
- Main
- Catalog
- News and Media
- Advertising on the Telegram channel «𝗔𝗕𝗖 𝗡𝗘𝗪𝗦 𝗔𝗠𝗛𝗔𝗥𝗜𝗖»
Advertising on the Telegram channel «𝗔𝗕𝗖 𝗡𝗘𝗪𝗦 𝗔𝗠𝗛𝗔𝗥𝗜𝗖»
This public channel features all aspects of life in # Ethiopia, # News # Zena # News #Reviews
Channel statistics
⚫️ " ትክክል ነው። የተገደሉት ሰባት ሰዎች ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አስከሬናቸው ተገኝቷል። እነዚህ ትናንት ወዲያ ከተገደሉት 21 ምዕመናን ውጭ የተገደሉ ናቸው " - የአርሲ ዞን ሀገረስብከት
ከትናንትና ወዲያ " 21 ምዕመናን ሲገደሉ " ፣ ስምንት የደረሱበት አልታወቀም " ፣ " ስምንት ሆስፒታል ገብተዋል " ፣ " ሁለት ታግተዋል " በተባለበት በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ትናንት ምሽት ተጨማሪ " ምዕመናን " መገደላቸው ታውቋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የአርሲ ዞን ሀገረ ስብከት፣ እንዲሁም በዞኑ የሽርካ ወረዳ ቤተክህነት፣ ከትናንት ወዲያ ግድያ በተፈጸመበት በሽርካ ወረዳ ጃዌ ዋጩ ቀበሌ፣ ትናንት ምሽትም ሌላ ጥቃት ተፈጽሞ " ሰባት ምዕመናን " በታጣቁት አካላት ተገድለዋል ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አንድ የሽርካ ወረዳ ቤተክህነት አካል ዛሬ ከሰዓት በሰጡን ቃል፣ " ትናንት ምሽትም ሰባት ሰዎች ተገድለዋል። ቀብራቸው ዛሬ ተፈጽሟል " ብለዋል። በዚህም እስካሁን ተረጋገጠው መረጃ ብቻ በሁለት ቀናት በቀበሌው የተገደሉት ምዕመናን ብዛት 28 ደርሷል።
" ትናንት ማታም በርካታ ቤቶች ተቃጥለዋል። ሲቃጠሉም ነው ያደረሩት። አንድ ቤተክርስቲያን ተዘርፏል" ያሉን የቤተክህነቱ አካል፣ "ቤተክርስቲያን ዙሪያ ያለ ደጀሰላም እና አዳራሽ ተቃጥለዋል " ብለዋል።
" ስጋቱ አሁንም እንዳለ ነው " ያሉም ሲሆን፣ ይህ ጥቃት የተሰነዘረበት ቤተክርስቲያን ጃዊ አቦ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እንደሚባል ገልጸው፣ " የተወሰነ ኃይል ብቻ ከዞን መጥቷል። ሟቾቹ እንዲቀበሩ ያደረጉት እነርሱ ናቸው። ግን ይቆዩ፣ ይሄዱ ይሆን አይታወቅም " ነው ያሉት።
የአርሲ ዞን ሀገረ ስብከት በበኩሉ፣ " የሚያገኟትን ነገር እየተጠቀሙ " ቤተክርስቲያን ውስጥ ተጠግተው ሲኖሩ የነበሩ " አቃቢት " እና " ነዳያን " በተጠቀሰው ቦታ ትናንት ምሽት በተሰነዘረ ጥቃት " ተድለዋል " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ይህን ያሉት አንድ የሀገረ ስብከቱ አመራር በሰጡን ቃል፣ " ትክክል ነው። የተገደሉት ሰባት ሰዎች ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አስከሬናቸው ተገኝቷል። እነዚህ ትናንት ወዲያ ከተገደሉት 21 ምዕመናን ውጭ የተገደሉ ናቸው " ብለዋል።
ከሟቾቹ ባሻገር " ጀደሰላሙ ሙሉ ለሙሉ ተቃጥሏል። የሰበካ ጉባዔው ጽሕፈት ቤት የስንዴ እህል ነበረው እሱም ወድሟል። ብዙ ቤቶችም ተቃጥለዋል " ሲሉ አክለዋል።
የአትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ ትናንት ወዲያ የተገደሉትን 21 ኦርቶዶክሳውያን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም በሽርካ ወረዳ ጃዊ ቀበሌ በታጣቂዎች ጥቃት የካቲት 19 ለ 20/2018 ዓ/ም 21 ኦርቶዶክሳውያን በግፍ መገደላቸውን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ " ለጽ/ቤታችን ከጻፉት ደብዳቤ ስንመለከት እጅግ በከፍተኛ ኀዘን ተሰምቶናል " ብለዋል። ትናንት ምሽት ተገደሉ ስለተባሉ ሰባቱ ሰዎች እስካሁን ያሉት ነገር የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
⚫️ " ትክክል ነው። የተገደሉት ሰባት ሰዎች ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አስከሬናቸው ተገኝቷል። እነዚህ ትናንት ወዲያ ከተገደሉት 21 ምዕመናን ውጭ የተገደሉ ናቸው " - የአርሲ ዞን ሀገረስብከት
ከትናንትና ወዲያ " 21 ምዕመናን ሲገደሉ " ፣ ስምንት የደረሱበት አልታወቀም " ፣ " ስምንት ሆስፒታል ገብተዋል " ፣ " ሁለት ታግተዋል " በተባለበት በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ትናንት ምሽት ተጨማሪ " ምዕመናን " መገደላቸው ታውቋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የአርሲ ዞን ሀገረ ስብከት፣ እንዲሁም በዞኑ የሽርካ ወረዳ ቤተክህነት፣ ከትናንት ወዲያ ግድያ በተፈጸመበት በሽርካ ወረዳ ጃዌ ዋጩ ቀበሌ፣ ትናንት ምሽትም ሌላ ጥቃት ተፈጽሞ " ሰባት ምዕመናን " በታጣቁት አካላት ተገድለዋል ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አንድ የሽርካ ወረዳ ቤተክህነት አካል ዛሬ ከሰዓት በሰጡን ቃል፣ " ትናንት ምሽትም ሰባት ሰዎች ተገድለዋል። ቀብራቸው ዛሬ ተፈጽሟል " ብለዋል። በዚህም እስካሁን ተረጋገጠው መረጃ ብቻ በሁለት ቀናት በቀበሌው የተገደሉት ምዕመናን ብዛት 28 ደርሷል።
" ትናንት ማታም በርካታ ቤቶች ተቃጥለዋል። ሲቃጠሉም ነው ያደረሩት። አንድ ቤተክርስቲያን ተዘርፏል" ያሉን የቤተክህነቱ አካል፣ "ቤተክርስቲያን ዙሪያ ያለ ደጀሰላም እና አዳራሽ ተቃጥለዋል " ብለዋል።
" ስጋቱ አሁንም እንዳለ ነው " ያሉም ሲሆን፣ ይህ ጥቃት የተሰነዘረበት ቤተክርስቲያን ጃዊ አቦ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እንደሚባል ገልጸው፣ " የተወሰነ ኃይል ብቻ ከዞን መጥቷል። ሟቾቹ እንዲቀበሩ ያደረጉት እነርሱ ናቸው። ግን ይቆዩ፣ ይሄዱ ይሆን አይታወቅም " ነው ያሉት።
የአርሲ ዞን ሀገረ ስብከት በበኩሉ፣ " የሚያገኟትን ነገር እየተጠቀሙ " ቤተክርስቲያን ውስጥ ተጠግተው ሲኖሩ የነበሩ " አቃቢት " እና " ነዳያን " በተጠቀሰው ቦታ ትናንት ምሽት በተሰነዘረ ጥቃት " ተድለዋል " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ይህን ያሉት አንድ የሀገረ ስብከቱ አመራር በሰጡን ቃል፣ " ትክክል ነው። የተገደሉት ሰባት ሰዎች ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አስከሬናቸው ተገኝቷል። እነዚህ ትናንት ወዲያ ከተገደሉት 21 ምዕመናን ውጭ የተገደሉ ናቸው " ብለዋል።
ከሟቾቹ ባሻገር " ጀደሰላሙ ሙሉ ለሙሉ ተቃጥሏል። የሰበካ ጉባዔው ጽሕፈት ቤት የስንዴ እህል ነበረው እሱም ወድሟል። ብዙ ቤቶችም ተቃጥለዋል " ሲሉ አክለዋል።
የአትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ ትናንት ወዲያ የተገደሉትን 21 ኦርቶዶክሳውያን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም በሽርካ ወረዳ ጃዊ ቀበሌ በታጣቂዎች ጥቃት የካቲት 19 ለ 20/2018 ዓ/ም 21 ኦርቶዶክሳውያን በግፍ መገደላቸውን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ " ለጽ/ቤታችን ከጻፉት ደብዳቤ ስንመለከት እጅግ በከፍተኛ ኀዘን ተሰምቶናል " ብለዋል። ትናንት ምሽት ተገደሉ ስለተባሉ ሰባቱ ሰዎች እስካሁን ያሉት ነገር የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በእስራኤል እና በአሜሪካ አጋሮች ላይ የሚሳኤል ናዳ እያወረደች ትገኛለች።
ከኢራን ጥቃት ሰለባዎች አንዷ የተባበሩት አረብ ኤሬትስ (UAE) ስትሆን ከጥዋቱ የቀጠለ ጥቃት ምሽቱን እያስተናገደች ነው።
በተለይ በዱባይ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት (DXB) በአንድ የመንገደኞች ማረፊያ ላይ ጥቃት ደርሶ 4 ሰዎች ተጎድተዋል።
መጠነኛ የንብረት ጉዳትም ደርሷል።
ከላይ የተያያዘውንና ኤርፖርቱ ውስጥ የነበረውን ሁኔታ የሚያሳይ ቪድዮ አልጀዚራ ማረጋገጡን አሳውቋል።
ዱባይ እንዲሁም አቡዳቢ አውሮፕላን ማረፊያዎች ሁሉም በረራዎች ለጊዜው ተቋርጠዋል።
የመንገደኞች ደህንነትን ለመጠበቅም የኤምሬትስ አየር ክልል በከፊል ተዘግቷል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) መንግስት ሁሉም በረራዎች እስከሚቀጥለው ማስታወቂያ ድረስ ስለተሰረዙ ሰዎች ወደ አውሮፕላን ማረፊያ ከመሄድ እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
በሌላ በኩል ፥ የሀገሩ መከላከያ ሚኒስቴር ከኢራን የተተኮሱ 132 ሚሳይሎችን ማውደሙን እና 195 ድሮኖችን ጥቃት ሳያደርሱ ማክሸፉን አስታውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 22 ቀን 2018
@tikvahethiopia
በእስራኤል እና በአሜሪካ አጋሮች ላይ የሚሳኤል ናዳ እያወረደች ትገኛለች።
ከኢራን ጥቃት ሰለባዎች አንዷ የተባበሩት አረብ ኤሬትስ (UAE) ስትሆን ከጥዋቱ የቀጠለ ጥቃት ምሽቱን እያስተናገደች ነው።
በተለይ በዱባይ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት (DXB) በአንድ የመንገደኞች ማረፊያ ላይ ጥቃት ደርሶ 4 ሰዎች ተጎድተዋል።
መጠነኛ የንብረት ጉዳትም ደርሷል።
ከላይ የተያያዘውንና ኤርፖርቱ ውስጥ የነበረውን ሁኔታ የሚያሳይ ቪድዮ አልጀዚራ ማረጋገጡን አሳውቋል።
ዱባይ እንዲሁም አቡዳቢ አውሮፕላን ማረፊያዎች ሁሉም በረራዎች ለጊዜው ተቋርጠዋል።
የመንገደኞች ደህንነትን ለመጠበቅም የኤምሬትስ አየር ክልል በከፊል ተዘግቷል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) መንግስት ሁሉም በረራዎች እስከሚቀጥለው ማስታወቂያ ድረስ ስለተሰረዙ ሰዎች ወደ አውሮፕላን ማረፊያ ከመሄድ እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
በሌላ በኩል ፥ የሀገሩ መከላከያ ሚኒስቴር ከኢራን የተተኮሱ 132 ሚሳይሎችን ማውደሙን እና 195 ድሮኖችን ጥቃት ሳያደርሱ ማክሸፉን አስታውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 22 ቀን 2018
@tikvahethiopia
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን አሳወቁ።
ትራምፕ ባወጡት መግለጫ " ኻሜኒ ሞቷል " ብለዋል።
ፕሬዜዳንቱ " በታሪክ ውስጥ ካሉ እጅግ ክፉ ሰዎች አንዱ የሆነው ኻሜኒ ሞቷል። ይህ ለኢራን ህዝብ፣ ለአሜሪካውያን እና በኻሜኒ የደም ጥማት ባላቸው ወሮበሎች ለተገደሉና ለተሰቃዩ የዓለም ህዝቦች ሁሉ የተገኘ ፍትህ ነው " ብለዋል።
ኻሜኒ የአሜሪካን የመረጃ እና እጅግ የተራቀቁ የመከታተያ ዘዴዎችን ማምለጥ እንዳልቻሉ ገልጸዋል።
" አሜሪካ ከእስራኤል ጋር በቅርበት በመስራቷ እርሱም ሆነ አብረውት የተገደሉት ሌሎች መሪዎች ሊያደርጉት የሚችሉት ምንም ነገር አልነበረም " ብለዋል።
ይህ የኢራን ህዝብ ሀገሩን መልሶ ለመረከብ የሚያገኘው ትልቁ ዕድል መሆኑን ጠቁመዋል።
" ብዙዎቹ የኢራን አብዮታዊ ዘብ አባላት ፣ የጦር ሰራዊት እና የፖሊስ አባላት መዋጋት እንደማይፈልጉና ምህረት እየጠየቁ መሆኑን ሰምተናል " ያሉት ትራምፕ "አሁን ምህረት ማግኘት ይችላሉ ቆይተው ግን የሚያገኙት ሞትን ብቻ ነው " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
" ኢራን በአንድ ቀን ውስጥ ክፉኛ ብትመታም፣ በመካከለኛው ምስራቅ እና በዓለም ላይ ሰላምን ለማረጋገጥ ሲባል ከባድ እና ኢላማውን የጠበቀ ድብደባ አስፈላጊ እስከሆነ ድረስ ለአንድ ሳምንት ወይም ከዚያ በላይ ያለማቋረጥ ይቀጥላል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 22 ቀን 2018
@tikvahethiopia
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን አሳወቁ።
ትራምፕ ባወጡት መግለጫ " ኻሜኒ ሞቷል " ብለዋል።
ፕሬዜዳንቱ " በታሪክ ውስጥ ካሉ እጅግ ክፉ ሰዎች አንዱ የሆነው ኻሜኒ ሞቷል። ይህ ለኢራን ህዝብ፣ ለአሜሪካውያን እና በኻሜኒ የደም ጥማት ባላቸው ወሮበሎች ለተገደሉና ለተሰቃዩ የዓለም ህዝቦች ሁሉ የተገኘ ፍትህ ነው " ብለዋል።
ኻሜኒ የአሜሪካን የመረጃ እና እጅግ የተራቀቁ የመከታተያ ዘዴዎችን ማምለጥ እንዳልቻሉ ገልጸዋል።
" አሜሪካ ከእስራኤል ጋር በቅርበት በመስራቷ እርሱም ሆነ አብረውት የተገደሉት ሌሎች መሪዎች ሊያደርጉት የሚችሉት ምንም ነገር አልነበረም " ብለዋል።
ይህ የኢራን ህዝብ ሀገሩን መልሶ ለመረከብ የሚያገኘው ትልቁ ዕድል መሆኑን ጠቁመዋል።
" ብዙዎቹ የኢራን አብዮታዊ ዘብ አባላት ፣ የጦር ሰራዊት እና የፖሊስ አባላት መዋጋት እንደማይፈልጉና ምህረት እየጠየቁ መሆኑን ሰምተናል " ያሉት ትራምፕ "አሁን ምህረት ማግኘት ይችላሉ ቆይተው ግን የሚያገኙት ሞትን ብቻ ነው " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
" ኢራን በአንድ ቀን ውስጥ ክፉኛ ብትመታም፣ በመካከለኛው ምስራቅ እና በዓለም ላይ ሰላምን ለማረጋገጥ ሲባል ከባድ እና ኢላማውን የጠበቀ ድብደባ አስፈላጊ እስከሆነ ድረስ ለአንድ ሳምንት ወይም ከዚያ በላይ ያለማቋረጥ ይቀጥላል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 22 ቀን 2018
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢራን በሆርሞዝጋን ግዛት በምትገኘው ሚናብ የአንደኛ ደረጃ የሴቶች ትምህርት ቤት ላይ የእስራኤል ጥቃት ተከትሎ የ40 ሰዎች ህይወት አልፏል።
በመጀመሪያ በቴህራን ቀጥሎም በተቀረው የሀገሪቱ ክፍል በተዘገበው የእስራኤል-አሜሪካ የአየር ጥቃት በሴቶች ትምህርት ቤት 40 ሰዎች ተገድለዋል። የኢራን ፓራሚሊተሪ አብዮታዊ ጥበቃ በሚናብ ውስጥ የጦር ሰፈር አለው።
በኢራን ላይ ከደረሰው ጥቃት በኋላ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራን ህዝብ እጣ ፈንታውን እንዲቆጣጠሩ እና ከ1979 ጀምሮ ሀገሪቱን እየመራ ባለው አመራር ላይ እንዲነሱ ጥሪ አቅርበዋል ።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
⚫️ " ለጊዜው በየቤታቸው ቢቆዩ ይመከራል ! "
በመካከለኛው ምስራቅ እየተከሰተ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ በዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አቅርቧል።
በሚኒስቴሩ የመካከለኛው ምሥራቅ፣ ኤዥያ እና የፓስፊክ ሀገራት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ደዋኖ ከድር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፤ መንግስት ቀውሱ ያለበትን ሁኔታ በአንክሮ እየተከታተለ መሆኑን ገልጸው፣ ዜጎች በአካባቢያቸው የሚሰጡ መመሪያዎችንና መረጃዎችን በጥንቃቄ እንዲከታተሉ አሳስበዋል።
አምባሳደር ደዋኖ " ዜጎቻችን አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው ፤ ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተልን ነው " ብለዋል።
አክለውም ዜጎች ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን ለመቀነስ በአካባቢያቸው የሚወጡ መረጃዎችን በትኩረት እንዲያዳምጡና " ለጊዜው በየቤታቸው ቢቆዩ ይመከራል " ሲሉ የደህንነት ምክረ-ሃሳባቸውን ለግሰዋል።
መንግስት ለዜጎቹ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተር ጀነራሉ፤ " ከእኛ በኩል እንደ መንግስት የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ እናደርጋለን፤ ለጊዜው ግን ከዜጎች የሚጠበቀው ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ብቻ ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
እንደ አምባሳደር ደዋኖ ገለጻ፣ ሁኔታው አዲስና በየጊዜው የሚቀያየር በመሆኑ ሂደቱ ወዴት ሊያመራ እንደሚችል በአሁኑ ወቅት ለመገመት አስቸጋሪ ነው።
ይሁን እንጂ መንግስት ጉዳዩን በትኩረት እየተከታተለ መሆኑንና ተጨማሪ መረጃዎች ሲኖሩ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረጉ አስታውቀዋል።
ሁኔታው እየተባባሰ ቢሄድ ከዜጎች ደህንነት አንጻር መንግስት ምን አይነት እርምጃዎችን ሊወስድ ይችላል ? በሚል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረብንላቸው ጥያቄ ሲመልሱም፤ " እንደ ሁኔታው ነው የሚሆነው፤ ወደፊት ምን ሊከሰት እንደሚችል አሁን ላይ ለመገመት ይከብዳል የሚወሰዱ እርምጃዎች በሚፈጠሩትና በሚቀጥሉት ሁኔታዎች ላይ የተመሰረቱ ይሆናሉ " ብለዋል።.
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvaheth
⚫️ " ለጊዜው በየቤታቸው ቢቆዩ ይመከራል ! "
በመካከለኛው ምስራቅ እየተከሰተ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ በዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አቅርቧል።
በሚኒስቴሩ የመካከለኛው ምሥራቅ፣ ኤዥያ እና የፓስፊክ ሀገራት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ደዋኖ ከድር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፤ መንግስት ቀውሱ ያለበትን ሁኔታ በአንክሮ እየተከታተለ መሆኑን ገልጸው፣ ዜጎች በአካባቢያቸው የሚሰጡ መመሪያዎችንና መረጃዎችን በጥንቃቄ እንዲከታተሉ አሳስበዋል።
አምባሳደር ደዋኖ " ዜጎቻችን አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው ፤ ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተልን ነው " ብለዋል።
አክለውም ዜጎች ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን ለመቀነስ በአካባቢያቸው የሚወጡ መረጃዎችን በትኩረት እንዲያዳምጡና " ለጊዜው በየቤታቸው ቢቆዩ ይመከራል " ሲሉ የደህንነት ምክረ-ሃሳባቸውን ለግሰዋል።
መንግስት ለዜጎቹ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተር ጀነራሉ፤ " ከእኛ በኩል እንደ መንግስት የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ እናደርጋለን፤ ለጊዜው ግን ከዜጎች የሚጠበቀው ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ብቻ ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
እንደ አምባሳደር ደዋኖ ገለጻ፣ ሁኔታው አዲስና በየጊዜው የሚቀያየር በመሆኑ ሂደቱ ወዴት ሊያመራ እንደሚችል በአሁኑ ወቅት ለመገመት አስቸጋሪ ነው።
ይሁን እንጂ መንግስት ጉዳዩን በትኩረት እየተከታተለ መሆኑንና ተጨማሪ መረጃዎች ሲኖሩ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረጉ አስታውቀዋል።
ሁኔታው እየተባባሰ ቢሄድ ከዜጎች ደህንነት አንጻር መንግስት ምን አይነት እርምጃዎችን ሊወስድ ይችላል ? በሚል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረብንላቸው ጥያቄ ሲመልሱም፤ " እንደ ሁኔታው ነው የሚሆነው፤ ወደፊት ምን ሊከሰት እንደሚችል አሁን ላይ ለመገመት ይከብዳል የሚወሰዱ እርምጃዎች በሚፈጠሩትና በሚቀጥሉት ሁኔታዎች ላይ የተመሰረቱ ይሆናሉ " ብለዋል።.
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvaheth
በሌላ በኩል የኩዌት መንግሥት ሁኔታው እስስኪረጋጋ ነዋሪዎች በቤታቸው እንዲቆዩ አሳስቧል
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
በወጣቷ ላይ የመግደል ሙከራ ወንጀል ፈፅሞ የተሰወረን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር አውሎ ለአማራ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ማስረከቡን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህር ዳር ከተማ ነዋሪ የሆነችና የግል ተበዳይ ወ/ሪት ትዕግስት አየነው የተባለች ወጣት ላይ የመግደል ሙከራ በመፈፀም በፖሊስ ክትትል ሲደረግበት የነበረው የቀድሞው ፍቅረኛዋ ኢዮብ ወይም ናትናኤል ጫኔ በቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አባላት በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን ፖሊስ አመልክቷል።
ተከሳሹ ከዚህ ቀድም በፍቅረኛው ላይ ወንጀሉን ፈፅሞ የባህር ዳርና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በሌለበት በ8 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖቡ ነበር። ይሁን እንጂ ተፈላጊው ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ተሰውሮ ቆይቷል።
ፖሊስ በተፈላጊው ላይ የወጣበትን የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ መሰረት በማድረግ ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪውን የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 12፡00 ሠዓት አካባቢ ገርጂ ዱባይ ሞል አካባቢ በቁጥጥር ስር በማዋል ለአማራ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እንዳስረከበ አሳውቋል።
አዲስ አበባ ፖሊስ
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
በወጣቷ ላይ የመግደል ሙከራ ወንጀል ፈፅሞ የተሰወረን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር አውሎ ለአማራ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ማስረከቡን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህር ዳር ከተማ ነዋሪ የሆነችና የግል ተበዳይ ወ/ሪት ትዕግስት አየነው የተባለች ወጣት ላይ የመግደል ሙከራ በመፈፀም በፖሊስ ክትትል ሲደረግበት የነበረው የቀድሞው ፍቅረኛዋ ኢዮብ ወይም ናትናኤል ጫኔ በቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አባላት በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን ፖሊስ አመልክቷል።
ተከሳሹ ከዚህ ቀድም በፍቅረኛው ላይ ወንጀሉን ፈፅሞ የባህር ዳርና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህዳር 19 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በሌለበት በ8 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖቡ ነበር። ይሁን እንጂ ተፈላጊው ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ተሰውሮ ቆይቷል።
ፖሊስ በተፈላጊው ላይ የወጣበትን የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ መሰረት በማድረግ ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪውን የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 12፡00 ሠዓት አካባቢ ገርጂ ዱባይ ሞል አካባቢ በቁጥጥር ስር በማዋል ለአማራ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እንዳስረከበ አሳውቋል።
አዲስ አበባ ፖሊስ
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸውን ተከትሎ ኢራንም የአጸፋ እርምጃ እየወሰደች ነው።
በየሰዓቱ እየከፋ የመጣው የመካከለኛው ምሥራቅ ሁኔታ ለዓለም የነዳጅ ንግድ " የልብ ትርታ ነው " በሚባለው የሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ስጋት አሳድሯል።
በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፉ መርከቦች ለጥቃት የመጋለጥ እድላቸው ከፍተኛ ሆኗል።
በርካታ ግዙፍ የነዳጅ ኩባንያዎች በጸጥታ ስጋት በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል የሚያደርጉትን የነዳጅ ማጓጓዝ ስራ ለጊዜው ማቋረጣቸውን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያሳድር የሚችለው ይህ ጉዞ የማቋረጥ እርምጃ ኩባንያዎቹ የመርከቦቻቸውን እና የሠራተኞቻቸውን ደህንነት ለመጠበቅ ሲሉ የወሰዱት ጥንቃቄ መሆኑ ተገልጿል።
ብዙ መርከቦች ወደ ሰርጡ ከመግባት ይልቅ በቅርብ ወደሚገኙ ወደቦች ተጠግተው ሁኔታውን በመከታተል ላይ ናቸው።
ይህ ሰርጥ የዓለም ወሳኙ የነዳጅ ዘይት መተላለፊያ ነው።
20% ወይም በቀን እስከ 21 ሚሊዮን በርሜል ገደማ የዓለም ነዳጅ ዘይት የሚያልፈው በዚህ ጠባብ መስመር ነው።
ከዚህ ባለፈ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የኳታር ተፈጥሮ ጋዝ የሚያልፈው በዚህ ነው።
- ሳውዲ አረቢያ፣
- ኢራቅ፣
- የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣
- ኩዌት እና ኳታር ነዳጃቸውን የሚልኩበት ዋና መስመር ነው።
የኤነርጂ ተንታኞች እንደሚሉት፣ የመካከለኛ ምሥራው ውጥረት ካልረገበ የነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ ሊያሳይ ይችላል።
መርከቦች ጉዟቸውን ካቆሙ በዓለም ዙሪያ የነዳጅ እጥረት ሊከሰትም ይችላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸውን ተከትሎ ኢራንም የአጸፋ እርምጃ እየወሰደች ነው።
በየሰዓቱ እየከፋ የመጣው የመካከለኛው ምሥራቅ ሁኔታ ለዓለም የነዳጅ ንግድ " የልብ ትርታ ነው " በሚባለው የሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ስጋት አሳድሯል።
በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፉ መርከቦች ለጥቃት የመጋለጥ እድላቸው ከፍተኛ ሆኗል።
በርካታ ግዙፍ የነዳጅ ኩባንያዎች በጸጥታ ስጋት በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል የሚያደርጉትን የነዳጅ ማጓጓዝ ስራ ለጊዜው ማቋረጣቸውን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያሳድር የሚችለው ይህ ጉዞ የማቋረጥ እርምጃ ኩባንያዎቹ የመርከቦቻቸውን እና የሠራተኞቻቸውን ደህንነት ለመጠበቅ ሲሉ የወሰዱት ጥንቃቄ መሆኑ ተገልጿል።
ብዙ መርከቦች ወደ ሰርጡ ከመግባት ይልቅ በቅርብ ወደሚገኙ ወደቦች ተጠግተው ሁኔታውን በመከታተል ላይ ናቸው።
ይህ ሰርጥ የዓለም ወሳኙ የነዳጅ ዘይት መተላለፊያ ነው።
20% ወይም በቀን እስከ 21 ሚሊዮን በርሜል ገደማ የዓለም ነዳጅ ዘይት የሚያልፈው በዚህ ጠባብ መስመር ነው።
ከዚህ ባለፈ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የኳታር ተፈጥሮ ጋዝ የሚያልፈው በዚህ ነው።
- ሳውዲ አረቢያ፣
- ኢራቅ፣
- የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣
- ኩዌት እና ኳታር ነዳጃቸውን የሚልኩበት ዋና መስመር ነው።
የኤነርጂ ተንታኞች እንደሚሉት፣ የመካከለኛ ምሥራው ውጥረት ካልረገበ የነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ ሊያሳይ ይችላል።
መርከቦች ጉዟቸውን ካቆሙ በዓለም ዙሪያ የነዳጅ እጥረት ሊከሰትም ይችላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ቪድዮዎቹ ከማህበራዊ ሚዲያ የተገኙ ናቸው።
@tikvahethiopia
ቪድዮዎቹ ከማህበራዊ ሚዲያ የተገኙ ናቸው።
@tikvahethiopia
በመካከለኛው ምስራቅ እጅግ እየተባባሰ የመጣውን ቀጠናዊ ውጥረት ተከትሎ የኤምሬትስ አየር መንገድ ወደ ዱባይ የሚገቡና የሚወጡ በረራዎችን በሙሉ በጊዜያዊነት ማገዱን አስታውቋል።
አየር መንገዱ ለተጓዦች ደህንነት ሲባል በረራዎች መቋረጣቸውን ገልጿል።
ተጓዦች ወደ ኤርፖርት ከመሄዳቸው በፊት የበረራቸውን ሁኔታ በድረ-ገጽ እንዲያረጋግጡ አሳስቧል።
በዱባይና በአቡ ዳቢ የተለያዩ አካባቢዎች የፍንዳታ ድምጾች መሰማታቸውን የዓይን እማኞችና ዓለም አቀፍ የዜና ወኪሎች ዘግበዋል።
ይህ የሆነው የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መከላከያ ኃይል ወደ ሀገሪቱ የተተኮሱ ሚሳይሎችን በአየር ላይ ለማክሸፍ በሚያደርገው ጥረት እንደሆነ ተገልጿል።
እስካሁን ባለው መረጃ በአቡ ዳቢ በወደቀ ፍርስራሽ የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን በዱባይ ስላለው የጉዳት መጠን የተባለ ነገር የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
Reviews channel
4 total reviews
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
Advertising on the Telegram channel «𝗔𝗕𝗖 𝗡𝗘𝗪𝗦 𝗔𝗠𝗛𝗔𝗥𝗜𝗖» is a Telegram channel in the category «Новости и СМИ», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 813 subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 12.3, with 4 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 2.4 ₽, and with 4 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий