
- Main
- Catalog
- News and Media
- 𝗔𝗕𝗖 𝗡𝗘𝗪𝗦 𝗔𝗠𝗛𝗔𝗥𝗜𝗖
𝗔𝗕𝗖 𝗡𝗘𝗪𝗦 𝗔𝗠𝗛𝗔𝗥𝗜𝗖
This public channel features all aspects of life in # Ethiopia, # News # Zena # News #Reviews
Channel statistics
መንግስት ከግምጃ ቤትና ከተለያዩ ምንጮች ሀብት ለማምጣት ቢጥርም፣ አሁንም በዘርፉ ትልቅ የፋይናንስ ክፍተት (Funding Gap) መኖሩን ገልጸዋል።
በሽታው አሁንም ከባድ የጤና ስጋት ሲሆን በተለይም እንደ ማረሚያ ቤቶችና የማዕድን ፋብሪካዎች ያሉ ብዙ ሰው የሚገኝባቸው ቦታዎች ለቲቢ ይበልጥ ተጋላጭ ናቸው።
እነዚህ አካባቢዎች ከአጋር አካላት ከፍተኛ ትኩረትና ተጨማሪ ሀብት እንደሚሹ ዴኤታው ጠቁመዋል።
ዶክተር ደረጄ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሽታውን አስቀድሞ ለመለየት የሚረዱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የታገዙ ከ225 በላይ የዲጂታል ኤክስሬይ ማሽኖችን በመግዛት ትልቅ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።
የቲቢ መከላከያ ሕክምና (TPT) ትግበራም በተስፋ ሰጪ መንገድ ላይ ይገኛል ብለዋል።
ከዚህ ባለፈ ፦
✅ የቲቢ ሕክምና ሽፋን 89% መድረሱን
✅ የቲቢ ሞት መጠን ከ21% ወደ 11% ዝቅ ማለቱን ተናግረዋል።
ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ስጋ ደዌን እና ሌሎች የሳንባ በሽታዎችን ለማጥፋት ተጨማሪ ሀብትና የባለብዙ ዘርፍ ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
ተጨማሪ 👇
www.facebook.com/61588053582297/posts/122107837191268452/?app=fbl
#WorldTBDay
ፎቶ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
➡️ " አንድ የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " - ነዋሪ
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞችን እና ሌሎችን ጨምሮ በሁለት ቀናት ብቻ ዘጠኝ ሰዎች ሲገደሉ፣ ሌሎች መጎዳታቸውን የፋብሪካው ሠራተኞች እና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ጉዳዩን ያጣራ አንድ የአካባቢው ነዋሪ በሰጠን ማብራሪያ፣ የፋብሪካው ሠራተኞች በታጣቂዎች የተገደሉት መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም መሆኑን ገልጾ። " አንድ የፋብሪካውን አመራር ለማጥቃት ሂደው ነው ሰባቱን አጃቢዎቹን የገደሏቸው " ብሏል።
ጥቃት አድራሾቹ፣ " መሬታችን ተወስዷል " የሚል ጥያቄ እንዳላቸውም ገልጿል። ጥቃቱ የደረሰው " ጮሬ " በሚባለው የፋብሪካው ካምፕ መሆኑን ያስረዳው ነዋሪው፣ " ሟቾቹ የስኳር ፋብሪካው የጥበቃ ሠራተኞች ናቸው። ታጣቂዎቹ ድንገት መጥተው ተኩስ ፈጽመውባቸው ወዲያው ነው ጫካ የሚገቡት " ሲልም ተናግሯል።
በተያያዘ፣ " ሰባቱ ሰዎች ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፊት መተሐራ እና ወለንጭቲ መካከል የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። በአካባቢው የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " ሲልም ገልጿል።
ሌላኛው ነዋሪ፣ ከ2010 ጀምሮ በየዓመቱ እስከ ዘጠኝ ሰው " የሚገደልበት " ሁኔታ መኖሩን አስረድተው፣ " ህዝቡ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ እያገኘ አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።
የሰሞኑን ጎድያ በተመከለተም፣ " በአንድ መኪና ላይ ነው ሰባቱንም የመንግስት ተቀጣሪዎች፤ የስንት ልጆች አባቶችን በአንድ ቀን ገድለውብናል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ሰሞኑን የተገደሉት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች " ትልልቅ ሰዎች ናቸው " ሲሉ ያስረዱ አንድ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ የፋብሪካው ሠራተኛ ደግሞ፣ ጥቃቱን " አሳዛኝ " ሲሉ ጠርተውታል።
ሰባቱ ሠራተኞች የተገደሉት አንድ የፋብሪካውን አመራር አጅበው በነበረበት ወቅት መሆኑን ተናግረዋል።
የታጣቁት አካላት የፋብሪካው ሠራተኞች ላይ ተኩስ የከፈቱባቸው " ገና ከፒካፕ መኪና ላይ ሳይወርዱ " መሆኑን፣ በዚህም ሌሎቹ ሲገደሉ አብረው የነበሩት አመራሩ " የውሃ ቦይ ውስጥ ገብተው፣ እየተሳቡ " የተኩሱን ቦታ በመራቅ በህይወት መትረፋቸውን አስረድተዋል።
እኚሁ የፋብሪካው ሠራተኛ፣ ይህ ጥቃት ተፈጽሟል ብሎ ለመናገር እንኳ ከፍተኛ ስጋት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ሌላኛው የፋብሪካው ሠራተኛ በበኩላቸው፣ ግድያው የተፈጸመበት " ጮሬ " በተሰኘው ቦታ አጠገብ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ከሟቾቹ ጋር ዘጠኝ ሰዎች ነበሩ ብለው፣ " ሰባቱ ወዲያው ተገደሉ። አንዱ የሞተ መስሏቸው ጥለውት ሄዱ። አልሞተም ግን እግሩ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። አንዱ ደግሞ ተርፏል " ብለዋል። " ስድስቱ በሰፊ ጉድጓድ በአንድ ቦታ ተቀብረዋል " ነው ያሉት።
አዲስ የመጡት የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ ለሟች ቤተሰቦች " በየቤታቸው ሂደው ለእያንዳንዳቸው 150 ሺሕ ብር ሰጥተዋል። 'የተማረ ልጅ ካላቸው በቋሚነት ሥራ እንቀጥራን፣ ካልተማሩ በመደብ 6 የአባታቶቻቸውን ቦታ ይይዛሉ' ሲሉም ቃል ገብተዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ጥቃቱ ከደረሰ በኋላ ያለውን ድባብ ሲያስረዱ ደግሞ፣ ለጊዜው "መከላከያ ገብቷል" ብለዋል።
የአካባቢው ነዋሪ ግን፣ " በአካባቢው የጸጥታ ችግር ተንሰራፍቷል። በሰላም ወጥቶ መግባት በጣም አስቸጋሪ ሆኗል " ሲሉም የሁነቱን አሳሳቢነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ከአንድ ወር በፊት ሁለት ልጆች ታግተው 2 ሚሊዮን ብር ተጠይቆባቸው ነበር። 2 ሚሊዮን ብር ተሰብስቦ አንድ ልጅ ወስዶ ሰጣቸው። በኋላም ለቀቋቸው። ከፍተኛ ድብደባ እና ራሳቸውን እስኪስቱ ድረስ የረሃብ ስቃይ አድርሰውባቸው መንገድ ላይ ነው የጣሏቸው " ሲሉም አስታውሰዋል።
" ገንዘቡን ያደረሰው ልጅ ግን ተገድሏል" በማለት አዝነዋል። ከመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች መካከል አንዱ በበኩላቸው፣ ታጣቂዎቹ "ከአዳማ መተሐራ መንገድ በኃይለኛው እያገቱ ነው፤ ተሳፋሪም መውሰድ ጀምረዋል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካውንም ሆነ ሌሎች የአካባቢውን ኃላፊዎች ለማግኘት ለቀናት ያደረገው ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ጥረቱ ይቀጥላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
➡️ " አንድ የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " - ነዋሪ
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞችን እና ሌሎችን ጨምሮ በሁለት ቀናት ብቻ ዘጠኝ ሰዎች ሲገደሉ፣ ሌሎች መጎዳታቸውን የፋብሪካው ሠራተኞች እና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ጉዳዩን ያጣራ አንድ የአካባቢው ነዋሪ በሰጠን ማብራሪያ፣ የፋብሪካው ሠራተኞች በታጣቂዎች የተገደሉት መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም መሆኑን ገልጾ። " አንድ የፋብሪካውን አመራር ለማጥቃት ሂደው ነው ሰባቱን አጃቢዎቹን የገደሏቸው " ብሏል።
ጥቃት አድራሾቹ፣ " መሬታችን ተወስዷል " የሚል ጥያቄ እንዳላቸውም ገልጿል። ጥቃቱ የደረሰው " ጮሬ " በሚባለው የፋብሪካው ካምፕ መሆኑን ያስረዳው ነዋሪው፣ " ሟቾቹ የስኳር ፋብሪካው የጥበቃ ሠራተኞች ናቸው። ታጣቂዎቹ ድንገት መጥተው ተኩስ ፈጽመውባቸው ወዲያው ነው ጫካ የሚገቡት " ሲልም ተናግሯል።
በተያያዘ፣ " ሰባቱ ሰዎች ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፊት መተሐራ እና ወለንጭቲ መካከል የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። በአካባቢው የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " ሲልም ገልጿል።
ሌላኛው ነዋሪ፣ ከ2010 ጀምሮ በየዓመቱ እስከ ዘጠኝ ሰው " የሚገደልበት " ሁኔታ መኖሩን አስረድተው፣ " ህዝቡ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ እያገኘ አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።
የሰሞኑን ጎድያ በተመከለተም፣ " በአንድ መኪና ላይ ነው ሰባቱንም የመንግስት ተቀጣሪዎች፤ የስንት ልጆች አባቶችን በአንድ ቀን ገድለውብናል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ሰሞኑን የተገደሉት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች " ትልልቅ ሰዎች ናቸው " ሲሉ ያስረዱ አንድ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ የፋብሪካው ሠራተኛ ደግሞ፣ ጥቃቱን " አሳዛኝ " ሲሉ ጠርተውታል።
ሰባቱ ሠራተኞች የተገደሉት አንድ የፋብሪካውን አመራር አጅበው በነበረበት ወቅት መሆኑን ተናግረዋል።
የታጣቁት አካላት የፋብሪካው ሠራተኞች ላይ ተኩስ የከፈቱባቸው " ገና ከፒካፕ መኪና ላይ ሳይወርዱ " መሆኑን፣ በዚህም ሌሎቹ ሲገደሉ አብረው የነበሩት አመራሩ " የውሃ ቦይ ውስጥ ገብተው፣ እየተሳቡ " የተኩሱን ቦታ በመራቅ በህይወት መትረፋቸውን አስረድተዋል።
እኚሁ የፋብሪካው ሠራተኛ፣ ይህ ጥቃት ተፈጽሟል ብሎ ለመናገር እንኳ ከፍተኛ ስጋት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ሌላኛው የፋብሪካው ሠራተኛ በበኩላቸው፣ ግድያው የተፈጸመበት " ጮሬ " በተሰኘው ቦታ አጠገብ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ከሟቾቹ ጋር ዘጠኝ ሰዎች ነበሩ ብለው፣ " ሰባቱ ወዲያው ተገደሉ። አንዱ የሞተ መስሏቸው ጥለውት ሄዱ። አልሞተም ግን እግሩ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። አንዱ ደግሞ ተርፏል " ብለዋል። " ስድስቱ በሰፊ ጉድጓድ በአንድ ቦታ ተቀብረዋል " ነው ያሉት።
አዲስ የመጡት የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ ለሟች ቤተሰቦች " በየቤታቸው ሂደው ለእያንዳንዳቸው 150 ሺሕ ብር ሰጥተዋል። 'የተማረ ልጅ ካላቸው በቋሚነት ሥራ እንቀጥራን፣ ካልተማሩ በመደብ 6 የአባታቶቻቸውን ቦታ ይይዛሉ' ሲሉም ቃል ገብተዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ጥቃቱ ከደረሰ በኋላ ያለውን ድባብ ሲያስረዱ ደግሞ፣ ለጊዜው "መከላከያ ገብቷል" ብለዋል።
የአካባቢው ነዋሪ ግን፣ " በአካባቢው የጸጥታ ችግር ተንሰራፍቷል። በሰላም ወጥቶ መግባት በጣም አስቸጋሪ ሆኗል " ሲሉም የሁነቱን አሳሳቢነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ከአንድ ወር በፊት ሁለት ልጆች ታግተው 2 ሚሊዮን ብር ተጠይቆባቸው ነበር። 2 ሚሊዮን ብር ተሰብስቦ አንድ ልጅ ወስዶ ሰጣቸው። በኋላም ለቀቋቸው። ከፍተኛ ድብደባ እና ራሳቸውን እስኪስቱ ድረስ የረሃብ ስቃይ አድርሰውባቸው መንገድ ላይ ነው የጣሏቸው " ሲሉም አስታውሰዋል።
" ገንዘቡን ያደረሰው ልጅ ግን ተገድሏል" በማለት አዝነዋል። ከመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች መካከል አንዱ በበኩላቸው፣ ታጣቂዎቹ "ከአዳማ መተሐራ መንገድ በኃይለኛው እያገቱ ነው፤ ተሳፋሪም መውሰድ ጀምረዋል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካውንም ሆነ ሌሎች የአካባቢውን ኃላፊዎች ለማግኘት ለቀናት ያደረገው ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ጥረቱ ይቀጥላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በቡርጂ ዞን በውርስ ምክንያት 3 የቤተሰባቸውን አባላትን በጥይት ደብድበው የገደሉ ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ።
ይህ በአከባቢው የመጀመሪያው የሞት ፍርድ ውሳኔ እንደሆነ ተገልጿል።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ነሐሴ 16/2017 ዓ/ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሶያማ ዙሪያ ወረዳ ገራ ቀበሌ መሆኑን በዞን ፍትህ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ነጋልኝ ዓለሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በዚሁ ቀበሌ አቶ ዋቶ ወርቁ የተባሉ አዛውንት ዕድሜያቸው እየገፋ መምጣቱን ተከትሎ በአከባቢው ባህል መሰረት ልጆቻቸውን ጠርተው የመሬት ውርስ ክፍፍል ማድረግ ይጀምራሉ።
ይህ እየሆነ ባለበት በሂደቱ ተቃርኖ የነበራቸው የአዛውንቱ የመጀመሪያ ልጅ እና የልጅ ልጃቸው ሁለቱም የክላሽ ኮቭ መሳሪያ በመታጠቅ በቤተሰብ አባላቱ ላይ ተኩስ መክፈታቸውን አቶ ነጋልኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በጥቃቱ አዛውንቱ አቶ ዋቶ ወርቁን እና ሁለት ልጆቻቸው ወዲያውኑ ሲሞቱ ሁለት የቤተሰብ አባላት ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ አርባምንጭ ሪፌራል ሆስፒታል መላካቸውን ገልፀዋል።
ፖሊስም ግለሰቦቹን ከነመሳሪያቸው ኤግዚቢትነት በመያዝ ምርመራ ማድረግ ይጀምራል። መዝገቡንም አደራጅቶ ለዞኑ ዐቃቤ ሕግ ያቀርባል።
ዐቃቤ ሕግ መዝገቡን በማደራጀት በሁለቱ ተከሳሾች ላይ በዋና ወንጀል አድራጊነት ፦
• በሶስት የግድያ ወንጀል ክስ በወንጀል ህጉ አንቀጽ 539/1/ሀ መሠረት በከባድ የሰዉ ነብስ ማጥፋት ወንጀል
• ሁለት በህይወት በተረፉ የግል ተበዳዮች ወንጀል ሁለት ክስ በወንጀል ህግ አንቀጽ 27 እና 539/1/ሀ መሠረት ክስ ማቅረቡን አቶ ነጋልኝ አስረድተዋል።
ተከሳሾች ፍርድ ቤት ቀርበው የወንጀል ድርጊቱን ስለመፈፀማቸው ተጠይቀው " አልፈፀምንም " በማለት ክደዉ ተከራክረዋል።
አቃቤ ህግ በሰዉና በሰነድ ማስረጃ አምስቱንም ክስ በሚገባ ያስረዳ ሲሆን ተከሳሾች የቀረበባቸዉን ክስ መከላከል ባለመቻላቸው የቡርጂ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ተከሳሾችን በቀረበባቸው ክሶች ጥፋተኛ ናቸው ብሏል።
የፈፀሙት ወንጀል ጭካኔ የተሞላበትና አስነዋሪ መሆኑ ፤ በአከባቢው ከዚህ ቀደም ተደርጎ የማይታወቅ ፤ ከሁለት በላይ የሆነ የቤተሰብ አባላት ላይ በአንድ ጊዜ የተፈፀመ ግድያ መሆኑን ከግምት ውስጥ ገብቷል።
ፍርድ ቤቱ ሁለቱም ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፏል።
ይህ አይነቱ የወንጀል ድርጊት በአከባቢው ሲፈፀም የመጀመሪያ ነው ያሉት አቶ ነጋልኝ የሞት ፍርድ ውሳኔም በዞኑ የመጀመሪያ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
በቡርጂ ዞን በውርስ ምክንያት 3 የቤተሰባቸውን አባላትን በጥይት ደብድበው የገደሉ ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ።
ይህ በአከባቢው የመጀመሪያው የሞት ፍርድ ውሳኔ እንደሆነ ተገልጿል።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ነሐሴ 16/2017 ዓ/ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሶያማ ዙሪያ ወረዳ ገራ ቀበሌ መሆኑን በዞን ፍትህ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ነጋልኝ ዓለሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በዚሁ ቀበሌ አቶ ዋቶ ወርቁ የተባሉ አዛውንት ዕድሜያቸው እየገፋ መምጣቱን ተከትሎ በአከባቢው ባህል መሰረት ልጆቻቸውን ጠርተው የመሬት ውርስ ክፍፍል ማድረግ ይጀምራሉ።
ይህ እየሆነ ባለበት በሂደቱ ተቃርኖ የነበራቸው የአዛውንቱ የመጀመሪያ ልጅ እና የልጅ ልጃቸው ሁለቱም የክላሽ ኮቭ መሳሪያ በመታጠቅ በቤተሰብ አባላቱ ላይ ተኩስ መክፈታቸውን አቶ ነጋልኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በጥቃቱ አዛውንቱ አቶ ዋቶ ወርቁን እና ሁለት ልጆቻቸው ወዲያውኑ ሲሞቱ ሁለት የቤተሰብ አባላት ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ አርባምንጭ ሪፌራል ሆስፒታል መላካቸውን ገልፀዋል።
ፖሊስም ግለሰቦቹን ከነመሳሪያቸው ኤግዚቢትነት በመያዝ ምርመራ ማድረግ ይጀምራል። መዝገቡንም አደራጅቶ ለዞኑ ዐቃቤ ሕግ ያቀርባል።
ዐቃቤ ሕግ መዝገቡን በማደራጀት በሁለቱ ተከሳሾች ላይ በዋና ወንጀል አድራጊነት ፦
• በሶስት የግድያ ወንጀል ክስ በወንጀል ህጉ አንቀጽ 539/1/ሀ መሠረት በከባድ የሰዉ ነብስ ማጥፋት ወንጀል
• ሁለት በህይወት በተረፉ የግል ተበዳዮች ወንጀል ሁለት ክስ በወንጀል ህግ አንቀጽ 27 እና 539/1/ሀ መሠረት ክስ ማቅረቡን አቶ ነጋልኝ አስረድተዋል።
ተከሳሾች ፍርድ ቤት ቀርበው የወንጀል ድርጊቱን ስለመፈፀማቸው ተጠይቀው " አልፈፀምንም " በማለት ክደዉ ተከራክረዋል።
አቃቤ ህግ በሰዉና በሰነድ ማስረጃ አምስቱንም ክስ በሚገባ ያስረዳ ሲሆን ተከሳሾች የቀረበባቸዉን ክስ መከላከል ባለመቻላቸው የቡርጂ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ተከሳሾችን በቀረበባቸው ክሶች ጥፋተኛ ናቸው ብሏል።
የፈፀሙት ወንጀል ጭካኔ የተሞላበትና አስነዋሪ መሆኑ ፤ በአከባቢው ከዚህ ቀደም ተደርጎ የማይታወቅ ፤ ከሁለት በላይ የሆነ የቤተሰብ አባላት ላይ በአንድ ጊዜ የተፈፀመ ግድያ መሆኑን ከግምት ውስጥ ገብቷል።
ፍርድ ቤቱ ሁለቱም ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፏል።
ይህ አይነቱ የወንጀል ድርጊት በአከባቢው ሲፈፀም የመጀመሪያ ነው ያሉት አቶ ነጋልኝ የሞት ፍርድ ውሳኔም በዞኑ የመጀመሪያ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ከየካቲት 21/2018 ዓ/ም ጀምሮ አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ የሰነዘሩትን መጠነ ሰፊ ጥቃት ተከትሎ በዓለም የንግድ መስመር ላይ ከፍተኛ ቀውስ ተፈጥሯል።
በዚህም ምክንያት 1,900 የሚጠጉ የንግድ መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ አካባቢ መንቀሳቀስ አቅቷቸው ቆመዋል።
ቴህራን " ከጥቃት አድራሾቹ አገራት ጋር ንክኪ ያላቸው መርከቦች ወሳኝ በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ እንዳያልፉ " በመዝጋቷ የባህር ላይ እንቅስቃሴው ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ሊቆም ችሏል።
መንቀሳቀሻ አጥተው ከቆሙት መርከቦች መካከል ፦
° የነዳጅ ጫኝ፣
° የኬሚካል እና የንግድ ዕቃዎች የያዙ ግዙፍ መርከቦች ይገኙበታል።
ይህም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋና የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል።
መረጃው የአናዱሉ ዜና ወኪል ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
#MiddleEastWar
ፊሊፒንስ ከነዳጅ ጋር በተያያዘ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀች።
በመካከለኛው ምስራቅ በአሜሪካ-እስራኤል እና ኢራን መካከል እየተካሄደ ያለው ጦርነት በዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት ላይ ከፍተኛ እክል መፍጠሩን ተከትሎ ፊሊፒንስ ብሄራዊ የኢነርጂ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጅለች።
ጦርነቱ በመቀጠሉ የነዳጅ ማመላለሻ መስመሮች ከፍተኛ ስጋት ላይ እንደወደቁ ናቸው። ይህም ወደ እስያ የሚላከው የነዳጅ መጠን እንዲቀንስና ዋጋው እንዲንር አድርጓል።
ፊሊፒንስ ከኢነርጂ ጋር በተያያዘ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያወጀችው የመጀመሪያ ሀገር ስትሆን ቀውሱ መላውን የእስያ ቀጠና እያናወጠ ነው።
አህጉሪቱ ከሌሎች በበለጠ በመካከለኛው ምስራቅ ነዳጅ ላይ ጥገኛ በመሆኗ ጦርነቱ የኢኮኖሚ ቀውስ ሊያስከትል እንደሚችል ተሰግቷል።
የነዳጅ ጭነት መርከቦች በጦርነቱ ቀጠና ውስጥ ለማለፍ በመቸገራቸው እና የኢንሹራንስ ዋጋም እጅግ በመጨመሩ መደበኛው የነዳጅ ስርጭት ተገትቷል።
ፊሊፒንስ ያወጀችው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሀገሪቱ መንግስት፦
- የነዳጅ ፍጆታን ለመቀነስ፣
- ዋጋን ለመቆጣጠር፣
- ያሉትን ተጠባባቂ የኃይል አማራጮች በአግባቡ ስራ ላይ ለማዋል ተጨማሪ ስልጣን ይሰጠዋል።
መረጃው ኤቢሲ ኒውስ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ብሔራዊ ባንክ ያወጣው አዲስ መመሪያ በኢንሹራንስ ዘርፉ ላይ ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትን እና የተጠናከረ የኮርፖሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያለመ ነው።
ብሔራዊ ባንክ ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፣ ማንኛውም የኢንሹራንስ ኩባንያ የቦርድ አባላት ስብጥር አንድን ጾታ ብቻ የያዘ መሆን የለበትም። እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ቢያንስ ሁለት ሴት የቦርድ አባላት ሊኖሩት እንደሚገባ መመሪያው የግዴታ መስፈርት አስቀምጧል።
በተጨማሪም አንድ የቦርድ አባል ለመሆን ዝቅተኛው የዕድሜ ገደብ 30 ዓመት መሆን እንዳለበት ተደንግጓል።
እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ሦስት ገለልተኛ (Independent) የቦርድ አባላት ሊኖሩት ይገባል። እነዚህ ግለሰቦች የሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው እና በፋይናንስ ዘርፍ ወይም ተያያዥ መስኮች የ10 ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል ተብሏል።
እንደ መመሪያው ከሆነ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎች በገለልተኛ የቦርድ አባልነት ሊመረጡ ይችላሉ።
አንድ ግለሰብ የኢንሹራንስ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆኖ ለመሾም በኢንሹራንስ ዘርፍ ቢያንስ የ12 ዓመት የሥራ ልምድ ሊኖረው ይገባል። ከዚህ ውስጥ ቢያንስ አምስት ዓመቱን በከፍተኛ የሥራ መሪነት (Senior Executive Officer) ደረጃ የሰራ መሆን ይኖርበታል።
ትምህርትን በተመለከተ ዝቅተኛው መመዘኛ የመጀመሪያ ዲግሪ ወይም በኢንሹራንስ ሙያ ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው ዲፕሎማ (CII) እንዲኖረው ይጠይቃል።
የወንጀል ሪከርድ ያለባቸው፣ በሙስና ወይም በማጭበርበር ድርጊት የተሰማሩ ግለሰቦች በዘርፉ አመራር መሆን አይችሉም።
በፋይናንስ ረገድም ግለሰቡ የከሰረ (Bankrupt) ወይም በባንክ ዕዳ ምክንያት ንብረቱ የተያዘበት መሆን የለበትም።
ኩባንያዎች ስለ አመራሮቻቸው ብቃት ጥርጣሬ ሲኖራቸው ወዲያውኑ ለብሔራዊ ባንክ ማሳወቅ አለባቸው።
እንዲሁም የጥቆማ (Whistleblowing) ሥርዓት መዘርጋት እንዳለባቸው መመሪያው ያዝዛል።
የከፍተኛ ሥራ አስፈጻሚዎችን ሹመት በተመለከተ መመሪያው በሚጠይቀው የጊዜ ገደብ ውስጥ ፈቃድ ያልጠየቁ ኩባንያዎች ለእያንዳንዱ የሥራ መደብ የ10,000 ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
ይህ መመሪያ "በኢንሹራንስ ኩባንያ ውስጥ ተፅዕኖ ያላቸው ግለሰቦች መመዘኛ መመሪያ ቁጥር SIB/63/2026" ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ ከዛሬ ከመጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም (March 26, 2026) ጀምሮ የጸና እንደሚሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከመመሪያው ተመልክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ብሔራዊ ባንክ ያወጣው አዲስ መመሪያ በኢንሹራንስ ዘርፉ ላይ ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትን እና የተጠናከረ የኮርፖሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያለመ ነው።
ብሔራዊ ባንክ ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፣ ማንኛውም የኢንሹራንስ ኩባንያ የቦርድ አባላት ስብጥር አንድን ጾታ ብቻ የያዘ መሆን የለበትም። እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ቢያንስ ሁለት ሴት የቦርድ አባላት ሊኖሩት እንደሚገባ መመሪያው የግዴታ መስፈርት አስቀምጧል።
በተጨማሪም አንድ የቦርድ አባል ለመሆን ዝቅተኛው የዕድሜ ገደብ 30 ዓመት መሆን እንዳለበት ተደንግጓል።
እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ሦስት ገለልተኛ (Independent) የቦርድ አባላት ሊኖሩት ይገባል። እነዚህ ግለሰቦች የሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው እና በፋይናንስ ዘርፍ ወይም ተያያዥ መስኮች የ10 ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል ተብሏል።
እንደ መመሪያው ከሆነ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎች በገለልተኛ የቦርድ አባልነት ሊመረጡ ይችላሉ።
አንድ ግለሰብ የኢንሹራንስ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆኖ ለመሾም በኢንሹራንስ ዘርፍ ቢያንስ የ12 ዓመት የሥራ ልምድ ሊኖረው ይገባል። ከዚህ ውስጥ ቢያንስ አምስት ዓመቱን በከፍተኛ የሥራ መሪነት (Senior Executive Officer) ደረጃ የሰራ መሆን ይኖርበታል።
ትምህርትን በተመለከተ ዝቅተኛው መመዘኛ የመጀመሪያ ዲግሪ ወይም በኢንሹራንስ ሙያ ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው ዲፕሎማ (CII) እንዲኖረው ይጠይቃል።
የወንጀል ሪከርድ ያለባቸው፣ በሙስና ወይም በማጭበርበር ድርጊት የተሰማሩ ግለሰቦች በዘርፉ አመራር መሆን አይችሉም።
በፋይናንስ ረገድም ግለሰቡ የከሰረ (Bankrupt) ወይም በባንክ ዕዳ ምክንያት ንብረቱ የተያዘበት መሆን የለበትም።
ኩባንያዎች ስለ አመራሮቻቸው ብቃት ጥርጣሬ ሲኖራቸው ወዲያውኑ ለብሔራዊ ባንክ ማሳወቅ አለባቸው።
እንዲሁም የጥቆማ (Whistleblowing) ሥርዓት መዘርጋት እንዳለባቸው መመሪያው ያዝዛል።
የከፍተኛ ሥራ አስፈጻሚዎችን ሹመት በተመለከተ መመሪያው በሚጠይቀው የጊዜ ገደብ ውስጥ ፈቃድ ያልጠየቁ ኩባንያዎች ለእያንዳንዱ የሥራ መደብ የ10,000 ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
ይህ መመሪያ "በኢንሹራንስ ኩባንያ ውስጥ ተፅዕኖ ያላቸው ግለሰቦች መመዘኛ መመሪያ ቁጥር SIB/63/2026" ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ ከዛሬ ከመጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም (March 26, 2026) ጀምሮ የጸና እንደሚሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከመመሪያው ተመልክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ በየአንድ ሰዓቱ የሁለት ሰዎች ሕይወት በቲቢ በሽታ ምክንያት እንደሚቀጠፍና ሀገራችን የበሽታው ከፍተኛ ጫና ካለባቸው 30 የዓለም ሀገራት ውስጥም አንዷ መሆኗ ተገለጸ።
ይህ የተገለጸው የዓለም የቲቢ ቀንን ምክንያት በማድረግ በጤናው ዘርፍና በሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ጤና ሚኒስቴር ባዘጋጀው የሚዲያ ፎረም ላይ ነው።
በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ህይወት ሠለሞን እንደገለጹት ፤ መንግሥት ለአንድ የቲቢ ታካሚ በዓመት ከ6 እስከ 8 ሺህ ዶላር ወጪ እያደረገ ይገኛል።
" የቲቢ መድኃኒት ለታማሚዎች በነፃ ነው የሚሰጠው ፤ ከዚህ ውጭ መድኃኒቱን ከፍሎ የሚወስድ ሰው ካለ እየገዛ ያለው የተሰረቀ መድኃኒት ነው " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ከ2,000 በላይ የግል ጤና ተቋማት ምርመራና ሕክምና እየሰጡ ሲሆን ለ1,000 ተቋማት መመርመሪያ መሣሪያዎች መሰራጨታቸውን ገልጸዋል። በገጠሩ አካባቢ ለሚገኙ 690 ላቦራቶሪዎች የሶላር ፓነል ዝርጋታ መከናወኑን አመልክተዋል።
በሚኒስቴሩ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዴስክ ኃላፊ አቶ ታዬ ለታ በበኩላቸው ፥ ባለፉት 6 ወራት ብቻ የሶማሌ ክልልን ሳይጨምር ለ138,000 ሰዎች በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) የታገዘ ምርመራ ተደርጎ 3,500 ያህል የቲቢ ተጠቂዎች መገኘታቸውን ተናግረዋል።
አክለውም ፥ በሀገራችን ከሚከሰቱ የቲቢ አይነቶች 70% ሳምባን የሚያጠቁ ሲሆኑ፣ 30% ደግሞ ሌሎች ሁሉንም የሰውነት ክፍሎችን እንደሚያጠቁ ተናግረዋል።
ምልክቶቹ ፦
• ለሁለት ሳምንትና ከዚያ በላይ የሚቆይ ሳል፣
• ትኩሳት፣
• ማታ ማታ ማላብ፣
• የሰውነት ክብደት መቀነስ፣
• አልፎ አልፎ ደም የቀላቀለ አክታ ናቸው።
አቶ ታዬ በዓለም ላይ በየዓመቱ 10.7 ሚሊዮን ሰዎች በቲቢ እንደሚያዙ ከ1.2 እስከ 1.3 ሚሊዮን የሚደርሱትም ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በዓመት 19,000 ሰዎች ይሞታሉ።
" አንድ የታመመ ሰው ሲያስል ወይም ሲያስነጥስ እስከ 40,000 ሚደርሱ ጥቃቅን ጠብታዎችን ፤ ለ5 ደቂቃ ብቻ ሲያወራ ደግሞ 3,000 ጠብታዎችን ወደ አየር በመልቀቅ በሽታውን በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው ያሰራጫል " ብለዋል።
ሰዎች ሲያስነጥሱ ወይም ሲያስሉ አፍና አፍንጫቸውን በክንድ ወይም ባማስክ መሸፈን አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል።
በየዓመቱ የብዙ ሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ቢሆንም ብዙ ሰው ግድ አይሰጠውም ብለዋል።
እስካሁን 150,000 ታካሚዎች ወደ ሕክምና ማስገባት ቢቻልም አሁንም 30,000 "የተደበቁ" ታማሚዎችን ለማግኘት የጤና ባለሙያዎች ቤት ለቤት ፍለጋ እያደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
ለቲቢ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑት ፦
- ከታካሚ ጋር የሚኖሩ፣
- ስኳርና ኤችአይቪ ያለባቸው
- የአየር ዝውውር በሌለው ቤት የሚኖሩ ናቸው።
በሌላ መረጃ ፥ ባለፉት 6 ወራት 1,460 አዳዲስ የሥጋ ደዌ ታማሚዎች ተለይተዋል። በአሁኑ ወቅት 1,800 ሰዎች በሕክምና ላይ ናቸው። ይህ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በዚህ በሽታ በዓመት እስከ 3000 ሰዎች ይሞታሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ በየአንድ ሰዓቱ የሁለት ሰዎች ሕይወት በቲቢ በሽታ ምክንያት እንደሚቀጠፍና ሀገራችን የበሽታው ከፍተኛ ጫና ካለባቸው 30 የዓለም ሀገራት ውስጥም አንዷ መሆኗ ተገለጸ።
ይህ የተገለጸው የዓለም የቲቢ ቀንን ምክንያት በማድረግ በጤናው ዘርፍና በሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ጤና ሚኒስቴር ባዘጋጀው የሚዲያ ፎረም ላይ ነው።
በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ህይወት ሠለሞን እንደገለጹት ፤ መንግሥት ለአንድ የቲቢ ታካሚ በዓመት ከ6 እስከ 8 ሺህ ዶላር ወጪ እያደረገ ይገኛል።
" የቲቢ መድኃኒት ለታማሚዎች በነፃ ነው የሚሰጠው ፤ ከዚህ ውጭ መድኃኒቱን ከፍሎ የሚወስድ ሰው ካለ እየገዛ ያለው የተሰረቀ መድኃኒት ነው " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ከ2,000 በላይ የግል ጤና ተቋማት ምርመራና ሕክምና እየሰጡ ሲሆን ለ1,000 ተቋማት መመርመሪያ መሣሪያዎች መሰራጨታቸውን ገልጸዋል። በገጠሩ አካባቢ ለሚገኙ 690 ላቦራቶሪዎች የሶላር ፓነል ዝርጋታ መከናወኑን አመልክተዋል።
በሚኒስቴሩ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዴስክ ኃላፊ አቶ ታዬ ለታ በበኩላቸው ፥ ባለፉት 6 ወራት ብቻ የሶማሌ ክልልን ሳይጨምር ለ138,000 ሰዎች በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) የታገዘ ምርመራ ተደርጎ 3,500 ያህል የቲቢ ተጠቂዎች መገኘታቸውን ተናግረዋል።
አክለውም ፥ በሀገራችን ከሚከሰቱ የቲቢ አይነቶች 70% ሳምባን የሚያጠቁ ሲሆኑ፣ 30% ደግሞ ሌሎች ሁሉንም የሰውነት ክፍሎችን እንደሚያጠቁ ተናግረዋል።
ምልክቶቹ ፦
• ለሁለት ሳምንትና ከዚያ በላይ የሚቆይ ሳል፣
• ትኩሳት፣
• ማታ ማታ ማላብ፣
• የሰውነት ክብደት መቀነስ፣
• አልፎ አልፎ ደም የቀላቀለ አክታ ናቸው።
አቶ ታዬ በዓለም ላይ በየዓመቱ 10.7 ሚሊዮን ሰዎች በቲቢ እንደሚያዙ ከ1.2 እስከ 1.3 ሚሊዮን የሚደርሱትም ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በዓመት 19,000 ሰዎች ይሞታሉ።
" አንድ የታመመ ሰው ሲያስል ወይም ሲያስነጥስ እስከ 40,000 ሚደርሱ ጥቃቅን ጠብታዎችን ፤ ለ5 ደቂቃ ብቻ ሲያወራ ደግሞ 3,000 ጠብታዎችን ወደ አየር በመልቀቅ በሽታውን በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው ያሰራጫል " ብለዋል።
ሰዎች ሲያስነጥሱ ወይም ሲያስሉ አፍና አፍንጫቸውን በክንድ ወይም ባማስክ መሸፈን አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል።
በየዓመቱ የብዙ ሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ቢሆንም ብዙ ሰው ግድ አይሰጠውም ብለዋል።
እስካሁን 150,000 ታካሚዎች ወደ ሕክምና ማስገባት ቢቻልም አሁንም 30,000 "የተደበቁ" ታማሚዎችን ለማግኘት የጤና ባለሙያዎች ቤት ለቤት ፍለጋ እያደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
ለቲቢ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑት ፦
- ከታካሚ ጋር የሚኖሩ፣
- ስኳርና ኤችአይቪ ያለባቸው
- የአየር ዝውውር በሌለው ቤት የሚኖሩ ናቸው።
በሌላ መረጃ ፥ ባለፉት 6 ወራት 1,460 አዳዲስ የሥጋ ደዌ ታማሚዎች ተለይተዋል። በአሁኑ ወቅት 1,800 ሰዎች በሕክምና ላይ ናቸው። ይህ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በዚህ በሽታ በዓመት እስከ 3000 ሰዎች ይሞታሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
በጁቡቲ የባህር ዳርቻ አቅራቢያ ከትናንት በስተያ የሰመጠች ጀልባ ውስጥ ከነበሩት ስደተኞች ዘጠኙ መሞታቸውን ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ጉዳይ ድርጅት (IOM) አስታወቀ።
ሌሎች 45 ስደተኞች ደግሞ በህይወት ይኑሩ ይሙቱ እንደማይታወቅ ድርጅቱ ገልጿል።
አደጋው የደረሰው ከትናንት በስተያ መጋቢት 15/ 2018 ዓ.ም. ለሊት ጅቡቲ ከምትገኘው ኦቦክ ከተባለችው ትንሽ ከተማ በስተሰሜን ባለ የባህር ዳርቻ መሆኑን IOM አስታውቋል።
ጀልባዋ 320 ሰዎችን አሳፍራ ነበር።
በፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገባ መሠረት የምሥራቅ መስመር በሚባለው በዚህ የፍልሰት መንገድ ከሚሰደዱት አብዛኛዎቹ ከኢትዮጵያ የሚመጡ ናቸው።
በዚህ መስመር እ.ኤ.አ 2024 የ922 ስደተኞች ሕይወት አልፏል። ይህም እስከዛሬ ከተመዘገበው ሞት ከፍተኛው ተብሏል።
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
ፎቶ፦ IOM
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
በጁቡቲ የባህር ዳርቻ አቅራቢያ ከትናንት በስተያ የሰመጠች ጀልባ ውስጥ ከነበሩት ስደተኞች ዘጠኙ መሞታቸውን ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ጉዳይ ድርጅት (IOM) አስታወቀ።
ሌሎች 45 ስደተኞች ደግሞ በህይወት ይኑሩ ይሙቱ እንደማይታወቅ ድርጅቱ ገልጿል።
አደጋው የደረሰው ከትናንት በስተያ መጋቢት 15/ 2018 ዓ.ም. ለሊት ጅቡቲ ከምትገኘው ኦቦክ ከተባለችው ትንሽ ከተማ በስተሰሜን ባለ የባህር ዳርቻ መሆኑን IOM አስታውቋል።
ጀልባዋ 320 ሰዎችን አሳፍራ ነበር።
በፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገባ መሠረት የምሥራቅ መስመር በሚባለው በዚህ የፍልሰት መንገድ ከሚሰደዱት አብዛኛዎቹ ከኢትዮጵያ የሚመጡ ናቸው።
በዚህ መስመር እ.ኤ.አ 2024 የ922 ስደተኞች ሕይወት አልፏል። ይህም እስከዛሬ ከተመዘገበው ሞት ከፍተኛው ተብሏል።
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
ፎቶ፦ IOM
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ከአሰቃቂ የጅብ ጥቃት መትረፍ የተቀናጀ የህክምና እርዳታ ውጤት !
አንድ ህጻን በጅብ ጥቃት ምክንያት በደረሰበት ከፍተኛ የፊት አካል ጉዳት ምክንያት ወደ አለርት ኮፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከክልል በሪፈር ይላካል።
በጥቃቱ ምክንያት ህጻኑ ሁለቱንም ዓይኖቹን ያጣ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ማየት አይችልም። ከዚህ በተጨማሪ በዓይን አካባቢ፣ በግንባር እና በሁለቱ ጉንጮች ላይ ያለው ቆዳ በጣም ተጎድቶ ነበር። የላይኛው መንጋጋ (maxilla) ከፊል ጠፍቶ የቀሩት አጥንቶች ደግሞ ተሰባብረው ነበር።
ህጻኑ ወዲያውኑ ወደ ህጻናት ጽኑ ህክምና ክፍል (PICU) በመግባት የህይወት አድን ህክምና ተደርጓል። እንዲተነፍስ በአንገቱ በኩል ቀዳዳ በመክፈት (Tracheostomy) ተደርጓል።
በቀጣዮቹ ቀናት የቀዶ ጥገና ቡድኑ ኢንፌክሽንን ለመከላከል እና የሞቱ ቲሹዎችን ለማስወገድ ተከታታይ የጽዳት ሂደቶች (debridement) አከናውኗል።
ቁስሉ ለተሃድሶ ቀዶ ህክምና ዝግጁ ከሆነ በኋላ የፊት ተሃድሶ ስራዎች ተጀምረዋል ፦
1. የቆዳና ቲሹ ንቅለ ተከላ (Free Tissue Transfer)
የፕላስቲክ እና ተሃድሶ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች ከህጻኑ ጭን ላይ 7 ሴ.ሜ x 17 ሴ.ሜ መጠን ያለው ቆዳና ስጋ ከነ ደም ስሩ በመውሰድ ወደ ፊት ተተክሏል። ይህም በጥቃቅን የደም ስር ቀዶ ጥገና (Microsurgery) ቴክኒክ ከፊት ያሉ የደም ስሮች ጋር ተገናኝቶ ተሰርቷል።
2. የአጥንት ተሃድሶ ህክምና
የተሰባበሩት የመንጋጋ አጥንቶች ተስተካክለው የፊት ቅርጽ እንዲመለስ በታይታኒየም ፕሌት እና ስክሩ ተደግፈዋል።
እስካሁን ድረስ ህጻኑ ቢያንስ 8 ቀዶ ጥገናዎችን ያከናወነ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ የፊት ተሃድሶ ስራዎች ይፈልጋሉ። በአሁኑ ወቅት ህጻኑ በመሻሻል ላይ ይገኛል።
ይህ ክስተት የተቀናጀ የህክምና ቡድን (Multidisciplinary Team Approach) ያለውን ትልቅ ፋይዳ እንደሚያሳይ ተገልጿል።
የህጻናት ሐኪሞች፣ የጽኑ ህክምና ባለሙያዎች፣ የጠቅላላ ቀዶ ጥገና እና የፕላስቲክ እና ተሃድሶ ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስቶች በተቀናጀ መልኩ በመስራት የህጻኑን ህይወት ለማዳን እና የፊቱን ቅርጽ ለመመለስ ተግተዋል።
ነገር ግን ይህ አደጋ ብቸኛው አይደለም፤ በአሁኑ ጊዜ በተመሳሳይ የጅብ ጥቃት ጉዳት የደረሰበት ሌላ ህጻን በሆስፒታሉ ተጨማሪ ቀዶ ህክምና በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
ህፃናትን ከጅብ ጥቃት ለመጠበቅ ማህበረሰቡ ህፃናትን ብቻቸውን ባለመተው፣ ንቁ እንክብካቤ በማድረግ እና የመከላከያ እርምጃዎች መውሰድ እጅግ አስፈላጊ ነው።
የተሃድሶ ቀዶ ጥገና (Reconstructive Microsurgery) የጠፋውን መልክና ተግባር ሊመልስ ቢችልም፣ ከሁሉ በላይ ግን አደጋን ከመጀመሪያው መከላከል ነው ዋናው መፍትሄ።
በቀዶ ጥገናው የተሳተፉ ባለሙያዎች፦
• ዶ/ር አብዱረዛቅ አሊ – የፕላስቲክ፣ ሪኮንስትራክቲቭ እና ማይክሮሰርጅን (መሪ ሀኪም)
• ዶ/ር አታክልቲ ባራኪ – የፕላስቲክ፣ ሪኮንስትራክቲቭ እና የእጅ ቀዶ ጥገና ሀኪም
• ዶ/ር ዘቢባ መካ – የፕላስቲክ ሪኮንስትራክቲቭ ሀኪም
• ዶ/ር ተስፋሁን አሊ – ሬዚደንት
• ዶ/ር ዮሃንስ ኤሊያስ – ፌሎው
• ሲራጅ ሙሼ – ማደንዝዣ ባለሙያ
• ናትናኤል ብርሃኑ – ነርስ
• ጫልቱ ተገኔ – ነርስ
• አለሙ ቦጋለ – ነርስ
• ኪሩቤል እሸቱ – ፖርተር
• አባይነው ሰውነት – ፖርተር
• ዘቢደር ፈንቴ – ጽዳት
• እና ሌሎች በርካታ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
(አለርት ኮፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል)
@tikvahethiopia
ከአሰቃቂ የጅብ ጥቃት መትረፍ የተቀናጀ የህክምና እርዳታ ውጤት !
አንድ ህጻን በጅብ ጥቃት ምክንያት በደረሰበት ከፍተኛ የፊት አካል ጉዳት ምክንያት ወደ አለርት ኮፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከክልል በሪፈር ይላካል።
በጥቃቱ ምክንያት ህጻኑ ሁለቱንም ዓይኖቹን ያጣ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ማየት አይችልም። ከዚህ በተጨማሪ በዓይን አካባቢ፣ በግንባር እና በሁለቱ ጉንጮች ላይ ያለው ቆዳ በጣም ተጎድቶ ነበር። የላይኛው መንጋጋ (maxilla) ከፊል ጠፍቶ የቀሩት አጥንቶች ደግሞ ተሰባብረው ነበር።
ህጻኑ ወዲያውኑ ወደ ህጻናት ጽኑ ህክምና ክፍል (PICU) በመግባት የህይወት አድን ህክምና ተደርጓል። እንዲተነፍስ በአንገቱ በኩል ቀዳዳ በመክፈት (Tracheostomy) ተደርጓል።
በቀጣዮቹ ቀናት የቀዶ ጥገና ቡድኑ ኢንፌክሽንን ለመከላከል እና የሞቱ ቲሹዎችን ለማስወገድ ተከታታይ የጽዳት ሂደቶች (debridement) አከናውኗል።
ቁስሉ ለተሃድሶ ቀዶ ህክምና ዝግጁ ከሆነ በኋላ የፊት ተሃድሶ ስራዎች ተጀምረዋል ፦
1. የቆዳና ቲሹ ንቅለ ተከላ (Free Tissue Transfer)
የፕላስቲክ እና ተሃድሶ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች ከህጻኑ ጭን ላይ 7 ሴ.ሜ x 17 ሴ.ሜ መጠን ያለው ቆዳና ስጋ ከነ ደም ስሩ በመውሰድ ወደ ፊት ተተክሏል። ይህም በጥቃቅን የደም ስር ቀዶ ጥገና (Microsurgery) ቴክኒክ ከፊት ያሉ የደም ስሮች ጋር ተገናኝቶ ተሰርቷል።
2. የአጥንት ተሃድሶ ህክምና
የተሰባበሩት የመንጋጋ አጥንቶች ተስተካክለው የፊት ቅርጽ እንዲመለስ በታይታኒየም ፕሌት እና ስክሩ ተደግፈዋል።
እስካሁን ድረስ ህጻኑ ቢያንስ 8 ቀዶ ጥገናዎችን ያከናወነ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ የፊት ተሃድሶ ስራዎች ይፈልጋሉ። በአሁኑ ወቅት ህጻኑ በመሻሻል ላይ ይገኛል።
ይህ ክስተት የተቀናጀ የህክምና ቡድን (Multidisciplinary Team Approach) ያለውን ትልቅ ፋይዳ እንደሚያሳይ ተገልጿል።
የህጻናት ሐኪሞች፣ የጽኑ ህክምና ባለሙያዎች፣ የጠቅላላ ቀዶ ጥገና እና የፕላስቲክ እና ተሃድሶ ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስቶች በተቀናጀ መልኩ በመስራት የህጻኑን ህይወት ለማዳን እና የፊቱን ቅርጽ ለመመለስ ተግተዋል።
ነገር ግን ይህ አደጋ ብቸኛው አይደለም፤ በአሁኑ ጊዜ በተመሳሳይ የጅብ ጥቃት ጉዳት የደረሰበት ሌላ ህጻን በሆስፒታሉ ተጨማሪ ቀዶ ህክምና በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
ህፃናትን ከጅብ ጥቃት ለመጠበቅ ማህበረሰቡ ህፃናትን ብቻቸውን ባለመተው፣ ንቁ እንክብካቤ በማድረግ እና የመከላከያ እርምጃዎች መውሰድ እጅግ አስፈላጊ ነው።
የተሃድሶ ቀዶ ጥገና (Reconstructive Microsurgery) የጠፋውን መልክና ተግባር ሊመልስ ቢችልም፣ ከሁሉ በላይ ግን አደጋን ከመጀመሪያው መከላከል ነው ዋናው መፍትሄ።
በቀዶ ጥገናው የተሳተፉ ባለሙያዎች፦
• ዶ/ር አብዱረዛቅ አሊ – የፕላስቲክ፣ ሪኮንስትራክቲቭ እና ማይክሮሰርጅን (መሪ ሀኪም)
• ዶ/ር አታክልቲ ባራኪ – የፕላስቲክ፣ ሪኮንስትራክቲቭ እና የእጅ ቀዶ ጥገና ሀኪም
• ዶ/ር ዘቢባ መካ – የፕላስቲክ ሪኮንስትራክቲቭ ሀኪም
• ዶ/ር ተስፋሁን አሊ – ሬዚደንት
• ዶ/ር ዮሃንስ ኤሊያስ – ፌሎው
• ሲራጅ ሙሼ – ማደንዝዣ ባለሙያ
• ናትናኤል ብርሃኑ – ነርስ
• ጫልቱ ተገኔ – ነርስ
• አለሙ ቦጋለ – ነርስ
• ኪሩቤል እሸቱ – ፖርተር
• አባይነው ሰውነት – ፖርተር
• ዘቢደር ፈንቴ – ጽዳት
• እና ሌሎች በርካታ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
(አለርት ኮፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል)
@tikvahethiopia
ፕሬዝዳንት ትራምፕ 15 ነጥቦችን የያዘ ዕቅድ ለኢራን መላካቸው ሲዘገብ ፤ ኢራን በበኩሏ " ጦርነቱ የሚያበቃው እራሴ ስወስን እና የራሴ ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ብቻ ነው " የሚል መልስ ሰጥታለች።
ዛሬ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ትልቅ መነጋገሪያ የሆነው የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱ እንዲያበቃ 15 ነጥቦችን የያዘ ዕቅድ ለኢራን መላካቸው ነው።
የስምምነት ነጥቦቹ ይፋ አልወጡም።
ቻናል 12 የተባለው የእስራኤል የቴሌቪዥን ጣቢያ ግን በትራምፕ ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ናቸው ያላቸውን የሚከተሉትን ነጥቦች አስቀምጧል፦
- በናታንዝ፣ ኢስፋሃንና ፎርዶ የሚገኙ የኒውክሌር ተቋማት ሥራ እንዲያቆሙ እና እንዲወድሙ እንዲደረጉ
- በኢራን ውስጥ የሚከናወኑ የኒውክሌር መረሃ ግብሮች ግልጽ እና ዓለም አቀፍ ቁጥጥር እንዲደረግባቸው
- ኢራን በቀጣናው ያሉ ታጣቂ ቡድኖችን መርዳት እና ማስታጠቅ እንድታቆም
- የተከማቹ የኒውክሌር ቁሶችን በሙሉ ማውደም
- ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት ለመሆን ፈጽሞ ላለመሞከር ቃል እንድትገባ
- ምንም ዓይነት የኒውክሌር ቁስ በኢራን ውስጥ እንዳይዳብር፣ የዳበሩትም ለዓለም አቀፉ ተቋም እንዲሰጡ
- የሆርሙዝ ወሽመጥ ክፍት እንዲሆን እና " ነጻ የባሕር ቀጣና " እንዲሆን ማድረግ
- የኢራን ሚሳዔል በመጠን እና በሚደርስበት ርቀት ውስን እንዲሆን እና እራስን ለመከላከል ላይ ብቻ እንዲውል
በዚህ ዕቅድ ውስጥ ኢራን የሚከተሉትን ድጋፎች ከስምምነቱ የምታገኝ ይሆናል፦
• ኢራን ቡሽሄር ውስጥ ለኤሌክትሪክ ማመንጫነት ለምታካሂደው የኒውክሌር ግንባታ አሜሪካ ድጋፍ ታደርጋለች።
• በኢራን ላይ የተጣሉ ሁሉም ማዕቀቦች እንዲነሱ ይደረጋሉ
አዲስ ሊጣሉባት የሚችሉ ማዕቀቦች ይቀራሉ።
• በተጨማሪም በሁለቱ ወገኖች መካከል ድርድር በሚደረግበት ጊዜ ለአንድ ወር የሚቆይ የተኩስ አቁም ይኖራል ተብሏል።
ነገር ግን ከዋይት ሐውስ አስካሁን ምንም ዓይነት ዝርዝርም ሆነ ማረጋገጫ አልተሰጠም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ኢራን ምላሽ ሰጥታለች።
የኢራን መንግሥት በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኩል የቀረበውን የድርድር ዕቅድን ውድቅ አድርጓል።
ኢራን " ጦርነቱን የሚያበቃው እራሴ ስወስን እና የራሴ ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ነው " ብላለች።
ኢራን መሟላት አለበት ያለቻቸውን የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ነው።
➡ በጠላት የሚፈጸመው " ወረራ እና ግድያ " ሙሉ ለሙሉ መቆም።
➡ ጦርነቱ በድጋሚ በኢራን ላይ እንደማይከፈት የሚያረጋግጥ አስተማማኝ ሁኔታ መፍጠር።
➡ የተረጋገጠ እና በግልጽ የሚታወቅ በጦርነቱ ለደረሰው ጉዳት እና ካሳ መክፈል።
➡ በቀጣናው ባሉ ቡድኖች ላይ የተከፈቱት ሁሉም ጦርነቶች እንዲቆሙ ማድረግ።
➡ ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ያላትን መብት እና ሉዓላዊነት ዓለም አቀፍ ዕውቅና መስጠት።
የኢራን ባለሥልጣናት እስካሁን ድርድር የሚባል ነገር አለመጀመሩን አሳውቀዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ፕሬዝዳንት ትራምፕ 15 ነጥቦችን የያዘ ዕቅድ ለኢራን መላካቸው ሲዘገብ ፤ ኢራን በበኩሏ " ጦርነቱ የሚያበቃው እራሴ ስወስን እና የራሴ ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ብቻ ነው " የሚል መልስ ሰጥታለች።
ዛሬ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ትልቅ መነጋገሪያ የሆነው የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱ እንዲያበቃ 15 ነጥቦችን የያዘ ዕቅድ ለኢራን መላካቸው ነው።
የስምምነት ነጥቦቹ ይፋ አልወጡም።
ቻናል 12 የተባለው የእስራኤል የቴሌቪዥን ጣቢያ ግን በትራምፕ ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ናቸው ያላቸውን የሚከተሉትን ነጥቦች አስቀምጧል፦
- በናታንዝ፣ ኢስፋሃንና ፎርዶ የሚገኙ የኒውክሌር ተቋማት ሥራ እንዲያቆሙ እና እንዲወድሙ እንዲደረጉ
- በኢራን ውስጥ የሚከናወኑ የኒውክሌር መረሃ ግብሮች ግልጽ እና ዓለም አቀፍ ቁጥጥር እንዲደረግባቸው
- ኢራን በቀጣናው ያሉ ታጣቂ ቡድኖችን መርዳት እና ማስታጠቅ እንድታቆም
- የተከማቹ የኒውክሌር ቁሶችን በሙሉ ማውደም
- ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት ለመሆን ፈጽሞ ላለመሞከር ቃል እንድትገባ
- ምንም ዓይነት የኒውክሌር ቁስ በኢራን ውስጥ እንዳይዳብር፣ የዳበሩትም ለዓለም አቀፉ ተቋም እንዲሰጡ
- የሆርሙዝ ወሽመጥ ክፍት እንዲሆን እና " ነጻ የባሕር ቀጣና " እንዲሆን ማድረግ
- የኢራን ሚሳዔል በመጠን እና በሚደርስበት ርቀት ውስን እንዲሆን እና እራስን ለመከላከል ላይ ብቻ እንዲውል
በዚህ ዕቅድ ውስጥ ኢራን የሚከተሉትን ድጋፎች ከስምምነቱ የምታገኝ ይሆናል፦
• ኢራን ቡሽሄር ውስጥ ለኤሌክትሪክ ማመንጫነት ለምታካሂደው የኒውክሌር ግንባታ አሜሪካ ድጋፍ ታደርጋለች።
• በኢራን ላይ የተጣሉ ሁሉም ማዕቀቦች እንዲነሱ ይደረጋሉ
አዲስ ሊጣሉባት የሚችሉ ማዕቀቦች ይቀራሉ።
• በተጨማሪም በሁለቱ ወገኖች መካከል ድርድር በሚደረግበት ጊዜ ለአንድ ወር የሚቆይ የተኩስ አቁም ይኖራል ተብሏል።
ነገር ግን ከዋይት ሐውስ አስካሁን ምንም ዓይነት ዝርዝርም ሆነ ማረጋገጫ አልተሰጠም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ኢራን ምላሽ ሰጥታለች።
የኢራን መንግሥት በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኩል የቀረበውን የድርድር ዕቅድን ውድቅ አድርጓል።
ኢራን " ጦርነቱን የሚያበቃው እራሴ ስወስን እና የራሴ ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ነው " ብላለች።
ኢራን መሟላት አለበት ያለቻቸውን የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ነው።
➡ በጠላት የሚፈጸመው " ወረራ እና ግድያ " ሙሉ ለሙሉ መቆም።
➡ ጦርነቱ በድጋሚ በኢራን ላይ እንደማይከፈት የሚያረጋግጥ አስተማማኝ ሁኔታ መፍጠር።
➡ የተረጋገጠ እና በግልጽ የሚታወቅ በጦርነቱ ለደረሰው ጉዳት እና ካሳ መክፈል።
➡ በቀጣናው ባሉ ቡድኖች ላይ የተከፈቱት ሁሉም ጦርነቶች እንዲቆሙ ማድረግ።
➡ ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ያላትን መብት እና ሉዓላዊነት ዓለም አቀፍ ዕውቅና መስጠት።
የኢራን ባለሥልጣናት እስካሁን ድርድር የሚባል ነገር አለመጀመሩን አሳውቀዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
Reviews channel
4 total reviews
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
𝗔𝗕𝗖 𝗡𝗘𝗪𝗦 𝗔𝗠𝗛𝗔𝗥𝗜𝗖 is a Telegram channel in the category «Новости и СМИ», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 810 subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 17.4, with 4 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 2.4 ₽, and with 5 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий