ተኮስኩ....ቀይ ቻፒስቲኬን አወጣሁ....በዚህ በኩል የዮናስ ንዝንዝ አቅሌን ሊያስተኝ ሲደርስ አናግሬ ልሸኘው ብዬ ፀጉሬን ልሰራ በሚል ሰበብ ከቤት ወጥቼ ዞሮ መግቢያዬ ተሰየምኩ.......
ዮናስ እጁን አውለበለበልኝ.....የአረንጓዴ ቢጫና ቀይ ድብልቅ የሆነ ሹራቡ ውስጥ ያለው እጁ ሲውለበለብ 'የዜግነት ክብር' ሊዘመር መስሎኝ ተስተካክዬ እንደመቆም ስል ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደመቀመጫው መራኝ።
አሁን ገና ልቤ ሰንጠቅ ሲል ታወቀኝ.....ይሄ gut feeling የሚባለው ነገር የለም.... ቀልቤ 'የሆነ ነገር አለ' ይለኝ ጀመረ.....
"አንድ ሲንግል ድገመኝ....ለሷም ታዘዛት...."....አለው አስተናጋጁን።
"ምን ልታዘዝ....?....".....አለኝ አስተናጋጁ ጠብ እርግፍ እያለ።
"እኔ ምንም አልፈልግም...."....ስለው የገላመጠኝ አገለማመጥ ካፌው የሱ ነው እንዴ እንድል አረገኝ።
"እንዴት እንደምነግርሽ አላውቅም.....".....አለኝና ሲንግሉን በአንድ ትንፋሽ ጨለጠው።
አላለቀም......
✍ሸዊት
551
18:26
17.05.2025
እቤት ስገባ አባዬ እህቴን እያሳሳቀ ያጎርሳታል.....መክብብ ያባረረው እምባዬ ተመልሶ መጣ.....
"ምንድን ነው እንዲህ ጥላሸት መልበስ...."....ብሎ ተቆጣኝ....ጊቢ የማውቃት ልጅ እናቷ ሞታ ለቅሶ ሄጄ ነበር ብዬ ዋሸሁ።
"ጓደኛሽ ማን ናት" እንዲለኝ ጠብቄ መልስ ማሰብ ከመጀመሬ "ጓደኛሽ ያደላት ናት...." አለኝና በእጁ የጨበጠውን ምግብ ከሳህኑ መልሶ ትክዝ ነገር አለ።
እህቴ አንዴ እሱን አንዴ እኔን ታያለች።
"አባዬ ግን እሷን ብቻ ነዋ የምታጎርሳት....."....ብዬ አጠገባቸው ቁጭ አልኩ......"ኧረ ለምን" አለና እብድ የሚያህል ጉርሻ ሰደደብኝ.....የጉንጬ መወጠር እያዩ ሁለቱም ሳቁ....እንደምንም ውጬ ሳቃቸውን ተቀላቀልኩ..... ሳቃችን ግን ውስጡ እንባ ነበረው።
አላለቀም.....
✍ሸዊት
729
16:14
16.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-12✨✨
ከምሽቱ 4 ሰአት ሆኗል....እውነትም ሩቅ መጥቼ ነበር እስክል ድረስ ሰፈሬ እስክደርስ መንፈቅ ፈጀብን....ምንም አላወራንም....የተቀመጥኩበትን ጋቢና መስኮት በለሆሳስ ከፍቼዋለሁ....ልክ እናቴ ትመለሳለች ብዬ እንደምገረብበው አይነት....ሁሉም ነገር እሷን እሷን ይሸታል....ሁሉም ነገር ስሟን ይጠራል።
ስልኬ ጠራ....አባዬ ነበር።
አንስቼ እየመጣሁ እንደሆነ አሳወቅኩት....ቶሎ እንድደርስ ካሳወቀኝ በኃላ "እህትሽ እራት አልበላም ብላለች....እንቅልፍ ሳይወስዳት ድረሺና አንድ በያት" አለኝ የቅድሙ ንዴቱን ድራሹን አጥፍቶ።
አባቴ አንዴ ለብ....አንዴ ሞቅ...አንዴ ግግር ማለቱን ያመጣው እናታችን ከሄደች በኃላ ነው....ሲመስለኝ እናትም አባትም የመሆን ሀላፊነት ስለወደቀበት ሳይወድ በግዱ እንደ ሴት ለስለስ እንደ ወንድ ጠጠር ማለት ነበረበት.... ፈጣሪ ያለ ነገር አንድን ልጅ 'እናት እና አባት' ተብለው ከተሰየሙ ወላጆች አልፈጠረውም....ለሰው ልጅ የእናት ለስላሳነት እና የአባት ጠጣርነት የሚበላለጥ ሳይሆን እኩል የሚያስፈልግ ነገር ስለሆነ ነው.....
አበባ ላይ እሾህ ምን ይሰራል....?....ማንም እንደልቡ እንዳይቀጥፈው አይደል.....ቅንጡ ጊቢ ላይ ለምን አደገኛ አጥር ይታጠራል....?....ማንም እንደልቡ ገብቶ እንዳይዘርፈው አይደል.....
ባንድ በኩል ደግሞ ምንም እንኳን አባቴ እስከጥግ ድረስ እናትም አባትም ለመሆን ቢሞክርም እውነታው ግን 'አባት' መሆኑ ላይ ነው....ቁጣው እና ጩኧቱ አይደለም አባትነቱ....እናትም እኮ ስትናደድ ጩኧት አለባት.....በቃ አባትነት ይሄ ነው ብዬ የማላስረዳው ስሜት ነው።
መክብብ አልፎ አልፎ ዞሮ እያየኝ እንደነበር በጎን እያስተዋልኩት ነበር....
"ደህና ነሽ....?".....አለኝ.....ልዋሸው አልፈለግኩም።
"ደህና መሆን እንዴት ነው....?".....ጥያቄውን ወደራሱ አዞርኩት....እሳት የላሰ ጠበቃነቱ የማያስመልጠውን ጥያቄ እንደጠየቅኩ የገባኝ መልሱ ዝምታ ሲሆንብኝ ነበር።
"ማንም የማይሞላልህ ቦታ አለ ....ማንም ቢመጣ ደህና የማትሆንበት ክፍተት አለ....ያንተን አላውቅም እኔ ግን አለኝ....በማይተካ ሰው መፈተን እና የማይመጣን ሰው መጠበቅ ወና ቤት እንደማንኳኳት ነው....እንደማይከፈትልህ እያወቅክ ታንኳኳለህ....ምን አልባት እጅህ እስኪላጥ ድረስ....ልብህ ይታክተዋል ግን በቃኝ አትልም...."
"እመጣለሁም አልመጣምም ያለለህ ሰው...አንተን ለማምጣት የመጀመሪያውን ስቃይ የተቋደሰው ሰው....እህህህህ ብሎ ያማጠህ ሰው....በስቃይ ያገኘህ ሰው....የመጀመሪያው አቃፊህ....የመጀመሪያው መጋቢህ....ወዳጅህ....አስተማሪህ....የመጀመሪያው ሰው.....".....እንባዬ ሲያቋርጠኝ ሶፍት አቀበለኝ።
መኪናውን አቆመው እና ንፋስ እንድቀበል ጋበዘኝ አላንገራገርኩም.....አብሮኝ ወረደ።
ጎርደድ እያልኩኝ በረጅሙ እተነፍሳለሁ....አብሮኝ ይንጎራደዳል....ጮክ ብዬ ላለቅስ እልና መክብብ እንዳለ ሳስብ እውጠዋለሁ.....
"አልቅሺ እና ይውጣልሽ.....".....አለኝ ፊት ለፊቴ ቆሞ.....ማስተዋሉ ገረመኝ....ከልቡ እያየኝ ነበር ማለት ነው።
"አይወጣልኝም.....አትወጣልኝም.....አትወጣም.....ክፉ ናት አላልኩህም አትወጣም....አትመጣም....አትወጣም....አትወጣም.....አትመጣም......".....እያልኩ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ.....ትንፋሼን ከፍ ዝቅ እያለ ሳግ ሲያሯሩጠኝ ወደራሱ ስቦ አቀፈኝ።
ዮናስን ካቀፍኳቸው መቶ ምናምን እቅፎች የማይወዳደር እፎይታ ተሰማኝ....ይሄ መናበብ አለው....ያ ሌጣ ስሜት ብቻ ነበር....ሰው እቅፍ ውስጥ ሳለቅስ የመጀመሪያዬ ነው...ማንም ይሄ ጎኔን አይቶት አያውቅም....ለስንት አመት ጓደኛዬ እራሱ ስለ እናቴ መሄድ እንጂ ስለፈጠረብኝ ጉድለት አላብራራሁም....ጉድለቱን መገመት ባይከብዳትም አላሳየኃትም.....
እቅፍ እንደዚህ ደልቶኝ አያውቅም....እቅፍ እንዲህ ሰብሰብ አርጎኝ አያውቅም....
ከእቅፉ ስወጣ በሁለት እጆቹ ቀኝ እና ግራ ጉንጮቼን ይዞ ቀና አርጎ በትኩረት አየኝ.....ቀጥሎም በእንባ የቦዘዙ አይኖቼን በየተራ ሳመ....አይኔን እንዲህ ተስሜ አላውቅም....ዮናስ እንኳን እንባ ያረጠባቸውን አይኖቼን ተኩለው የደመቁትም አይኖቼን አልጋ ላይ ካልሆንን አይነካቸውም....ደግሞስ እንባዬኔ ለማየት መች በቃና...(የሴት ልጅ ትልቁ በሽታ....'ማነፃፀር').....እያንዳንዱን ድርጊት የማወዳድረው ከፈረደበት ዮናስ ጋር ነበር....
ፀጉሩ በራ ነው....ግን አያስጠላበትም....አይኖቼን ሊስም ሲል ነው ኮፍያውን ያወለቀው....እጄን ያዘኝ....መዳፉ በጣም ይለሰልሳል....ቀጥሎም እጄን ሳመ....በጣም እንዳሳዘንኩት አይኑ ይናገራል....እንዴት እንደሚያደርገኝ ግራ እንደገባው ሁኔታው ያስታውቃል....
በጣጥሼ የነገርኩትን የእናቴን ታሪክ ሳይጠይቀኝ ነገርኩት....ልቡን ቡርቅቅ አድርጎ ሰማኝ....የቅድሙን እቅፍ ደገመው.....እንባዬን በዛ መዳፉ ጠረገልኝ....አለም።
አባቴ ለሁለተኛ ጊዜ ሲደውል ወደመኪናው ገባን....ሙሉ መንገዱን እያየሁት ነበር....እሱም የማያሰጋ መንገድ ላይ ሲሆን ያየኝ እና ፈገግ ይላል.....ምን እየሆንኩ እንደሆነ በውል ባላውቅም እረፍት ይሰማኝ እንደነበር አውቃለሁ....
"ሁሉም ለበጎ ነው" ከሚሉት ወገን አይደለሁም....አሁን እግዜር ያሳያችሁ የእናቴ መሄድ ምኑ ላይ ነው በጎነቱ....እንዲሁ ሰው የሚያፅናናበት ቃል ሲያጣ የሚሰነዝረው ነው የሚመስለው....መክብብ ይሄን ቃል አላለኝም...ልቤ ላይ ካብኩት።
"አታልቅሺ ጠንከር በይ" የሚሉ ሰዎች አንጀቴን ያበግኑታል....የታፈነ ስሜት ይወጣ ዘንድ በተበጀለት ቀዳዳ መውጣት አለበት ባይ ነኝ....ለኔ ማልቀስ ድክመት አይደለም....ስሜትን አስተንፍሶ ለቀጣዩ ትግል ስንቅ መሰነቂያ ነው.....መክብብም "አልቅሺ" ነበር ያለኝ...ሰገነት ላይ አወጣሁት።
ልቤን ሲሞቀው ይታወቀኝ ነበር...መክብብ ሀሳቤን ብቻ ሳይሆን ስሜቴን እየተቆጣጠረው ነበር....እናቴን ልቤ ውስጥ ቆልፌባት መክብብን ማሰብ ጀመርኩ...ነገ ኖረም አልኖረም ዛሬ መክብብ የተላከልኝ ከፈጣሪ ነው አልኩ..እስካሁን ብቻዬን የተብሰለሰልኩት ብቻዬን ያለቀስኩባቸው ቀናቶች እንደዚህ ማብቂያቸው ተስፋ አልነበረም..
እንባዬ በቅጡ ሳይደርቅ አይኔን የሳመኝ መሳም ተራ 'መሳም' ብቻ አልነበረም....የሆነ መልእክት ነበረው...."ህመም አለብሽ ብዬ አልሸሽሽም...."..አይነት መልእክት.....የሆነ "ከነህመምሽ አለሁ...."....አይነት ነገር....."ጎዶሎሽ አያርቀኝም...."..ያለኝ መሰለኝ።
እንዳፈጠጥኩበት ቤቴ ደረስን።
"አሁንስ ደህና ነሽ..?"....አለኝ ዝቅ ብሎ እያየኝ።
"አታስብ ደህና እሆናለሁ....".....አልኩት።
አቅፎ ተሰናበተኝ....መኪናው ከአይኔ እስኪሰወር ቆሜ በአይኔ ሸኘሁት....
"በጣም ደህና ነኝ....አመሰግናለሁ.....ማንንም ባልጋበዝኩበት የእናቴ ቀብር አብረኧኝ ስለነበርክ አመሰግናለሁ.....ሁሌም እንደዛሬው ብትኖር ደህና እሆን እንነበር አትጠራጠር....".....ያለው ልቤ ነበር....አፌን ገፍትሮ ሊወጣ የፈራው የቃላት ጥርቅም ይሄ ነበር.....የመጀመሪያው ሰው ነው....እኔን ለመሰብሰብ የመጀመሪያው ሰው.....እንባዬን ለማየት የመጀመሪያው ሰው....ታሪኬን ለመስማት የመጀመሪያው ሰው.....
ከእናቴ ጀምሮ የመጀመሪያ ሰው ያስፈራኛል።
568
16:13
16.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-11✨✨
ያዘጋጀሁትን ጥቁር ልብስ ለበስኩ....ጥቁር ጫማና ጥቁር ሻርፕም አክዬበት አመሻሽ ላይ ወጣሁ....ከጨለማው ጋር ተመሳሰልኩ....ፊቴ ባይቀላ ኑረቴ እስካያስታውቅ ድረስ ድብን ብያለሁ።
ካለሁበት በጣም ርቄ መሄድ ፈለግኩኝ...."ሩቅ ውሰደኝ" የሚል ቀጭን ትዕዛዝ የሰጠሁት የራይድ ሹፌር በተባለው መሰረት ይርቃል እስካለው ድረስ እየነዳ ነው....በምፈልገው ፍጥነት ግን እየሄድን አይደለም....የኃላ ታሪኩ ዘሎ እንደሚያንቀው ሰው አስር ጊዜ "ፍጠንልኝ" እያልኩት ነው....እሱ እቴ "ልሻገር አልሻገር" ብሎ የሚወላውለውን ሰው ሳይቀር ቆም ብሎ ሊያማክር ይዳዳዋል.....ሰረቅ እያደረገ ያስጀመረውን ሰአት መቁጠሪያ እያየ አካሄዱን ይገመግማል።
"መራቅ አርቄሻለሁ....የት ነው ግን መውረድ የምትፈልጊው...?...የት ልውሰድሽ...?"
"መቃብር ቦታ ውሰደኝ"....ስለው ተንደርድሮ ፍሬኑን ያዘው።
"ከዚህ በላይ መሄድ አልችልም....መመለሻ ነዳጅ የለኝም....እባክሽ ውረጂ የእኔ እህት...."....አለኝ ፍራቻ በቀላቀለ አክብሮት...
ወደ ሰማይ ቤት ለመሄድ መሳፈሪያ ቢኖረው ልከፍለው የምችለውን ገንዘብ አስረክቤ ወረድኩ....እንደወረድኩ መኪናውን አዙሮ ቀደም ባልነበረው ፍጥነት ነዳ።
ሹፌሩ የጣለኝን ቦታ ስቃኘው አካባቢው ግርግር የማይበዛው ሰው አልፎ አልፎ ያለበት ነው...ከምሽቱ አንድ ሰአት ተኩል ይላል....መብራት አልፎ አልፎ ያለበት ቦታ ጋር ተጠግቼ ስለ አካባቢው የምጠይቀውን ሰው መረጣ ገባሁ።
አንድ ከኑሮ የሚከብድ ፊት ያላቸውን አዛውንት አስቁሜ....
"የት ነው ያለሁት" አልኳቸው.....
"አፍዝዘውሽ ነው የኔ እናት....?...አፍዝዘው እዚ ጥለውሸ ነው....?"....አሉኝ እንስፍስፍ ባለ ድምፅ።
"አይደለም አይደለም....ትንሽ የመርሳት ችግር አለብኝ...."....አልኳቸው ሚስኪን ፊት እያሳየኃቸው።
ያለሁበትን ካሳወቁኝ በኃላ ጥያቄ ደገምኩ።
"እዚህ አካባቢ የመቃብር ስፍራ የለም....?."
መልስ አልሰጡኝም.....
ሁለት እግር ሳይሆን አራት እግር እንዳለው ተሽከርካሪ ብን ብለው ከአካባቢው ጠፉ።
ለሰአታት ሲነዝረኝ የነበረው ስልኬ አሁን አደቡን ገዝቷል....በተደጋጋሚ መክብብ እየደወለልኝ እንደነበር አስታውሳለሁ....ምሳ ሰአት የተቃጠርንበት ቦታ ተሰይሞ እየጠበቀኝ እንደሆነ በፅሁፍ መልዕክት አሳውቆኛል....መልስ አልሰጠሁትም።.....ደጋግሞ ደውሎልኛል አላነሳሁትም።.....ቀርተሽ ነው ወይ ብሎ ጠይቆኛል ቀረሁም መጣሁም አላልኩትም....ደህና ነሽ ወይ ብሎኝ ነበረ....እንዲህም ነኝ እንዲያም ነኝ አላልኩትም።
"Are u okay....".....የሚል ስድስተኛ መልዕክት ገባልኝ.....
ደወልኩለት....
"ደህና ነሽ.....?...."....ነበር ያለኝ ስልኩን ከማንሳቱ.....
ድምፄ መቆራረጥ ጀመረ....አንድ ቃል መናገር ጀምሬ ልጨርስህ ስለው ሳጌ መሀል ይገባል....
ጥርሴን ከገለጥኩለት ይልቅ እምባዬን ያሳየሁትን መልቀቅ ይተናነቀኛል....በተቻለኝ አቅም ለመክብብ እምባዬን ላለማሳየት እየሞከርኩ ነበር....የሆነ ነገሬ "የሆድሽን አንድ ሳታስቀሪ ንገሪው" ይለኛል....የሆነ ነገሬ ደግሞ "ገና ትናንት ያወቅሽው ሰው እምባሽን ለማየት ብቁ አይደለም እረፊ" ይለኛል.....በዚህ ትንቅንቅ ውስጥ እያለሁ "የት ነሽ.....?....".....አለኝ....ሁለቴም ሳላስብ የቅድሟ ሴትዮ ነሽ ያሉኝን ቦታ ነገርኩት....በብርሀን ፍጥነት አጠገቤ ተገኘ።
ከመኪናው ወርዶ ፊት ለፊቴ ቆመ....ቀና ብዬ አየሁት....
"የተፈጠረ ነገር አለ....ደህና አይደለሽም.....ሀዘን ነው....ማን ሞቶብሽ ነው....?.....የምረዳሽ ነገር አለ.....?...."....አንዴ አይኔን አንዴ ጥላሸት ልብሴን እያየ በጥያቄ አጣደፈኝ።
"እሙን ታውቃታለህ....?....እናቴ ናት....በጣም ጨካኝ ናት....በ.በ..በጣም በጣም ክፉ ናት....እሙዬ ክፉ ናት...ጨከነችብን....እሙ.."....እቅፉ ውስጥ ሆኜ በእንባ እየታጠብኩኝ እናቴን አማሁለት....
ምንም ሳይለኝ በዝምታ ሰበሰበኝ።
እንደሌሎቹ ቢደናገጥም ፍላጎቴን አክብሮ እዛው አካባቢ ካለ ደብር መቃብር ስፍራ ወሰደኝ......በጤናዬ መቃብር ስፍራ እንደምፈራ ፈጣሪዬን ራሱ አልፈራም....ዛሬ ደፈርኩት....እናቴ ትኖርበታለች ብዬ ስላሰብኩ ነው መሰለኝ ፍርሀቴ በነነ።
ጭው ያለ ዝሞታ መሀል ዝም ያሉ ሟቾች ተኝተው....በቁም የሞትኩት እኔ እና እግር የጣለው መክብብ ቆመን አለን....ጨረቃ ሙሉ ነበረች....በጨረቃ ብርሀን ከሁሉም ገንጠል ብላ እንደመደበቅ ያለች መቃብር ታየችኝ...."እሙ እዛ ጋር ናት" አልኩት በስሜት.....መክብብ ፈርቷል....ወንድነቱ ይዞት ወይ አሳዝኜው እንጂ ቦታው እንዳስጨነቀው ኮፍያ ጥሶ የሚንቆረቆረው ላቡ ያሳብቅበታል።
"እናቴን ማወራት አለኝ እዚሁ ጠብቀኝ..."....አልኩት።
"ጥሩ አይደለም ብቻሽን....አብሬሽ ልምጣ...."....አለኝ በአይበሉባው የግንባሩን ላብ እየጠረገ....
"አታስብ እናቴ አለች....".....ስለው 'ያማታል እንዴ' አስተያየት አየኝ።
"የተከልሻቸውን አትክልቶች እግርሽ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወር ብሎ የሚያያቸው ጠፍቷል....ያሳደግሻት ውሻ ሞታለች....አልነገርኩሽም አይደል ቀዬው ጥላ ርቆታል....የቡናው ሽታ እንደ ድሮው አይደለም....አንቺ ያልጠመቅሽው ጠላ ደም ደም ይላል...ያለአንቺ ህይወት ከእሬት ይመራል.....".....የማላውቃት ሴትዮ መቃብር ፊት ቆሜ መለፍለፍ ጀመርኩ።
"ባለፈው ታናሽ ወንድምሽ መጥቶ ለአባዬ 'ለአስካል ለምን የቁም ተስካር አታወጡላትም....እስከመቼ ትጠብቃላችሁ.....እኛ አውጥተን ነው እርማችንን ያወጣነው....'....ሲለው ጥንብ እርኩሱን ብሎ አባረረው....አየሽ አባዬም ይጠብቅሻል።
ሞተሻል እናልቅስልሽ....?....ትመጫለሽ እንጠብቅሽ...?...."......የመቃብሩን አፈር እየዳበስኩ እጠይቃለሁ።
ተይ እሙ......የኔ ወርቅ ተይ...የኔ እናት የት ነው ያለሽው.....እዚህ ነኝ ማለት ይከብዳል....?....እዚህ ነኝ አትድረሱብኝ ብትዪን ምን አለ....ነብሴ ተጨነቀችብሽ እኮ....አባዬን ፀፀት አስረጀው እኮ....
እሙ ተይ....
ተይ እማ....
እዚህ ነኝ ሳልል ለጨዋታ ስሄድ እንዴት ነብስሽ ትጨነቅ ነበር.....?....እዚህ ነኝ ሳይሉ መሄድን ከየት አመጣሸው....
እንደወጡ መቅረትን ከየት ተማርሽው...
እህቴን ባየሻት ምን እንዳከለች....ልጅሽን ብታያት እንዴት ቆንጆ እንደሆነች....
ባንድ ጊዜ ፍቅርም ጥላቻም እየተፈራረቁ አሳሬን አበሉኝ።
መክብብ ከኃላ ትከሻዬን እስኪነካኝ ድረስ በማላውቃት ሴትዮ በድን ፊት ከእናቴ ጋር ነበርኩ።
ይበቃል እንሂድ አለኝና እጄን አጥብቆ ያዘኝ.....
**
"ግን ለምንድን ነው በጨለማ እዚህ መምጣት የፈለግሺው" አለኝ መኪናው ውስጥ ከገባን በኃላ።
"በጨለማ የወጣችውን እናቴን በጨለማ መቅበር ፈልጌ...." አልኩት።
መልስ አልሰጠኝም።
አላለቀም..
✍ሸዊት
639
09:56
16.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-10✨✨
ትናንት ከፋም ለማም እንደ ጠዋት የምወደው ነገር የለም....ሊነጋጋ ሲል ሰማዩ የምይዘውን ከለር እወደዋለሁ....የሆነ postive energy ውስጤ ክትት ይላል....ለቀኑ የሚሆነኝን ብርታት የምሰንቀው ጠዋት ላይ ነው....
መስኮቴን ገርበብ አድርጌ ወደ ውጪ እያየሁ ነበር ስልኬ የነዘረኝ....የማላውቀው ቁጥር ነው....ሰሞኑን በማላውቀው ቁጥር እየደወለ "አበሩ ነሽ አይደል....ተይ እንደዚህ አያዋጣም ወደ ቤትሽ ተመለሺ....".....የሚለኝ ሰውዬ ትዝ ብሎኝ ስልኬን ናቅኩት።
ደግሞ ጠራ።
ስልኬን በሆዱ አስኛሁት.....
ሰለሰ።
"አበሩ አይደለሁም አንተ ሰውዬ በምን አይነት ቋንቋ ብነግርህ ነው የሚገባህ....."....ከማለቴ ሞቅ ያለ ፈገግታ ከስልኩ ወጣ....
"አውቃለሁ እድል...."....ያለኝ መክብብ ነበር።
እንደማፈር ያለ ፈገግታ አስከትዬ ሰላምታ ሰጠሁት....ቁጥሬን ሀኒ እንካ እንደማትለው ግልፅ ነው....ኧረ እንደውም የሚጠይቃትም አይመስለኝም....ብቻ ከየትም ያምጣው....ዋናው ቁም ነገሩ መደወሉ ላይ ነው።
"ምሳ ልጋብዝሽ.....?...."....ሲለኝ ሳልደፋ "እሺ" አልኩት.... ...ወደፊት ልጆቼን ሰብስቤ 'አባታችሁ እኔን አንድ ምሳ ለመጋበዝ አስር ሽማግሌ ልኮ ነበር....እንዴት ያለሁ ኩሩ ነበርኩ መሰላችሁ....'....ብላቸው እኮ ደስ ይለኝ ነበር....ምኞቴን ትቼ 'የእነሱ ጊዜ እና የእኛ ጊዜ አራምባና ቆቦ ነው....የዛሬ ወንድ ምን ትዕግስት አለው....' ብዬ ራሴን አፅናንቼ ቀዝቃዛ ሻወር ወሰድኩ.....
መስታወት ፊት ተቀምጬ እንዴት እንደምስቅ ተለማመድኩ....ስለ ዮናስ ልጠየቅ እንደምችል በመገመት ተጎጂነቴን የሚያጎላ መልስ አዘጋጀሁ.....ቀይ ስለሆንኩ መልክ አልፈጅም....."ይቺ እኮ ባትቀላ አታምርም" የሚለኝ ይበዛል...."እንግዲህ ቀላሁ ምን ማድረግ ይቻላል".....መልሴ ነው....የእኛ ሰው በሆንነው ከማድነቅ ይልቅ ባንሆን ያለውን በማሰብ ላለመበለጡ ያስተባብላል....
የማወራው ስለ መልክ ብልጫ ብቻ አይደለም...."ያለፈለት እኮ ጠንቋይ ጋር ሄዶ ነው" ስለሚሉ ያላለፈላቸው ሀሜተኞችም ጭምር ነው ....ሰው ያልበላውን ሲያክ አልወድም... እንደ እኔ እንደ እኔ ጨዋ አፉን የገራ ነው።
የሆነ ጊዜ ሁለት የሰፈራችን አሮጊቶች ዱላ ቀረሽ ፀብ ውስጥ ይገባሉ....የወጣት ሴቶች ፀብ ሲሆን መሰዳደቡ ላይ ቡጭርያ የበዛበት ድብድብ ይኖረዋል....የአሮጊት ፀብ ግን ከመሰዳደቡ ያልፍና በቡጭርያ ፋንታ ሰነድ እየተማዘዙ መካሰስ ይበዛዋል...
የእነዚህ አሮጊቶች ፀብ ላይም ሳይታሰብ ሰነድ ወጣ......
"አንቺ የጠንቋይ ካዳሚ....".....ሲሉ አንደኛዋ
"ዝጊ ወራዳ ራስሽ አይደለሽ አንቀልቅለሽ የወሰድሽኝ....".....ይላሉ ሌላኛዋ.....አልፎ ነገ ለሚባል ቀን አፈር እስኪገቡ ድረስ ሁለቱም በሰው አፍ ተላመጡ.....
*
ምሳ ሰአት እንደ ዛሬ የራቀበትን ቀን አላስታውስም....መስታወት ፊት እንደተሰየምኩ አባቴ ታናሽ እህቴን ያጮላት ጥፊ ከሳሎን አልፎ መኝታ ቤት ድረስ ተሰማኝ....ተንደርድሬ ስወጣ እህቴ ድፍት ብላ ማልቀስ ስትጀምር አባቴ ደግሞ መናገር ሲጀምር እኩል ሆነ።
"አባዬ ምን ነካህ ምን አጥፍታ ነው ይሄን ያሀል...."....አልኩት እየተንዘረዘርኩ....በእህቴ ጉዳይ ልል ነኝ....እምባዋን ሳየው የእናቴን አደራ እንደበላሁ ይሰማኛል።
"እዚ ታች ሰፈር የአቶ አንበርብርን ለቅሶ ደርሼ ጎኔን ላሳርፍ መምጣቴ ነው....ይቺ ከንቱ እያለች በየት በኩል ቱቱ እናትሽስ ይሄን ሳታይ ጓዟን ጠቅልላ ሄደች...."......አባቴ እንቅጩን ለመንገር ማገዶ እንደሚፈጅ ሲገባኝ አረጋግቼው እህቴን ይዣት መኝታ ቤት ገባሁ.....
"ምንድን ነው ያጠፋሺው.....".....ጠየቅኩ።
"ምንም አላጠፋሁም.....እያየሁት የነበረው ድራማ አልቆ ሌላ ጣቢያ ላይ ከመቀየሬ አባዬ ገባ.....ጣቢያው ላይ ማስታወቂያ ነበር....ከማስታወቂያ በኃላ የጀመረው የፍቅር ፊልም ነበር....ጥንዶቹ ሲሳሳሙ ደርሶ ሪሞቱን አናቴ ላይ ወረወረው...በእውነት እህቴ እኔ መሳሳም ያለበት ፊልም አልመሰለኝም ነበር.....ይቅርታ".....ብላኝ በረጅሙ ተናፈጠች።
ምንም ሳልል አቀፍኳት....
"እድል" ከእቅፌ ሳትወጣ ጠራችኝ....
"ወዬ...."
"እናቴ የት ነው የሄደችው...."
የሚተናነቀኝን እንባ አደብ ለማስገዛት እየተጣጣርኩ "ሞታለች.....ሁሉም ወደማይቀርበት ነው የሄደችው" አልኳት....
"የሞተ ሰው ጓዙን ጠቅልሎ ነው እንዴ የሚሄደው.....?...."....ሌላ ጥያቄ....እዚህ ጋር ማቆም እንዳለብን ተሰማኝና እንደማንኛውም ታላቅ "ስታድጊ እነግርሻለሁ" ብዬ መልስ ከሌለው ጥያቄዋ ለዛሬ ተረፍኩ።
የጓጓሁለት ምሳ ሰአት ሲደርስ ራስ የሚፈልጥ ምታት ያዘኝ....ስለ እናቴ ከተነሳ እንዲህ ነው የሚያደርገኝ....ልሽቀረቀርበት ያዘጋጀሁትን ቀይ ቀሚስ እና ነጭ ቦርሳ ወደ ቁም ሳጥኑ መለስኩ....በምትኩ ጥቁር ሱሪ እና ጥቁር ቲሸርት አወጣሁ....
ሁላችንም ስንነካ የሚያመን አንድ ቦታ አለን አይደል....ሲነካ የሚቆጠቁጠን ቁስል....ተንጠልጥሎ የቀረ ጥያቄ....ስስ ብልት....እሱ ቁስሌን አመመኝ።
"እየጠበቅኩሽ ነው...."....የሚል ቴክስት ሲገባልኝ አስረኛ ሶፍቴን እየመዘዝኩ እያነባሁ ነበር....
ልጅ እያለሁ እናቴ ከሄደችበት ጊዜ አንስቶ የጊቢያችንን በር መዝጋት አልፈልግም ነበር....የምትመለስ የምትመለስ ስለሚመስለኝ በሩ ዝግ ሆኖባት እንዳትመለስ ስለምፈራ እንደነገሩ ገርበብ አደርገው ነበር....ሲብስብኝ በረንዳ ላይ ቁጭ ብዬ በር በሩን እመለከታለሁ....በወጣችበት በኩል እንድትመለስ አይኔን አማትራለሁ።
"ስሙን እያነሳሁ የማጫውታችሁ
ቆንጆ ነው ያሳሳል ብዬ የምላችሁ
የተረታሁለት ሸጋ ይኧውላችሁ....".....የአስቴር ድምፅ ከጎናችን ካለው ሙዚቃ ቤት ይወጣል....
"ብቻዬን....ብቻዬን....ብቻዬን......"......ስትል ስቅስቅ ብዬ አለቅሳለሁ.....አስቴር አወቀ "ብቻዬን" የምትለው እናቷም ሄዳባት ይሆናል ብዬ ስለማስብ ታሳዝነኛለች....
መቼም እናቷ ጥላት ካልሄደች ለአንድ ጎረምሳ ውበት በዚህ ልክ አታቀነቅንም ብዬ አብሬያት "ብቻዬን....ብቻዬን....ብቻዬን....".....እላለሁ።
**
የስልኬ ንዝረት....የአስቴር ሙዚቃ....የመክብብ ድምፅ....የሀኒ ሳቅ....የዮናስ አካሄድ.....የእናቴ ጠረን...አእምሮዬ ሚገባበት አጣ።
አላለቀም.....
✍ሸዊት
812
16:20
14.05.2025
✨✨ፍቅር ቅብ-9✨✨
እንደ ትናንት ትዝ ይለኛል ስምንተኛ ክፍል ነበረ....ከእስፖርት ክፍለ ጊዜ መልስ ምሳቃዬ መማሪያ ጠረጴዛዬ ላይ በግላጭ ተቀምጧል....እየተንደረደርኩ ሄጄ ሳነሳው ገለባ ሆነብኝ.....ፈራ ተባ እያልኩ ስከፍተው በግዢ እንጀራ እና በአባቴ ምስር ያሸበረቀችው ምሳቃዬ ሌጣዋን ነች....ድንጋጤዬን ሳስታውሰው ምግብ የተበላብኝ ሳይሆን የአባቴን መርዶ የተረዳሁ ነበር የምመስለው።
ደንግጬ ብቻ ብተወውም መልካም ነበር...ጡጦውን እንደተቀማ ህፃን እሪሪሪሪ ብዬ አለቀስኩ.....ያኔ ነው ሀኒ ወደ ህይወቴ የገባችው.....
የበላብኝን ልጅ ፈልጋ ለማግኘት የፈጀባት ረፍት ሰአት ብቻ ነበረ.....ፊት ለፊቴ አምጥታ እንደ እባብ ስትቀጠቅጠው ፊቴ ላይ የነበረውን ደስታ አስታውሳለሁ...
ያን እለት ምሳቃዋን አጋርታኝ ጓደኝነታችንን ሀ ብለን ጀመርን.....'ጓደኛሞች እንሁን' ሳንባባል ጓደኛሞች ሆንን....እንዴት ብለን እንደተግባባን....ምን ሰአት ነብሶቻችን እንደተሳሰሩ ሁለታችንም አናውቅም።
*
ዛሬ ፊት ለፊቴ ተቀምጣ አፍ አፌን የምትለኝ ሴት ግርድፍድፍ ቃሌን አቃንታ የምታስተጋባልኝ....ገበና ከታቼ....ጓዳዬ....ጓ'ደኛዬ እንደሆነች ማሰብ ከበደኝ.....
"case አለ እንዴ" አለ ሸዋፈራሁ ደስአለኝ....ጉዳይ ቢኖራትስ ገና ፀጉር ይኑረው አይኑረው ላላወኩት ወንድ አናት አናቴን ማለት አለባት....ደግሞ እኔ የማላውቀው ጉዳይ ከመቼ ጀምሮ።
****
በአንድ ትሪ የቀረበልንን ቋንጣ ፍርፍር እና ዶሮ ቀና ሳልል መብላት ጀመርኩ....እኔ እና ሀኒ ስንበላ አንተያይም.....ምግብ እና ጓደኝነት ይለያያል ባይ ነን.....አንጎራረስም.....ይቺን ያዙልኝ አንጎራረስም።
"መኬ ግን ይሄ ወስፋታምነትህ መቼ ነው ሚለቅህ".....ካለች በኃላ እብድ የሚያህል ጉርሻ ወደ አፉ ሰደደች.....ሁለቱ ጉንጮቹ እንደፊኛ ተነፍተው ጥርሱ አልታዘዝ ያለው ይመስል ለሰከንዶች ከቆየ በኃላ ነው ተንፈስ ያለው....ጉርሻ ሳይሆን የግድያ ሙከራም ይመስል ነበር።
"ሀኒ በቃ ካላጎረስሽ አይሆንልሽማ...."....አለ ጉርሻውን በውሀ አለቃልቆ ከዋጠ በኃላ....ይሄን ጊዜ እኔ ጋር ያለችው ሀኒ እና እሱ ጋር ያለችው ሀኒ የተለያዩ ሰዎች እንደሆኑ ተገለጠልኝ....
"ርቀትሽን ጠብቂ እድል...."....አልኩኝ በሆዴ።
'አይኗ ካንተ ላይ አይነቀልም....እንስፍስፍ ብላ ነው የምታይህ....አውቃለሁ ሰው ሲያፈቅር ምን እንደሚሆን....በተለይ ሴት ስታፈቅር....'....የሀኒ አሰተያየት እና አኳሀን አሌክስ አብርሀም መፅሀፍ ላይ ያነበብኳትን ፅሁፍ አስታወሰኝ....አይኗ ፍቅር አለበት....ድርጊቷ የተጠና ባይሆንም እንከን አልባ ለማድረግ እንደለፋችበት ያስታውቃል።
በየመሀሉ መታጠቢያ ቤት እየሄደች የምታረጥበው ከንፈሯ እና መላ ምትለው ፀጉሯ ላይ ሳይቀር ፍቅር አለ....እኔ ሳውቃት እጇን አነባብራ ጥፍሯን የምታፍተለትለው አስተማሪ መልስ ሲጠይቃት ብቻ ነበር....ጭንቀት ከእግር እስከራሷ የሚወራት....ትንፋሽ የሚያጥራት ፕረዘንቴሽን ላይ ነበረ.... የተቆራረጠ ድምፅ ከተገለጠ ቅናት ጋር ያየሁት ዛሬ ነው....አሁን።
አስር አስር ፍቅረኞች ብንይዝ አይቀየርም ያልኳችሁን የአብሮነት ጊዜያችንን የጣሰው አንዱ መክብብ ነው....ከማውቃቸው የተፈቀደለት እርሱ ብቻ ነው....
"በህይወቴ የምጠላው ነገር ቢኖር በወንድ ምክንያት ከሴት ጓደኛ ጋር መናቆር ነው....ለምን ጥርግ አይልም ጓደኝነት ይበልጣል...."....ያለችኝ በቅርቡ ነበር....
"እድሌ ስለ ዮኒ አጫውችን እስኪ እንዴት ሆናችሁ...ብታይ መኬ እንዴት ደስ የሚሉ ጥንዶች መሰሉህ"....ስትል በንዴት አፍንጫዬ ራሱ ቀላ....በዮናስ ጉዳይ አይኔን ያስከፈተችኝ ሀኒ ናት ይቺ....?....እንዳልኳችሁ ይቺን ሀኒ አላውቃትም።
በጀርመንኛ 'ፍቅረኛ አላት አይንህን አንሳ' ማለቷ ነው....ሀኒ በወንድ ፊት pick me ጨዋታ ስትጫወት ሳያት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው....ለድርጊቷ እንዴት ያለ ምላሽ እንደምሰጥም አላውቅም.....አኳሀኗ ያልሆነ እልህ ውስጥ እንዳይከተኝ እየፈራሁ በደፈናው "ደህና ነን" ብቻ አልኳት....
"ይሄ ቅዳሜን ጠብቆ ካላወጣሁሽ የሚለው ልጅ አለ.....?.....".....ስትለኝ ንዴቴ ፀጉሯን እንዳያስነጨኝ እየተጠነቀቅኩ ደረቅ ፈገግታ አሳየኃት.....'ምን ነካሽ ሀኒ' መሆኑ ነው.....በእርግጥ የሆነ ነገሬ 'የእሷን ጉድ ለምን አታፍረጠርጪውም' ሲለኝ ነበረ.....የሆነ ነገሬ ደግሞ 'እንዲያ ካደረግሽማ እሷኑ ሆነሽ አረፍሽው' ሲለኝ ተውኩት እንጂ።
"ወንድ ልጅ የተያዘች ሴትን መጠጋት ላይ እንብዛም ነው....ልቧ ሙጫ እንደሆነ ያውቃል....ድንግልናሽን የሚፈልገው ትግል አምሮት ብቻ አይምሰልሽ....አብዛኛዋ ሴት ልቧን ከተኛችው ወንድ ጋር ታጣብቃለች....እዚም እዚያም ጋር የተበታተነ ልብ ርጋፊው ከውስጥ አይገባም....አለ አይደል ብዙ እጅ የነካካው አበባ መአዛው እስከዚም ነው.....".....ያለቺኝ እሷ ነበረች.....
ከጅምሩ እኔ በመምጣቴ የተቆጨች ትመስላለች.....እውነቱን ለመናገር መክብብን ልቧ እንደከጀለው ለማወቅ ደይቃዎች አልፈጁብኝም....ቀድማ ብታሳውቀኝ እንደ ሎጥ ዘመን ዘር ሊጠፋ ሆኖ አንድ ያንጠለጠለ እርሱ ብቻ ቢቀር በእንጨት አልነካውም ነበር.... የተጠቀመችው ግን ተቃራኒውን ነበር....እኔን በእሱ ፊት እፍኝ ማሳከል.... በፊቱ ልታሳንሰኝ ስትሞክር ፍላጎቴ ናረ.... ውበቱ ባሳነሰችኝ ቁጥር ጎላ.....መላጣ ይሁን በራ ያልታወቀ አናቱ ሚዶ የተሰካበት ጎፈሬ መስሎ ታየኝ።
አላለቀም....
✍ሸዊት
892
17:34
13.05.2025
close
Reviews channel
keyboard_arrow_down
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
5.0
2 reviews over 6 months
Excellent (100%) In the last 6 months
c
**ffeenold@******.io
On the service since June 2022
24.04.202515:42
5
Everything is fine. Thank you!
Show more
New items
Channel statistics
Rating
17.6
Rating reviews
5.0
Сhannel Rating
6
Subscribers:
4.4K
APV
lock_outline
ER
7.9%
Posts per day:
0.0
CPM
lock_outlineSelected
0
channels for:$0.00
Subscribers:
0
Views:
lock_outline
Add to CartBuy for:$0.00
Комментарий