
- Main
- Catalog
- News and Media
- 𝗔𝗕𝗖 𝗡𝗘𝗪𝗦 𝗔𝗠𝗛𝗔𝗥𝗜𝗖
𝗔𝗕𝗖 𝗡𝗘𝗪𝗦 𝗔𝗠𝗛𝗔𝗥𝗜𝗖
This public channel features all aspects of life in # Ethiopia, # News # Zena # News #Reviews
Channel statistics
" በምንም መልኩ ከአርቲስቱ ጋር የሚገናኝ የወንጀል ምርመራ ስራ የለንም/አልሰራንም ፤ እሱ ላይ የቀረበ ጥቆማም የለም ፤ እሱ የኛ ተጠርጣሪ አይደለም ! " - የፌዴራል ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) " ኢትዮሪካ " አልበሙን ለአድማጭ አድናቂዎቹ ካቀረበበት ጊዜ አንስቶ በእሱና በእሱ ዙሪያ ባሉ ሰዎች ላይ ጫና እየደረሰ መሆኑ እየተነገረ ነው።
" ምክትል ማናጀሩን ጨምሮ የረጅም ጊዜ የቅርብ ጓደኛው " መታሰራቸውም ተመላክቷል።
ከዚህ ባለፈ ታጥቀው በመኪና የመጡ አካላት " ሲኤምሲ " አካባቢ የሚገኝ የሙዚቃ ስቱዲዮ እና ስራዎችን የሚያዘጋጅበት ቦታን በምሽት በኃይል በመስበር መዝረፋቸው ተነግሯል።
የጀርመን ድምጽ ሬድዮ ጣቢያም የቴዲ አፍሮን የቅርብ ሰዎች ዋቢ በማድረግ ስቱዲዮው " ተዘርፏል " ብሏል። ጠባቂዎችም መደብደባቸውን ገልጿል። ከተዘረፉት ውስጥ ያልወጡ የሙዚቃ ስራዎች ያሉባቸው ፋይሎች እንዳሉ አመልክቷል።
እስካሁን ድረስ እየደረሱ ነው ስለተባሉት ጫናዎች እና በስቱዲዮው ላይ በታጠቁ አካላት " ተፈጽሟል " ስለተባለው ዝርፊያ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በይፋ የሰጠው ቃል፣ በማነጀሩ በኩል የሰጠው ማብራሪያ የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ ቴዲ አፍሮ ላይ እየደረሰ ነው ስለተባለው ከፍተኛ ጫና እንዲሁም " ተፈጽሟል " ስለተባለው ዝርፊያ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስን ጠይቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምርያ የወንጀል ምርመራ ኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ አብዲሳን ነው።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ ፥ " የፌደራል ፖሊስ እንደዚህ አይነት ውንብድና አይሰራም። ስብእናውም አይደለም። የሚሰራው በህግና በህግ ብቻ ነው " ብለዋል።
" ብዙ ኦፕሬሽኖችን እንሰራለን በነዚህ ኦፕሬሽኖች ውስጥ ከእሱ (ከቴዲ አፍሮ) ጋር የሚገናኙ እኛ ያደረግነው ነገር የለም " ሲሉ ገልጸዋል።
ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ተጠርጣሪ እንዳልሆነ ፣ በእሱ ላይ ምንም አይነት ምርመራ እንዳልተደረገ / የምርመራ ስራ እንዳልተሰራ ፣ እንዲሁም ከእሱ ጋር የሚገናኝ ጥቆማ ለፖሊስ እንዳልደረሰውና ፌዴራል ፖሊስ እሱ ላይ አንድም ነገር እንዳላደረገ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ህዝቡም ይሄን ይወቅልን " ብለዋል።
" እሱ አርቲስት ነው ሙዚቃውን አውጥቷል ፤ ቤቱ ነው ያለው በስርዓት እየኖረ ነው ያለው ፤ በእሱ ላይ የተደረገ ምንም አይነት ነገር የለም " ሲል ገልጸዋል።
" እኛም እንደማንኛውም ሰው ሚዲያ ላይ እናያለን ፤ በየቀኑ በሺዎች የሚቆጠሩ የፈጠራ ወሬዎች ይፈጠራሉ። ስለዚህ አርቲስቱን እንደማስያዣ ይዘው የፖለቲካ አጀንዳ ማራገብ የሚፈልጉትንም እያየናቸው ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ ፥ " ይሄ ዜጋ ህገመንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ሙዚቃ ሰርቷል። ድጋፊዎቹ ይደግፉታል፤ የሚቃወሙትም አሉ ፤ ያ ሌላ ሜዳ ነው። ስለዚህ ከእሱ ጋር የሚገናኝ ምንም አይነት ንክኪ ያለው ጉዳይ ላይ ተሳትፎ አላደርግንም " ሲሉ አብራርተዋል።
" ህግ ጥሶ ከተገኘ እንደማንም ሰው ሊጠየቅ የሚችል ሰው ነው ዜጋ እስከሆነ ድረስ " ያሉት አቶ ሙሊሳ ፥ " በአሁኑ ጊዜ ከእሱ ጋር የሚገናኝ ምንም አይነት የምርመራ ስራ አልሰራንም " ብለዋል።
" ዋናውና ትልቁ ነገር ህዝቡም በደምብ ሊገነዘብ የሚገባው ዝም ብሎ ኮሽ ባለ ቁጥር ድሮ ሰው ' እንደዚህ ዘፈንክ ' ተብሎ እንደሚያስር እንደዚህ አይነት ነገር graduate አድርጎ አልፏል የጸጥታ ተቋሙ። ወንጀል ከሰራ ማንም ሰው ይጠየቃል ፤ የመንግሥት አካል ፣ አመራርም ቢሆን በህግ በማስረጃ ይጠየቃል። ወንጀል ያልሰራ ሰው ግን በፍጹም አይጠየቅም " ሲሉ ተናግረዋል።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ አብዲሳ፥ " ' ክልከላ ተደርጓል ' ሲባል የነበረውም ውሸቶች ናቸው " ያሉ ሲሆን " ሁሉም መሰረተ ቢስ ነው። ይሄ ልጁን (ቴዲን) ተጠቅመው ህዝብ ላይ ሽብር ለመፍጠር የሚደረግ የሳይበር ወሬ ነው እንጂ በተግባር ቤቱ ሆኖ በስርዓት እየኖረ ያለ ሰው ነው " ብለዋል።
" አርቲስት ሆኖ ሙዚቃ መስራት ፤ የፈለከውን opinion (አመለካከት) የመያዝ ህገመንግስታዊ መብት ነው። ከዚህ ውጪ ያለ ማስረጃ ሰው የማይያዝበትን ሂደት ፈጥረናል ለዚህ ቴክኖሎጂ ተጠቅመን የትኛውም አይነት የምርመራ ስራዎችን እንሰራለን የምንሰራቸውንም በግልጽ ለህዝብ እናሳውቃለን " ብለዋል።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ " ሰው ሊታወቅ ይችላል ፣ ወንድምህ ሊታሰር ይችላል አናውቅም ፣ ጓደኛህ ሊታሰር ይችላል አናውቅም ግን ይህ ሰው ከማን ጋር ይውላል ማነው ብለን አናስርም ፤ የምንሰራቸው ስራዎች legitimate ናቸው ፍ/ቤት አቅርበን በስርዓት ጊዜ ቀጠሮ ጠይቀን እንመረምራለን ይሄ የማስረጃ ጉዳይ ነው ሂደታችንም ይኸው ነው። ከዚህ ውጭ ምንም ከአርቲስቱ ጋር የሚገናኝ ምርመራ አልሰራንም " ሲሉ አስረድተዋል።
" ሌላ የፖለቲካ ፍላጎት ያላቸው ሰዎች እሱን መጠቀሚያ ማድረግ ስለሚፈልጉ እሱ ስለማያዋጣቸው ቢተውት ጥሩ ነው " ብለዋል።
ከቴዲ ጋር የተያያዘው ጉዳይ ቀድሞ መጀመሩን ያነሱት አቶ ሙሊሳ " ' መግለጫ ተከለከለ ' ተባለ ምን ስለሆነ ? ሚስቱ እኮ አለች ሚዲያ አላት እሱ መስጠት አይችልም ? ቤቱ ሆኖ መስጠት አይችልም ? በሞባይል ስልኩ መስጠት ይችላል። መንግሥት ' ከለከለ ' የሚለው ከመነሻው መሰረተ ቢስ ነው፤ ለምን ይከለከላል ? ሰው የታገለው እንደዚህ አይነት መብቶች እንዲከበሩለት ነው። እንደ law enforcement የምንሰራው መብት እንዲከበር ነው " ሲሉ አብራርተዋል።
" ከአርቲስቱ ጋር የተገናኘና እሱንም መሰረት የሚያደርግ ምንም ነገር ባልሰራንበት ፤ ሳይበር ተጠቅመው ብዙ የፖለቲካ ፍላጎት ያላቸው ህዝቡን በሌላ ነገር ማንቀሳቀስ ያልቻሉ እሱ እንደተነካ አድርገው የሚፈጽሙት ተግባር መሰረተ ቢስ ነው " ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ አብዲሳ ህዝቡ የሚሰማውን ሁሉ ከማመን እንዲጠነቀቅ ጥሪ አቅርበዋል።
" የሰማነው ነገር ፣ የሚወራው ሁሉ እውነት አይደለም። ዛሬ AI አለ ፤ ለምሳሌ፦ ' የሙዚቃው መሳሪያ ተወሰደ ' ተብሎ የተሰራው ሙሉ በሙሉ ውሸት ነው። በሳይበር፣ በሚዲያ የተወራው ሁሉ እውነት አይደለም። ህዝቡ ይሄን ማመዛዘን አለበት። የነ ብርቱካንን ኬዝ ታስታውሳላችሁ አምና ምን እንደሆነ ህዝቡ ከተረጋጋ በኋላ እውነታው ወጣ " ሲሉ ተናግተዋል።
" ዛሬ ላይ ማንም ሰው ፣ ግለሰብ ሚዲያ በእጁ ነው ይሄንን መከልከል አይቻልም ፤ መረጃ ተጠቃሚው ህዝብ ግን በደምብ ቆሞ ማሰብ ያለበት የትኛው ነው የሚጠቅመው የሚለውን ነው ፤ እየለየ ሊጠቀም ይገባል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
" በምንም መልኩ ከአርቲስቱ ጋር የሚገናኝ የወንጀል ምርመራ ስራ የለንም/አልሰራንም ፤ እሱ ላይ የቀረበ ጥቆማም የለም ፤ እሱ የኛ ተጠርጣሪ አይደለም ! " - የፌዴራል ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) " ኢትዮሪካ " አልበሙን ለአድማጭ አድናቂዎቹ ካቀረበበት ጊዜ አንስቶ በእሱና በእሱ ዙሪያ ባሉ ሰዎች ላይ ጫና እየደረሰ መሆኑ እየተነገረ ነው።
" ምክትል ማናጀሩን ጨምሮ የረጅም ጊዜ የቅርብ ጓደኛው " መታሰራቸውም ተመላክቷል።
ከዚህ ባለፈ ታጥቀው በመኪና የመጡ አካላት " ሲኤምሲ " አካባቢ የሚገኝ የሙዚቃ ስቱዲዮ እና ስራዎችን የሚያዘጋጅበት ቦታን በምሽት በኃይል በመስበር መዝረፋቸው ተነግሯል።
የጀርመን ድምጽ ሬድዮ ጣቢያም የቴዲ አፍሮን የቅርብ ሰዎች ዋቢ በማድረግ ስቱዲዮው " ተዘርፏል " ብሏል። ጠባቂዎችም መደብደባቸውን ገልጿል። ከተዘረፉት ውስጥ ያልወጡ የሙዚቃ ስራዎች ያሉባቸው ፋይሎች እንዳሉ አመልክቷል።
እስካሁን ድረስ እየደረሱ ነው ስለተባሉት ጫናዎች እና በስቱዲዮው ላይ በታጠቁ አካላት " ተፈጽሟል " ስለተባለው ዝርፊያ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በይፋ የሰጠው ቃል፣ በማነጀሩ በኩል የሰጠው ማብራሪያ የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥ ቴዲ አፍሮ ላይ እየደረሰ ነው ስለተባለው ከፍተኛ ጫና እንዲሁም " ተፈጽሟል " ስለተባለው ዝርፊያ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስን ጠይቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምርያ የወንጀል ምርመራ ኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ አብዲሳን ነው።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ ፥ " የፌደራል ፖሊስ እንደዚህ አይነት ውንብድና አይሰራም። ስብእናውም አይደለም። የሚሰራው በህግና በህግ ብቻ ነው " ብለዋል።
" ብዙ ኦፕሬሽኖችን እንሰራለን በነዚህ ኦፕሬሽኖች ውስጥ ከእሱ (ከቴዲ አፍሮ) ጋር የሚገናኙ እኛ ያደረግነው ነገር የለም " ሲሉ ገልጸዋል።
ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ተጠርጣሪ እንዳልሆነ ፣ በእሱ ላይ ምንም አይነት ምርመራ እንዳልተደረገ / የምርመራ ስራ እንዳልተሰራ ፣ እንዲሁም ከእሱ ጋር የሚገናኝ ጥቆማ ለፖሊስ እንዳልደረሰውና ፌዴራል ፖሊስ እሱ ላይ አንድም ነገር እንዳላደረገ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ህዝቡም ይሄን ይወቅልን " ብለዋል።
" እሱ አርቲስት ነው ሙዚቃውን አውጥቷል ፤ ቤቱ ነው ያለው በስርዓት እየኖረ ነው ያለው ፤ በእሱ ላይ የተደረገ ምንም አይነት ነገር የለም " ሲል ገልጸዋል።
" እኛም እንደማንኛውም ሰው ሚዲያ ላይ እናያለን ፤ በየቀኑ በሺዎች የሚቆጠሩ የፈጠራ ወሬዎች ይፈጠራሉ። ስለዚህ አርቲስቱን እንደማስያዣ ይዘው የፖለቲካ አጀንዳ ማራገብ የሚፈልጉትንም እያየናቸው ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ ፥ " ይሄ ዜጋ ህገመንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ሙዚቃ ሰርቷል። ድጋፊዎቹ ይደግፉታል፤ የሚቃወሙትም አሉ ፤ ያ ሌላ ሜዳ ነው። ስለዚህ ከእሱ ጋር የሚገናኝ ምንም አይነት ንክኪ ያለው ጉዳይ ላይ ተሳትፎ አላደርግንም " ሲሉ አብራርተዋል።
" ህግ ጥሶ ከተገኘ እንደማንም ሰው ሊጠየቅ የሚችል ሰው ነው ዜጋ እስከሆነ ድረስ " ያሉት አቶ ሙሊሳ ፥ " በአሁኑ ጊዜ ከእሱ ጋር የሚገናኝ ምንም አይነት የምርመራ ስራ አልሰራንም " ብለዋል።
" ዋናውና ትልቁ ነገር ህዝቡም በደምብ ሊገነዘብ የሚገባው ዝም ብሎ ኮሽ ባለ ቁጥር ድሮ ሰው ' እንደዚህ ዘፈንክ ' ተብሎ እንደሚያስር እንደዚህ አይነት ነገር graduate አድርጎ አልፏል የጸጥታ ተቋሙ። ወንጀል ከሰራ ማንም ሰው ይጠየቃል ፤ የመንግሥት አካል ፣ አመራርም ቢሆን በህግ በማስረጃ ይጠየቃል። ወንጀል ያልሰራ ሰው ግን በፍጹም አይጠየቅም " ሲሉ ተናግረዋል።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ አብዲሳ፥ " ' ክልከላ ተደርጓል ' ሲባል የነበረውም ውሸቶች ናቸው " ያሉ ሲሆን " ሁሉም መሰረተ ቢስ ነው። ይሄ ልጁን (ቴዲን) ተጠቅመው ህዝብ ላይ ሽብር ለመፍጠር የሚደረግ የሳይበር ወሬ ነው እንጂ በተግባር ቤቱ ሆኖ በስርዓት እየኖረ ያለ ሰው ነው " ብለዋል።
" አርቲስት ሆኖ ሙዚቃ መስራት ፤ የፈለከውን opinion (አመለካከት) የመያዝ ህገመንግስታዊ መብት ነው። ከዚህ ውጪ ያለ ማስረጃ ሰው የማይያዝበትን ሂደት ፈጥረናል ለዚህ ቴክኖሎጂ ተጠቅመን የትኛውም አይነት የምርመራ ስራዎችን እንሰራለን የምንሰራቸውንም በግልጽ ለህዝብ እናሳውቃለን " ብለዋል።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ " ሰው ሊታወቅ ይችላል ፣ ወንድምህ ሊታሰር ይችላል አናውቅም ፣ ጓደኛህ ሊታሰር ይችላል አናውቅም ግን ይህ ሰው ከማን ጋር ይውላል ማነው ብለን አናስርም ፤ የምንሰራቸው ስራዎች legitimate ናቸው ፍ/ቤት አቅርበን በስርዓት ጊዜ ቀጠሮ ጠይቀን እንመረምራለን ይሄ የማስረጃ ጉዳይ ነው ሂደታችንም ይኸው ነው። ከዚህ ውጭ ምንም ከአርቲስቱ ጋር የሚገናኝ ምርመራ አልሰራንም " ሲሉ አስረድተዋል።
" ሌላ የፖለቲካ ፍላጎት ያላቸው ሰዎች እሱን መጠቀሚያ ማድረግ ስለሚፈልጉ እሱ ስለማያዋጣቸው ቢተውት ጥሩ ነው " ብለዋል።
ከቴዲ ጋር የተያያዘው ጉዳይ ቀድሞ መጀመሩን ያነሱት አቶ ሙሊሳ " ' መግለጫ ተከለከለ ' ተባለ ምን ስለሆነ ? ሚስቱ እኮ አለች ሚዲያ አላት እሱ መስጠት አይችልም ? ቤቱ ሆኖ መስጠት አይችልም ? በሞባይል ስልኩ መስጠት ይችላል። መንግሥት ' ከለከለ ' የሚለው ከመነሻው መሰረተ ቢስ ነው፤ ለምን ይከለከላል ? ሰው የታገለው እንደዚህ አይነት መብቶች እንዲከበሩለት ነው። እንደ law enforcement የምንሰራው መብት እንዲከበር ነው " ሲሉ አብራርተዋል።
" ከአርቲስቱ ጋር የተገናኘና እሱንም መሰረት የሚያደርግ ምንም ነገር ባልሰራንበት ፤ ሳይበር ተጠቅመው ብዙ የፖለቲካ ፍላጎት ያላቸው ህዝቡን በሌላ ነገር ማንቀሳቀስ ያልቻሉ እሱ እንደተነካ አድርገው የሚፈጽሙት ተግባር መሰረተ ቢስ ነው " ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ም/ኮሚሽነር ሙሊሳ አብዲሳ ህዝቡ የሚሰማውን ሁሉ ከማመን እንዲጠነቀቅ ጥሪ አቅርበዋል።
" የሰማነው ነገር ፣ የሚወራው ሁሉ እውነት አይደለም። ዛሬ AI አለ ፤ ለምሳሌ፦ ' የሙዚቃው መሳሪያ ተወሰደ ' ተብሎ የተሰራው ሙሉ በሙሉ ውሸት ነው። በሳይበር፣ በሚዲያ የተወራው ሁሉ እውነት አይደለም። ህዝቡ ይሄን ማመዛዘን አለበት። የነ ብርቱካንን ኬዝ ታስታውሳላችሁ አምና ምን እንደሆነ ህዝቡ ከተረጋጋ በኋላ እውነታው ወጣ " ሲሉ ተናግተዋል።
" ዛሬ ላይ ማንም ሰው ፣ ግለሰብ ሚዲያ በእጁ ነው ይሄንን መከልከል አይቻልም ፤ መረጃ ተጠቃሚው ህዝብ ግን በደምብ ቆሞ ማሰብ ያለበት የትኛው ነው የሚጠቅመው የሚለውን ነው ፤ እየለየ ሊጠቀም ይገባል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ከባለቤታቸው ሜላኒያ ጋር የነበሩት ዶናልድ ትራምፕ በጠባቂዎቻቸው ተሸፍነው ከመድረኩ እንዲነሱና እንዲወጡ ሲደረጉ ሚዛናቸውን ስተው መሬት ላይ ወድቀዋል።
ሌላው ለቫንስ የተመደቡ የጥበቃና ደህንነት አካላት በፍጥነት ይዘዋቸው ሲወጡ በዶናልድ ትራምፕ በኩል የነበሩት መዘግየታቸው መነጋገሪያ ሆኗል።
የትዳር አጋሮቻቸው ሁኔታስ ? እንዲህ ያሉ ነገሮች ሲፈጠሩ የትዳር አጋሮች ወይም ቤተሰብ ቢኖር እንኳን ለፕሬዚዳንቱ/ምክትሉ የተመደቡት የደህንነት ሰዎች ቅድሚያ የሚሰጡት ለእነሱ ብቻ ነው፤ እነሱን ከአደጋ ቀጠና ማስወጣት።
ሁኔታው ለተመልካች "ቤተሰብን ጥሎ መሸሽ" ወይም " ቸልተኝነት " ቢመስልም ይህ የተለመደ የደህንነት አሰራር ነው። " ዋና ሰዎች /የሀገሪቱ ውሳኔ ሰጪዎች " በራሳቸው ደህንነት አካላት በፍጥነት እንዲወጡ ይገደዳሉ።
"ቆዩኝ ሚስቴን ላምጣት" ቢል እንኳን የደህንነት ቡድኑ እድል አይሰጠውም። ፕሬዝዳንቱ ሆነ ምክትላቸው በእንዲህ ያለ ጊዜ የደህንነትና ጥበቃ ቡድንን ትእዛዝ ነው የሚከተሉት።
በተመሳሳይ ሌላ የተመደበ የደህንነትና ጥበቃ ቡድን የትዳር አጋሮቻቸውን ፤ ቤተሰቦቻቸውን ይጠብቃል።
Video Source - MS NOW
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ለአድማጭ አድናቂዎቹ ያቀረበው 18 ዘፈኖችን የያዘው " ኢትዮሪካ " አልበም በ9 ቀናት ውስጥ ብቻ በዩትዩብ ከ100 ሚሊዮን በላይ እይታን አገኘ።
" ዳስ ጣል/አንሳው " የተሰኘው ሙዚቃ በዚሁ በ9 ቀን ውስጥ 18,000,000 እይታን/አድማጭ በማግኘት ቀዳሚውን ስፍራ የያዘ ሲሆን ፤ ሌሎች ከፍተኛ እይታ/አድማጭ ካገኙት ውስጥ ስምምነ 8,000,000 ፣ ጀምበር 7,700,000 ይገኙበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ትላንት ምሽት በአሜሪካ፣ ዋሽንግተን ሂልተን ሆቴል በተካሄደ የዋይት ሐውስ ዘጋቢዎች የእራት ግብዣ ላይ ጥቃት ለማድረስ የጦር መሣሪያና ቢላዋ ታጥቆ የገባ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተነገረ።
በምሽቱ እራት ግብዣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በርካታ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተገኙበት ነበር።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው በፍጥነት ከአዳራሹ መውጣታቸው ታውቋል።
እንግዶች ጠረጴዛዎች ስር የተሸገጉ ሲሆን አንዳንዶቹ ዝግጅቱ ከተካሄደበት የዋሽንግተን ሂልተን ውጭ የተኩስ ድምጽ እንደሰሙ ተናግረዋል።
አንድ የፖሊስ ኃላፊ ለኤፒ ዜና ወኪል ግለሰቡ ተኩስ እንደከፈተ ገልጸው ፤ " አንድ የፖሊስ አባል የጥይት መከላከያው ላይ ቢመታም በጥሩ ሁኔታ ይገኛል " ብለዋል።
ተጠርጣሪው ኮል ቶማስ አለን የተባለ የ31 አመት ሰው እንደሆነ ይፋ የተደረገ ሲሆን ትራምፕ " የታመመ ሰው " ሲሉ ገልጸውታል።
" ተፅዕኖ ስታሳድር ይከታተሉሃል። ተፅዕኖ በማትፈጥርበት ጊዜ ደግሞ ይረሱሃል " ሲሉ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከጥቃቱ ከሁለት ሰዓታት በኋላ ተናግረዋል።
እራቱ ግብዣ ላይ፦
- ፕሬዝዳንት ትራምፕ ፣
- ም/ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ፣
- የመከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴት፣
- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እና ሌሎች በርካታ የትራምፕ አስተዳደር ባለሥልጣናት ተገኝተው ነበር።
በአገሪቱ የደህንነት አባላት ጥበቃ የሚደረግላቸው ሁሉም ባለሥልጣናት ከቦታው እንዲወጡ መደረጋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
ቪድዮ 1፦ በአዳራሹ ጥቃት ሊያደርስ የነበረው ግለሰብ በርካታ ጥበቃዎችን በሩጫ ጥሶ ሲያልፍ ያሳያል።
ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ትላንት ምሽት በአሜሪካ፣ ዋሽንግተን ሂልተን ሆቴል በተካሄደ የዋይት ሐውስ ዘጋቢዎች የእራት ግብዣ ላይ ጥቃት ለማድረስ የጦር መሣሪያና ቢላዋ ታጥቆ የገባ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተነገረ።
በምሽቱ እራት ግብዣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በርካታ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተገኙበት ነበር።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው በፍጥነት ከአዳራሹ መውጣታቸው ታውቋል።
እንግዶች ጠረጴዛዎች ስር የተሸገጉ ሲሆን አንዳንዶቹ ዝግጅቱ ከተካሄደበት የዋሽንግተን ሂልተን ውጭ የተኩስ ድምጽ እንደሰሙ ተናግረዋል።
አንድ የፖሊስ ኃላፊ ለኤፒ ዜና ወኪል ግለሰቡ ተኩስ እንደከፈተ ገልጸው ፤ " አንድ የፖሊስ አባል የጥይት መከላከያው ላይ ቢመታም በጥሩ ሁኔታ ይገኛል " ብለዋል።
ተጠርጣሪው ኮል ቶማስ አለን የተባለ የ31 አመት ሰው እንደሆነ ይፋ የተደረገ ሲሆን ትራምፕ " የታመመ ሰው " ሲሉ ገልጸውታል።
" ተፅዕኖ ስታሳድር ይከታተሉሃል። ተፅዕኖ በማትፈጥርበት ጊዜ ደግሞ ይረሱሃል " ሲሉ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከጥቃቱ ከሁለት ሰዓታት በኋላ ተናግረዋል።
እራቱ ግብዣ ላይ፦
- ፕሬዝዳንት ትራምፕ ፣
- ም/ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ፣
- የመከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴት፣
- የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እና ሌሎች በርካታ የትራምፕ አስተዳደር ባለሥልጣናት ተገኝተው ነበር።
በአገሪቱ የደህንነት አባላት ጥበቃ የሚደረግላቸው ሁሉም ባለሥልጣናት ከቦታው እንዲወጡ መደረጋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
ቪድዮ 1፦ በአዳራሹ ጥቃት ሊያደርስ የነበረው ግለሰብ በርካታ ጥበቃዎችን በሩጫ ጥሶ ሲያልፍ ያሳያል።
ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ግለገል በለስ እና ቡለን ወረዳዎች ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ በቀናት ውስጥ የ11 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ ሁለት ሰዎች ደግሞ አካላዊ ጉዳት እንደደረሰባቸው የክልሉ ምክር ቤት አባል አቶ ለሜሳ ኔኖ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በግልገል በለስ ከተማ ትናንት ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ ሳቢያ፣ "የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ጠፍቷል። ሁለት ሰዎች ቆስለዋል" ሲሉ ገልጸው፣ በአጠቃላይ 11 ሰዎች ላይ ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
በተያያዘ፣ በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ከቀናት በፊት "ሁለት ሰዎች ተገድለዋል" ሲሉም በዞኑ የታጣቂዎች ጥቃት መደጋገሙን አስረድተዋል። በዚህም በአጠቃላይ በሁለቱ ወረዳዎች ባለፉት አራት ቀናት ብቻ 11 ሰዎች ሲገደሉ ሁለት ደግሞ ቆስለዋል።
ትናንት ግልገል በለስ ላይ የሰው ህይወት የቀጠፈው የተኩስ ልውውጡ የነበረው፣ "ግልገል በለስ ከተማ ማረሚያ ሰፈር አካባቢ ነው። እዚያው ከተማው ላይ ነው" ሲሉ አቶ ለሜሳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ይህንኑ ተኩስ የከፈተው ማን እንደሆነ ሲያስረዱ ደግሞ፣ "ጥቃት አድራሹ አቶ መኩሪያ በሚባል ሰው የሚመራ ኃይል ነው። አቶ መኩሪያ ማለት ከዚህ በፊት የጉሙዝ ህዝብ ታጣቂ ነበር፤ ከሰላም ጥሪ አፈንግጦ ወደ ጫካ የተመለሰ ሰው ነው" ብለዋል።
ይህን ማረጋገጥ ተችሏል? በሚል ስንጠይቃቸው የምክር ቤት አባሉ፣ "አዎ ተረጋግጧል። የእርሱ ትውልድ ቦታም እዚያው ግልገል በለስ ነው። የተኩሱ አላማ ማረሚያ ቤቱ ላይ ጥቃት ማድረስ ነው" በማለት የጥቃቱ አላማ እስረኛ ሳይሆን እንዳልቀረ ገልጸዋል።
ከሟቾቹ መካከል ቄራ አገልግሎት ለማግኘት የሄዱ ንጹሐን እንደሚገኙበት በመግለጽ፣ ከዚህ ቀደምም ዳንጉርና ፓዊ አካባቢ ተመሳሳይ ጥቃት መድረሱን፣ የአሁኑ ጥቃት ለሦስተኛ ጊዜ የደረሰ መሆኑን ገልጸዋል።
እንዲሁም፣ "ቡለን ጎዶራሬ ላይም ከመከላከያ ጋር ተጋጭተው ሁለት ሰዎች ተገድለዋል፤ ጥቃቱ ዛሬ አራተኛ ቀኑ ነው። ይህን ያደረገው ደግሞ ኦነግ 'ሸኔ' ነው" በማለትም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በዞኑ መሰል ጥቃቶች የተደጋገሙ ሲሆን፣ የምክር ቤት አባሉ መፍትሄ ሀሳቡን በተመለከተ በአካባቢው "በተጠናከረ" የመንግስት የጸጥታ ኃይል ዘላቂ ጥበቃ ማድረግ፣ ጥቃት አድራሾቹ ላይ "ዘላቂ እርምጃ" መውሰድ መሆኑን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ተጨማሪ የአካባቢውን የጸጥታ አካላት ምላሽ ለማካተት ጥረት ቢያደርግም ያልተሳካ ሲሆን፣ ከቦታው እየወጡ ያሉ መረጃዎች ግን የተኩስ ጥቃቱ መፈጸሙን ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ግለገል በለስ እና ቡለን ወረዳዎች ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ በቀናት ውስጥ የ11 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ ሁለት ሰዎች ደግሞ አካላዊ ጉዳት እንደደረሰባቸው የክልሉ ምክር ቤት አባል አቶ ለሜሳ ኔኖ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በግልገል በለስ ከተማ ትናንት ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ ሳቢያ፣ "የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ጠፍቷል። ሁለት ሰዎች ቆስለዋል" ሲሉ ገልጸው፣ በአጠቃላይ 11 ሰዎች ላይ ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
በተያያዘ፣ በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ከቀናት በፊት "ሁለት ሰዎች ተገድለዋል" ሲሉም በዞኑ የታጣቂዎች ጥቃት መደጋገሙን አስረድተዋል። በዚህም በአጠቃላይ በሁለቱ ወረዳዎች ባለፉት አራት ቀናት ብቻ 11 ሰዎች ሲገደሉ ሁለት ደግሞ ቆስለዋል።
ትናንት ግልገል በለስ ላይ የሰው ህይወት የቀጠፈው የተኩስ ልውውጡ የነበረው፣ "ግልገል በለስ ከተማ ማረሚያ ሰፈር አካባቢ ነው። እዚያው ከተማው ላይ ነው" ሲሉ አቶ ለሜሳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ይህንኑ ተኩስ የከፈተው ማን እንደሆነ ሲያስረዱ ደግሞ፣ "ጥቃት አድራሹ አቶ መኩሪያ በሚባል ሰው የሚመራ ኃይል ነው። አቶ መኩሪያ ማለት ከዚህ በፊት የጉሙዝ ህዝብ ታጣቂ ነበር፤ ከሰላም ጥሪ አፈንግጦ ወደ ጫካ የተመለሰ ሰው ነው" ብለዋል።
ይህን ማረጋገጥ ተችሏል? በሚል ስንጠይቃቸው የምክር ቤት አባሉ፣ "አዎ ተረጋግጧል። የእርሱ ትውልድ ቦታም እዚያው ግልገል በለስ ነው። የተኩሱ አላማ ማረሚያ ቤቱ ላይ ጥቃት ማድረስ ነው" በማለት የጥቃቱ አላማ እስረኛ ሳይሆን እንዳልቀረ ገልጸዋል።
ከሟቾቹ መካከል ቄራ አገልግሎት ለማግኘት የሄዱ ንጹሐን እንደሚገኙበት በመግለጽ፣ ከዚህ ቀደምም ዳንጉርና ፓዊ አካባቢ ተመሳሳይ ጥቃት መድረሱን፣ የአሁኑ ጥቃት ለሦስተኛ ጊዜ የደረሰ መሆኑን ገልጸዋል።
እንዲሁም፣ "ቡለን ጎዶራሬ ላይም ከመከላከያ ጋር ተጋጭተው ሁለት ሰዎች ተገድለዋል፤ ጥቃቱ ዛሬ አራተኛ ቀኑ ነው። ይህን ያደረገው ደግሞ ኦነግ 'ሸኔ' ነው" በማለትም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በዞኑ መሰል ጥቃቶች የተደጋገሙ ሲሆን፣ የምክር ቤት አባሉ መፍትሄ ሀሳቡን በተመለከተ በአካባቢው "በተጠናከረ" የመንግስት የጸጥታ ኃይል ዘላቂ ጥበቃ ማድረግ፣ ጥቃት አድራሾቹ ላይ "ዘላቂ እርምጃ" መውሰድ መሆኑን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ተጨማሪ የአካባቢውን የጸጥታ አካላት ምላሽ ለማካተት ጥረት ቢያደርግም ያልተሳካ ሲሆን፣ ከቦታው እየወጡ ያሉ መረጃዎች ግን የተኩስ ጥቃቱ መፈጸሙን ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ሁለተኛው ዙር የስራ ኃላፊነታቸው ከተራዘመላቸው ሁለት ሳምንት የሆናቸው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ትላንት ነባሩ ካቢኔያቸውን ሰብስበው ውለዋል።
ፕሬዜዳንቱ እስከ አሁን አዲስ ካቢኔ አላወቀሩም ፤ የቆየው ካቢኔ ይቀጥል እንደሆነ አላሳወቁም ፤ አዲሱ እቅዳቸውንም ይፋ አላደረጉም።
ሹመታቸው ከተራዘመ በኋላ ሦስት ጊዜ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት ፕሬዜዳንቱ ፤ ትላንት አርብ ሚያዝያ 16/2018 ዓ/ም ጨምሮ ሁለቴ የካቢኔ ስብሰባ አካሄደዋል።
በመጀመሪያው የፕሬዜዳንቱ የካቢኔ ስብሰባ የህወሓቱ ምክትል ሊቀ-መንበርና የጊዚያዊ አስተዳዳሩ ምክትል ፕሬዜዳንት አማኒኤል አሰፋ የሚገኙባቸው ህወሓትን የወከሉ አባላት አልተገኙም።
ከፍተኛ የህወሓት አመራሮቹ የጊዚያዊ አስተዳደሩን መደበኛ የካቢኔ ስብሰባ ወደ ጎን በመተው በተመሳሳይ ጊዜ ድርጅታቸው በአክሱም ከተማ የጠራውን የ " ነባሩ መንግስት ይመለስ " ስብሰባ መሳተፍን አስቀድመዋል።
ፕሬዚዳንቱ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ሙሉ ካቢኔያቸውን የሰበሰቡ ሲሆን ስብሰባው ላይ ምክትል ፕሬዚዳንት አማኑኤል አሰፋን ጨምሮ ሁሉም ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ካቢኔው በትላንት መደበኛ ውሎው መሬት፣ ማዕድንና ውሃ በሚመለከቱ ጉዳዮች ተወያይተው ውሳኔዎች አሳልፈዋል ብሏል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ምንጮች።
በምርጫ ቦርድ የተሰረዘው ህወሓት ሚያዝያ 7/2018 ዓ.ም የጀመረው የ " ነባሩ መንግስትና ምክር ቤት ይመለስ " ወሳኔ በዘመቻ መልኩ ከዞን እስከ ወረዳ ተከታታይ ሰብሰባዎች በማካሄድ ላይ ይገኛል።
የፓርቲ ስብሰባዎች በመደበኛ የመንግስት የስራ ሰዓት መካሄድ ቢቀጥሉም 'አቁሙ' የሚል ሃይ ባይ የመንግስት አካል አልተገኘም።
ህወሓት በፌደራል መንግስት ስልጣናቸው የተራዘመላቸው ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) በኋላፊነት እንዲቀጥሉ እንደማይፈቅድላቸው በመግለጫ ቢያስታውቅም " ስልጣኔን በግርግር አልለቅም " በማለት ስራቸውን ቀጥለዋል።
ፕሬዜዳንቱ ስልጣናቸው ከተራዘመላቸው ማግስት ጀምሮ የሹመት ማራዘሙ " ከኔ እውቅና ውጪ ነው " የሚል ተቃውሞ ማሰማቱን ተከትሎ ከመቐለ ወደ አክሱም ከተማ በመጓዝ የሁለት ቀናት ውይይት በማካሄድ " ነባሩ መንግስት ይመለሳል " ሲል ወስኗል።
ውሳኔውን ተከትሎ እሮብ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በመቐለ ከተማ ለአንድ ቀን በተጠራ የድርጅቱ ከፍተኛ ካድሬዎች ስብሰባ ውሳኔውን በማጠናከር ከትናንት በስቲያ እና ትላንት ስብሰባው በመላ ከተሞችና የገጠር ወረዳዎች ተካሂዶ የ " ነባሩ መንግስት ይመለስ ውሳኔ " በክልሉ ሚድያዎች እየተስተጋባ ይገኛል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ሁለተኛው ዙር የስራ ኃላፊነታቸው ከተራዘመላቸው ሁለት ሳምንት የሆናቸው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ትላንት ነባሩ ካቢኔያቸውን ሰብስበው ውለዋል።
ፕሬዜዳንቱ እስከ አሁን አዲስ ካቢኔ አላወቀሩም ፤ የቆየው ካቢኔ ይቀጥል እንደሆነ አላሳወቁም ፤ አዲሱ እቅዳቸውንም ይፋ አላደረጉም።
ሹመታቸው ከተራዘመ በኋላ ሦስት ጊዜ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት ፕሬዜዳንቱ ፤ ትላንት አርብ ሚያዝያ 16/2018 ዓ/ም ጨምሮ ሁለቴ የካቢኔ ስብሰባ አካሄደዋል።
በመጀመሪያው የፕሬዜዳንቱ የካቢኔ ስብሰባ የህወሓቱ ምክትል ሊቀ-መንበርና የጊዚያዊ አስተዳዳሩ ምክትል ፕሬዜዳንት አማኒኤል አሰፋ የሚገኙባቸው ህወሓትን የወከሉ አባላት አልተገኙም።
ከፍተኛ የህወሓት አመራሮቹ የጊዚያዊ አስተዳደሩን መደበኛ የካቢኔ ስብሰባ ወደ ጎን በመተው በተመሳሳይ ጊዜ ድርጅታቸው በአክሱም ከተማ የጠራውን የ " ነባሩ መንግስት ይመለስ " ስብሰባ መሳተፍን አስቀድመዋል።
ፕሬዚዳንቱ ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ሙሉ ካቢኔያቸውን የሰበሰቡ ሲሆን ስብሰባው ላይ ምክትል ፕሬዚዳንት አማኑኤል አሰፋን ጨምሮ ሁሉም ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ካቢኔው በትላንት መደበኛ ውሎው መሬት፣ ማዕድንና ውሃ በሚመለከቱ ጉዳዮች ተወያይተው ውሳኔዎች አሳልፈዋል ብሏል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ምንጮች።
በምርጫ ቦርድ የተሰረዘው ህወሓት ሚያዝያ 7/2018 ዓ.ም የጀመረው የ " ነባሩ መንግስትና ምክር ቤት ይመለስ " ወሳኔ በዘመቻ መልኩ ከዞን እስከ ወረዳ ተከታታይ ሰብሰባዎች በማካሄድ ላይ ይገኛል።
የፓርቲ ስብሰባዎች በመደበኛ የመንግስት የስራ ሰዓት መካሄድ ቢቀጥሉም 'አቁሙ' የሚል ሃይ ባይ የመንግስት አካል አልተገኘም።
ህወሓት በፌደራል መንግስት ስልጣናቸው የተራዘመላቸው ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) በኋላፊነት እንዲቀጥሉ እንደማይፈቅድላቸው በመግለጫ ቢያስታውቅም " ስልጣኔን በግርግር አልለቅም " በማለት ስራቸውን ቀጥለዋል።
ፕሬዜዳንቱ ስልጣናቸው ከተራዘመላቸው ማግስት ጀምሮ የሹመት ማራዘሙ " ከኔ እውቅና ውጪ ነው " የሚል ተቃውሞ ማሰማቱን ተከትሎ ከመቐለ ወደ አክሱም ከተማ በመጓዝ የሁለት ቀናት ውይይት በማካሄድ " ነባሩ መንግስት ይመለሳል " ሲል ወስኗል።
ውሳኔውን ተከትሎ እሮብ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በመቐለ ከተማ ለአንድ ቀን በተጠራ የድርጅቱ ከፍተኛ ካድሬዎች ስብሰባ ውሳኔውን በማጠናከር ከትናንት በስቲያ እና ትላንት ስብሰባው በመላ ከተሞችና የገጠር ወረዳዎች ተካሂዶ የ " ነባሩ መንግስት ይመለስ ውሳኔ " በክልሉ ሚድያዎች እየተስተጋባ ይገኛል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
@tikvahethiopia
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
@tikvahethiopia
አሜሪካ እና ኢራን ሁለተኛ ዙር ንግግር የማድረጋቸው ጉዳይ እስካሁን ማረጋገጫ ባይሰጥበትም አሸማጋይ ሆና እየሰራች ያለችው ፓኪስታን ድርድሩን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗ ተነግሯል።
የኢራንን የተደራዳሪ ልዑክ የሚመሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አባስ አራግቺ ዛሬ ማታ ኢስላማባድ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የፓኪስታን መንግሥት ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ሮይተርስ ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የሚጓዙት አነስተኛ ቁጥር ያለው አባላትን የያዘ ቡድን አስከትለው እንደሆነ እና ከአሜሪካ ጋር የሚደረግ ንግግር ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዘግቧል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዚህ ቀደም ወደ ፓኪስታን፣ ኢስላማባድ የተደራዳሪ ልዑካቸውን እንደሚልኩ ማሳወቃቸው ይታወሳል።
መረጃው የቢቢሲ እና ሮይተርስ ነው።
ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 የትምህርት ዘመን ያሉ ፈተናዎች የሚሰጡባቸውን ቀናትን እና የመሠረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና (EGRA and EGMA) የሚካሄድበትን ጊዜ ይፋ አደረገ።
አገልግሎቱ በትምህርት ዘርፉ እየተደረገ ያለውን ውጤታማ ሪፎርም ተከትሎ የአጠቃላይና የከፍተና ትምህርት ፈተናዎች እየሠጠ እንደሚገኝ ገልጿል።
በመሆኑም " ተፈታኞች አስፈላጊውን የይዘትና የስነ-ልቦና ዝግጅት እንዲደርጉ እንዲሁም ወላጆች፣ መምህራንና በየደረጃው ያለው የትምህርት አመራር ተፈታኞቻቸው የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንዲያደርጉ " የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ ጊቾሮ (ዶ/ር ) አሳስበዋል።
በተያያዘም የመሠረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና (EGRA and EGMA) ጥናትና ምርምር ሥራ ለትምህርት ልማትና ጥራት መሻሻል ያለውን አይተኬ ሚና በመገንዘብ ትምህርት ቤቶች እና በተዋረድ ያለው የትምህርት አመራር ተገቢውን ትብብር እንዲያደርጉም ዋና ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 የትምህርት ዘመን ያሉ ፈተናዎች የሚሰጡባቸውን ቀናትን እና የመሠረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና (EGRA and EGMA) የሚካሄድበትን ጊዜ ይፋ አደረገ።
አገልግሎቱ በትምህርት ዘርፉ እየተደረገ ያለውን ውጤታማ ሪፎርም ተከትሎ የአጠቃላይና የከፍተና ትምህርት ፈተናዎች እየሠጠ እንደሚገኝ ገልጿል።
በመሆኑም " ተፈታኞች አስፈላጊውን የይዘትና የስነ-ልቦና ዝግጅት እንዲደርጉ እንዲሁም ወላጆች፣ መምህራንና በየደረጃው ያለው የትምህርት አመራር ተፈታኞቻቸው የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንዲያደርጉ " የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ ጊቾሮ (ዶ/ር ) አሳስበዋል።
በተያያዘም የመሠረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና (EGRA and EGMA) ጥናትና ምርምር ሥራ ለትምህርት ልማትና ጥራት መሻሻል ያለውን አይተኬ ሚና በመገንዘብ ትምህርት ቤቶች እና በተዋረድ ያለው የትምህርት አመራር ተገቢውን ትብብር እንዲያደርጉም ዋና ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
Reviews channel
4 total reviews
- Added: Newest first
- Added: Oldest first
- Rating: High to low
- Rating: Low to high
Catalog of Telegram Channels for Native Placements
𝗔𝗕𝗖 𝗡𝗘𝗪𝗦 𝗔𝗠𝗛𝗔𝗥𝗜𝗖 is a Telegram channel in the category «Новости и СМИ», offering effective formats for placing advertising posts on TG. The channel has 809 subscribers and provides quality content. The advertising posts on the channel help brands attract audience attention and increase reach. The channel's rating is 17.4, with 4 reviews and an average score of 5.0.
You can launch an advertising campaign through the Telega.in service, choosing a convenient format for placement. The Platform provides transparent cooperation conditions and offers detailed analytics. The placement cost is 2.4 ₽, and with 5 completed requests, the channel has established itself as a reliable partner for advertising on Telegram. Place integrations today and attract new clients!
You will be able to add channels from the catalog to the cart again.
Комментарий